en
Feedback
Joyfull Gifts

Joyfull Gifts

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel Joyfull Gifts

Channel Joyfull Gifts (@joyfullgift) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 14 615 subscribers, ranking 6 425 in the Religion & Spirituality category and 1 946 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 14 615 subscribers.

According to the latest data from 05 January, 2025, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -174 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

Channel description not provided.

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 06 January, 2025), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

14 615
Subscribers
No data24 hours
-217 days
-17430 days
Posts Archive
የዛሬው ቀን ስም" ሊጣላ የማለ አሥራ አንደኛው ጣት የታለ ይላል" ይባላል። ጭልፊቶች ተሰብስበው ጫጩቶቿን ሊነጥቋት ሲያንዣብቡ ያየች ዶሮ " ምን ፈለጋችሁ?" አለቻቸው። "የጫጩቶችሽ ነገር ያሳስበናል" አሏት ። ነገሩ ገርሟት አሽካካችና፧ ምን ብትላቸው ጥሩ ነው "አለማለቃቸው ነው ያሳሰባችሁ?" ሊጣላ የማለ፣ አሥራ አንደኛው ጣት የታለ? ይላል አሉ። የተመድ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ ስታይል።

የዛሬው ቀን ስም "ኢትዮጵያ ይሆናል" ይባላል። C'est la lutte finale Groupons-nous, et demain, L'Internationale, Sera le ethiopie. የፍጻሜው ጦርነት ነው፣ ሁሉም ዘብ ይቁም በቦታው ፤ ኢንተርናሲዮናል፣ ኢትዮጵያ ይሆናል። #NoMore

የዛሬው ሌሊት ስም "መሐረቤን ያያችሁ" ይባላል። የተመድ የሰብአዊ መብት ምክር ቤት፣ ከዚህ በፊት ከኢሰመኮ ጋር ያደረገውን ጥናት ረስቶ "መሐረቤን ያያችሁ" እየተጫወተ ነው። መሐረቡን አይተናል። ጨዋ
የዛሬው ሌሊት ስም "መሐረቤን ያያችሁ" ይባላል። የተመድ የሰብአዊ መብት ምክር ቤት፣ ከዚህ በፊት ከኢሰመኮ ጋር ያደረገውን ጥናት ረስቶ "መሐረቤን ያያችሁ" እየተጫወተ ነው። መሐረቡን አይተናል። ጨዋታው ፈርሷል። የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ጥሼ እወስንባችኋለሁ ካለ ደግሞ "ውሻ ምን አገባት ከእርሻ?" የሚለውን እንደ #NoMore እንዘምትበታለን!

ተኩላው ተኩላ በጎችን ሁለት ጊዜ ነው የሚያጠቃቸው፡፡ በሩቁና በቅርቡ፡፡ በሩቁ፣ ተራራ ላይ ወጥቶ መጥፎውን ጠረኑን ወደ ታች በነፋሱ መምጫ በኩል ይለቅባቸዋል፡፡ በጎቹም ጠረኑን ስለሚያውቁት በፍርሃት ይርበደበዳሉ፡፡ በዚህ መጣ በዚያ መጣ የሚለውን ግን ስለማይለዩት ፍርሃቱ ይተርፋቸዋል፡፡ አንዳንዶቹ በጠረኑ ሽታ ፈርተው አካባቢውን ጥለው ይጠፋሉ፡፡ ሌሎቹ ደግሞ ግራ ተጋብተው ባሉበት መስክ መረጋጋት ይሳናቸዋል፡፡ በተለይም ደግሞ ገላግልቱ ልምድ ስለሌላቸው በጣም ይሸበራሉ፡፡ በዚህ አጋጣሚ በተነዛው ሽታ ተደናግጠው መስኩን ጥለው ከሚፈረጥጡት ገላግልት የተወሰኑትን ተኩላው ያለ ድካም ይነጥቃል፡፡ የተኩላውን ጠባይ ያላወቁት ጠቦቶቹ በአካባቢያቸው ያገኙትን የራሳቸውን ወገን ተኩላ እየመሰላቸው መውጋት ይጀመራሉ፡፡ በዚህ መሐል ተወግቶና ተዳክሞ የሚወድቅ ጠቦት ይገኛል፡፡ አትራፊው ግን ያው ተኩላ ብቻ ነው፡፡ ሽብር በመንዛት በበቂ ሁኔታ ያልተሳካለት ከሆነ ደግሞ፣ ተኩላው ተራራው ላይ ሆኖ ይመለከትና ቁልቁል ወደ መስኩ ከሰሜን ወደ ደቡብ ይሸመጥጣል፡፡ ያን ጊዜ በጎቹ በፍርሃት ለሁለት ይከፈላሉ፡፡ ቀጥሎ ደግሞ ከምሥራቅ ወደ ምዕራብ ይሸመጥጣል፡፡ አሁን ደግሞ በጎቹ ለአራት ይከፈላሉ፡፡ እንዲህ እንዲህ እያለ ለስድስት፣ ለስምንት፣ ለአሥር፣ ለአሥራ ሁለት፣ ይበታትናቸዋል፡፡ በዚህ መካከል ግርግር ይፈጠራል፡፡ አካባቢው ይሸበራል፤ የበረታ ይሮጣል፤ የደከመ ያዘግማል፤ የተደናገረ ባለበት ይቆማል፡፡ ተኩላውም ያለ ብዙ ድካም ከግርግሩ ያተርፋል፡፡ የወያኔ ስልት የተኩላ ስልት ነው፡፡ አንድም በሽብር ወሬ ይበታትናል፤ አንድም ራሱ ገብቶ ይከፋፍላል፡፡ በጎች ከተኩላ የሚተርፉት በሁለት መንገድ ብቻ ነው፡፡ አንደም የተኩላውን ጠረን ዐውቀው ነቅተው ከጠበቁት፤ አንድም ሁሉም በአንድነት ሰብሰብ ብለው፤ ቀንዳቸውን ወድረው ከጠበቁት፡፡ ያኔ ተራራው ላይ ሆኖ ነገሩን ይገመግምና፡- በጎች፣ ካልተከፋፈሉ ወይ ካልተሸበሩ ርሃብ ነው ጠኔ ነው የተኩላው አዳሩ፤ ብሎ እያንጎራጎረ ወደ ዱሩ ይመለሳል፡፡ በተኩላው ወያኔ ላይ እንወቅበት፡፡

ተኩላው ተኩላ በጎችን ሁለት ጊዜ ነው የሚያጠቃቸው፡፡ በሩቁና በቅርቡ፡፡ በሩቁ፣ ተራራ ላይ ወጥቶ መጥፎውን ጠረኑን ወደ ታች በነፋሱ መምጫ በኩል ይለቅባቸዋል፡፡ በጎቹም ጠረኑን ስለሚያውቁት በፍርሃት ይርበደበዳሉ፡፡ በዚህ መጣ በዚያ መጣ የሚለውን ግን ስለማይለዩት ፍርሃቱ ይተርፋቸዋል፡፡ አንዳንዶቹ በጠረኑ ሽታ ፈርተው አካባቢውን ጥለው ይጠፋሉ፡፡ ሌሎቹ ደግሞ ግራ ተጋብተው ባሉበት መስክ መረጋጋት ይሳናቸዋል፡፡ በተለይም ደግሞ ገላግልቱ ልምድ ስለሌላቸው በጣም ይሸበራሉ፡፡ በዚህ አጋጣሚ በተነዛው ሽታ ተደናግጠው መስኩን ጥለው ከሚፈረጥጡት ገላግልት የተወሰኑትን ተኩላው ያለ ድካም ይነጥቃል፡፡ የተኩላውን ጠባይ ያላወቁት ጠቦቶቹ በአካባቢያቸው ያገኙትን የራሳቸውን ወገን ተኩላ እየመሰላቸው መውጋት ይጀመራሉ፡፡ በዚህ መሐል ተወግቶና ተዳክሞ የሚወድቅ ጠቦት ይገኛል፡፡ አትራፊው ግን ያው ተኩላ ብቻ ነው፡፡ ሽብር በመንዛት በበቂ ሁኔታ ያልተሳካለት ከሆነ ደግሞ፣ ተኩላው ተራራው ላይ ሆኖ ይመለከትና ቁልቁል ወደ መስኩ ከሰሜን ወደ ደቡብ ይሸመጥጣል፡፡ ያን ጊዜ በጎቹ በፍርሃት ለሁለት ይከፈላሉ፡፡ ቀጥሎ ደግሞ ከምሥራቅ ወደ ምዕራብ ይሸመጥጣል፡፡ አሁን ደግሞ በጎቹ ለአራት ይከፈላሉ፡፡ እንዲህ እንዲህ እያለ ለስድስት፣ ለስምንት፣ ለአሥር፣ ለአሥራ ሁለት፣ ይበታትናቸዋል፡፡ በዚህ መካከል ግርግር ይፈጠራል፡፡ አካባቢው ይሸበራል፤ የበረታ ይሮጣል፤ የደከመ ያዘግማል፤ የተደናገረ ባለበት ይቆማል፡፡ ተኩላውም ያለ ብዙ ድካም ከግርግሩ ያተርፋል፡፡ የወያኔ ስልት የተኩላ ስልት ነው፡፡ አንድም በሽብር ወሬ ይበታትናል፤ አንድም ራሱ ገብቶ ይከፋፍላል፡፡ በጎች ከተኩላ የሚተርፉት በሁለት መንገድ ብቻ ነው፡፡ አንደም የተኩላውን ጠረን ዐውቀው ነቅተው ከጠበቁት፤ አንድም ሁሉም በአንድነት ሰብሰብ ብለው፤ ቀንዳቸውን ወድረው ከጠበቁት፡፡ ያኔ ተራራው ላይ ሆኖ ነገሩን ይገመግምና፡- በጎች፣ ካልተከፋፈሉ ወይ ካልተሸበሩ ርሃብ ነው ጠኔ ነው የተኩላው አዳሩ፤ ብሎ እያንጎራጎረ ወደ ዱሩ ይመለሳል፡፡ በተኩላው ወያኔ ላይ እንወቅበት፡፡

የዛሬው ቀን ስም "የቁንጫ መላላጫ" ይባላል። ሒዊ በዚህ ሄድኩ፣ ያንን ያዝኩ፣ ይሄንን ዘለልኩ፤ ጂኦግራፊ ተማርኩ፣ ቦታ ቀየርኩ፤ ትላለች። ነገሩ ይሳካል ወይ? ቢሉ፤ ከቁንጫ መላላጫ ይገኛል ወይ?
የዛሬው ቀን ስም "የቁንጫ መላላጫ" ይባላል። ሒዊ በዚህ ሄድኩ፣ ያንን ያዝኩ፣ ይሄንን ዘለልኩ፤ ጂኦግራፊ ተማርኩ፣ ቦታ ቀየርኩ፤ ትላለች። ነገሩ ይሳካል ወይ? ቢሉ፤ ከቁንጫ መላላጫ ይገኛል ወይ?

የዛሬው ሌሊት ስም "የሞኝ ዘፈን" ይባላል። ኒውዮርክ ታይምስ(ኒታ) "ኖቤል ኖቤል" ብሎ ታንቆ ሊሞት ነው። ኖቤል ብርቅ ነው እንዴ! ኒታ ኖቤልን የሚያነሣውን ያህል የሽልማት ድርጅቱ ራሱ አንሥቶት አያውቅም። "የሞኝ ዘፈን ሁልጊዜ አበባዬ" አሉ።

የዛሬው ቀን ስም "ፍሬን ብጠሳ"ይባላል። የአራዳ ልጆች "ሒዊ ፍሬን በጥሳለች" ይላሉ። ፍሬን የበጠሰ መኪና ያሳፈረውንና መንገደኛውን ይገድላል። ያገኘውን ንብረት ያወድማል፤ በመጨረሻም ራሱን ይገለብጣ
የዛሬው ቀን ስም "ፍሬን ብጠሳ"ይባላል። የአራዳ ልጆች "ሒዊ ፍሬን በጥሳለች" ይላሉ። ፍሬን የበጠሰ መኪና ያሳፈረውንና መንገደኛውን ይገድላል። ያገኘውን ንብረት ያወድማል፤ በመጨረሻም ራሱን ይገለብጣል። ባሉካው ግን ሩቅ ሆኖ ነው ዜናውን የሚሰማው።

የዛሬው ሌሊት ስም "አስወስጄ መጣሁ" ይባላል። ወያኔ ከደርግ ጋር ሲዋጋ 60ሺ ሰው ገብሬያለሁ ይላል። በሰሞኑ ጦርነት ግን ከዚህ በላይ ሳያልቅበት አይቀርም። የተረፈው ኃይል በአራት ማዕዘን ተከብቦ "አስወስጄ መጣሁ" የሚለውን እያንጎራጎረ ነው።

አንዳንድ የምዕራቡ ዓለም ሚዲያዎችን በተመለከተ አንዱ የገባንበት አረንቋ ይሄው ጠላትን የማመን በሽታ ነው፡፡ ከጠላቶቻችን ጋር መወገናቸውን እያወቅን እንኳን ልባችን ሊያምናቸው ይዳዳዋል፡፡ ተሰልበናልና፡፡ ጀግና ሕዝብ ግን የሚያምንበትን ይሠራል፤ የሚሠራውንም ያምናል፤ ራሱንም ያምናል፡፡ ጠላቱን ግን ይጠራጠራል፡፡ በክሥተት ሳይሆን በመርሕ ላይ አቋም ይይዛል፡፡

ጠላትን ማመን በጦርነት ሂደት ውስጥ ተዋጊዎች ከሚፈጠርባቸው ወይም እንዲፈጠርባቸው ከሚደረጉ ሥነ ልቡናዊ ጫናዎች መካከል አንዱ ጠላትን ማመን ነው፡፡ የሚገድልህን፣ የሚያጠፋህንና የሚያወድምህን ጠላት መረጃዎች የመቀበልና የራስህን መረጃዎች የማጣጣል አባዜ፡፡ ጠላት በጦር መሣሪያዎቹ አማካኝነት ከሚያደርሳቸው ጉዳቶች በላይ ለጠላት የሚጠቅመው በሚጎዳቸው ወገኖች ዘንድ ለመታመን መቻሉ ነው፡፡ ጠላትን ማመን በሦስት ምእራፍ የሚዳብር አደገኛ ሥነ ልቡና ነው፡፡ የመጀመሪያው ምእራፍ ራስን መጠራጠር ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ጠላትን ማድነቅ ነው፡፡ ሁለቱ ተደምረው ጠላትን ወደ ማመን ያሻግሩናል፡፡ ራስን መጠራጠር የሁለት ነገሮች ውጤት ነው፡፡ የአፍራሽ ፕሮፓጋንዳ እና የተሳሳተ ግምገማ፡፡ አፍራሽ ፕሮፓጋንዳ ከጠላት በኩል የሚሠነዘር ነው፡፡ በተደጋጋሚና ተጠየቃዊ በሆነ መልኩ የሚወርድ የፕሮፓጋንዳ ናዳ ሲሆን ዓላማው የቆሙበትን መሬት ማጠራጠር ነው፡፡ በተለይ ደግሞ ፍናፍንት ፕሮፓጋንዳ በጣም ጎጂ ነው፡፡ ፍናፍንት ፕሮፓጋንዳ ማለት በጥቂት እውነት ላይ የተመሠረተ ፕሮፓጋንዳ ነው፡፡ ይህ ፕሮፓጋንዳ ጠላትን ለማዳከምም ሆነ ወገንን ለመስለብ ሊውል የሚችል ነው፡፡ ሰይጣን ሔዋንን ‹ንግሥተ ሰማይ ወምድር› ብሎ ሲጠራት ከፊል እውነት ነበረው፡፡ ‹ንግሥተ ምድር› የሚለው እውነት ነው፡፡ ‹ንግሥተ ሰማይ› የሚለው ውሸት ነው፡፡: እርሷም የታለለችው በእውነቱ በኩል ውሸቱን አሾልኮ ስላስገባባት ነው፡፡ ፍናፍንት ፕሮፓጋንዳ በከፊል ወይም በጥቂት እውነት ላይ ተመርኩዞ የሚፈበረክ ፕሮፓጋንዳ ነው፡፡ ይሄንን ፕሮፓጋንዳ ራኬብም ተጠቅማበታለች፡፡ ራኬብ የኢያሪኮ ሰዎች ወደ ቤቷ መጥተው ‹ሁለቱ ሰላዮች ወደ ቤትሽ የታሉ?› ብለው ሲጠይቋት ‹አዎ ወደ ቤቴ ገብተው ነበር፤ ነገር ግን ወጥተው ሄዱ› አለቻቸው፡፡ የራኬብ ንግግር በከፊል እውነት ነው፡፡ ሰዎቹ ገብተው ነበር፡፡ ነገር ግን በላይኛው ደርብ ላይ በተልባ እግር ሥር ተሸሽገው ነበር እንጂ አልወጡም፡፡ የኢያሪኮ ሰዎች ግን ከፊል እውነት ስለነገረቻቸው ተቀብለዋት ወጥተው ሰዎቹን ሊያባርሩ ሄዱ፡፡ በሀገራችንም ወያኔ ከተጠቀመባቸው ፕሮፓጋንዳዎች አንዱ ፍናፍንት ፕሮፓጋንዳ ነው፡፡ ስለ መከላከያው፣ ስለ መንግሥት፣ ስለ ልዩ ኃይል፣ ስለ ፋኖ፣ ስለ ኤርትራ እና ስለ ራሱ ከሚነዛቸው ፕሮፓጋንዳዎች ብዙዎቹ በፍናፍንት ፕሮፓጋንዳ ስልት የተቀመሙ ናቸው፡፡ ወያኔ ሰዎችን ወደ ፕሮፓጋንዳ መረቡ የሚያስገባበት ጥቂት እውነታ ይይዛል፡፡ ልክ ዓሣ በብርብራ እንደ ማጥመድ፡፡ ብርብራው ለዓሣ ምግብ መሆኑ እውነት ነው፡፡ መቃጥኑ የተወረወረው ግን ዓሣውን ለመመገብ ሳይሆን ለማጥመድ ነው፡፡ ፍናፍንት ፕሮፓጋንዳም እንደዚሁ ነው፡፡ ወይም በወጥመድ አካባቢ ጥቂት ጥራጥሬ በትኖ ወፍ እንደ መያዝ ያለ፡፡ ‹በሬ ሆይ በሬ ሆይ ሳሩን አየህና ገደሉን ሳታይ› የተባለው ለዚሁ ዓይነት ፕሮፓጋንዳ ነው፡፡ የኛ ሀገር የምግብ አቀራረብና የፈረንጆች ይለያያል፡፡ እኛ ዶሮ ወጥ ብለን ካቀረብን የምናቀርበው ዶሮ ወጥ ነው፡፡ ያውም ከነ ድስቱ፡፡ ቢበዛ አይብ ከጎኑ ይኖራል፡፡ ፈረንጅ ግን ዶሮ አሮስቶ ብሎ ካቀረበ፣ ግማሹ አትክልት፣ ግማሹ ድንች፣ ግማሹ ሩዝ፣ ቀሪው ነው ዶሮ፡፡ ስሙ ነው ዶሮ፡፡ ያውም አንዲት አጥንት፡፡ ፕሮፓጋንዳውም በዚሁ መልክ የሚቀናበር ነው፡፡ በፈረንጅ የዶሮ አቀራረብ፡፡ የዚህ ፕሮፓጋንዳ ሰለባ የሆነ አካል ራሱን ይጠራጠራል፡፡ ከራሱ ወገን የሚያገኛቸውን መረጃዎችና የራሱንም ጥንካሬ ይጠራጠረዋል፡፡ የቆመበትን መሬት ማመን ያቅተዋል፡፡ ለዚህ ጥሩ ምሳሌ የሚሆነን የባለ በጉ ታሪክ ነው፡፡ በግ ሊሸጥ እየጎተተ የሚሄደውን ሰው ለመቀማት የተስማሙ ሌቦች ራቅ ራቅ ብለው ጠበቁት፡፡ የመጀመሪያው ሌባ መንገድ ላይ አገኘውና ‹ምነው ውሻ ትጎትታለህ› አለው፡፡ በግ ሻጩም ተገርሞ ዝም ብሎ አለፈው፡፡ እልፍ እንዳለ ሌላው ሌባ አግኝቶት ያንኑ ጥያቄ ደገመለት፡፡ አሁን በግ ሻጩ ተጠራጠረ፡፡ በጉን በእጁ አሻሽቶ አረጋገጠ፡፡ እልፍ እንዳለ ደግሞ ሦስተኛው ሌባ አግኝቶት እየተደነቀ ‹ምነው እርስዎ ካልጠፋ ነገር ውሻ ወደ ገበያ ይጎትታሉ› አለው፡፡ ይሄኔ በግ ሻጩ ራሱን ተጠራጠረ፡፡ ‹እንዴት ሦስት ሰዎች አንድ ነገር ይነግሩኛል፤ ተሳስቼ በግ የያዝኩ መስሎኝ ውሻ አምጥቻለሁ ማለት ነው› ብሎ አመነ፡፡ ከዚያ ውሻውን ፈትቶ በግ ፍለጋ ተመለሰ፡፡ በጉም የሌቦች ሲሳይ ሆነ፡፡ ራስን መጠራጠር ማለት እንደዚህ ነው፡፡ ፍናፍንት ፕሮፓጋንዳ በድግግሞሹና በዒላማው ላይ አተኩሮ በመሥራቱ የሚያስከትለው አሉታዊ ውጤት የቆምክበትን እውነት እንድትጠራጠረው ማድረግ ነው፡፡ እውነት ከክሥተት በላይ በመርሕ ላይ በመመርኮዝ የሚገኝ ነው፡፡ ለምሳሌ በጣልያን ወረራ ወቅት የኢትዮጵያ ጦር በጣልያን ጦር ተሸንፏል፡፡ ‹ኢትዮጵያ ተሸንፋለች› ወይም ‹ኢትዮጵያ አሸንፋለች› የሚለው ጉዳይ ግን የመርሕ ወይም የእምነት ጉዳይ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ተሸንፋለች ያሉ ለጣልያን አደሩ፡፡ ኢትዮጵያ ታሸንፋለች ብለው ያመኑ ደግሞ መሣሪያቸውን ወልውለው በረሐ ገቡ፡፡ ከአምስት ዓመት ትግል በኋላም የኢትዮጵያን አሸናፊነት አረጋገጡ፡፡ ዐርበኞቹ እውነታቸውን እንዲጠራጠሩ ብዙ ፕሮፓጋንዳ በፋሽስት ጣልያን በኩል ተሠርቷል፡፡ አንዳንዶቹም በሂደት ተሸንፈው ተቀብለውት ከእውነታቸው ወድቀዋል፡፡ ሌሎቹ ግን ከሚያዩት ይልቅ የሚያምኑትን ተቀብለው አሸንፈዋል፡፡ ማሸነፍ የመርሕ ጉዳይ መሆኑን የሚያሳየን አንድ ጥሩ ምሳሌ የሰማዕታት ታሪክ ነው፡፡ ሰማዕታት በወደረኞቻቸው ፊት ቀርበው፤ በዓላማቸው ጸንተው፤ አንገታቸውን ሳይሰብሩ፣ ልባቸውን ሳይከፍሉ፣ የሞትን ጽዋ ጠጥተዋል፡፡ ያሸነፈው ማነው? የተሠዉት ሰማዕታት ወይስ ገዳዮቻቸው? ሰማዕታቱ በዓላማቸውና በመርሐቸው በመጽናታቸው የተነሣ ሞትን አሸንፈውታል፤ የጠላቶቻቸውን ዓላማም አክሽፈውታል፡፡ ሞትንም ክብር አድርገውታል፡፡ ለዚህም ነው የሰማዕታት ታሪክ የአሸናፊዎች ታሪክ የሚሆነው፡፡ በፍናፍንት ፕሮፓጋንዳ የተሰለበ እና ራሱን የተጠራጠረ ሰው መጨረሻው ክሥተት ተከትሎ ጠላቱን ማድነቅ ይሆናል፡፡ ለጠላትህ ተገቢው ቦታ መስጠት አንድ ጉዳይ ነው፡፡ ጠላትን ማድነቅ ግን በሽታ ነው፡፡ ጠላትህን በራስህ መንገድ ማየት አንድ ጉዳይ ነው፡፡ ራስህን በጠላትህ ዓይን ማየት ግን ራስን አውርዶ ጠላትን ማድነቅና ማግዘፍ ያስከትላል፡፡ ‹እነርሱ እንዲህ ሲያደርጉ እኛ ግን..› የሚል የተሰለበ ትንታኔ ውስጥ ይጥላል፡፡ ባዶ እጁን የቆመውን ጠላትህን አንተው በኅሊናህ መሣሪያ ታስጣቀዋለህ፤ ታጀግነዋለህ፤ ተአምር ፈጣሪ ታደርገዋለህ፡፡ አለቀልህ ሲልህ አለቀልኝ ትላለህ፤ ጨረስኩት ሲልህ አለቀ ትላለህ፤ ደረስኩ ሲልህ መጣ ትላለህ፤ በመጨረሻም ትፈራዋለህ፡፡ ከፈራኸው ደግሞ ፍርሃት ወደሚወልደው ደካማ እምነት ትገባለህ፡፡ ያም ጠላትን ማመን ነው፡፡ ጠላቱን ያመነ ሰው ራሱን በጠላቱ መመዘኛ ወደ መገምገም ይገባል፡፡ በጠላቱ ዕቅድ ይመራል፡፡ ስለራሱ ከጠላቱ ለመስማት ልቡን ይሰጣል፡፡ ‹ለምን እንዲህ ሆነ?› ብሎ ሲጠይቅ ለዚያ ሐሳቡ መነሻው የጠላቱ መረጃ ይሆናል፡፡ ነገሮችን የሚበይንለት ጠላቱ ይሆናል፡፡ በመጨረሻ ማሰቢያውን ጠላቱ ይቆጣጠረዋል፡፡ ነገሮችን የሚሰይመውና ቅርጽ የሚሰጠው ጠላት ይሆናል፤ በህልውና ዘመቻው ወቅት የጦርነቱን ባህሪይ፣ ውጤት፣ የአሸናፊነት መለኪያና ድል በተመለከተ በጠላት ብያኔና ስያሜ ለመተንተን የሚሞክሩ ወገኖች የዚህ ተጠቂ ነበሩ፡፡ አጠቃላይ የጦርነቱን መገለጫ ከቦታ መያዝና መለቀቅ አንጻር ብቻ እንዲታይ ያደረገው ይሄ በሽታ ነበር፡፡

የዛሬው ሌሊት ስም "ገለፈንት" ይባላል። ገለፈንት፣ በአማራና አፋር ክልሎች ከወደሙት ሆስፒታሎች ይልቅ የሉሲ ጤንነት ያሳስባቸዋል።
የዛሬው ሌሊት ስም "ገለፈንት" ይባላል። ገለፈንት፣ በአማራና አፋር ክልሎች ከወደሙት ሆስፒታሎች ይልቅ የሉሲ ጤንነት ያሳስባቸዋል።

እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን! የጌታችንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደትን ምክንያት በማድረግ በሁሉም የስጦታ እቃዎቻችን ላይ ታላቅ ቅናሽ ማድረጋችንና ለደንበኞ
እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን! የጌታችንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደትን ምክንያት በማድረግ በሁሉም የስጦታ እቃዎቻችን ላይ ታላቅ ቅናሽ ማድረጋችንና ለደንበኞቻችን ልዩ ስጦታ ማዘጋጀታችንን ስንገልጽ በታላቅ ደስታ ነው! እንኳን አደረሳችሁ እየተባባላችሁ በስጦታ ተንበሽበሹ ... !!! ከታህሳስ 1 - 30 / 2014 ዓ.ም አትኒ ስጦታዎች ከደስታዎች ሁሉ ጋር! 0911692155 / @orderatni 0912384590 / @gedianasimos

የዛሬው ሌሊት ስም "የማሾ ላይ አይጥ" ይባላል። ሁሉም ነገር ተዘግቶባት መውጫ ያጣች አይጥ ማሾ ላይ ትንጠለጠላለች። አትተዋት አይጥ ናት። አትመታት ማሾ ነው። መጨረሻ ግን... የሒዊ የዛሬ ነገር።

የዛሬው ቀን ስም "ልብማ" ይባላል ። "ቅምቡርስ የት ትሄዳለህ መተማ፤ ትደርሳለህ? ልብማ!"

የዛሬው ሌሊት ስም "ስለምወድሽ ነው" ይባላል። ብመታሽ በርግጫ ባቀምስሽ በጥፊ፣ ስለምወድሽ ነው ቆንጂት አትከፊ፤ ጌች ስታይል። ከተሞቻችሁን ሁሉ ያወደምነው ስለምንወዳችሁ ነው።
የዛሬው ሌሊት ስም "ስለምወድሽ ነው" ይባላል። ብመታሽ በርግጫ ባቀምስሽ በጥፊ፣ ስለምወድሽ ነው ቆንጂት አትከፊ፤ ጌች ስታይል። ከተሞቻችሁን ሁሉ ያወደምነው ስለምንወዳችሁ ነው።

የዛሬው ቀን ስም "ውሻ ቀንድ ልታወጣ ሄዳ፤ ጆሮዋን ተቆርጣ ተመለሰች" ይባላል። ለሒዊ አመጣጥ እና አካሄድ።

ሆዴ ተላወሰ ተቃጠለ አንጀቴ ሲተርክ ሰምቼ እሸቴን እሸቴ
ሆዴ ተላወሰ ተቃጠለ አንጀቴ ሲተርክ ሰምቼ እሸቴን እሸቴ

የዛሬው ቀን ስም "በቃ አይጣፍጥም" ይባላል። የበሰለው ወይን ላይ ዘላ ዘላ መድረስ ያቃታት ቀበሮ "በቃ አይጣፍጥም" ብላ ተመለሰች። የጌች መግለጫ ስታይል።
የዛሬው ቀን ስም "በቃ አይጣፍጥም" ይባላል። የበሰለው ወይን ላይ ዘላ ዘላ መድረስ ያቃታት ቀበሮ "በቃ አይጣፍጥም" ብላ ተመለሰች። የጌች መግለጫ ስታይል።

የዛሬው ቀን ስም " ፈለቀ አይፎክሩ" ይባላል። በበዛብህ ጊዜ በሸዋ ሰነፍ ገብስ መጠቀም ተከልክሎ ነበር። ለንጉሡ ግብር እንጂ ለቆሎም ለገንፎም ለአጥሚትም አትጠቀሙ ተባለ። ይሄን ሊያስፈጽሙ ፈለቀ አይፎክሩ የተባሉ ሹም በየሠፈሩ ይዞሩ ነበር። ሕዝቡ ግን ተቃወመ። እርሳቸው ሳይደርሱ በደቦ ይወጣና ሰነፍ ገብሱን ቆልቶ ይወቅጠው ጀመር። ስሙም ሰነፍ ቆሎ ተባለ። ፈለቀ አይፎክሩ ሰነፍ ቆሎን ከመቆላትና ከመወቀጥ ሊያተርፉት አልቻሉም። እናም የአንኮበር አዝማሪ፦ ሀገሩ በሙሉ ምሎ ተማምሎ ቆልቶ እየፈጨው ነው ይሄን ሰነፍ ቆሎ አተርፋለሁ ብለው ቢዞሩ ቢዞሩ እፍኝ አያተርፉም ፈለቀ አይፎክሩ አለቻቸው አሉ። የኛ ዘመን ፈለቀ አይፎክሩ ከአሜሪካ እየመጡ ዙሪያችንን የሚዞሩ ናቸው።