en
Feedback
Joyfull Gifts

Joyfull Gifts

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel Joyfull Gifts

Channel Joyfull Gifts (@joyfullgift) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 14 615 subscribers, ranking 6 425 in the Religion & Spirituality category and 1 946 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 14 615 subscribers.

According to the latest data from 05 January, 2025, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -174 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

Channel description not provided.

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 06 January, 2025), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

14 615
Subscribers
No data24 hours
-217 days
-17430 days
Posts Archive
ወይ ኢትዮጵያ! የመከራሽን ያህል የጀግናሽ ብዛቱ፤ ዓይነቱ። አንቺን አሸንፋለሁ ብሎ መምጣት የጅልነት የመጨረሻ ደረጃ ነው። እስኪ እነ ኢክራምን የመሰሉ መንፈሰ ጠንካራ፣ ከእድሜያቸው የቀደሙ፣ ኢትዮጵ
ወይ ኢትዮጵያ! የመከራሽን ያህል የጀግናሽ ብዛቱ፤ ዓይነቱ። አንቺን አሸንፋለሁ ብሎ መምጣት የጅልነት የመጨረሻ ደረጃ ነው። እስኪ እነ ኢክራምን የመሰሉ መንፈሰ ጠንካራ፣ ከእድሜያቸው የቀደሙ፣ ኢትዮጵያን የተሸከሙ፣ እንደ ወርቅ በእሳት ተፈትነው ያለፉ ልጆች እያልሉሽ፣ ምን ልትሆኝ። እንኳንም በአንቺ ዘመን ተፈጠርኩ።

እንቡዝ በገድለ ተክለ ሃይማኖት የምናገኘው ሞተለሚ የተባለው የዳሞት ንጉሥ ለ25 ዓመታት እንቡዝ ሆኖ መኖሩን ይነግረናል። እንቡዝ የሚለውን ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ሲተረጉሙት፦ በቁሙ ልቡ የጠፋ፣ የተነበዘ፣ ነባዛ፣ ንብዝ፣ ቅብዝብዝ፣ ሰካር፣ እብድ፡፡ ሰብእ እንቡዛን፡፡ ብእሲት እንብዝት፡፡ እንቡዛነ ልብ ወድንቅዋነ እዝን (ኢሳ፳፭፡ ፭፡፡ ፶፬፡ ፮፡፡ መጽ፡ ምስ) ይሉታል። "ቅብዝብዝ ሰካር፣ እብድ" በሚሉት ነው አለቃ ለመበየን የሞከሩት። ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን ታሪክ በጻፉ ጊዜ ሁሉ "እንቡዝ" የሚለውን "Insane" ብለው ነው የሚተረጉሙት። ኦክስፎርድ የእንግሊዝኛ መዝገበ ቃላት "Insane" የሚለውን ሲፈታ "in a state of mind which prevents normal perception, behaviour, or social interaction; seriously mentally ill." ይላል። ሞተለሚ እንቡዝ ከሆነ በኋላ ያደረገው ነገር ይሄንን ትርጉም ያጠናክረዋል። ሥራው ያገኘውን ሁሉ ማጥፋት ነበር። ዓለም ልትጠፋ የሚገባት፣ ነገር ግን በደካሞች ምክንያት ሳትጠፋ የቀረች ትመስለው ነበር። እንቡዝን ለመግለጥ አለቃ ኪዳነ ወልድ የተጠቀሙባቸውን ቃላት መመርመር የተሻለ ነገሩን ያሳየናል። መቅበዝበዝ - የመንፈስ አለመረጋጋት ነው። ይሄንን መጀመሪያ የተጠቀመው ቃየል ነው። ቃየል ወንድሙን በግፍ ከገደለ በኋላ መንፈሱ ያልተረጋጋ በመሆኑ ቅብዝብዝ ነበር። ወያኔም ገና ከጅምሩ መንገዱ የቃየል ነበር። ሰካር የአእምሮ መናወዝ ነው። በተጠጣ አስካሪ ነገር የሚመጣ ነው። ወያኔ ጎሰኝነት የሚባል አስካሪ መጠጥ ወስዷል። እብደት የልቡና መናወጽ ነው። ሥነ ልቡናዊ በሽታ ነው። እንቡዝ ሰው የሚሠራውንና የሚናገረውን በጤነኛ አእምሮ መረዳት አይቻልም። ጤነኛ አእምሮ በተጠየቅ፣ በሞራል ሕግ፣ በመረጃ፣ በማስረጃ፣ በሐሳብ ሙግት፣ ወዘተ. ነው የሚረዳው። እንቡዝ ጋ ይህ ሁሉ የለም። መቅበዝበዝ፣ መስከርና ማበድ አንድ ላይ ሆነው የሚፈጥሩት ሰብእና ነው። ወያኔ እንቡዝ ስለሆነ ለጤነኛ ሰው የሚሰጡ ነገሮች አይስማሙትም። የሚናገረውና የሚሠራው ከሰብእና ውጭ የሆነው በንብዘቱ ምክንያት ነው። ለምን አደረገ? ብትሉ ንዴቱ እናንተን ያሳምማችኋል እንጂ ወያኔ አይሰማውም። ያንን ሁሉ ጥፋት ሠርቶ፣ ያንን ሁሉ ወጣት አስፈጅቶ ፈገግ ይላል። ለምን ቢሉ? እንቡዝሰ እንቡዝ ውእቱ። እንቡዝ ምን ብታደርጉት እንቡዝ ነው።

በኦሮምኛ አንድ አባባል አለ። Namni mana tokko ijaaru citaa wal hin saamu. አንድ ቤት የሚሠሩ ሰዎች ሣር አይሻሙም። ኢትዮጵያን መገንባት የሚቻለው በዚህ መርሕ ነው።

ታላቅ መንፈስዊ ጉባዔ! በቦሌ 24 ምዕራፈ ሰማዕታት ቅዱስ ገብርኤል ወቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን ። ሼር ሼር ሼር...
ታላቅ መንፈስዊ ጉባዔ! በቦሌ 24 ምዕራፈ ሰማዕታት ቅዱስ ገብርኤል ወቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን ። ሼር ሼር ሼር...

በሰላም ጊዜ ለጦርነት መዘጋጀት “Si vis pacem, para bellum” ጥንታዊ የሆነ የላቲን አባባል ነው። "ሰላምን ከፈለግህ ለጦርነት ተዘጋጅ" ማለት ነው። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የአሜሪካ መከላከያ ዋናው መርሕ መሆኑ ይነገራል። ጦርነት የተደረገበት ሀገር ምን እንደሚመስል ከአውሮፓ ያዩት አሜሪካውያን "ጦርነት ወደ አሜሪካ እንዳይመጣ፣ አሜሪካ ወደ ጦርነት ቀድማ ትሂድ" በሚል መርሕ ኖረዋል። የሀገራችን ገበሬም "የቅርብ ጠላት ያለው ሰው ጠመንጃውን አርቆ አይሰቅልም" ይላል። ወትሮ ዝግጁ መሆንን ሲያመለክት ነው። የኢትዮጵያና የኢትዮጵያውያን መጪው ዘመን መቃኘት ያለበት በዚህ መርሕ ቢሆን ጥሩ ነው። ሰላምን ፍለጋ ለጦርነት በመዘጋጀት። ኢኮኖሚያችን፣ ዲፕሎማሲያችን፣ መከላከያችንና አኗኗሯችን ወትሮ ዝግጁነትን መሠረት ማድረግ አለበት። አጥብቆና አልቆ ለክፉ ቀን በመዘጋጀት። ወጣቶቻችን በደኅና ጊዜ አምራች በክፉ ጊዜ ዘማች ሆነው በወታደራዊ ሰብእና መዘጋጀት አለባቸው። ኢኮኖሚያችን በክፉ ጊዜ ሊነቀነቅ የማይችል ሆኖ ዐቅሙን መገንባት አለበት። የምናመርተው ምርት መትረፍረፍ ያለበት ክፉ ጊዜን እንዲሻገር ሆኖ ነው። ብሔራዊ የውጭ ምንዛሬ ተቀማጫችንን ስናስብ ነገ በሩ ሁሉ ቢዘጋ እንድናስከፍትበት ሆኖ ነው። ሌሎችን ፈላጊ ብቻ ሳትሆን በሌሎችም ዘንድ ተፈላጊ ሀገር መገንባት ይገባናል። ለስፖርት፣ ለእግር ጉዞ፣ ለአካል ብቃትና ለወታደራዊ ሥልጠና ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጥ ማኅበረሰብ ሊኖረን ይገባል። "ዓለም አቀፍ" የምንላቸው ሚዲያዎች በክፉ ቀን እንደ ሸረሪት ጥለውን መጥፋታቸውን ካየን ዓለምን የሚያዳርስ ሚዲያ መገንባት ነው አማራጩ። በየሀገሩ የተበተነው ኢትዮጵያዊ ራሱን ለብቁ ዲፕሎማትነት ማሠልጠን አለበት። የየሀገሩ የኮሚኒቲ አደረጃጀቶች ለክፉ ቀን በሚሆን መልኩ ራሳቸውን ማዋቀር አለባቸው። የኢትዮጵያ ጉዳይ የአሜሪካና የአውሮፓ የምርጫ መወዳደሪያ መሆን ይገባዋል። መከላከያችንን መገንባት ያለብን ሦስተኛውን የዓለም ጦርነት እንዲያሸንፍ አርገን ነው። የራሳችንን መሣሪያ ማምረት፣ አዳዲስ ቴክኖሎጂ መፍጠር፣ ለመከላከያ የምንሰጠውን ክብርና ጥቅም ማሳደግ፣ መከላከያ የምርምርና የፈጠራ ማዕከል እንዲሆን ማድረግ አለብን። አንድነት የሀገራችን የመልካም ጊዜ ማረፊያ የክፉ ጊዜ ማለፊያ ነው። ከአንድነታችን በላይ ኢትዮጵያን ከመከራ የሚያሻግር ዕሴት የለም። በማንኛውም ሁኔታ የሕዝቡን አንድነት የሚያጠናክሩ ሥራዎችን ይሁነኝ ብለን መሥራት አለብን። አንድነት - ሰላምን ፍለጋ ለጦርነት የምንዘጋጅበት መርሕ ቋሚ ዓምድ ነው። ትምህርታችን እርስ በርስ እንድንተዋወቅና እንድንደናነቅ ማድረግ አለበት። ከሶማሌ ተነሥቶ አፋር እየሞተ፣ ከሐመር ተነሥቶ አማራ እየሞተ፣ ከጎንደር ተነሥቶ ወለጋ እየተሠዋ አይተናል። ከባሌ ተወልዶ ጎንደር፣ ከሶማሌ ተወልዶ አፋር፣ ከዋግ ተወልዶ ወለጋ፣ ከወላይታ ተወልዶ ሶማሌ ያለ ችግር የሚኖርበትንና የሚሠራበትን መፍጠር ግን ይቀረናል። በሚሞትበት ቦታ እንዳይኖርበት መከልከል ለክፉ ቀን አያዛልቀንምና! የጤና ተቋሞቻችን በዐቅምና በአደረጃጀት ክፉን ቀን እንዲሻገሩ ማብቃት አለብን። የሕክምና መሣሪያዎችንና መድኃኒቶችን በሀገር ውስጥ ማምረት ለነገ አይባልም። ተንቀሳቃሽ ክሊኒክና ሆስፒታል ሊኖረን ይገባል። ባህላዊ ሕክምና ለክፉ ቀን ብቁ ሆኖ ዛሬ ቦታ ሊያገኝ የግድ ነው። ብቻ ነገሩ ብዙ ነው፤ በጦርነት ጊዜ ለጦርነት መዘጋጀት ከባድ ነው። በሰላም ጊዜ ለጦርነት መዘጋጀት ግን ቢቻል ጦርነትን ያስቀራል፤ ባይቻል በአነስተኛ መሥዋዕትነት እና በፈጣን ጊዜ ለማሸነፍ ይጠቅማል። እሥራኤላውያን ተዘልለው በተቀመጡ ቁጥር መጠቃት ሰልችቷቸው ነው ወትሮ ዝግጁ የሆነ ማኅበረሰብ የገነቡት። አይመጣምን ትተን ይመጣልን አስበን፣ በሰዓታት ውስጥ ከአምራችነት ወደ ዘማችነት የሚቀየር ሕዝብና ሀገር እንገንባ። ከእንግዲህ ለእኛ ያለነው እኛው ነን። እንደ ሞኝ አንድ እባብ ሁለት ጊዜ ሊነድፈን፣ አንድ ዕንቅፋት ሦስቴ ሊመታን አይገባም። ሰላምን ከፈለግን ለጦርነት እንዘጋጅ።

ጊንጣውያን ጊንጥ ነፍሳት ስታይ መጀመሪያ መርዘኛ ትንፋሽ ትለቅባቸዋለች። ያን ጊዜ ነፍሳቱ ሽባ ይሆናሉ። ከዚያ ሽባ የሆኑትን ነፍሳት እንደፈለገች ትጫወትባቸዋለች። ሕዝባችንን መጀመሪያ ልቡን ሰልበው ዐቅመ ቢስ ያደርጉታል። ከዚያ ይነድፉታል። ይሄንን ታላቅ ሕዝብ ፈሪ፣ ድንጉጥ፣ አድርጋችሁ፤ እንደ ሕጻን ልጅ "መጡብህ፣ ደረሱብህ፣ ተነሡብህ" የሚሉ ጊንጣውያን ዓላማቸው ማስነደፍ ነው።

የዛሬው ሌሊት ስም "የትንኝ ግንባር" ይባላል። ትንኝ ቢሰበሰብ መግላሊት አይከፍትም። ለኢትዮጵያ ጠላቶች።

የዛሬው ቀን ስም "እያሾፉ መሞት" ይባላል። ሰውዬው ወንዝ ሲወስደው "እኔም ቆላ ልወርድ አስቤ ነበር" አለ አሉ።

የዛሬው ሌሊት ስም "መጥረቢያውን መሳል" ይባላል። ብልጥ ሰው ዝም ብሎ ሲጠርብ አይከርምም። ጠረብ ጠረብ ያደርግና፣ ፋታ ወስዶ፣ ለተሻለ ውጤት መጥረቢያውን ይስላል። ሞኝ እንጨቶች ደግሞ መጠረብ የቀረ ይመስላቸዋል። እየተሳለ ነው!

አካታችነት/Inclusiveness/ የብሔራዊ ውይይት አንዱ መስፈርት እንደመሆኑ መጠን የትግራይ ህዝብ እንዴት መወከል አለበት ብለው ያምናሉ?
Anonymous voting

ይህንን መጠይቅ ይሙሉ! ወያኔ ከኢትዮጵያ ጋር እያደረገ ባለው ጦርነት የትግራይ ማህበረሰብ በአብዛኛው ከወያኔ ጎን ቆሟል ብለው ያምናሉ?
Anonymous voting

ወያኔ ከኢትዮጵያ ጋር እያደረገ ባለው ጦርነት የትግራይ ማሕበረሰብ በአብዛኛው ከወያኔ ጎን ቆሟል ብለው ያምናሉ?
Anonymous voting

የዛሬው ቀን ስም "ብዙ ነው ጣጣቸው" ይባላል፤ ነገረኛ ናቸው በጣም ቅበሯቸው፤ የተነሡ እንደሆን ብዙ ነው ጣጣቸው፤ ለሒዊ

የዛሬው ሌሊት ስም "እንጣጥ እንደ ፌቆ፣ ሙልጭ እንደ ስብቆ" ይባላል። ሒዊ ስትመጣ "እንጣጥ እንደ ፌቆ" እያለች ነበር፤ ተቀጥቅጣና ተደምስሳ ስትወጣ ደግሞ "ሙልጭ እንደ ስብቆ" እያለች ነው። "ተደምስሰናል"ና "ተመልሰናል" በሒዊኛ አንድ ነው እንዴ!

የዛሬው ቀን ስም "የማይሆን ነው ከቶ" ይባላል። መንደርና ሀገር ተጣልቶ፣ ቅልና ድንጋይ ተማቶ፤ ቀበሮና እረኛ ተሟግቶ፤ ወንበዴና ጨዋ ተዋግቶ፤ የማይሆን ነው ከቶ!

የዛሬው ሌሊት ስም"በምላስ መግደል"ይባላል። ባል ሚስቱ ጥላ ስትቀጠቅጠው"ተጋደልን" እያለ ይጮሃል አሉ። ጎረቤቶቹ በሩን ሰብረው ሲገቡ ከሥር ወድቆ ሊሞት ደርሷል። "ተጋደልን ከምትል ገደለችኝ አትልም ወይ " ቢሉት" ባይሆን በምላሴ ልግደላት ብዬ ነው" አለ አሉ፤ የደጺ መግለጫ፤

#ይምጡ_ሱቃችንን #ይመርቁ #በቅናሹ_ይጠቀሙ እንኳን አደረሳችሁ! ልዩ የገና በዓል ጥቅሎችን ይዘን ቀርበናል። 📍 22 አክሱም ሆቴል አጠገብ #ትጋት_የገበያ_ማዕከል_4ኛ_ፎቅ F3-08 አትኒ ስጦታዎች
#ይምጡ_ሱቃችንን #ይመርቁ #በቅናሹ_ይጠቀሙ እንኳን አደረሳችሁ! ልዩ የገና በዓል ጥቅሎችን ይዘን ቀርበናል። 📍 22 አክሱም ሆቴል አጠገብ #ትጋት_የገበያ_ማዕከል_4ኛ_ፎቅ F3-08 አትኒ ስጦታዎች 0911692155 / @orderatni 0912384590 / @gedianasimos

የዛሬው ቀን ስም "ፍየሎች አበዱ" ይባላል ። ዕንቆቅልሽ? "ፍየሎች አበዱ፣ ተንበርክከው እሳት አነደዱ" ምንድን ነው? እሳቱ ነደደ፣ ብረቱ ጋለ፣ ተቀጠቀጠ ፣ ስለታማ ሆነ። ከዚያ- የቱ ፍየል ከስለቱ ፊት ይቆማል። ሃይ ብሎ የመጣ ዋይ ብሎ መፈርጠጥ ነው።

የዛሬው ቀን ስም "አራቱ ቆራጦች" ይባላል። ከበጎቻቸው ጋር ለመሞት ቆርጠው ሕዝብን የታደጉ አራቱ ቆራጦች፦ አቡነ አትናቴዎስ(ደሴ)፣ አቡነ ቄርሎስና አቡነ ኤርምያስ(ወልድያ)፣ አቡነ በርናባስ(ሰቆጣ)። እንዲህ ለሚያልፍ ጊዜ ስንቱ እረኛ ከዳ፣ ስንቱ እረኛ ፈርቶ ዝም አለ፤ ስንቱ እረኛ አጥር ላይ ቆመ።

የዛሬው ሌሊት "ተንከባለለ እንደ ሙቀጫ"ይባላል፤ ጠላትህን የማሸነፊያ ትልቁ በር ድንቁርናው ነው። የሒዊ ድንቁርናዋ ዕብሪቷ ነው።ሒዊ ድል አድርጋ አታውቅም፤ድል ሰርቃ ግን ታውቃለች።ወጣ ወጣና እንደ
የዛሬው ሌሊት "ተንከባለለ እንደ ሙቀጫ"ይባላል፤ ጠላትህን የማሸነፊያ ትልቁ በር ድንቁርናው ነው። የሒዊ ድንቁርናዋ ዕብሪቷ ነው።ሒዊ ድል አድርጋ አታውቅም፤ድል ሰርቃ ግን ታውቃለች።ወጣ ወጣና እንደ ሸንበቆ ተንከባለለ እንደ ሙቀጫ ማለት ዛሬ ነው።