ግጥም እና አባባል
Open in Telegram
╭─┅─┅──┅─═┅❀┅═─┅─┅─┅─╮ እንኳን :¨·.·¨: ወደ `·.🇪🇹ግጥም እና አባባል ቻናል መጡ ╰─┅─┅──┅─═┅❀┅═─┅─┅─┅─╯ ━ ━━━━━━•●✠ተ✠●•━━━━━━ ━ 「❝ ዓለሙን፡ሁሉ፡ቢገዛ ነፍሱን፡ግን፡ቢያጠፋ ለሰው፡ምን፡ይጠቅመዋል? ሰው፡ለነፍሱ፡ቤዛ፡ምን፡ይሰጣል? ❞」 ━ ━━━━━━•●✠ተ✠●•━━━━━━ ━ ማር ፰፥፴፮።
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
4 049
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Data loading in progress...
Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
December '24
December '24
+73
in 0 channels
November '240
in 0 channels
Get PRO
October '24
+50
in 0 channels
Get PRO
September '240
in 0 channels
Get PRO
August '240
in 0 channels
Get PRO
July '240
in 0 channels
Get PRO
June '240
in 0 channels
Get PRO
May '240
in 0 channels
Get PRO
April '240
in 0 channels
Get PRO
March '240
in 0 channels
Get PRO
February '240
in 0 channels
Get PRO
January '240
in 0 channels
Get PRO
December '230
in 0 channels
Get PRO
November '230
in 0 channels
Get PRO
October '230
in 0 channels
Get PRO
September '230
in 0 channels
Get PRO
August '230
in 0 channels
Get PRO
July '230
in 0 channels
Get PRO
June '230
in 0 channels
Get PRO
May '230
in 0 channels
Get PRO
April '230
in 0 channels
Get PRO
March '23
+32
in 0 channels
Get PRO
February '23
+76
in 0 channels
Get PRO
January '23
+165
in 0 channels
Get PRO
December '22
+156
in 0 channels
Get PRO
November '22
+150
in 0 channels
Get PRO
October '22
+105
in 0 channels
Get PRO
September '22
+105
in 0 channels
Get PRO
August '22
+133
in 0 channels
Get PRO
July '22
+166
in 0 channels
Get PRO
June '22
+134
in 0 channels
Get PRO
May '22
+143
in 0 channels
Get PRO
April '22
+121
in 0 channels
Get PRO
March '22
+127
in 0 channels
Get PRO
February '22
+109
in 0 channels
Get PRO
January '22
+115
in 0 channels
Get PRO
December '21
+261
in 0 channels
Get PRO
November '21
+226
in 0 channels
Get PRO
October '21
+212
in 0 channels
Get PRO
September '21
+92
in 0 channels
Get PRO
August '21
+170
in 0 channels
Get PRO
July '21
+159
in 0 channels
Get PRO
June '21
+129
in 0 channels
Get PRO
May '21
+99
in 0 channels
Get PRO
April '21
+104
in 0 channels
Get PRO
March '21
+92
in 0 channels
Get PRO
February '21
+81
in 0 channels
Get PRO
January '21
+113
in 0 channels
Get PRO
December '20
+4 740
in 0 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 21 December | +7 | |||
| 20 December | +13 | |||
| 19 December | +5 | |||
| 18 December | 0 | |||
| 17 December | +4 |
Channel Posts
🇪🇹ቅዳሜ ጳጉሜ ፭ ፳፻፲፬ ዓ.ም
╭─┅┅─┅─┅─═┅❀┅═─┅─┅─┅┅─╮
「❝ ሶስት፡ነገሮች
በጣም፡ያስደንቁኛል።
፩ አባቱ፡የማይቀድመው፡ልጅ
፪ እናቱን፡የፈጠረ፡ልጅ
፫ የፈጠራትን፡የወለደች፡እናት ❞」
╰─┅┅─┅─┅─═┅❀┅═─┅─┅─┅┅─╯
🗣 አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
ለመቀላቀል 👉🏽 @poemandquote
አስተያየት 👉🏽 @poemandquotebot
┏─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┓
❘ ❝ ሰው፡ከሆኑ፡በቂያችን፡ነው። ❞ ᴀ ❘
┗─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┛
| 2 | 🇪🇹 ቅዳሜ ጳጉሜ ፭ ፳፻፲፬ ዓ.ም
━━━━━━━━━━━━━✠━━━━━━━━━━━━━
┈┈┈┈•◦●✠ተ✠●••┈┈┈
╭─┅┅──┅──┅─═┅❀┅═─┅──┅──┅┅─╮
「❝ ቀደም፡ብዬ
በቅዳሜ፡ቀን ሐምሌ ፯ ፳፻፲፬ ዓ.ም
በዚህ፡ቻናል፡ላይ
ከ ፳፻፲፬ ዓ.ም በኋላ
ለሀገሬ፡ኢትዮጵያ፡በጎው፡ዘመን
እስኪመጣላት፡ድረስ
ምንም፡አይነት፡አዲስ፡መልዕክት
እንደማይለቀቅ፡ባሳወቁት፡መሠረት
በሚቀጥለው፡አባባል፡ተሰነባብተን
አገልግሎት፡መስጠቱን፡ያቆማል።
ፍቃዳችሁ፡ሆኖ
አብራችሁኝ፡ስለቆያችሁ
እግዚአብሔር፡ያክብርልኝ። ❞」
╰─┅┅──┅──┅─═┅❀┅═─┅──┅──┅┅─╯
┈┈┈┈•◦●✠ተ✠●••┈┈┈
━━━━━━━━━━━━━✠━━━━━━━━━━━━━
እግዚአብሔር፡ይመስገን!!!
┈┈┈┈┈┈•◦●፲፪ ፳፩ ፲፱●••┈┈┈┈┈┈ | 0 |
| 3 | 🇪🇹ቅዳሜ ጳጉሜ ፭ ፳፻፲፬ ዓ.ም
╭─┅┅─┅─┅─═┅❀┅═─┅─┅─┅┅─╮
「❝ እስኪ፡የሰማሃውን
ለማሰላሰል፡ጊዜ፡ይኑርህ። ❞」
╰─┅┅─┅─┅─═┅❀┅═─┅─┅─┅┅─╯
🗣 ዓለማየሁ ዋሴ
📔 ሰበዝ
ለመቀላቀል 👉🏽 @poemandquote
አስተያየት 👉🏽 @poemandquotebot
┏─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┓
❘ ❝ ሰው፡ከሆኑ፡በቂያችን፡ነው። ❞ ᴀ ❘
┗─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┛ | 0 |
| 4 | 🇪🇹ቅዳሜ ጳጉሜ ፭ ፳፻፲፬ ዓ.ም
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
የለም!
የለም! የለም! የለም!
ይህ ስንኝ
ይህ ግጥም ፥ ፖለቲካ አይደለም!
ከተደማመጥን ፥ ተራ ጎጡን ትተን
እንዲህ ነው የሚመስለኝ ፥ ሀገር ሲተነተን
ትንቢት ፩
የሞተው ወንድምሽ
ትንቢት ፪
የገደለው ባልሽ
ጥያቄ
አንቺን ምን እንበልሽ ?
ማን እንበልሽ አንቺን ?
የሟች እህት ዘመድ ፥ የገዳይ ባለቤት
ከፊት አይታይም ፥ ሀገር የሌለው ቤት?
እኔን ይታየኛል ፥ ወንድምሽ ሲቀበር
ይኸውልሽ እንግዲህ!
የገደለው ባልሽ ፥ ከፊት ቆሞ ነበር
የባልን ቃልኪዳን
የነፍስን ደም ክዳን
የወንድም ከለላ
አለች የሚያስብልሽ ፥ የአካልሽ ጥላ
ለደሀ እናት ሀገር ፥ ሁለቱንም ማጣት
ጥፋት እያሰቡ ፥ ሰርክ መቀጣጣት
እንዴት አርጎሽ ይሆን? ፥ ዘመን ምስቅልቅሉ
ቀራኒዮሽ የት ነው? ፥ የሚወርደው መስቀሉ
እንዴት አርጎሽ ይሆን?
የት ሄድሽ? እስከወዴት?
ያገር ጌታ ሲሞት ፥ በአንድ ባርያ ንዴት
እንዴት አርጎሽ ይሆን?
የነደደው ሲገድል ፥ የሞተው ሲሆን ገል
ዘመድሽ ሲጋደል
ዘመንሽ ሲነደል ፥ ነፍስሽን ሲያደማት
እንደው ምን ተሰማሽ? ፥ እንደው ምን ተሰማት?
ብቻ...
በዚህ በወንድሟ ፥ በዚህም በባሏ
ከሁለት እሳት መሐል ፥ የቆመች አካሏ
የጦቢያን እናት ፥ ይመስለኛል ምስሏ
ያቺ ምስኪንዬ...
ያቺ ምስኪንዬ ፥ በልጇ ሆድ በልታ
ያቺ ምስኪንዬ
ከሳር ፍራሿ ላይ
ወርቅ ከምትለው ፥ ከአብራኳ ተኝታ
የምትጽናናውን
የምትረካውን
የዚያችን ምስኪን ሴት ፥ የእምዬን ገላ
እሷን ነው የረሳን
ድንጋይ ስንወረውር ፥ አንገቴን ስትቀላ
እሷን ነው የረሳን ፥ እናቴን ከእናትህ
ከገላዬም ያልፋል
ተስፋዋን ይገላል ፥ የያዝከው ጥይትህ።
የለም!
የለም! የለም! የለም!
ይህ ስንኝ
ይህ ግጥም ፥ ፓለቲካ አይደለም!
ፖለቲካ ስም ነው
ፖለቲካ ቃል ነው ፥ ከሥልጣንም በታች
የአንዲት እናት ስም ነው ፥ ገመናህን ከታች።
ፖለቲካ ሆሄ
የዓለማት ጸሎት ፥ የዘመን ኤሎሄ
ፖለቲካ ፍዳ ፥ የመከራ ድርድር
የራስ ሰማይ መስራት ፥ ማጥፋት የሰው ምድር !
ትንቢት ፩
የገደለው ባልሽ
ትንቢት ፪
የሞተው ወንድምሽ
ጦቢያ
አንቺን ምን እንበልሽ ?
የጠፋው ወንድምሽ
ያጠፋው ያ ባልሽ
የሚሞተው እሱ ፥ ስጋዋ ወንድሟ
ገዳዩዋ ባሏ ነው ፥ የሌሊት ሰው ደሟ
ዘመድሽ ሲጋደል
ዘመንሽ ሲነደል
ከማን መሬት ገባሽ? ፥ ከምን አፈር ጉድጓድ?
ምን ጥግ አስከለለሽ? ፥ ሓሳብ ልጅሽ ሲናድ
ምን ጫካ ላይ ከተምሽ? ፥ ከወዴት ውጥንቅጥ?
መጋደል ንዳድ ነው ፥ ነፍስ የሚሰነጥቅ
ወንድምን በሬሳ ፥ ወዲያ እየሸኙ
የአብራክን ክፋይ ፥ በሞት እየሸኙ
ትዳር እንዴት ይቁም ፥ ከጉዳይ ከተኙ ?
የለም!
የለም! የለም! የለም!
ይህ ስንኝ
ይህ ግጥም ፥ ፖለቲካ አይደለም!
ብቻ...
ስንወረውር ፥ ልብህን ሳደማው
ባሩድ ስትተኩስ ፥ ነፍሴን ስትቀማው
ጉድጓድ ስምስልህ ፥ አንተም ቃታ ስትስብ
እናቴን አስታውሳት! ፥ እናትህን ላስብ!
ብቻ...
ዘሬ በአንተ ዘር ላይ ፥ ሳላድበሰብሰው
ወላድህን አስብ ፥ በቂ ነው መባል ሰው!
እሷን ማሰብ በቂ ፥ ከማለቅ ያግዳል
ካርታማ ሞኝ ነው ፥ ሲያሰምሩት ይሄዳል
ካርታ ስናሰምር
እኔም ይቅር አልሙት ፥ አንተም ይቅር አትሙት
የትኛውም ስሜት ፥ ሞኝ ነው ከሰሙት
እኔም አልቀበር ፥ ደሜን አላሙቀው
ቀልብ እኮ መንጋ ነው ፥ አረኛ ከራቀው
እናም...
ቀልባችን ሲከተት
ጠንካራ እንደብረት ፥ ንጹሕ እንደወተት
ጠንካራ ስትሆን ፥ ዋርካ ነህ መጽናኛ
ጠንካራ ሕዝብማ ፥ እርሱ ራሱ እረኛ
ጠንካራ ሕዝብማ
መሪ በሌለበት ፥ ጠላቱን አዋርዷል
ጠንካራ ሕዝብማ
ንጉሥ በሌለበት ፥ ዙፋኑን ጠብቋል
ጠንካራ ሕዝብማ
ሀገር ያሻግራል ፥ ንግሥና ሳይቀማ!
ጠንካራ ሕዝብማ ፥ ዕምነቱ ብዙ ነው
ድንጋይ እና ጥይት
እንኳን ከጭንቅላት ፥ ከእግር በታች ነው
በጣልነው ስንዋስ...
በናቅነው ስናለቅስ...
ከሬሳችን እኩል ፥ ዕንባ ሚታበስ
ይሄ...
ይሄ...
ለሺህ ዘመን ሙሉ ፥ እረኛ ሚከሰው
ለሺህ ዘመን ሙሉ ፥ እረኛ ሚወቅሰው
ደግ መሪ ስጠኝ ፥ ብሎ የሚያለቅሰው
ይህ ሁሉ ምስኪን ሰው ፥ ጸሎቱ የደመነ
የመሪዎቹ ምንጭ ፥ እርሱ ስለሆነ።
መሪ ንጉሥ ማለት ፥ ከአብራክህ የወጣ
እኛው የፈጠርነው ፥ ወልደነው የመጣ !
ጨካኙም ከእኛው ነው።
አጥፊውም ከእኛው ነው።
ሰናዩም ከእኛው ነው።
ካሌብም ከእኛው ነው።
ቴዎድሮስ ከእኛ ነው።
ምኒልክ ከእኛ ነው።
ዮሐንስ ከእኛው ነው።
አሉላም ከእኛው ነው።
ተፈሪም ከእኛው ነው።
መንግሥቱም ከእኛው ነው።
መለስም ከእኛው ነው።
ግፈኛው ከእኛው ነው።
ከእኛው ነው ሁሉም
ከሀዲውም ከኛ ፥ ከቋጥኝ የሚከብድ
አንተ የኔ ወገን
ከመሪዎች በፊት ፥ ሕዝብህን ነው መውለድ።
የለም!
የለም! የለም! የለም!
ይህ ስንኝ
ይህ ግጥም ፥ ፖለቲካ አይደለም!
እውነት ነው ማወራህ ፥ ዘላለም ያኖረን
ከኪዳን የቀረን...
ከእማማ የቀረን...
ከአባባ የቀረን...
ይሄ ነው የሚያኖረን።
ይሄ ነው ያኖረን።
ስንሰቃይ ኖርን ፥ በመከራ ታንኳ
አንተ የሀገሬ ሰው
ዝም ብለህ አትክፈት ፥ ማንም ሰው ሲያንኳኳ
ያ ነው የሚያኖረን ፥ ትንቢት እንዳንፈራ
ለጤፍ እያረስን ፥ እንዴት ቂም እናፍራ ?
የቂም በቀል መንገድ
መድረሻው ግራ ነው ፥ ጉዞው ማይለካ
መንጋነት ያስንቃል ፥ በእረኛ ሲለካ
ለዘመን መመዘን ፥ ለችጋር መንጋጋ
ይበቃሻል ጦቢያ!
በሞትሽ አይጨልም ፥ በሞትሽ አይንጋ
"ያፅናሽ!" ብል አልፀናም ፥ አታውቂም ስሜቴን
ብቻ...
ማንም ሞተ ሲሉኝ ፥ አይሻለው አንቺን
አያለሁ እናቴን
አያለሁ...
አያለሁ...
አያለሁ...
ብቻ
ማሰብም ከእኛ ነው
አለማሰብ ከእኛ ፥ ከቋጥኝ የሚከብድ
አንተ የኔ ወገን
ከመሪዎች በፊት ፥ ሕዝብህን ነው መውለድ።
ልባችን ልብ ይግዛ
በነገር...
በሐሜት በሆሄ ፥ በጦር ስም አትምቱት!
እስቲ ነጻ ይውጣ ፥ አሳሪውን ፍቱት
ሁሉም ነጻ ይውጣ!
ሁሉም ነጻ ይሁን! ፥ የተፈታ ወጥቶ
ሁሉም ነጻ ይሁን! ፥ የአጠፋ ተቀጥቶ!
ታድያ እኔ እና አንተ
ዘርን ወዲያ ቀብረን ፥ ትንቢትን አንፍተል !
ዘርን ወዲያ ቀብረን ፥ ትንቢትን አንፍተል !
ወይ ደግ ቀን አምጣ
ወይ ባለደግ ቀን ፥ ፈልገህ ተከተል !
┈┈┈┈•◦●◉❖◉●••┈┈ ┈
✍🏽© ኤልያስ ሽታኹን
╰══•••┈ ┈ ┈•◦●◉❖◉●••┈┈ ┈
ለመቀላቀል 👉🏽 @poemandquote
አስተያየት 👉🏽 @poemandquotebot
┏─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┓
❘ ❝ ሰው፡ከሆኑ፡በቂያችን፡ነው። ❞ ᴀ ❘
┗─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┛ | 0 |
| 5 | 🇪🇹አርብ ጳጉሜ ፬ ፳፻፲፬ ዓ.ም
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
መቼም...
የጠቢብ ሀገር ነው!
ሁሉ በየመልኩ
ሁሉ በየልኩ
ሁሉ በአቋሙ
ሁሉ በአቅሙ
የሚቀጣጥለው ፥ የሚያቀጣጥለው
የሚያንጠለጥለው ፥ የሚያብጠለጥለው የሚበታትነው ፥ የሚተነትነው
ጊዜው ተምታቶ እንጂ ፥ ሀገሩስ ጠቢብ ነው!
አታይም?! በምሁራን መንደር
ፈውስ ሽባ ሆኖ ፥ ደዌ ሲንደረደር
አትሰማም?! በጠቢባን ሀገር
መሲሁ ተቀምጦ ፥ መጻጉእ ሲናገር
ተምታቶ ነው እንጂ ፥ ሀገሩስ ጠቢብ ነው!
ምጸትና ጸጸት ፥ የተቀላቀለው!
ተምታቶ ነው እንጂ ፥ ሀገሩስ ሀገር ነው!
ምጸትና ጸጸት ፥ የተቀላቀለው!
ምጸትና ጸጸት
ሰው የሚሉት ፍጥረት ፥ ክብሩ እንዳይገባው
ዓይኑን አሳወረው ፥ ተንኮልና ደባው
የጅራፍ አመሉ ፥ ለጅራፉ ተርፎ
ራሱ ይጮሃል ፥ ራሱ ተጋርፎ
እኛን አይመስልም ?
ወደራስ ነው መጮህ ፥ ወደገዛ ልብህ
ቀለብህን ትተህ ፥ መሠብሠብ በቀልብህ
ወገን!
ወደቤትህ ግባ
ወደጓዳህ ግባ
ወደውስጥህ ግባ ፥ የሚል ደዌ ካለ?
ከህማሙ ጀርባ ፥ አንዳች ትርጉም አለ!
አንዳች ትርጉም ሀ
ሁሉም ከበር ወዲያ...
ሀገሬው መንደሩ
ከራሱ ጋር ሽሽት ፥ ስለተላመደ
ወደቤትህ ግባ! ፥ የሚል ሞት ወለደ።
ወደራስህ ግባ
ወደቤትህ ግባ ፥ የመባልህ ነገር
ትርጉሙ ይሰፋል ፥ ለሕይወት ለሀገር።
ለእኛማ ሌላ ነው...
ለእኛማ ሌላ ነው...
የቤት ግቡ ቅኔ ፥ የትርጉሙ ሚዛን
ነጭን አሸንፈን ፥ በነጭ የተገዛን
ለእኛማ ሌላ ነው...
በዙፋን ላጠፋ ፥ ዙፋን የምንቀጣ
ነጻነትን እንኳን ፥ ነጻ ምናወጣ
አጀብ!
ለእኛማ ሌላ ነው...
ልባችን ተከደቶ
ክራችን ተፈቶ ፥ ማህተባችን ላልቶ
አለማመን እውቀት ፥ ማመን ተሸልቶ
ለምንነዋወጥ! ፥ ለማንደማመጥ!
ለእኛማ ሌላ ነው ፥ ከእኛ ጋር መቀመጥ።
ቤት ማለት ገመና! ፥ ገመና ምሥጢርህ
ምሥጢርህ ራስህ
ልብህ ሰውን ይርሳ ፥ አንተን እንዲከስህ።
የመዋቀስ ልማድ
ከገዛ ራሳችን ፥ ሊላምደን ሽቶ
አፋችን ተዘጋ ፥ ከሰው ጆሮ ሸሽቶ
ወደቤትህ ግባ...
ወደጓዳህ ግባ...
ወደውስጥህ ግባ ፥ የሚል ደዌ ካለ?
ከህማሙ ጀርባ ፥ አንዳች ትርጉም አለ!
አንዳች ትርጉም ለ
ላንቺማ ሌላ ነው ፥ ውጪውጪ ላልሽው
በቀልብም
በልብም
በመንፈስ በሃሳብ
ለምትሰደጂው ፥ ለምታሳድጂው
ሽል ይበልጣል ብለሽ
የገዛ ልጅሽን ፥ ለምታሶርጂው
ላንቺማ ሌላ ነው...
ከሊቅ እስከደቂቅ ፥ ለሚተነትንሽ
ዘርሽን በትነሽ ፥ ዘር ለሚበትንሽ
ላንቺማ ሌላ ነው...
ስም እየቀያየርሽ ፥ ጠሪ የሚከፋ
በእውቀት በሙቀት ፥ ጨለማሽ ሚሰፋ
ላንቺማ ሌላ ነው...
የለመድሺው እደጅ
የለመድሺው በራፍ ፥ የለመድሺው አጥር
ጎበዝሽን ሁሉ ፥ ለሞት የሚቀጥር።
ላንቺማ ሌላ ነው...
በእግዜር ተጠብቀሽ
እግዜርን ለረሳሽ ፥ እምነትን ላነሳሽ !
በተለይም ላንቺ
የታይታ ሆኖ ፥ ያፈራሺው ሁሉ
አስከበሩኝ ብለሽ ፥ በዘመን ቢቀሉ
ላንቺማ ሌላ ነው...
ሃሳብና ነፍስሽ ፥ ስለተቃጠረ
ተመስገን በይ አንቺ!
ስምሽን አስቀምጦ ፥ ሰሚሽን ፈጠረ
ተመስገን በይ አንቺስ...
ተመስገን በይ አንቺስ...
ዛሬም ተስፋሽ ቆሟል
መዳንሽ ባይቀርም ፥ መንፈስሽ ግን ታሟል።
ወደቤትህ ግባ
ወደውስጥህ ግባ
ወደጓዳህ ግባ ፥ የሚል ደዌ ካለ?
ከህማሙ ጀርባ ፥ አንዳች ትርጉም አለ!
አንዳች ትርጉም ሐ
በጊዜ ታሪክ ላይ...
በሕይወት ታሪክ ላይ...
በሀገር ታሪክ ላይ ፥ ደም ከሞት የሚኩል
አንዳንድ ማለፍ አለ ፥ ከአለማለፍ እኩል።
ምሑር ሊቃውንትሽ
ይኼም ጊዜም ያልፋል! ፥ እያሉ ሲያቀሉት
የማለፍን ትርጉም ፥ ወዴት ነው ያጠኑት?
ከመሰበር ወዲያ...
ከማለቅም ወዲያ....
ማለፍ ነው እያለ ፥ አስኳላሽ ያሾፋል!
የማይቀብሩት ዘመድ ፥ በስንት ዕምባ ያልፋል?
በስንት ዕምባ ያርፋል?
በጦርነት ሁሉ...
በረሀቡ ሁሉ...
በህማሙ ሁሉ...
ያልፋል ባልነው ሁሉ...
ሰው እየገበርን ፥ ሰው እየቀበርን
"ግድየለም!" እያልን ፥ ግድየለሽ የሆንን!
ሰውን እያሳለፍን
"ያልፋል" እንደማለት ፥ ለኮሮጆ ቁማር
መቼም የማንማር !
ወገን! ፥ ረሀቡ ቢያልፍም
የረሀብ ሀገር ናት ፥ ከመባል አንተርፍም።
ጦርነቱ ቢያልቅም
ልብሳችን ነው እንጂ ፥ ልባችን አይለቅም።
ቸነፈር ቢታለፍ
ከጠላት አፍ ምላስ ፥ ዘላለም አያተርፍ።
ዛሬም ቁስል አለ ፥ ደነነዋል ያልነው
በወሬ በምላስ ፥ አልፈን ያላለፍነው
ወትሮም...
ሰው ገብረንብት
የምንሻገረው ፥ እያንዳንዱ መቅሰፍት
አለፍን አይባልም ፥ ሞት ከተጻፈበት!
ወትሮም...
ወትሮም...
ሰው ገብረንበት
የምንሻገረው ፥ እያንዳንዱ መቅሰፍት
አለፍን አይባልም ፥ ሞት ከተጻፈበት!
በጊዜ ታሪክ ላይ...
በሕይወት ታሪክ ላይ...
በሀገር ታሪክ ላይ ፥ ደም ከሞት የሚኩል
አንዳንድ ማለፍ አለ ፥ ከአለማለፍ እኩል።
ሁሉም ከበር ወዲያ...
ሁሉም ከአጥር ወዲያ...
ሁሉም ቤቱን ትቶ
ሁሉም ከራስ ሽሽት ፥ ስለተላመደ
ወደራስህ ግባ ፥ የሚል ሞት ወለደ።
እንጂማ የጠቢብ ሀገር ነው!
ሁሉ በየመልኩ
ሁሉ በየልኩ
ሁሉ በአቋሙ
ሁሉ በአቅሙ
የሚቀጣጥለው ፥ የሚያቀጣጥለው የሚያንጠለጥለው ፥ የሚያብጠለጥለው የሚበታትነው ፥ የሚተነትነው
ጊዜው ተምታቶ እንጂ ፥ ሀገሩስ ጠቢብ ነው!
አላስተውል ስንል ፥ ማስተዋል ቢያነሳን
ሁሉን እንድናስብ ፥ ሁሉን ነገር ነሳን።
┈┈┈┈•◦●◉❖◉●••┈┈ ┈
✍🏽© ኤልያስ ሽታኹን
╰══•••┈ ┈ ┈•◦●◉❖◉●••┈┈ ┈
ለመቀላቀል 👉🏽 @poemandquote
አስተያየት 👉🏽 @poemandquotebot
┏─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┓
❘ ❝ ሰው፡ከሆኑ፡በቂያችን፡ነው። ❞ ᴀ ❘
┗─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┛ | 0 |
| 6 | 🇪🇹አርብ ጳጉሜ ፬ ፳፻፲፬ ዓ.ም
╭─┅┅─┅─┅─═┅❀┅═─┅─┅─┅┅─╮
「❝ ጌታ፡ሆይ
የአንተ፡አምላክነት
ለእኔ፡ያስፈልገኛል፡እንጂ
የእኔ፡ፍጡርነት
ለአንተ፡አያስፈልግህም። ❞」
╰─┅┅─┅─┅─═┅❀┅═─┅─┅─┅┅─╯
🗣 ቅዱስ ባስልዮስ
ምንጭ ➸ ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ለመቀላቀል 👉🏽 @poemandquote
አስተያየት 👉🏽 @poemandquotebot
┏─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┓
❘ ❝ ሰው፡ከሆኑ፡በቂያችን፡ነው። ❞ ᴀ ❘
┗─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┛ | 0 |
| 7 | 🇪🇹አርብ ጳጉሜ ፬ ፳፻፲፬ ዓ.ም
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
#ጠያቂ_ነኝ_እኔ
ያስቀየምኩት ካለ ፥ በስካሁን ቆይታ
ያስከፋሁት ካለ ፥ ልቡ በኔ ደምታ
በአምላክ ስም በሉኝ ፥ ከልባቹ ይቅርታ።
ደካማ ፍጡር ነኝ ፥ በስራዬም ዘንጊ
በማላውቀው ነገር ፥ የሰው ስሜት ወጊ
ይሆናል ባላልኩት ፥ ጭራሽ ባልገመትኩት
ጎድቼ ይሆናል ፥ የአንዳችሁን ስሜት
ግና...
አስቤም ባይሆንም ፥ ክፋትም አስቤ
ይቅር በሉኝና ፥ ይሰብሰብ ሃሳቤ
ለፈጣሪ ብዬ ፥ ሁሉን እወዳለሁ
ያስቀየምኩት ካለ ፥ ይቅርታ ብያለሁ
ቅርን ያሰኘሁት ፥ በምሰራው ስራ
ያበገንኩት ካለ ፥ ሊነግረኝ የፈራ
ይቅር እንድትሉኝ ፥ እላለሁ አደራ።
ማንን እንዳስቆጣሁ ፥ ከቶ አላውቅም እኔ
እንደው በደፈናው
ይቅር በሉኝና ፥ ይረፍልኝ ጎኔ።
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
ለመቀላቀል 👉🏽 @poemandquote
አስተያየት 👉🏽 @poemandquotebot
┏─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┓
❘ ❝ ሰው፡ከሆኑ፡በቂያችን፡ነው። ❞ ᴀ ❘
┗─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┛ | 0 |
| 8 | 🇪🇹ኀሙስ ጳጉሜ ፫ ፳፻፲፬ ዓ.ም
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
#ነገረ_ማድያት
ከድፍርስ አይኖቿ...
ከድፍርስ አይኖቿ ፥ ከፍ ብሎ ወደላይ
ማኃል ፥ ግንባሯ ላይ
ጽሑፍ ስለሌለ
ጠባዋን ለማወቅ ፥ ምን ቢከብድም እንኳን
እንደሚከተለው እነግራቹሃለሁ
ማድያት ያጠቃው ፥ ያ ደም መልኳን።
እነሆ ታሪኳን
ከዘመናት በፊት...
ከዘመናት በፊት...
ይችህን የቀይ ዳማ
ታፍረው ያስከበሯት ፥ ሦስት ባሎች ነበሯት።
የቀደመው ባሏ
የእግዜር አበጋዙ ፥ ካህን ሰው ነበረ
ለስምንት ዘመናት ፥ አብሮ ፈቅዷት ኖረ
በነዚህ ዘመናት
ሁለት ልጅ አፍርቶ ፥ በአብሮነት ከረመ
ከወራት ኋላ ግን
ፍም ፀሐይ ገላዋን ፥ መሞቁን አቆመ
"ወቅቱ በረድ ሣለ ፥ ለምን ተውከኝ?!" አለች
እቅፍ ሠንሠለቷ
እንደአገዳ ሲሆን ፥ እያንሰላሰለች
ምክንያቱን ነገራት
"እህቴ ውዴ ሆይ" አላት
"እህቴ ውዴ ሆይ
እንዴት ደስ እንዳሰኝ ስላንቺ እያሰብኩኝ
በፍጹም ልብና
በፍጹም መንፈስህ
አምላክህን ውደድ ፥ የሚል ህግን ጣስኩኝ
በርግጥ እመቤቴ
በርግጥ አስቀድሞ
የትዳር ምኝታው
ንጹሕ እንደሆነ ፥ ወንጌል ቢናገርም
መንኩስና መልካም ፥ መሆኑን አይሽርም።"
ደግሞ ሌላ ምክንያት...
ሐሳቡን ሳይጨርስ ፥ ሳጓ ገፍቶ አስቆማት
ሐዘኗን ለመግለጽ ፥ መቻሏ ጠቀማት
ቃል ሐይሉ ጨነቃት ፥ ሁኔታው ከበዳት
ዕንባ ውኃ ሲሆን ፥ በአፏ መጮህ ዳዳት
ክፉ ድንጋጤ ፥ ፍርሃት ከበባት
ውላ ያደረችው
በደመና ጎጆ ፥ እንደሆነ ገባት!
ሕይወት...
ሕይወት አልወርድ ብሎ
እንደኮረት ድንጋይ ፥ አንገቷን አነቃት
ሐሳቡን ተፋቺው
"አይሆንም!" አለችው
"አይሆንም!" ስትለው ፥ ፈታት! ጠላት! ናቃት!
አሁንን መረጠች ፥ ነገ ስለራቃት።
ሁለተኛው ባሏ...
ሁለተኛው ባሏ ፥ ዛፍ ቆራጭ ነበረ
ለስድስት ዓመታት
በአንድ ጎጆ ኖሮ
እድሜዋን ቆጠረ ፥ እድሜውን ቆጠረ
በነዚህ ዓመታት...
በነዚህ ዓመታት...
ወንድ ልጅን ወልዶ
የሴት አባት መሆን ፥ ልቦናውን ሲያምረው
እንደቆረጠው ዛፍ
ስል የሞት ገጀራ ፥ ድንገት መነጠረው።
እንዴት ያሳዝናል ?
እንዴት ያሳዝናል? ፥ ቅስሟን ሰባበረው!
ሌላ ሦስተኛ ባል
ሌላ ሦስተኛ ባል
የባል መጨረሻው ፥ የውድቀት መነሻው
ሁሉን አውቃለሁ ባይ ፥ አንዳች ግን የሌለው!
ያልታሠበ ንክ ቀን ፥ ደጇ ላይ የጣለው
ሰው ነበር!
ይከውልህ ደሴ...
የሚገርምህ ነገር
እብድ ቀን ያመጣው ፥ ወፈፌ ሰውዬ
ሰባት ወር ያህል ነው ፥ በአብሮነት የቆዬ
በነዚህም ወራት
ፈቃደ ሥጋውን ከመፈጸም በቀር
አንዳች አዲስ ነገር የፈጠረው የለም
በባዶው እንደመጣ
ባዶውን ተለየ
ባዶነት ምክንያቱ...
መሰልቸት ያለበት ፥ ታካች ማንነቱ
እንግዲህ ወዳጄ
ታይቷት ከጠፋት ሰው ፥ ከዚያን ቀን በኃላ
ትንከራተት ጀመር...
ትንቀዋለል ጀመር...
ልጆቿን የኔ የሚል
እሷን የሚጠብቅ ፥ አገኝ እንደው ብላ
አዎ...
አዎ ከዚህ በኃላ ነው
ሱሪ የለበሰ
የታጠቀው ሁሉ ፥ ወንድ እየመሰላት
ከእመቤትነቷ ወደ ገረድነት
ቁልቁል እየነዳ ፥ በቁም የገደላት።
አዎ ምልክት ያይደለ
በሽታን ያይደለ
ከዓይኗ ሥር ፥ ጉድ በታች
የመጣችበትን ፥ መንገድ አመላካች
ምስል የተወላት!
አዎ ከዚህ በኃላ ነው
በስተመጨረሻ...
በስተመጨረሻ...
የዚችን ሴት ጉዳይ ፥ ስናጠቃልለው
ይህቺን የቀይ ዳማ
አሁን ካለችበት ፥ ጎትቶ ሚያወጣት
ከእድሜ ምዕራፍ ስጋት
ልክ እንደበፊቱ
ማለት እንደነበረችው ፥ መልካም የሚያደርጋት
እሷ ሰውን ሳይሆን ፥ ሰው እንዲፈልጋት
የሚያስችል
መጠቀም ከቻለች ፥ ሁለት እድል አላት።
አንድ
የራስ ክብሯን ትታ
የአብራኳን ክፋዮች ተጠንቅቃ መያዝ
ለማዕረግ ማብቃት ተስፋ ይሆናታል
ሁለት
ሁሉም ነገር ቀርቶ
ከዓለም ጋር ተጣልቶ
ከዓለም ተለያይቶ
ለነፍሷ መመነን ክብር ያሰጣታል
ከነዚህ ከሁለቱ ፥ የቱ ይሸላታል?
┈┈┈┈•◦●◉❖◉●••┈┈ ┈
✍🏽© በቃሉ ሙሉ
╰══•••┈ ┈ ┈•◦●◉❖◉●••┈┈ ┈
ለመቀላቀል 👉🏽 @poemandquote
አስተያየት 👉🏽 @poemandquotebot
┏─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┓
❘ ❝ ሰው፡ከሆኑ፡በቂያችን፡ነው። ❞ ᴀ ❘
┗─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┛ | 0 |
| 9 | 🇪🇹ኀሙስ ጳጉሜ ፫ ፳፻፲፬ ዓ.ም
╭─┅┅─┅─┅─═┅❀┅═─┅─┅─┅┅─╮
「❝ የማይነጋ፡መስሎት
ቁርሱን፡ማታ፡በላ። ❞」
╰─┅┅─┅─┅─═┅❀┅═─┅─┅─┅┅─╯
ለመቀላቀል 👉🏽 @poemandquote
አስተያየት 👉🏽 @poemandquotebot
┏─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┓
❘ ❝ ሰው፡ከሆኑ፡በቂያችን፡ነው። ❞ ᴀ ❘
┗─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┛ | 0 |
| 10 | 🇪🇹ኀሙስ ጳጉሜ ፫ ፳፻፲፬ ዓ.ም
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
#ተመስገን_ለማለት
ማነሽ ባለ ስቃይ? ፥ ማነሽ ባለ ቁስል?
እዚህ ያመጣኝን ፥ ሲቃዬን አይተሻል?
ከፊቴ ስታልፊ
በእምነትሽ ተቋጥሮ ፥ እልፍ አእላፍ እምባ
ካይኖቼ ኮብልሎ
ካይኖችሽ ኮሮጆ ፥ ምናልባት ከገባ?
እስኪ ፈልጊልኝ?
የእንባዬን ዘለላ ፥ ነጠላ ሃዘኔን
ድንገት ያንቺ መስሎሽ
ከ'ንባሽ ጋር ጠቅልለሽ ፥ ወስደሽው እንዳይሆን?
ላለው ይጨመራል
ነውና አንቀፁ ፥ የፈለቅንበት ህግ
ለልቅሶሽ ሊደረብ
ለእንባሽ ሊጨመር ፥ ካይኔ ሲምዘገዘግ
አገኘው እንደኾን
ካይኖችሽ ባህር ውስጥ ፥ እንባዬን ልፈልግ።
እንጃ ግራ ገባኝ...
የመረረኝ ሁሉ ፥ ልቤን ያቆሰለ
በፊቴ ስታልፊ
ቀንበርሽን ሳየው ፥ ቀንበሬ ቀለለ
መከራዬ ካልኩት
ላፍታ ያጮለቅሁት ፥ መከራሽ ቢከፋ
ችግር የመሰለኝ
ለፀሎት ያመጣኝ ፥ ኡኡታዬ ጠፋ።
እንጃ ግራ ገባኝ...
በፊቴ ስታልፊ ፥ እንባዬ ተነነ
ከአዉደምህረቱ
ለፀሎት ያመጣኝ ፥ ችግሬ በነነ
ከመቅደሱ ቆሜ
ምን ጎደለኝ ልበል? ፥ ጠፍቶኛል ማጣቴ
"ስጠኝ!" "ስጠኝ! "እንጂ
" ተመስገን!" መች አዉቆ ፥ ሰዋዊ ስስቴ።
አንቺ ባለቁስሏ
አሁን ፊቴ መጥተሽ ፥ ጸልየሽ የሄድሽው
አለቅሰው ቸገረኝ
ተከትሎሽ እንደሁ ፥ እምባዬን መልሽው
አንቺ ባለ ሲቃ ፥ አንቺ ባለ ስቃይ
ከፊት ለፊት ቆመሽ ፥ ላምላክሽ ስትጸልይ
የምስጋናሽ ብዛት ፥ እምባሽን ሲያለብሰው
የኔ ጠፍቶብኛል ፥ ያንቺን ነው የማውቀው
እንዲህ ነበር ያልሽው....
"ተመስገን አምላኬ
ጎህ ቀዶ እስኪመሽ ፥ መሽቶ እስኪነጋ
አራቱን ልጆቼን
አርብ የወሰድክብኝ ፥ በመኪና አደጋ
ለካስ ለኔው ነበር
ምንይበሉ ይሆን ፥ ብዬ እንዳልሰጋ"
አዎ ባለቁስሏ
ከመቅደሱ ቆመሽ ፥ "ተመስገን" ስትይው
የኔ በኖ ጠፍቶ
ያንቺ ነው የቀረው ፥ እንዲህ የጸለዪሽው
"ተመስገን አምላኬ
ስለሆነው ሁሉ ፥ ስለምንሆነው
ባሌን ኀሙስ እለት
አዝለህ ያሳረግኸው ፥ በአክናፈ መብረቅ
ለካስ አስበህ ነው
ልጆቹ ሲሞቱ ፥ አይቶ እንዳይሳቀቅ"
አንቺ ባለ እምባ ፥ አንቺ ባለ ሲቃ
ተመስገን የጮህሽው ፥ ጉሮሮሽ እስኪነቃ
ያንቺን ተመስገን ነው
በቃሌ የማውቀው ፥ ሲቃዬ ሲከዳኝ
እንባዬ ሲሰወር
እንዲህ ነበር ያልሽው ፥ ቃልሽ መች ሊጠፋኝ?
"ዛሬ ቅዳሜ 'ለት
ሆስፒታል ደርሼ ፥ ሃኪሞች ነገሩኝ
ምድርን መልቀቂያ
ያንድ ሳምንት እድሜ ፥ እንደጨመርክልኝ
ተመስገን አምላኬ ፥ ጌታዬ ተመስገን
ቤተሰቤን ወስደህ ፥ ያልተውከኝ ብቻዬን"
አንቺ ባለ እምባ
ኧረ የኔ ጩኸት ፥ የት አባቱ ገባ?
ምን ስጠኝ ልል ነበር?
ስሮጥ አመጣጤ ፥ እንዲያ ያስጨነቀኝ
"ገንዘብ አጣሁ"
ልል ነው ? ፥ ወይስ "ትዳር ስጠኝ"?
ስራዬ ያስጠላል?
ቪላ ቤት ሰለቸኝ ? ፥ ባክህ ፎቅ ቤት ልስራ!
እስኪ ካገር ልውጣ? ፥ ቪዛዬን አደራ?
ሁሉም ቀለለብኝ ፥ ከአመድ ደቀቀ
ከቁስልሽ ተያይቶ ፥ ቁስሌ ተሳቀቀ
ለካስ እምባ ከእምባ ፥ አመዛዝኖ ማየት
"ተመስገን! "ያለምዳል ፥ "ተው ስጠኝ?" ከማለት።
┈┈┈┈•◦●◉❖◉●••┈┈ ┈
✍🏽© ረድኤት አሰፋ
╰══•••┈ ┈ ┈•◦●◉❖◉●••┈┈ ┈
ምንጭ ➸ አስተማሪ ታሪኮች
ለመቀላቀል 👉🏽 @poemandquote
አስተያየት 👉🏽 @poemandquotebot
┏─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┓
❘ ❝ ሰው፡ከሆኑ፡በቂያችን፡ነው። ❞ ᴀ ❘
┗─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┛ | 0 |
| 11 | 🇪🇹ረቡዕ ጳጉሜ ፪ ፳፻፲፬ ዓ.ም
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
#የሐዘን_እንጉርጉሮ_ከያዙ_ቅንጫቢ_ኢትዮጵያዊ_ቅኔዎች
ለጌታ አድሬ እንደዋዛ፣
አንዲት ላም እንኳን ሳልገዛ፣
ምን ይለኝ ይሆን ዘመድ፣
ወተት ብዬ ብሔድ፡፡
ሽህ ብረት በፊቱ የሚደባለቀው፣
'የዳሞት'ን መንገድ ብቻውን ዘለቀው፡፡
እንኳን ደኅና ገባህ ከሄድክበት አገር፣
ጠላቶችህ ሁሉ ይቅር ብለው ነበር፡፡
በዓለ ድባብ ንጉሥ ባለ ጥና አቡን፣
እየዞሩ ፈቷት አገራችንን፡፡
አሁን ምን ያደርጋል ሱሰኛ መሆን፣
ብዙ ቤት ፈረሰ ትላንት በዚያ አቡን፡፡
የዛሬ ዘመን ወዳጅም፣
ከሽሕ አንድ አይገኝም፣
አንቱ ብትለው ይኮራል
አንተ ያልከው ግን ይኖራል፡፡
ይድናል እያልን ዓይን ዓይኑን ስናይ፣
እንዲያ እንደፈራነው እውነት ሞተ ወይ?
ሞት ዕቃዬ ነው ብሎ፣
ወሰደው አሉ በቶሎ፣
ሌላውስ ይቅር ቢሻው፣
ዓይኑ እንኳን አሳስቶት በተወዉ፡፡
ምን ዕዳ ነበር ቢቀር፣
ከዕዳ ሞት መፈጠር፡፡
ንጉሥ የሠጡኝ ታላቅ ዕቃ፣
ላገር ለምድር የሚበቃ፣
አድጦኝ ወድቆ እስኪሠበር፣
ስይዘው ቀሎኝ ነበር፡፡
እኔን ከፋኝ እንጂ አገሬን ምን ከፋው፣
ግራር አበቀለ ዝሆን የማይገፋው፡፡
ተስቦ ገብቶ ከቤቴ፣
አልወጣ ብሎኝ ዓመቴ፡፡
የዛሬን ዘመን ምስክር፣
አልጣራውም ይቅር፤
ምነ እኔን ያልኸኝ አባይ፣
ጊዜው አይአለም ወይ?
ዛሬማ ጠጅ ማ ጠጥቶ፣
ሁሉ ጠላ ቤት ገብቶ፡፡
አሻግሬ ባይ መንገዱን፣
አረ ሰው ምናምን፡፡
ክፉ ቢናገር ተቆጥቶ፣
ጠላትህ ደሙ ፈልቶ፤
እሱም እንዳንተ ሰው ነው
እረተው ሰብቀህ አትውጋው፡፡
አገራችን ቆላ መስክ የለ ከደጅ፣
እንዲህ አፈር ላፈር እንጫዎት እንጂ፤
ከቆላ ሸንበቆው ማማሩ፣ ማማሩ፣
ቆርጠው ጣሉት እንጂ ለም አፍር እያሉ፡፡
ትንሹም ወይፈን ተጎዳ ትልቁም በሬ ደከመው፣
ወይፈን ታላገኘሁ በምን አርሼ ልብላው?
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
ምንጭ ➸ ዘጦቢያ
ለመቀላቀል 👉🏽 @poemandquote
አስተያየት 👉🏽 @poemandquotebot
┏─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┓
❘ ❝ ሰው፡ከሆኑ፡በቂያችን፡ነው። ❞ ᴀ ❘
┗─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┛ | 0 |
| 12 | 🇪🇹ረቡዕ ጳጉሜ ፪ ፳፻፲፬ ዓ.ም
╭─┅┅─┅─┅─═┅❀┅═─┅─┅─┅┅─╮
「❝ ይቅርታ
ዕድል፡ነው። ❞」
╰─┅┅─┅─┅─═┅❀┅═─┅─┅─┅┅─╯
ለመቀላቀል 👉🏽 @poemandquote
አስተያየት 👉🏽 @poemandquotebot
┏─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┓
❘ ❝ ሰው፡ከሆኑ፡በቂያችን፡ነው። ❞ ᴀ ❘
┗─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┛ | 0 |
| 13 | 🇪🇹ረቡዕ ጳጉሜ ፪ ፳፻፲፬ ዓ.ም
╭─┅┅─┅─┅─═┅❀┅═─┅─┅─┅┅─╮
「❝ በራሳቸው፡ቋንቋ፡ይረዱህና
በማታቀው፡ቋንቋ
ባልተፃፍክበት፡ፊደላት፡ያነቡሃል።
ያኔ፡ላልተገለፀለት
ራስን፡ከመግለፅ
ዝምታ፡ይሻላል። ❞」
╰─┅┅─┅─┅─═┅❀┅═─┅─┅─┅┅─╯
ለመቀላቀል 👉🏽 @poemandquote
አስተያየት 👉🏽 @poemandquotebot
┏─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┓
❘ ❝ ሰው፡ከሆኑ፡በቂያችን፡ነው። ❞ ᴀ ❘
┗─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┛ | 0 |
| 14 | 🇪🇹ረቡዕ ጳጉሜ ፪ ፳፻፲፬ ዓ.ም
╭─┅┅─┅─┅─═┅❀┅═─┅─┅─┅┅─╮
「❝ ሐሰተኛ፡ሰው
እንደ፡ፊኛ፡
ራሱን፡ከፍ፡ቢያደርግም
አንድ፡ቀን
በእውነት፡መርፌ፡ሲነካ
ባዶ፡መሆኑ፡ይገለጥበታል። ❞」
╰─┅┅─┅─┅─═┅❀┅═─┅─┅─┅┅─╯
ለመቀላቀል 👉🏽 @poemandquote
አስተያየት 👉🏽 @poemandquotebot
┏─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┓
❘ ❝ ሰው፡ከሆኑ፡በቂያችን፡ነው። ❞ ᴀ ❘
┗─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┛ | 0 |
| 15 | 🇪🇹ማክሰኞ ጳጉሜ ፩ ፳፻፲፬ ዓ.ም
╭─┅┅─┅─┅─═┅❀┅═─┅─┅─┅┅─╮
「❝ ሕዝቡ
መንግሥትን፡ሊቃወም፡ይችላል
መንግሥትን፡ሊደግፍ፡ይችላል
መብቱ፡ነው፡ግን
ሀገርን፡መቃወም፡እና
ሀገርን፡መደገፍ፡አይደለም። ❞」
╰─┅┅─┅─┅─═┅❀┅═─┅─┅─┅┅─╯
🗣 የትነበርሽ ንጉሤ
ለመቀላቀል 👉🏽 @poemandquote
አስተያየት 👉🏽 @poemandquotebot
┏─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┓
❘ ❝ ሰው፡ከሆኑ፡በቂያችን፡ነው። ❞ ᴀ ❘
┗─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┛ | 0 |
| 16 | 🇪🇹ማክሰኞ ጳጉሜ ፩ ፳፻፲፬ ዓ.ም
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
ሸህላ ሲነጋገር ፥ ሳልሰማ እንዳይመስልህ!
ሙት!
ከዕለታት አንድ ቀን ፥ አዳምጠኝ ልንገርህ
ከሸህላ ሠሪው ቤት ፥ ሄድኩና ማለዳ
እየጠፈጠፈ ጭቃ ፥ ሲያሰናዳ
"ዝግበል ጌታዬ! ፥ በቃህ! ጠፈጠፍከኝ!"
ጭቃው ሲጨቃጨቅ ፥ ሰምቼ ጨነቀኝ!
┈┈┈┈•◦●◉❖◉●••┈┈ ┈
✍🏽© ተስፋዬ ገሠሠ
╰══•••┈ 📔 መልክአ ዑመር
┈ ┈ ┈•◦●◉❖◉●••┈┈ ┈
፲፱፻፹፯ ዓ.ም
ለመቀላቀል 👉🏽 @poemandquote
አስተያየት 👉🏽 @poemandquotebot
┏─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┓
❘ ❝ ሰው፡ከሆኑ፡በቂያችን፡ነው። ❞ ᴀ ❘
┗─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┛ | 0 |
| 17 | 🇪🇹ማክሰኞ ጳጉሜ ፩ ፳፻፲፬ ዓ.ም
╭─┅┅─┅─┅─═┅❀┅═─┅─┅─┅┅─╮
「❝ ለማክሰኞ
የማይለቅ፡ሰኞ፡የለም። ❞」
╰─┅┅─┅─┅─═┅❀┅═─┅─┅─┅┅─╯
ለመቀላቀል 👉🏽 @poemandquote
አስተያየት 👉🏽 @poemandquotebot
┏─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┓
❘ ❝ ሰው፡ከሆኑ፡በቂያችን፡ነው። ❞ ᴀ ❘
┗─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┛ | 0 |
| 18 | 🇪🇹ሰኞ ነሐሴ ፴ ፳፻፲፬ ዓ.ም
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
አዉው ብትል ጅቦ ፥ መች እፈራሃለሁ
ና ብላኝ ና ብላኝ ፥ እደጅዋ ቆሜአለሁ
አዳራሹ ሰፊ ፥ ቤቱ አልጠበባችሁ
በተራ በተራ ፥ ምነዉ መግባታችሁ?
ከበጌምድር ጎጃም ፥ ተሻገር ያልከኝ
ሰሜን ወደሁዋላ ፥ ተመልከትልኝ
ለምን ገለበጡት ፥ ወተቱን በጋን
ችዬ እገፋዋለሁ ፥ የማልለዉን
ከዚያ ላይ ያለች ፥ ሸክላ ሰሪ
ድሃ ናት አሉ ፥ ጦም አዳሪ
ማን ነገራት ፥ ጥበቡን
ገልአፈር መሆኑን።
በጎጃም ያካፋል ፥ በሸዋ ፀሀይ
በጎንደር ደመና ፥ መቅረቱ ነውይ?
ቤተስኪያን ስሞ ፥ ለመኖር
መልካም ነው አሉ ፥ ጎንደር
አይቀርምና መዳኘት
ከተማሰው መግባት።
በገዛ አገራችን ፥ በገዛ ወንዛችን
በሉ እጠቡንና ፥ እንግባ እቤታችን
ቢወጡም ቢወርዱም ፥ ቢዞሩም በዓለም
እንደ ባልንጀራ ፥ የሚስማማ የለም
ቢጮኸው ቢያነባው ፥ ስላልጠቀመው
ድኾ በጉልበቱ ነው ፥ ያለቀሰው
ባለሁበት ሰፈር
እኔን ጠበበኝ ምድር
አንተ ነህና አለኝታዬ
አስፋ ወሰን ጌታዬ
ባልሻሪው ቢሠራ ፥ በዶማ ባካፋ
የዘሩትም ቀረ ፥ አልበቀለም ጠፋ
ባልሽ ወዴት ሄደ
ብለን ብንጠይቃት ፥ ስለ ጉዳያችን
ተሰብሮ አሁን መጥቶ ፥ ተኝቷል አለችን
ቢገዛን በጠላሁ ፥ የራስ ኃይሉ ልጅ
የኃላውን ካሳ ፥ ብፈራ ነው እንጅ
ባሁኑ ጦርነት ፥ ማንም ማን አይኮራ
ኃይለ ሥላሴ ነው ፥ ይኸንን የሠራ
አልነገርሽም ወይ ፥ ባላባት ነኝ ብለሽ
እንግዲያ ምነዋ ፥ ከዚህ ሃገር የለሽ?
የጠጅህን ማማር ፥ ብርሌህ ነገረኝ
ከጠላህ አደርስም ፥ ምንም ቢቸግረኝ።
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
ለመቀላቀል 👉🏽 @poemandquote
አስተያየት 👉🏽 @poemandquotebot
┏─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┓
❘ ❝ ሰው፡ከሆኑ፡በቂያችን፡ነው። ❞ ᴀ ❘
┗─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┛ | 0 |
| 19 | 🇪🇹ሰኞ ነሐሴ ፴ ፳፻፲፬ ዓ.ም
╭─┅┅─┅─┅─═┅❀┅═─┅─┅─┅┅─╮
「❝ ፫ ጥያቄ ልጠይቃችሁ
፩ ለምትፈልጉት፡ነገር፡ተዘጋጅታችኋል ?
፪ የምትፈልጉት፡ነገር፡በህይወታችሁ
ቢመጣ፡ደስተኛ፡ትሆናላችሁ ?
፫ የፀለያችሁት፡ነገር፡በህይወታችሁ
መምጣቱን፡እና፡አለመምጣቱን
አስተውላችሁ፡ታውቃላችሁ ? ❞」
╰─┅┅─┅─┅─═┅❀┅═─┅─┅─┅┅─╯
ምንጭ ➸ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ
እንወቃት እንኑራት
ለመቀላቀል 👉🏽 @poemandquote
አስተያየት 👉🏽 @poemandquotebot
┏─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┓
❘ ❝ ሰው፡ከሆኑ፡በቂያችን፡ነው። ❞ ᴀ ❘
┗─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┛ | 0 |
| 20 | 🇪🇹እሑድ ነሐሴ ፳፱ ፳፻፲፬ ዓ.ም
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
#ወንጌለ_ዘማይት
የቱ ጽድቄ ገዛህ?
ምን አይትህ ወደድከኝ? ፥ ምን ሳበህ ከነፍሴ?
ቀን ጥሎኝ ብሰየም
ከቤተ መቅደሱ ፥ እርሜን ለቅዳሴ
ይሄ አለት ልብህ…
በውበት አማልክት
በሹማምንት እንስት ፥ እንዳልተፈቀረ?
እንዴት ከዘማ ነፍስ?
ከሴት አዳሪ ልብ ፥ አጎንብሶ ቀረ?
ንገረኝ አንተዬ...
የእግዜር እንደልቡ ፥ የካህን ልጅ አንተ
ይሄ ንዑድ ልብህ
ከዘማ ሴት መዳፍ ፥ ምን ወዶ ሸፈተ?
አይተህልኝ አይደል?...
ከህመሙ ሊድን
ምሬታሙን ልቤን ፥ መፀፀት ቢገፋው
በገዛ መቅደሱ!
እግዜር ሳይቀየም ፥ አስቀዳሹን ከፋው።
ሰማህልኝ አይደል?...
ሐጢአት ቆጣሪዬን
የጽድቀቱን ዋጋ ፥ በእድፋቴ ጥጋት እያወራረደ
ከምስጋና አግዝፎ
የእርክሰቴን ዜማ ፥ እንዳመረገደ።
እንዲህ ባለ ሕማም...
መግታት ሞት ሆኖብኝ ፥ የእምባዬን ማዕበል
ሐፍረቴን ልታጠብ
ባርከህ በሰጠኸኝ ፥ የቅዳሴ ጸበል።
ምን ጋዬን ነካክተህ...
እንዴት ባለ ጥበብ? ፥ ስስ ነፍሴን ቃኘኸው!
እንዴት ብትበረታ?
ዐለቱ መንፈሴን ፥ በድል አገኘከው?
ተቅበዝባዡ ልቤ
ከጽሞናህ መንደር ፥ ምን ክብር አገኘ?
ከእልፍ ጻድቃን መሐል
ከመንፈስህ መንበር ፥ እንደምን ተገኘ?
አንተ እኮ...
ዘር ማንዘርህ ቅዱስ
አድባር የመረቀህ ፥ ለስምህ ከፍታ
አንተ የካህን ልጅ
ቤተ-እግዜር አገልጋይ ፥ እኔ ጋለሞታ
ለፍቅርህ በረከት...
ምን ኖሮኝ ምን ልስጥህ ፥ ግልብ ነው ታሪኬ
ሰውነቴ አይደለም
ዘማዊነት ነው ፥ የማንነት ልኬ።
አንተ እኮ...
ክህነተ ስልጣንህ
ዘመን እንዲጸና ፥ ሳይበጠስ ክሩ
ወይ መንኩሶ መኖር
ወይ ድንግል ማግባት ነው ፥ የሕግህ ድንበሩ!
የለህም ሌላ ፅንፍ !
አጉሎ ነው ሚያስቀርህ ፥ ከስስቴ ማጀት
አልታደልክልኝም
ለዘመኔ ዙፋን ፥ ሞገስ ሆነህ ማርጀት።
እመነኝ ዜማዬ...
ከማር ቢለሰልስ
ሸንጋላው ምላሴ፥ ቃሌን አታቃለው
እንዳትጠራጠር!
እስከ ጥግ ድረስ ፥ ወንድ ልጅ አውቃለው!
ከበደሌ ልሽር
ምሕረት ፍለጋዬ ፥ ከመቅደስ ቢያገባኝ
እርሜን ልድን ብቆም
የመታመን ልኩ ፥ ባንተ ነው የገባኝ፡፡
አቦጊዳዬ ሆይ..
ያልኖረውን ቁስል
በድፍን ስያሜ ፥ ደርሶ እያራከሰ
መች ይገባል ሕመም?
ንቀው የፈረዱት ፥ በራስ ካልደረሠ።
አስታወስክ እናቴን?...
የአድባሪቱ እመቤት
የቅዬው ፈገግታ ፥ በዘመኗ ሳለች
በቅጠል ሸጭ አቅሟ
በአንባሻ በብስኩት፥ አሳድግሃለች
ዕድሏ ሆነና...
ከእናትነቷ ጋር
የእንጀራዋ ገፈት ፥ እያንደፋደፋት
ጡቷን ሳታስጥለኝ
ሠካራሙ ባሏ ፥ አንገብግቦ ደፋት።
ከዛች ቀን በኃላ...
ህማሜን የሚያድስ ፥ ምን እውነት ቢረቅም
ሰውነት የገባኝ
በአባቴ ምስል ልክ ፥ ሌላ ሐቅ አላውቅም!
የአፍላነቴ ክታብ ፥ እንዲያ ነው ታሪኬ
ሠካራም የሰፋው ፥ ብርጭቆ ነው ልኬ!
አንተ ግን እንዲህ ነህ...
ለቀሚሴ በደል
ከከበረው መቅደስ ፥ ፈራጄ ቢሞላ
በፍቅር ስታብስ
ሀፍረት ያፈሰሰው ፥ የእንባዬን ዘለላ
አስቀዳሹ ሁሉ...
ሐቄን እንዳልሰማ
በነጠላ ሽፋን ፥ በሀሜት እያዳፋኝ
ሰው መሆን ሲቀደስ
ከልቦናህ መንበር ፥ እቃነቴ ጠፋኝ!
ግን እኮ...
ማዕረገ ክህነትህ
በኪዳን የጸና ፥ ዘመን አይበጥሰው
ስለ ፍቅርህ ዋጋ
የቀሚሴን ክብር ፥ አልገዛ አልመልሰው!
የስስትህ ስፍር
የጸጸቴ ልኩ ፥ በደሌን ቢሰፋም
ያገባኸኝ እንደው
ክህነትህ ተወግዞ ፥ አክሊል አትደፋም።
አምላክ ሆይ...
ምሕረትህ ሞገሱ!
ከጌትነት ማዕረግ
በባርነት ተርታ ፥ ፍቅር ካሳነሰው
ለይቅርታህ ዋጋህ
ከበደል መመለስ ፥ አይበቃም ወይ ለሰው?!
እንዴት ከፍቅር ውል ፥ ክብር ሚዛን ደፋ?
ምነው ምርቃትህ ፥ ከእርግማንህ ከፋ?
እንደ መግደላዊት
ናርዶሴን አንግቼ ፥ በዕንባ ባላርስህ
ቀሚሴን ቀድጄ
ዳግም ላልታደፍ ፥ ስምል ከቤተ መቅደስህ
የጸጸቴን ድርድር
በዕንባዬ በገና ፥ ሳዜም እያየኸኝ
አንድ እሺ አጣህ ፥ ሺህ ጊዜ ገለኸኝ?!
እኖርለት ሰበብ...
ከአይኖቹ በቀረ ፥ ማምሻ እድሜም የለኝም!
ደግሞ እንደልማድህ
ለበጎ ነው ብትል ፥ አታባብለኝም።
አጸናህልኝ ስል...
የበደሌን ፍትሕ ፥ በቅን ነፍሱ በኩል
ስትቀብረኝ አታዝንም ፥ ከኖረ ሰው እኩል?
ታውቃታለህ ልኬን ፥ ሞግቼህ አልዘልቅም
የእስትንፋሴ ክራር ፥ ዕንባ ነው የኔ አቅም።
እስቲ ዕምባዬ...
ልግባህ !
ህመሜን ሳትመስል ፥ አትፍሰስ ዘላለም
ሳል !
በጉንጮቼ ላይ ፥ የስሜቴን ቀለም
አስኪ ዕምባዬ...
ኑረኝ !
እናት ሁነኝ ባክህ? ፥ ቻል ከሰማይ ስፋ!
እንደርኩስ ቀሚሴ...
ለገለበህ ሁሉ
የትም አትሰፈር ፥ የትም አትሰፋ
ጀግን በፍቅርህ ፊት ፥ ፈሰህ አታሳጣኝ!
በቂ ነው ለሞቴ ፥ መተፋት የቀጣኝ።
ሰው ሁነኝ ዕንባዬ
ከሸንጎ አታዋርደኝ! ፥ በጠፋ ቀን ፈራጅ
ምስክር የለኝም
ዘማዊነቴ ስር
ስለተፀነሰው ፥ የክርስቶስ ውላጅ
ጨክንልኝ እስኪ!...
የልቤን አታሳይ! ፥ ሁን እንዳልወደደ
ዘመኑን ይመረቅ
በክህነተ ክብሩ ፥ እንደተወደደ
አያጎንብስ በኔ
ከአድባር አይነጠል ፥ አትፈር እናቱ
በሞገስ ይደፋ
ስለንጽህናው ፥ ውድ አክሊል ከአናቱ
ታመመኝ ዕንባዬ
ምጠህ አበድረኝ ፥ የኩራት ፈገግታ
እንደለመደችው
ጠግባ ነው እንዲለኝ ፥ ይቺ ጋለሞታ።
ነፍሷ እንደው ገነቱ
እሷ እንደው ዓለሟ ፥ ከደላት መጋደም
ይብላኝ ላፈቀርኳት
የማመኔን ጸበል ፥ ለወሰችው ከደም።
ይስደበኝ ከነፍሱ ፥ ስሜ መች አሳሳኝ?
እርግማኑ ቀንቶት ፥ ዘላለም በረሳኝ!
ሌላ አቅም የለኝም ፥ መራቅ ነው መባዬ
ጨክኜ ልሸኘው ፥ መርቀኝ ዕንባዬ!
አቦጊዳዬ ሆይ...
ናፍቆትህ ንጉሡ
አጎንብሶ ግብቶ ፥ ዘላለም ይረታል
ወዶ ማጣት ክፉ ፥ ከሞት ይበረታል!
አቦጊዳ ሆይ...
ለፈገግታ ስፍር ፥ ላልሞላ ብጎልም ?
ሰጠሁህ ነው እንጂ ፥ አጣሁህ አልልም!
ባነገስከኝ መቅደስ ፥ ለነፍስህ ሐቅ ዋሸው
ስለዕንባዬ መጣህ ፥ ስለክብርህ ሸሸሁ
በመሸሼም ክራር
አባብለዋለሁ ፥ የመተፋት ስንቄን
መጥላት በጸነሱ
ዕንባዎችህ መሐል ፥ አየዋለሁ ሳቄን!
እንዴት ባፈቅርህ ነው?!
┈┈┈┈•◦●◉❖◉●••┈┈ ┈
✍🏽© ህሊና ደሳለኝ
╰══•••┈ ┈ ┈•◦●◉❖◉●••┈┈ ┈
ለመቀላቀል 👉🏽 @poemandquote
አስተያየት 👉🏽 @poemandquotebot
┏─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┓
❘ ❝ ሰው፡ከሆኑ፡በቂያችን፡ነው። ❞ ᴀ ❘
┗─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┛ | 0 |
