EOTC BOOK PDF FREE/(የኢ/ኦ/ተ-መጽሐፍት )
Open in Telegram
ይኽን መጽሐፍ ብላ! ሕዝ.3:1 ꧁-------------------------꧂ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ክርስትናን የሚሰብኩ የቅዱሳት መጽሐፍት ማሕደር!! በ #PDF Free "መጽሐፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል አታውቁምና ትስታላችሁ።" ማቴ 22፥29 የመጽሐፍ ቅዱስ አርዕስቶችና አንድምታዎች ፣ የአባቶች የሊቃውንት መጽሐፍት ይገኙበታል። ኑ ༒
Show more655
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ጥቅም አልባ እውቀት
"ክርስቲያናዊ ፍጹምነትን ለማግኘት የምትፈልግ ከሆነ ሕሊናህን ለነፍስህ ከማይጠቅም ወሬ መጠበቅ አለብህ፡፡ እንደ አጋጣሚ ሆኖ ዘመኑ የመረጃና የመረጃ ጥበብ ዘመን ነው፡፡ ዓለም በቲቪ ፣ በመጻሕፍት ፣ በጋዜጦች ብቻ ሳይሆን በመረጃ መረብ ጭምር የሚያጥለቀልቅ መረጃን ከምንጊዜው በላይ እያቀረበችልን ነው፡፡
ነገር ግን ይህ ጥቅም የለሽ መረጃ እኔ የአእምሮ ብክለት ብዬ ለምጠራው ችግር ይዳርጋል፡፡ በዚህ ዘመን ለሥራቸው ውጤታማነት ቢጠቅምም ባይጠቅምም መረጃን በመረጃነቱ ብቻ የሚፈልጉ የመረጃ ሱሰኞች አሉ፡፡
ለጥቅም አልባ እውቀት የመጀመሪያው ምሳሌ ዜናን ከመጠን በላይ መመልከት ነው፡፡...."
ተግባራዊ ክርስትና ከሚለው የተወሰደ!
🌼 ልጄ ሆይ እንደ ዘመኑ አንተም ተለወጥ
ልጄ ሆይ....... ወጣትነት ፈትኖህ፤ለስጋህ አድልተህ፤ነፍስህን አቀጭጨኻት ከአለም የኖርክበትን ዓመትህን ጥለኸው በንሰሐ እንደ ዘመኑ አንተም ተለወጥ።
ልጄ ሆይ ..... በአዲስ አመት ለአምላክህ የሚገባህን ግብር ትፈፅም ዘንድ በፍቅሩ አፀድ እንድትገኝ ካለመታዘዘ ተለወጥ።
ልጄ ሆይ ....... በአፈር ከሚሸነፈው ስጋዊ ዘርህ ወጥተህ ሰማያዊነትን ከሚያለብስህ ከማይጠፋው ሰማያዊ ዘር ክብረት ታደርግ ዘንድ ሰውን ካለመውደድ ጥላቻ ተለወጥ።
ልጄ ሆይ ...... በምክንያቶች ተደልለህ አፅዋማትን ዘለህ፤ምስጋናን ነፍገህ፥አገልግሎትን ንቀህ ከአለም ጫጫታ ውስጥ የዘፈቀውን ማንነትህ እንዳያጠፋህ እንደ ዘመኑ አንተም ተለወጥ።
ልጄ ሆይ ...... ዲያቢሎስ በቃል እንዳያስትህ፤በማማለል እንዳይጠልፍህ የመንጋውን ጠባቂ ቃልን ስማ፤ የመታዘዝን በረከት ታገኝ ዘንድ ከትምህክትህ እንደ ዘመኑ አንተም ተለወጥ።
ልጄ ሆይ .....ቀናት ሳይሆን መንፈስህ ይለወጥ፤ፀሐይ ሳትሆን የህይወት ጀንበርህ ይለወጥ።
ልጄ ሆይ ......ዕለታት አይሰልጥኑብህ፤ ዘመናት እስከ ሞትህ ጥግ ድረስ እስኪገፉህ ሳትጠብቅ አንተም እንደ ዘመንህ ተለወጥ
ልጄ ሆይ .....የእግዚአብሔር ፍቅር ለተከፈተ ልብ ቸር ነው ። ርህራሄው ጥልቅ ነው ። በአምሳሉ ፈጥሮሃል እና እንዳትጠፋ አንድያ ልጁን ለሞት አሳልፎ እስከመስጠት የደረስ ጥልቅ ፍቅር አሳይቷል ። ስለዚህ ከዘመንህ ቀድመህ ተለወጥ።
ልጄ ሆይ ...አዛኝቷን ተለማመን፤መላአኩን ተማለደው ፤ቀደምት ቅዱሳን አባቶችህን ጥራ፤ ፃድቃንን ዘክር እንጅ ላለመለወጥ ተማምለው ቀናት ብቻ ከሚለወጥባቸው ሰልፈኞች ተርታ አትገኝ ።
በንስሐ ወደ በረቱ የምንመለስበት ዘመን ይሁንልን! አሜን
🌻 መልካም አዲስ አመት ይሁንልን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
“አምላክ ወዶ ያጻፋቸውን መጻሕፍት መመልከት አታቋርጥ። እነርሱ በጠበበችው ጎዳና ትጓዝ ዘንድ ይመሩኻል። መርተውም ወደ ዘለዓለም ሕይወት ወደ መንግሥተ ሰማያት ያደርሱኻል።“
[ አባ ወግሪስ ]
አምላክ ወዶ ያጻፋቸውን መጻሕፍት መመልከት አታቋርጥ። እነርሱ በጠበበችው ጎዳና ትጓዝ ዘንድ ይመሩኻል። መርተውም ወደ ዘለዓለም ሕይወት ወደ መንግሥተ ሰማያት ያደርሱኻል።
[ አባ ወግሪስ ]
“ንዑ ናስተብጽአ ለማርያም
ኑና ማርያምን እናመስግናት
ነገረ ማርያም (Mariology) በቅድስት ቤተክርስቲያን ሰፊ ትምህርት ሲሆን፤ እመቤታችን በነገረ ድኅነት(soteriology) በነበራት ሱታፌ (ድርሻ) ምክንያት ነገረ ማርያም ከሁሉም ትምህርት ጋር የተያያይዘ ትምህርተ ሃይማኖት ነው። በተለይ በነገረ ሥጋዌ። ለዛሬ ቀዳሚት ሔዋንን እና ዳግሚት ሔዋን እመቤታችንን በንጽጽር እናያለን።
የጽሑፌ ዓላማ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በቀደሙት ቅዱሳን አበው አንደበት እና ትምህርት ማየት ሲሆን፤ ከዚኽ በፊት “ማርያም ማለት” በሚል ጽሑፌ የስሟን ትሩጉ ከመሠረታዊው ትምህርት ጋር ማስነበቤ ይታወሳል።
ቅዱስ ጳውሎስ በቀዳሚ በቆሮንቶስ መልእክቱ ስለ ጌታችን መድኅኒታችን ሲናገር ይኽውም በቀዳሚው አዳም የሆነብንን ውድቀት፤ መረገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ ስላዳነን ሲናገር “ሁለተኛ አዳም” ብሎታል። “አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙታን ተነሥቶአል። ሞት በሰው በኩል ስለ መጣ ትንሣኤ ሙታን በሰው በኩል ሆኖአልና።ሁሉ በአዳም እንደሚሞቱ እንዲሁ ሁሉ በክርስቶስ ደግሞ ሕያዋን ይሆናሉና” 1ቆሮር.15:21-22
በዘፍጥረት ላይ ቀዳሚ ሔዋን ለሰው ውድቀት ምክንያት እንደሆነች እናነባለን። በመሆኑም ኢየሱስ ክርስቶስ የሁለተኛውን አዳምን ቦታ ከወሰደ ማለትም ሁለተኛ አዳም ከተባለ የሔዋንን ቦታ ማን ወሰደ የሚለው ጥያቄ ይነሳል።
የጥንት ክርስቲያኖች እንደሚያምኑት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ይህንን ቦታ ትወስዳለች ይላሉ። ቀዳሚት ሔዋን ሰይጣንን አመነች፤ አዳምን ወደ ኃጢአት መራች ። ዳግሚት ሔዋን የመልአኩን ቃል አመነች። አምላክን በመውለድ መድኅኒትን ለዓለም ሰጠች ። ዳግሚት ሔዋን የሚለውን ጽንሰ ሐሳብ የቀደሙት የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት የገለጡበትና ያስተማሩበትን መንገድ በጥቂቱ እንግለጽ።
ሰማዕቱ ጀስቲን (100-165) መ/ክ/ዘ
ድንግል በምትሆን በቀዳሚት ሔዋን (ሔዋንን ከመውለዷ በፊት ማለት ነው) የእባቡን ምክር ጸንሳ አለመታዘዝና ሞትን አመጣች። ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግሊቱ ሰው ሆነ። በዓለም የነበረውን አለመታዘዝ ወደ ቀዳሚ ክብሩ መለሰችው ይላል። እመቤታችን ተስፋን ተቀበለች። የመልአኩን ቃል በሰማች ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ወደ እርሷ መጣ፤ የአርያም ክብር ከበባት፤ ከአንቺ የሚወለደው የእግዚአብሔር ልጅ ነው ባላት ጊዜ እንደቃልህ ይሁንልኝ በማለት መለሰችለት። (Dialogue with Trypho, 100, A.D. 160)
ቅዱስ ኤሬኔዎስ (ከ130-201 ዓ.ም)
መናፍቃንን በተቃወሙት ጽኁፉ “ቀዳሚ ሔዋን ባለመታዘዝ ታሰረች (ማእሰረ ሔዋን)። የቀደመው የሔዋን አለመታዘዝ እስር በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በመታዘዝ ተፈታ(የባርያይቱን መዋረድ አይቷልና እንዳለች) ጸሎተ ማርያም። ሔዋን በሳተው (መልአክ) እባብ ተመርታ ከእግዚአብሔር ፊት ተሰደደች፤ ዳግሚት ሔዋን ድንግል ማርያም ከመልአኩ ጋር በተነጋገረች ጊዜ ለዘላለማዊ ደስታ ማሰርያ ሆነች። ለቃሉም ታዛዥ ሆነች ። ድንግል ማርያም ለቀዳሚት ሔዋን ካሳ ሆነች በሔዋን ምክንያት የሰው ዘር በሞት ማሰሪያ ተይዞ፤ በዳግሚት ሔዋን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ምክንያት ዳግም ዳነ። የሔዋን ያለመታዘዝ ሚዛን በተቃራኒው በድንግል ማርያም ተስተካከለ” ይላል (Against Heresies, III.22.4, A.D. 180)
ተርቱልያን (ከ160-220 ዓ.ም›)
ሔዋን ገና ድንግል ሳለች የጠላትን ማጥመጃ ቃል ወደ ጆሮዋ በገባ ጊዜ፤ የሞትን ግድግዳ ገነባ። በዳግሚት ሔዋን (እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም) በእግዚአብሔር ቃል ሕይወት ተመሠረተ። በሰው ዘር የሚተላለፈው ኃጢአት ያለወንድ ዘር በመጽነስ ወደ ድኅነት አመጣችው። የጠብ ግድግዳ ፈረሰ። ሔዋን አባቡን እንዳመነች እመቤታችን መልአኩን አመነች። ሔዋን የእባቡን ቃል በማሕጸን አልጸነሰችውም፤ ነገር ግን የሐዘን እና ከገነት የመሰደድ ዘር ሆነባት በክፋት የሚጣሉ ልጆችን ወለደች (ቃየን አቤልን መግደሉን ሲያስታውስ)። እመቤታችን በተቃራኒው እስራኤልን የሚያድነውን ወለደች ። በሥጋ የገዛ ወገኖቹ ግን ሰቀሉት። (The Flesh of Christ, 17)
ጎርጎርዮስ ገባሬ መንክራት (213-270 ዓ.ም)
የሔዋንን አለመታዘዝ ሳስብ አለቅሳለሁ፤ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ፍሬ ሳስብ እንደገና እታደሳለሁ። የማይሞተው ወደ እኛ መጣ፤ የማይታይ፡ የማይመረመር፤ ከዘመናት በፊት የብርሃናት ብርሃን የአብ የባህርይ አንድያ ልጁ የእግዚአብሔር ቃል ከእመቤታችን ሥጋን ለብሶ የሰው ዘር ከኃጢአት ፡ከብልየት(ከእርጅና) ያድሰው ዘንድ ዳግማይ አዳም በእመቤታችን እቅፍ ሆነ (Homily Concerning the Holy Mother of God Ever-Virgin, 1)
ቅዱስ ጄሮም
ሞት በሔዋን በኩል መጣ። ነገር ግን ሕይወት በድንግል ማርያም በኩል መጣ (Epistle 22, 21)
ቅዱስ ኤፍሬም (306- 373 ዓ.ም)
በሔዋን የገነት ደጅ ተዘጋ፤ ዳግመኛም በድንግል ማርያም ተከፈተልን። (ወዳሴ ማርያም ዘሐሙስ)
አውግስጢኖስ (354-430 ዓ.ም)
ጌታ ወንድ ሆኖ መጣ ከዚህ ጀርባ ትልቅ ምስጢር አለ።ሞት በሴቲቱ በኩል ስለገባ ነው ይላል።
እንግዲህ የቀደሙት ሊቃውንት እመቤታችን በነገረ ድኅነት ውስጥ ከቀዳሚ ሔዋን ጋር በማነጻጸር የተረጎሙበትን በአጭሩ መረዳት ያስፈልጋል።
መ/ር ንዋይ ካሳሁን
“ንዑ ናስተብጽአ ለማርያም
ኑና ማርያምን እናመስግናት
ነገረ ማርያም (Mariology) በቅድስት ቤተክርስቲያን ሰፊ ትምህርት ሲሆን፤ እመቤታችን በነገረ ድኅነት(soteriology) በነበራት ሱታፌ (ድርሻ) ምክንያት ነገረ ማርያም ከሁሉም ትምህርት ጋር የተያያይዘ ትምህርተ ሃይማኖት ነው። በተለይ በነገረ ሥጋዌ። ለዛሬ ቀዳሚት ሔዋንን እና ዳግሚት ሔዋን እመቤታችንን በንጽጽር እናያለን።
የጽሑፌ ዓላማ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በቀደሙት ቅዱሳን አበው አንደበት እና ትምህርት ማየት ሲሆን፤ ከዚኽ በፊት “ማርያም ማለት” በሚል ጽሑፌ የስሟን ትሩጉ ከመሠረታዊው ትምህርት ጋር ማስነበቤ ይታወሳል።
ቅዱስ ጳውሎስ በቀዳሚ በቆሮንቶስ መልእክቱ ስለ ጌታችን መድኅኒታችን ሲናገር ይኽውም በቀዳሚው አዳም የሆነብንን ውድቀት፤ መረገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ ስላዳነን ሲናገር “ሁለተኛ አዳም” ብሎታል። “አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙታን ተነሥቶአል። ሞት በሰው በኩል ስለ መጣ ትንሣኤ ሙታን በሰው በኩል ሆኖአልና።ሁሉ በአዳም እንደሚሞቱ እንዲሁ ሁሉ በክርስቶስ ደግሞ ሕያዋን ይሆናሉና” 1ቆሮር.15:21-22
በዘፍጥረት ላይ ቀዳሚ ሔዋን ለሰው ውድቀት ምክንያት እንደሆነች እናነባለን። በመሆኑም ኢየሱስ ክርስቶስ የሁለተኛውን አዳምን ቦታ ከወሰደ ማለትም ሁለተኛ አዳም ከተባለ የሔዋንን ቦታ ማን ወሰደ የሚለው ጥያቄ ይነሳል።
የጥንት ክርስቲያኖች እንደሚያምኑት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ይህንን ቦታ ትወስዳለች ይላሉ። ቀዳሚት ሔዋን ሰይጣንን አመነች፤ አዳምን ወደ ኃጢአት መራች ። ዳግሚት ሔዋን የመልአኩን ቃል አመነች። አምላክን በመውለድ መድኅኒትን ለዓለም ሰጠች ። ዳግሚት ሔዋን የሚለውን ጽንሰ ሐሳብ የቀደሙት የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት የገለጡበትና ያስተማሩበትን መንገድ በጥቂቱ እንግለጽ።
ሰማዕቱ ጀስቲን (100-165) መ/ክ/ዘ
ድንግል በምትሆን በቀዳሚት ሔዋን (ሔዋንን ከመውለዷ በፊት ማለት ነው) የእባቡን ምክር ጸንሳ አለመታዘዝና ሞትን አመጣች። ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግሊቱ ሰው ሆነ። በዓለም የነበረውን አለመታዘዝ ወደ ቀዳሚ ክብሩ መለሰችው ይላል። እመቤታችን ተስፋን ተቀበለች። የመልአኩን ቃል በሰማች ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ወደ እርሷ መጣ፤ የአርያም ክብር ከበባት፤ ከአንቺ የሚወለደው የእግዚአብሔር ልጅ ነው ባላት ጊዜ እንደቃልህ ይሁንልኝ በማለት መለሰችለት። (Dialogue with Trypho, 100, A.D. 160)
ቅዱስ ኤሬኔዎስ (ከ130-201 ዓ.ም)
መናፍቃንን በተቃወሙት ጽኁፉ “ቀዳሚ ሔዋን ባለመታዘዝ ታሰረች (ማእሰረ ሔዋን)። የቀደመው የሔዋን አለመታዘዝ እስር በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በመታዘዝ ተፈታ(የባርያይቱን መዋረድ አይቷልና እንዳለች) ጸሎተ ማርያም። ሔዋን በሳተው (መልአክ) እባብ ተመርታ ከእግዚአብሔር ፊት ተሰደደች፤ ዳግሚት ሔዋን ድንግል ማርያም ከመልአኩ ጋር በተነጋገረች ጊዜ ለዘላለማዊ ደስታ ማሰርያ ሆነች። ለቃሉም ታዛዥ ሆነች ። ድንግል ማርያም ለቀዳሚት ሔዋን ካሳ ሆነች በሔዋን ምክንያት የሰው ዘር በሞት ማሰሪያ ተይዞ፤ በዳግሚት ሔዋን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ምክንያት ዳግም ዳነ። የሔዋን ያለመታዘዝ ሚዛን በተቃራኒው በድንግል ማርያም ተስተካከለ” ይላል (Against Heresies, III.22.4, A.D. 180)
ተርቱልያን (ከ160-220 ዓ.ም›)
ሔዋን ገና ድንግል ሳለች የጠላትን ማጥመጃ ቃል ወደ ጆሮዋ በገባ ጊዜ፤ የሞትን ግድግዳ ገነባ። በዳግሚት ሔዋን (እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም) በእግዚአብሔር ቃል ሕይወት ተመሠረተ። በሰው ዘር የሚተላለፈው ኃጢአት ያለወንድ ዘር በመጽነስ ወደ ድኅነት አመጣችው። የጠብ ግድግዳ ፈረሰ። ሔዋን አባቡን እንዳመነች እመቤታችን መልአኩን አመነች። ሔዋን የእባቡን ቃል በማሕጸን አልጸነሰችውም፤ ነገር ግን የሐዘን እና ከገነት የመሰደድ ዘር ሆነባት በክፋት የሚጣሉ ልጆችን ወለደች (ቃየን አቤልን መግደሉን ሲያስታውስ)። እመቤታችን በተቃራኒው እስራኤልን የሚያድነውን ወለደች ። በሥጋ የገዛ ወገኖቹ ግን ሰቀሉት። (The Flesh of Christ, 17)
ጎርጎርዮስ ገባሬ መንክራት (213-270 ዓ.ም)
የሔዋንን አለመታዘዝ ሳስብ አለቅሳለሁ፤ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ፍሬ ሳስብ እንደገና እታደሳለሁ። የማይሞተው ወደ እኛ መጣ፤ የማይታይ፡ የማይመረመር፤ ከዘመናት በፊት የብርሃናት ብርሃን የአብ የባህርይ አንድያ ልጁ የእግዚአብሔር ቃል ከእመቤታችን ሥጋን ለብሶ የሰው ዘር ከኃጢአት ፡ከብልየት(ከእርጅና) ያድሰው ዘንድ ዳግማይ አዳም በእመቤታችን እቅፍ ሆነ (Homily Concerning the Holy Mother of God Ever-Virgin, 1)
ቅዱስ ጄሮም
ሞት በሔዋን በኩል መጣ። ነገር ግን ሕይወት በድንግል ማርያም በኩል መጣ (Epistle 22, 21)
ቅዱስ ኤፍሬም (306- 373 ዓ.ም)
በሔዋን የገነት ደጅ ተዘጋ፤ ዳግመኛም በድንግል ማርያም ተከፈተልን። (ወዳሴ ማርያም ዘሐሙስ)
አውግስጢኖስ (354-430 ዓ.ም)
ጌታ ወንድ ሆኖ መጣ ከዚህ ጀርባ ትልቅ ምስጢር አለ።ሞት በሴቲቱ በኩል ስለገባ ነው ይላል።
እንግዲህ የቀደሙት ሊቃውንት እመቤታችን በነገረ ድኅነት ውስጥ ከቀዳሚ ሔዋን ጋር በማነጻጸር የተረጎሙበትን በአጭሩ መረዳት ያስፈልጋል።
መ/ር ንዋይ ካሳሁን
