en
Feedback
Bernos -Media

Bernos -Media

Open in Telegram

ይህ የBernos media የቴሌግራም ገፅ ነው!

Show more
7 571
Subscribers
-224 hours
-367 days
-26930 days
Posts Archive
በደብረብርሃን ከተማ በአንድ ወጣት ባለሀብት እየተገነባ ያለ የዳቦ ማምረቻ ፋብሪካ በአጭር ጊዜ ወደ ስራ እንደሚገባ አስታውቋል። የዳቦ ማምረቻው ፋብሪካው ስራአስኪያጅ አቶ ምህረት ሙላቱ ለኢቲ ኒውስ
በደብረብርሃን ከተማ በአንድ ወጣት ባለሀብት እየተገነባ ያለ የዳቦ ማምረቻ ፋብሪካ በአጭር ጊዜ ወደ ስራ እንደሚገባ አስታውቋል። የዳቦ ማምረቻው ፋብሪካው ስራአስኪያጅ አቶ ምህረት ሙላቱ ለኢቲ ኒውስ እንደተናገሩት በከተማዋ የሚሰተዋለውን የዳቦ እጥረት ያስቀራል። በስራው ጅማሮ ለ150 የደብረብርሃን እናቶችና ወጣቶች ቋሚና ግዚያዊ የስራ እድል የሚፈጥር ይሆናል ብለዋል።ፋብሪካው በቀን ከ100 እስከ 150ሺ ዳቦ በቀን የማምረት አቅም እንደሚኖረውም አስረድተዋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በደብረብርሃን ከተማ በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎች እየተገነቡ ይገኛሉ።ሁሉም ወደ ስራ ሲገቡ ለከተማዋ እድገት ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚኖራቸው ተስፋ ተደርጓል።ለለውጥ የሚሰሩን ማበረታታት ይገባል።

ተወዳጁ አርቲስት ቴዲ አፍሮ (ቴዎድሮስ ካሳሁን) በሀገሪቱ እየሆነ ያለው ነገር እጅጉን አሰቃቂ ነው ብሏል!
ተወዳጁ አርቲስት ቴዲ አፍሮ (ቴዎድሮስ ካሳሁን) በሀገሪቱ እየሆነ ያለው ነገር እጅጉን አሰቃቂ ነው ብሏል!

የድሮን ጥቃት በሰ/ሸዋ ዞን ሞጃና ወራና ወረዳ ሳሲት የህፃን ልጅ ማህተመ ክርስትና ስርዓት በኋላ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ በተሽከርካሪ ላይ በተፈፀመ ጥቃት የንፁሃን ህይወት ተቀጥፏል። እጅግ ልብ ሰባሪ ነው😥

#ለክቡራን_ደንበኞቻችን የሸዋ ብርሃን አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ቤት ማህበራትን ጭማሪ ክፍያ እንዲዘጉ ባወጣው ማስታወቂያ ላይ ባስቀመጥናቸው የተቋማችን የሂሳብ
#ለክቡራን_ደንበኞቻችን የሸዋ ብርሃን አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ቤት ማህበራትን ጭማሪ ክፍያ እንዲዘጉ ባወጣው ማስታወቂያ ላይ ባስቀመጥናቸው የተቋማችን የሂሳብ ቁጥሮች መሰረት ማህበራቱ በቡድን በመሆን ብድር የሚያገኙበትን ምቹ ሁኔታ ስለፈጠርን የሚከተሉት አድራሻዎቻችን በመደወል እና በአካል በዋናው ቢሯችን በሚገኝበት የደብረ ብርሃን አጠቃላይ ሆስፒታል አጠገብ ወይንም የቀድሞ መዘጋጃ  በመምጣት የእድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ በአክብሮት እንገልፃለን ። ስልክ ቁ. - 0965917670        :- 0116375334

"በምን ሞራል ነው ተማሪዎችን አጥኑ ብለን የምንመክራቸው?" ደብረብርሃን አካባቢ ተወልጄ ከደብረብርሃን ዩንቨርስቲ በሚድዋይፍ የተመረቅሁ ስሜ ታልዬ በጋሻዉ ይባላል:: ለአገራችን በሙያችን ለማበርከት
+4
"በምን ሞራል ነው ተማሪዎችን አጥኑ ብለን የምንመክራቸው?" ደብረብርሃን አካባቢ ተወልጄ ከደብረብርሃን ዩንቨርስቲ በሚድዋይፍ የተመረቅሁ ስሜ ታልዬ በጋሻዉ ይባላል:: ለአገራችን በሙያችን ለማበርከት ቀን ከሌት ደፋ ቀና ብለን፣ አራት አመታትን ያለ እንቅልፍ እና እረፍት ስንደክም ቆይተን እጅግ በጣም ከፍተኛ የሚባል ውጤት CGPA 3.9 በላይ ዉጤት ተመርቄ ነበር:: አሁን 4 ኪሎ አካባቢ መንገድ ዳር ያለሙያዬ ጌጣጌጥ በመሸጥ ላይ እገኛለሁ። በምን ሞራል ነው ተማሪዎችን አጥኑ ብለን የምንመክራቸው? በአመት 400 እና ከዚያ በላይ የእናቶች ሞት ባለበት አገር ሆነን ያለስራ 1 አመት ሙሉ መቀመጥና የትገባችሁ የሚል አካል አጥተን ወንበር እያሞቅን ያለንበት ሁኔታ ነው ያለው:: ስልክ ቁጥር፡- 0919191172 መረጃዎቼ፡- የተመረቅኩበት ፎቶ እና ዶክመንቶቼ ሲሆኑ 1ኛ እና 4ኛ ላይ ያለዉ ፎቶ አሁን መንገድ ዳር ጌጣጌጦችን በማዞር መረጃው የ @Hakim ነው

በኦሮሚያ ልዩ ሀይል ወረራ የተፈፀመበት አውራ ጎዳና 😭 ምንጃር አውራ ጎዳና!

የኦሮሞ ልዩ ሀይል በርካታ ሰላማዊ ነዋሪዎችን በጅምላ ከገደለና ከዘረፈ በኋላ በዚህ መልኩ ወረራ እየፈፀመ ይገኛል። አሁን ሁሉንም ነገር ግልፅ እያደረጉት ነው። ዋና አላማቸው ወረራ መፈፀምና ንፁሃንን መግደል እንደሆነ አሳይተዋል። በወረራ የምትወስዱት አንድ ኢንች መሬት አይኖርም! ጊዜ ለኩሉ!

የኦሮሞ ልዩ ሀይል በርካታ ሰላማዊ ነዋሪዎችን በጅምላ ከገደለና ከዘረፈ በኋላ በዚህ መልኩ ወረራ እየፈፀመ ይገኛል። አሁን ሁሉንም ነገር ግልፅ እያደረጉት ነው። ዋና አላማቸው ወረራ መፈፀምና ንፁሃንን
+1
የኦሮሞ ልዩ ሀይል በርካታ ሰላማዊ ነዋሪዎችን በጅምላ ከገደለና ከዘረፈ በኋላ በዚህ መልኩ ወረራ እየፈፀመ ይገኛል። አሁን ሁሉንም ነገር ግልፅ እያደረጉት ነው። ዋና አላማቸው ወረራ መፈፀምና ንፁሃንን መግደል እንደሆነ አሳይተዋል። በወረራ የምትወስዱት አንድ ኢንች መሬት አይኖርም! ጊዜ ለኩሉ!

photo content
+1

#FakeNews !! በተለያዩ የሶሻል ሚዲያ አማራጮች የሚሰራጨው ይኼ መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን ከምንጮቻችን አረጋግጠናል። ከሀሰተኛ መረጃ እንቆጠብ!
#FakeNews !! በተለያዩ የሶሻል ሚዲያ አማራጮች የሚሰራጨው ይኼ መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን ከምንጮቻችን አረጋግጠናል። ከሀሰተኛ መረጃ እንቆጠብ!

▶️በሰሜን ሸዋ ዞን የአውራ ጎዳና መንደር ነዋሪዎች ላይ ጥቃት መፈፀሙን ነዋሪዎች ገለፁ በዐማራ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን ምንጃር ሸንኮራ ወረዳ አውራ ጎዳና ወይም ቆርኬ ከተማ ላይ፣ የኦሮሚያ ክልል የጸጥታ ኃይሎች ፈጽመውታል ባሉት ጥቃት፣ ሰላማዊ ዜጎች እንደተገደሉና ከቀዬአቸው እንደተፈናቀሉ፣ የአካባቢው ባለሥልጣናት እና ተጎጂዎች አስታወቁ፡፡ በ“ኦሮሚያ ልዩ ኀይል” እንደተፈጸመ በገለጹት ጥቃት፣ ከዐዲስ አበባ ወደ ጅቡቲ በሚወስደው አውራ ጎዳና ዳር የምትገኘዋ ከተማ ነዋሪዎች ንብረት እንደተዘረፈና እንደወደመ፣ በሕይወት የተረፉትም እንደተፈናቀሉ ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል፡፡ በዐማራ ክልል በኩል፣ በሰሜን ሸዋ ዞን ምንጃር ሸንኮራ ወረዳ የመስኖ እና አርብቶ አደር አካባቢ ልማት ጽ/ቤት ሓላፊ አቶ ሲራጅ አሊዬ አደም፣ ችግሩ የተከሠተው፣ ከትላንት በስቲያ እሑድ፣ “የኦሮሚያ ልዩ ኀይል አባላት፣ በከተማው ላይ ጥቃት መፈጸማቸውን ተከትሎ ነው፤” ብለዋል፡፡ ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ⤵️

ወራሪ በማለት ወረራን ወንጀል መሸፋፈን አይቻልም። ይሄንን ሀሳብ አንድ አክቲቪስት ይፃፈው እንጂ የኦሮሚያ ብልፅግና ሰዎች አውራ ጎዳናን ኮርኬ የሚል ስያሜ በመስጠት በOBN በኩል የወረራ እቅድ እንዳ
ወራሪ በማለት ወረራን ወንጀል መሸፋፈን አይቻልም። ይሄንን ሀሳብ አንድ አክቲቪስት ይፃፈው እንጂ የኦሮሚያ ብልፅግና ሰዎች አውራ ጎዳናን ኮርኬ የሚል ስያሜ በመስጠት በOBN በኩል የወረራ እቅድ እንዳላቸው ግልጽ አድርገዋል። ዛሬ አጋጣሚውን በመጠቀም ወረራ ፈፅመናል እያሉ ነው። አካባቢው ላይ በኦሮሚያ ልዩ ሀይል በርካታ ንፁሃን ዜጎች ተገድለዋል። በርካቶች ተፈናቅለዋል ሀብት ንብረታቸው ተዘርፏል።

በአማራ ክልል በፋኖ እና በመከላከያ መካከል ባለው ውጊያ ሳቢያ በንፁሃን ላይ የሚፈፀመው ጥቃት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል። በሰ/ሸዋ ዞን በአንኮበር እና በመንዝ ቀያ ወረዳዎች ንፁሃን ዜጎች ጥቃት እንደተፈፀመባቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ገልፀዋል። በአንኮበር ወረዳ አንዲት እናት ልጇ ሊወሰድ ሲል ጩኸት በማሰማቷ ከጀርባዋ በተተኮሰባት ጥይት ከጀርባዋ ተመታ ህይወቷ ሲያልፍ ልጇ ደግሞ ለምን እናቴን ገደላችሁ ብሎ በመቃወሙ ልጁ ላይ በተተኮሰበት ጥይት እግሩን ተመቶ በደብረብርሃን ሆስፒታል እየታከመ እንደሆነ ተሰምቷል። የእናትየዋ አስከሬን ከሁለት ቀን በላይ ቢሆነውም መቅበር እንዳልተቻለ ተነግሯል። በመንዝ ቀያ ቁጥራቸው ከ15 በላይ የሆነ ንፁሃን ዜጎች መገደላቸው ታውቋል።

#Update በአንኮበር በፋኖ እና በመከላከያ መካከል የተኩስ ልውውጥ እየተደረገ መሆኑን የአከባቢው ነዋሪዎች ገለፁ። የአንኮበር ወረዳ ከተማ ጎረቤላ በፋኖ ቁጥጥር ስር መዋሏን ጠቅሰው በአሁኑ ሰዓት ከደብረብርሃን 30 ኪ.ሜ ርቀት ቁንዲ የተባለች ቦታ ላይ የተኩስ ልውውጥ እየተካሄደ እንደሆነ ነዋሪዎች ገልፀዋል።

ከደብረብርሃን 30 ኪ.ሜ ርቀት ቁንዲ ላይ በመከላከያ እና በፋኖ መካከል ውጊያ እየተካሄደ ነው።

በማንነታችንና በቋንቋችን እየተፈናቀልን ነው! የደብረብርሃን ከተማ ከንቲባ ''አቶ ካሳሁን እምቢያለ'' በማንነታችን ምናልባትም ለሀገረ መንግስቱ ኢትዮጵያ ፀንታ እንድትቆም ስላደረግን ይመስለኛል በሁሉም አቅጣጫ ጫናው ብርታቱ እየጨመረ መጥቷል። በማንነታችን በቋንቋችን እየተፈናቀልን እንገኛለን! ይሄ የድሃ ሀሳብ ምናልባትም ያላዋቂዎች ተልዕኮ እንደሆነ እንገነዘባለን። የቱንም ያክል ልንፈተንና ልንገፋ እንችላለን። የአማራ ህዝብ ትላንትም ሲፈተን ነው የቆየው ዛሬም እየተፈተነ ነው ነገም መፈተኑ አይቀሬ ነው። ነገር ግን የአማራ ህዝብ የጠዋት ጤዛ አይደለም በማንም አልፎ ሒያጅ ዱካ አይረግፍም። የአባቶቻችን እሴት የእነ እምዬ ምኒልክ እሴት በእኔም በእናንተም በሁላችንም ልብ ውስጥ ያለ ስለሆነ ነው። አባቶቻችን ለማንነት፣ለክብር እና ለኢትዮጵያ ሲሉ ሞተው አሳይተውናል። ለማንነት፣ለክበር፣ለሀገር መሞት የአባቶቻችን እሴት ስለሆነ በክብራችን በማንነታችን፣በክብራችን እና በኢትዮጵያችን ለሚመጣሁ ሁሉ መክፈል ያለብንን መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆናችንን ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ። የሚያዋጣን አንድ መሆን ነው! በወንድማማችነት መደጋገፍ ነው! ሰው መሆን ነው! ኢትዮጵያዊነት ነው! ኢትዮጵያን ለብቻው ሊያደርጋት የሚችል ማንም ሀይል የለም። ትናንት ከአባቶቻችን በመስዋዕትነት የተረከብናትን ሀገር ነገ ለልጆቻችን ለማስረከብ ሁላችንም በአስተሳሰብ ብቻ ሳይሆን በተግባር አንድ ሆነን የአባቶቻችን ልጆች ሆነን ኢትዮጵያ እና ህዝቦቿን እንድናሻግር አሳስባለሁ። የአማራ ህዝብ ምናልባትም ነገ አይቀሬ ፈተና ሊፈተን ይችላል። ምናልባትም ካሳለፍነው በተለየ ምዕራፍ ልናሳልፍ እንችላለን። በፈተና ውስጥ ፅናት በፈተና ውስጥ ድል በፈተና ውስጥ አማራነት በፈተና ውስጥ ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት ብለን ትናንት እነ እምዬ ምኒልክ ምድራዊ ዘላለማዊ አባታችን ያስረከቡንን ሀገር እኛ መክፈል ያለብንን መስዋዕትነት ከፍለን ለትውልድ ልናስተላልፍ ልንዘጋጅ ይገባል። ኢትዮጵያን የማያውቋት የአባቶቻችንን ለሀገር፣ለክብር መሞትን የማያውቁ ግብዞች ኢትዮጵያን ለማፍረስ የተሰራችበትን ማገር እየመዘዙ ይገኛሉ። እነዚህን አካላት የምንታገል ከሆነ ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነትን የምናሻግር ከሆነ ከምንጊዜውም በላይ እኔና እናንተ የጎደለን አንድነት ነው። ከምንጊዜውም ጊዜ በላይ አንድ መሆን የሚያስፈልገን ወቅት ላይ ነው ያለነው። አንድ ስንሆን እንደመጣለን፣እንሰማለን አንድ ስንሆን እናሸንፋለን አንድ ከሆንን እንሻገራለን። ስለሆነም የሚያለያዩን የማያግባቡን ነገሮች ይኖራሉ በአመራሩም በህዝቡም ነገር ግን ምንም ልዩነት ቢኖር ማንነት፣ክብር ሀገር ይቀድማል። እኛ አመራሮች ልናጠፋ እንችላለን ነገር ግን በማንነት እና በቋንቋ ተለይቶ ከመፈናቀል፣ከመሰደድ ከመዋረድ በላይ ሌላ ነገር የለም። ልዩነታችን በጊዜ ይደርሳል እኛ አማራዎች ነን! እኛ ኢትዮጵያውያኖች ነን! ልዩነታችን ወደጎን ትተን ትላንት ሲፈትኑን ነበር። ዛሬም ደግሞ ከፈተናም አልፎ ሊቀብሩን የተዘጋጁ ሀይሎች ስላሉ እነዚህን ሀይሎች እረፉ ይቺ ሀገር የጋራችን ናት። ኢትዮጵያችን የሁላችንም ናት ማንም የግሉ ሊያደርጋት አይችልም ብለን በጋራ ቆመን አማራነትን ኢትዮጵያዊነትን ከፍ እንድናደርግ አንድ እንሁን እንተባበር እንሰባሰብ። የሚጠቅመን አንድ መሆኑ ነው! መንደርተኝነት፣ሰፈርተኝነት ዝቅ ያደርገናል። ያዋርደናል ያሳንሰናል እንጂ አያሻግረንም። አማራነትን ያደክመዋል ያቀጭጨዋል! ኢትዮጵያዊነትን ያጠፋ ካልሆነ አይጠቅምም። ይሄ ሀሳብ የባዕዳን ስለሆነ አንድ እንድንሆን ጥሪዬን አቀርባለሁ። የደብረብርሃን ከንቲባ አቶ ካሳሁን እምቢያለ! ሙሉ መረጃውን ለማዳመጥ ከታች ባለው ሊንክ ዩቲዩብ ላይ ይመልከቱ 📌https://youtu.be/jc4EEMQCfaw

#በድሬድዋ ዩንቨርስቲ የሚማሩ የአማራ ተወላጅ ተማሪዎች ጥቃት እየተፈፀመባቸው እንደሆነ ገለፁ!

የእምዬ ምኒልክን መታሰቢያ ሐውልት በትውልድ ቀያቸው እንገነባለን ስላልን የአዲስአበባን ጉዳይ የዘነጋነው የመሰላቸው ካሉ ተሳስተዋል! የደብረብርሃን ከተማ ከንቲባ አቶ ካሳሁን እምቢያለ ስለ ሐውልቱ ለታዳሚው ህዝብ ገለፃ አድርገዋል። በአማራ ህዝብ ላይ እየተፈፀመ ስላለፍ ግፍም ገለፃ አድርገዋል ክፍል ሁለት ይቀጥላል.... https://youtu.be/CRPeo_SxEaw