en
Feedback
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን🙏

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን🙏

Open in Telegram

የኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያንን ዶግማና ቀኖና የጠበቁ የነፍስ ስንቅ የምናገኝበት፦ ✍️"ማንም አንዳች የሚያውቅ ቢመስለው ሊያውቅ እንደሚገባው ገና አላወቀም" ፩ኛ ቆሮ. ፰፥፪ #ለተጨማሪ፦👇✞👇 https://www.youtube.com/EOTC2921 https://www.facebook.com/eotc2921 https://www.tiktok.com/@eotc2921 https://www.instagram.com/eotc2921

Show more
4 374
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
🌿🌾 #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ🌾🌿 ✔እውነተኛ ፈተና አንድና አንድ ብቻ ነው ፣ እርሱም ኃጢአት ነው፡፡ ✔አንተ የራስን ድርሻ ተወጥተ ስትጨርስ እግዚአብሔር የራሱን ድርሻ ይወጣል፡፡ ✔መውደቅ አዳማዊ ነው ወድቆ አለመነሳት ግን ዲያብሎሳዊ ነው፡፡ ✔ከውኃ እንዴት እንወለዳለን የሚል ሰው ካለ እንዴት ከአፈር ተወለድን ብዬ እጠይቀዋለው፡፡" ✔ደጋግመህ ኃጢአት ብትሠራም ደጋግመህ ንስሐ ግባ፡፡ ቤተክርስቲያን ሐኪም ቤት እንጂ ፍርድ ቤት አይደለችምና፡፡” ✔ትዕቢት የነበረንን መልካም ምግባር ሁሉ የሚያሳምም ደግሞም የሚገድል ክፋ ደዌ ነው፡፡ ✔ከእግዚአብሔር ጋር ታረቅ ፤ ከዚያም ሰማይና ምድር ከአንተ ጋር ይታረቃሉ ✔ዕውቀት የሚባለው የገዛ ራስን ሲያውቁ ነው፡፡ ራስን አለማወቅ ከለየለት ዕብደት እጅግ የከፋ ነውና፡፡ ምክንያቱም የለየለት ዕብደት የሚባለው ሳይወዱና ሳይፈቅዱ የሚመጣ በሽታ ሲኾን ራስን አለማወቅ ግን ወደውና ፈቅደው የሚያብዱት ዕብደት ነው፡፡ ✔ሰዎች ከፍቅር በላይ በየትኛውም ዓይነት መንገድ ከክፋታቸው ልንመልሳቸው አንችልም፡፡ ፍቅር ሰዎች ከአውሬነታቸው መልሳ ሰዎች እንድሆኑ የምታደርግ ታላቅ መምህርት ናት፡፡ ✔የበለስ ቅጠል ሰፊና ደስ የምታሰኝ ናት፤ ወደ ጥፋት የምትወስደው የኃጢአት መንገድም ሰፊ በር ናት፡፡ የበለስ ፍሬ ሲበሏትና ሲያላምጧት ጣፋጭ ናት፤ ኃጢአትም ሲሠሯት ደስ ታሰኛለች፡፡ ከሠሯት በኋላ ግን (እንደ በለሲቱ) መከራን ታመጣለች፡፡ በሚሠሯት ጊዜ ጣፋጭ ከሠሯት በኋላ ግን መራር ናትና እርሷን ከመሥራት ሽሽ፡፡ •••✞✞✞•••✞✞✞•••✞✞✞••• ✞ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያንን አስተምሮና ስርዓት የጠበቁ የተለያዩ መርሃ ግብሮች በየቀኑ ወደ እርስዎ ይቀርባሉ፡፡ ለወዳጅዎ #Share በመድረግ የበረከት ተካፋይ ያድርጓቸው ✞ ╭══•|❀:๑✞♡✞๑:❀|•══╮ https://t.me/EOTC2921 ╰══•|❀:๑✞♡✞๑:❀|•══╯

➍✝#ኃያል ኃያልነት የበሕርይ ገንዘቡ ነው "ኀይሉ ለአብ ወጸጋ ለአህዛብ…”የአብ ኃሉ እርሱ ነው ለአህዛብም ጸጋን የሚሰጥ “ እነዳለ መጽሐፈ ኪዳን፡፡ መንግሥትህ ያንተ ናትና ኃይል ምስጋና ክብር ለዘላለሙ” ማቴ 6፥13 በኃይሉ ኃይለኛው ቤት ገብቶ ዕቃዉን ሊነጥቀዉ እንዴት ይቻላል።ማቴ 12፥29👉“ክርስቶስም ስለ እናንተ አይደክምም /ደካማ/አይደለም ነገር ግን በእናንተ ኃለኛ ነው በድካም ተሰቅሏልና ነገር ግን በእግዚአበሔር /በእግዚአብሔር/ኃይል በሕይወት ይኖራል 1ኛ ቆሮ 13፥3-5 👉“የእግዚአብሔር ጥበብ የሆነው ክርስቶስ ነው” 1ቆሮ 1፣24-26 ሰዎች ይህንን የእግዚአብሔር ኃይል አላወቁም ነበር። 👉“የእግዚአብሔርን ኃይል አታዉቁም እና ትስታለችሁ” ማቴ 22፥22 ➎✝#አምላክ ➏✝#የዘላለም_አባት ➐✝#የሰላም_አለቃ { ትንቢተ ኢሳያስ (ምዕራፍ 9፥6:7) } 👉"ሕፃን ተወልዷልና ወንድ ልጅም ተሰቶናልና አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል፡ ስሙም ድንቅ መካር ሀያል አምላክ፡ የዘላለም አባት የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል፡ ለአለቆች ሰላምን ለዕርሱም ህይወትን አመጣለሁና፡ ከዛሬ ጀሞሮ እስከ ዘልአለም ድረስ በፍርድና በፅድቅ ያፀናውና ይደግፈው ግዛቱ ታላቅ ይሆናል፡ በዳዊት ዙፋን መንግስቱም ትፀናለች ለሰላሙም ፍፃሜ የለውም። የእግዚአብሔር ቅንነት ይህንን ያደርጋል።" 🌾🌾🌾🙏🙏🙏🌾🌾🌾 ውድ የተዋሕዶ ቤተሰቦች የሆናችሁ የእናቱ የእናታችን የቅድስተ ቅዱሳን የንጽሕይተ ንጹሐን የድንግል ማርያም የዓሥራት የአደራ ልጆች የሆናችሁ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን። በዓሉ፦ 🕊የሰላም 😁የደስታ 👩‍❤️‍👨የፍቅር 🧖‍♂የጤና 👨‍👩‍👧‍👦የመተሳሰብ 🐥የመተዛዘን 🌾የበረከት 🌽የእረድኤት ⛪️የስኬት 🌻የቅንነት ይሆንልን ዘንድ የፈጣሪ ቅዱስ ፈቃዱ ይሁን አሜን!!! ✞ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያንን አስተምሮና ስርዓት የጠበቁ የተለያዩ መርሃ ግብሮች በየቀኑ ወደ እርስዎ ይቀርባሉ፡፡ ለወዳጅዎ #Share በመድረግ የበረከት ተካፋይ ያድርጓቸው ✞ ╭══•|❀:๑✞♡✞๑:❀|•══╮ https://t.me/EOTC2921 ╰══•|❀:๑✞♡✞๑:❀|•══╯

🌾✞ #ሕፃን_ተወልዶልናልና ✞🌾 በስመ አብ ወወለወድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን 👉ልደታትን ስንመለከት ብዙ አሉ፦ ልደተ አዳም ከምድር፣ ልደተ ሔዋን ከአዳም ፣ልደተ ሙታን ከመቃብር፣ ልደተ ሕፃናት ከእናታቸው ማህፀን የሚጠቀሱት ናቸው፡፡የእነዚህ ሁሉ ልደት ለራሳቸው እንጂ ለእኛ አይደሉም። 👉#ህፃን_ተወለልዶልናልና የሚለው ግን ለእኛ ነው፡፡ የአምላክን መወለድ ብዙ ነቢያት በብዙ ሕብረ ትንቢት ተናግረዋል በብዙ ሕብረ አምሳል መስለዋል፡፡ 👉ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር በብዙ አይነትና በብዙ ጎዳና ለአባቶቻችን በነቢያት ተናግሮ ሁሉን ወራሽ ባደረገው ዳግምም ዓለማትን በፈጠረበት በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን።ዕብ፡1፥1 በብዙ ሕበረ አምሳል በብዙ ሕብረ ትንቢት እግዚአብሔር ከተናገረባቸው ነቢያት አንዱ ኢሳይያስ ነው። ኢሳይያስ ከነቢያት ወንድሞች በተለየ መልኩ የአምላክን ሰው መሆን የተናገረ ነቢይ ነው። መወለዱን፣ስሙን፣ከማን እነደሚወለድ ፣ለሰው ልጆች ያደረገውን የቤዛነት ስራ መከራ መቀበሉን ፣በጎል መወለዱን በግልፅ ከተናገሩ የተነሳ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ወንጌላዊ ነቢይ የሚል ቀጽል ሰጥተው ይጠሩታል፡፡የትንቢት መጽሐፉንም ደረቅ ሐዲስ በማለት ሰይመውታል፡፡ይህም ማለት ስለክርስቶስ መወለድ በምሰሌ ያይደለ በቀጥታ የተናገረ በመሆኑ ነው ለምሳሌ የሚከተሉትን ማየት ይቻላል፡፡ 👉"ጌታ ምልክት ይሰጣችኋል እነሆ ድንግል ትጸንሳለች ወንድ ልጅንም ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።"ኢሳ፡7፥14 ከላይ ባጭሩ እንዳየነው ከማን እንደምትወልድ ስሙን ማን አንደሆነ በግልጽ እስቀምጧል፡፡ 👉"በስድስተኛው ወር ገብርኤል መላክ ከእግዚአብሔር ዘንድ ተላከ ከዳዊት ወገን የሆነ ስሙ ዮሴፍ ለሚባል ሰው ከታጨች ከድንግል ዘንድ የዚህች ድንግል ስሟ ማርያም ነው"ሉቃ፡1፥26 በማለት ወንጌለዊው ገልጧል። 👉"በነቢይ ከጌታ ዘንድ እነሆ ድንገል ትፀንሳለች ወንድ ልጅም ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤል ይሉታል የተባለውን ይፈጸም ዘንድ ይህ ሁሉ ሆኗል ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ነው። ማቴ፡1፥22 ኢሳይያስ "ሕፃን ተወልዶልናል" ብሎ ለእኛ መዳን የተወለደው ነገረን ቀጥሎም ወንድ ልጅ ተሰጥቶናል።" ይላል። ሥጋውን በልተን ደሙን ጠጥተን መድኃኒት ለሆነን እንደመጣ ሊያሳይ፡፡ ከዚህ በመቀጠል እርሱን ለመግለጥ የተጠቀማቸው ቃላት በጣም የሚደንቁ ናቸው፡፡ #ስሙ_ድንቅ_መካር_ኃያል_አምላክ_የዘላዓለምአባት_የሰላምአለቃ በሚሉ #ሰባት ቃላት ገልጾታል ቁጥሩ በእብራዊያን ዘንድ ፍጹም ነው። ከላይ ኢሳይያስ የተጠቀማቸው ሰባት ቃላት ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው መሆኑን የሚያስረዱ ናቸው፡፡ ሕፃን ብሎት ነበር ሕፃን የሚለው ስም ታህታዊ ማንም በሥጋ የወለደ ሰው ሲወለድ የሚጠራበር ነው ፡፡ ሰው መሆኑን ለመግለጥ ሕጻን አለው አምላክነቱን ለማስረዳት ስሙም ብሎ ጀምሮ በሰባት ቃለት አስረድቶናል፡፡ ➊✝#ስሙ ስለ ስሙ ቅዱሳት መጻፍት ሲናገሩ ኢየሱስ ፣አማኑኤል፣ ክርስቶስ ፣መድኃኔዓለም የሚባሉት ስመ ስጋዌ ናቸው። ሰው በመሆኑ የተጠራባቸው ኢየሱስ፦ማለት መድሐኒት ማለት ነው፡፡ አማኑኤል፦ማለት እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ነው። ከእኛ ጋር፦ ሲባል ከስጋችን ሥጋ ከደማችን ደምን ነስቶ ሰው የሆነ አምላክ ማለት ነው። ክርስቶስ፦ማለት መሲህ ፣ሹም፣ንጉሥ ፣አለቃ ማለት ነው፡፡ መድኃኔዓለም፦ማለት የአለም መድኃኒት የዓለም ቤዛ ደሙን አፍስሶ ሥጋውን ቆርሶ በደሙ ዓለምን የዋጀ ማለት ነው፡፡ 👉"ልጅም ትወልዳለች እርሱም ሕዝቡን ከኃጢያታቸው ያድናቸዋልና ስሙን ኢየሱስ ትለዋለች" ማቴ፡1፥21 👉"ክርስቶስ የሚባል መሲሕ እንዲመጣ አውቃለሁ እርሱ በመጣ ጊዜ ሁሉን ይነግረናል አለችዉ ኢየሱስም የምትናገሪዉ እርሱ እኔ ነኝ አላት።"ዮሐ፡1፥42 👉"እኛ ራሳችን ሰምተነዋል አርሱም በእውነት ክርስቶስ የዓለም መድኃኒት እንደሆነ እናውቃለን።"ዮሐ፡4፥42 ከላይ የተመለከትናቸው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ስሙንና ግብሩን የሚገልጡ ናቸው፡፡ ትርጉሙ ከተግባር ጋር የተያያዘ ነውና ይህንን ነው ኢሳይያሰ “ሕፃን ተወለደልን” በማለት የተነገረለት ኢሳይያስም ሕጻን ብሎ የጠራዉ ሰዉ ሲሆን አምላክነቱ አልተለወጠምና አምላክነቱን መግለጥ የሚችሉ ቃላት ከስሙ ጀምሮ ተጠቅሟል ስሙ አዳኝ ነው። 👉"አቤቱ በስምህ አድነኝ።"መዝ፡53፥1 👉ስሙ ቅዱስ ነው፤ እርሱ ለእኔ ታላቅ ስራ አድርጎል እና ስሙም ቅዱስ ነው።"ሉቃ 1፥50 👉ስሙ፦ አጋንንትን ይገዛል "አጋንንት በስምህ ተገዙልን።"ሉቃ 10፥17 👉ያመኑትን እነዚህን ምልክቶች ይከተሏቸዋል በስሜ አጋንትን ያወጣሉ እባቦችን ይይዛሉ የሚያሰክር መርዝ ቢጠጡ አይገድላቸውም።ማር 16፥17 👉ስሙ፦ ስግደት የሚገባው ነው ?"እግዚአብሔር/እግዚአብሔርነቱ/ ያለልክ ከፍ ከፍ አድርገው ከስምም ሁሉ በላይ ያለዉን ስም ሰጠው ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ ለኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይንበርከኩ ዘንድ።" ቆላ 2፥9-11 👉ስሙ፦ ምስጋና ይገባዋል 👉"በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ ስምህ ይቀደስ.."ማቴ 6፥9 ➋✝#ድንቅ ድንቅ፦ማለት ቃል እነደሚገባው አድርጎ የማይገልጠዉ ቃላት ላጣንለት ነገር የምንጠቀመዉ ነዉ በህቱም ድንግልና ተጸንሶ በህቱም ድንግልና መወለዱን ሲደንቅ የሚኖር ነውና በኪሩቤል ላይ የሚገለጥ ስጋን ለብሶ መወለዱን የማይወስነዉ መወሰኑ የማይዳሰሰው መዳሰሱ የማይታየው መታየቱ የማይጨበጠው እሳተመለኮት በጨርቅ መጠቅለሉ በጎል መጣሉ የሚደንቀን ነው እነኳን ለኢሳይያስ ለመላእክትም ድነቅ ነው። ሰማይ ዙፋኑ የሆነ አምላክ በትህትና መገለጡ ድሆች እንኳ ባልተወለዱበት የከብቶቸች በረት መወለዱ ድንቅ ነው፡፡ 👉"በልዎ ለእግዚአብሔር ግሩም ግብርከ"(እግዚአብሔርን ስራህ ድንቅ ነው በሉት) መዝ፡65፥3 ሕፃናትን በእናታቸው ማህጸን የሚጠብቃቸው ሕጻን ሆነ ይህ እንዴት አይደንቅ 👉"ስራህ ድንቅ ነው ነፍሴም እጅግ ታዉቀዋለች።"መዝ 138፥12 በላይ በሰማይ በኪቤል ጀርባ በምድር በእናቱ እቅፍ መታየቱ ድንቅ ነው? "ግንበኞች የናቁት ድንጋይ እርሱ የማእዘን ራስ ሆነ ይህም ከጌታ ዘንድ ሆነ ለዓይናችን ድንቅ ነው።"መዝ 117፥22 ማቴ 22፥42 ➌✝#መካር ሰው ለመሆን መወሰኑን በልብ የመከረውን በነብያት ያናገረውን ያን የፈጸመ ምክረ ከይሲን በምክሩ የሻረ ዲያብሎስን ያሣፈረ በልቡ ጥበብ ከሰው ልጆች በተለየች ምክሩ አዳምን ነጻ ያወጣ መካር ነው፡፡👉"ግሩም ምክሩ እምጎለመኸያው (ምክሩ ከሰው ልጆች ይልቅ ልዩ ነው)"መዝ 65፥5 በዚህ በልዩ ምክሩ ዲያብሎስ የመከራቸውን የነፍስና የስጋ ተዋህዶ በሥጋ ተወለደ ይህ የዲያብሎስን ስራ ያፈርስ ዘንድ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ። 1ኛ ተሰ 3፥7👉"ውዕቱ ጥበቡ ወምክሩ ያድኅነነ መጸአ (እርሱ የአብ ጥበቡና ምክሩ ሊያድነን መጣ)" ይለዋል ቅዱስ ያሬድ፤

🌾✞ #ገድሉ_ታምራቱ ✞🌾 https://t.me/EOTC2921 ገድሉ ታምራቱ እጅግ ብዙ ነው ጣዖትን አዋርዶ የተሸለመው የተዋህዶ ኮከብ ተክለ ሐዋርያ አባ ተክለሃይማኖት ዘኢትዮጵያ #አዝ__________⏭✞⏮// ዳግማዊ ዩሐንስ ጠፍር የታጠቀ ፍፁም ባህታዊ ጠላት ያስጨነቀ የፀጋ ዘአብ ፍሬ ዛፍ ሆኖ በቀለ በደብረሊባኖስ መናኝ አስከተለ #አዝ__________⏭✞⏮// ደካማ መስሏቸው በአንድ እግሩ ቢያዩት ባለ ስድስት ክንፉ ተክልዬ የእኔ አባት እርሱስ አንበሳ ነው ይናገር ደብረ አስቦ ሌጊዮን ሲዋረድ እፍረት ተከናንቦ #አዝ__________⏭✞⏮// ከካህናት መካከል ህሩይ ነው ተክልዬ መጣሁ ከገዳምህ ልሳለምህ ብዬ ኢትዮጵያዊው ቅዱስ አባ ተክለሃይማኖት ወልድ ዋህድ ብለህ ምድሪቷን ቀደስካት #አዝ__________⏭✞⏮// የባረከው ውሃ የረገጥከው መሬት ጥላህ ያረፈበት ሆኗል ፀበል እምነት ኑና ተመልከቱ ድውያን ሲፈቱ ይሰብካል ተክልዬ ዛሬም እንደ ጥንቱ #አዝ__________⏭✞⏮//

✞ #ቅዱስ_ተክለ_ሃይማኖት_ሐዋርያዊ ✞ #ልደት፦ 🌾✞ መልካም ዛፍ መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን የወለዱት ደጋጉ: ጸጋ ዘአብ ካህኑና እግዚእ ኃረያ ናቸው:: እርሱ በክህነቱ: እርሷ በደግነቷ: በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ ፍሬን ሰጥቷቸዋል:: 🌾✞ በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ ቢደርስባቸው ቅዱስ ሚካኤል: ጸጋ ዘአብን ከሞት: እግዚእ ኃረያን ከትድምርተ አረሚ (ከአረማዊ ጋብቻ) አድኗቸዋል:: በሁዋላም የቅዱሱን መወለድ አብስሯቸዋል:: 🌾✞ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የጸነሱት መጋቢት 24 ቀን በ1206 ዓ/ም ሲሆን የተወለዱት ደግሞ ታሕሳስ24 ቀን በ1207 ዓ/ም ነው:: በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት ተገልጸዋል:: ቤታቸውም በበረከት ሞልቷል:: #ዕድገት፦ 🌾✞የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው "ፍሥሃ ጽዮን" ይሰኛል:: ይሕንን ስም ይዘው: አባታቸው ጸጋ ዘአብን ተከትለው አድገዋል:: በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን (ብሉያት: ሐዲሳትን) ተምረዋል:: በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል:: ዲቁናም ከወቅቱ ዻዻስ አባ ጌርሎስ ተቀብለዋል:: #መጠራት፦ 🌾✞አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮስ ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ ተሰማ:: የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላእክት እያመሰገኑ በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ:: 🌾✞የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ:: "ከዛሬ ጀምሮ ስምህ ተክለ ሃይማኖት (ተክለ ሥላሴ) ይሁን:: ከዚህ በሁዋላ አራዊትን ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ:: ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ" ብሎ በግርማ ዐረገ:: ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ ጊዜ በሁዋላ ሰዓትን አላጠፉም:: ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ ይዘው ቤታቸው እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ:: #አገልግሎት፦ 🌾✞ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዻዻሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል አገልግሎትን ጀመሩ:: በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ (ጽላልሽ) አካባቢ ብቻ በ10ሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው አጠመቁ:: ያን ጊዜ ኢትዮዽያ 2 መልክ ነበራት:: 🌾✞1ኛ ዮዲት (ጉዲት) በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽዕኖ ወደ ደቡብ አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዷል: ወይም በባዕድ አምልኮ ተጠምዷል:: 2ኛው ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር:: 🌾✞ግማሹ ሃገር በጨለመበት ወቅት የደረሱት ሐዲስ ሐዋርያ አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ:: ሕዝቡን: መሣፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው: ማርያኖችን (ጠንቁዋዮችን) አጥፍተዋል:: #ገዳማዊ_ሕይወት፦ 🌾✞ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮዽያን ከማብራታቸው ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል:: እርሳቸው ከሁሉ የተሻሉ ሳሉም በ3 ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል:: 🌾✞እነዚህም በአቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ለ12 ዓመታት: በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ ገዳም ለ7 ዓመታት: በደብረ ዳሞ ከአቡነ ዮሐኒ ጋር ለ7 ዓመታት: በአጠቃላይ ለ26 ዓመታት አገልግለዋል:: 🌾✞በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ በሁዋላም ወደ ምድረ ሽዋ (ዞረሬ) ተመልሰው በአንዲት በዓት ውስጥ ለ22 ዓመታት ቆመው ጸልየዋል:: በተሰበረ እግራቸውም 6 ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል:: #ስድስት_ክንፍ፦ 🌾✞ኢትዮዽያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከኢትዮዽያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት መካናት ተባርከዋል:: ጻድቁ ምድረ እሥራኤል የገቡት በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ: እያስተማሩና እያሳመኑ ነበር:: 🌾✞የወቅቱ ሊቀ ዻዻሳት አባ ሚካኤል ጋርም ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል:: ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ በሁዋላ ነው:: ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ እንባቸው ይፈስ ነበር:: 🌾✞ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም:: በገሃድ:- -በቤተ መቅደስ ብስራቱን -በቤተ ልሔም ልደቱን -በቤተ ዮሴፍ ግዝረቱን -በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን -በቤተ አልዓዛር ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር:: 🌾✞የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል ወደ ሆነው ቀራንዮ ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ ቢመለከቱት ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ:: በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ እመቤታችን ድንግል ማርያም ፈጥና ደርሳ ተክልየን ወደ ሰማይ አሳረገቻቸው:: 🌾✞በዚያም:- -የብርሃን ዐይን ተቀብለው -6 ክንፍ አብቅለው -የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው -ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው -ከ24ቱ ካህናተ ሰማይም ተደምረው -ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው -"ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል:: #ተአምራት፦ #የተክልየ ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው:: *ሙት አንስተዋል *ድውያንን ፈውሰዋል *አጋንንትን አሳደዋል *እሳትን ጨብጠዋል *በክንፍ በረዋል *ደመናን ዙፋን አድርገዋል:: 🌾✞ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን መሥርተዋል:: በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕጻናት አብረው ኑረዋል:: በዘመናቸው ሰይጣን ታሥሯልና:: #ዕረፍት፦ 🌾✞ጻድቅ: ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን ሆነው መከራን በብዙ ተቀብለው: እልፍ አእላፍ ፍሬን አፍርተው: በተወለዱ በ99 ዓመት: ከ8 ወር: ከ1 ቀናቸው ነሐሴ 24 ቀን በ1306 ዓ/ም ዐርፈዋል:: ጌታ: ድንግል ማርያምና ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል:: 10 ትውልድ የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል:: 🌾✞የጻድቁ አባታችን ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት የቅድስናና የክብር ስሞች፦ 1.ተክለ አብ: ተክለ ወልድ: ተክለ መንፈስ ቅዱስ 2.ፍስሐ ፅዮን 3.ሐዲስ ሐዋርያ 4.መምሕረ ትሩፋት 5.ካህነ ሠማይ 6.ምድራዊ መልዐክ 7.እለ ስድስቱ ክነፊሁ (ባለ ስድስት ክንፍ) 8.ጻድቅ ገዳማዊ 9.ትሩፈ ምግባር 10.ሰማዕት 11.የኢትዮዽያ መነኮሳት አለቃ 12.ፀሐይ ዘበፀጋ 13.የኢትዮዽያ ብርሃኑዋ 14.ብእሴ እግዚአብሔር (የእግዚአብሔር ሰው) 15.መናኒ 16.ኤዺስ ቆዾስ (እጨጌ) "ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል:: ጻድቅን በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል::" ማቴ.10:40 ከጻድቁ አባታችን ረድኤት በረከት ይክፈለን፤አሜን።

🌾✞ #መድኃኒት_ነህና ✞🌾 https://t.me/EOTC2921 መድኃኒት ነህና በስጋ በነፍስ እንጠራኀለን ብለን ኢየሱስ ጥዑመ ስም ያልነው ስለጣፈጠን ነው ከስም ሁሉ በላይ ስምህስ ልዩ ነው /፪/ ከሰማያት በላይ እንድንድንበት ተሰጠን ይሄ ስም እንድናምንበት ማእበሉን ያቆመ ባህር የከፈለው የአምላካችን ስሙ የጸና ግንብ ነው #አዝ ለፍርድ ቢያቆሙንም በሸንጓቸው ከሰው እንዳታስተምሩ በኢየሱስ ስም ብለው አይሁድን ሳንፈራ ሰበክነው በአዋጅ ስለተገለጠ ዓለሙን ሊዋጅ #አዝ ከሰው ይልቅ ለአምላክ ይገባል መታዘዝ እንዴት እንኖራለን ቅዱሱን ሥም ሳንይዝ ሞት ነው ወይስ እርሃብ ስደት ወይ መከራ እኛን የሚያዘገይ ስሙን እንዳንጠራ #አዝ ሽባውን ተርትረን እውር ያበራነው ጎባጣን አቅንተን ድንቅን ያደረግነው በእርሱ ስም ሰብከን ነው በእርሱ ስም ተማጽነን አልጫውን ዓለም በወንጌል ያጣፈጥን #አዝ የሚመጣው ቢሆን ያለውም ቢሆን ሊያቆመን አይችልም ከእርሱ ሊለየን ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ሥሙ ነው መድኀኒት ስሙ እኮ ነው ፈውስ #አዝ 🎤ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ

☞ “…ለሊሁ እግዚአብሔር ዘበአማን ወወልደ እግዚአብሔር ዋሕድ ብርሃን ዘእምብርሃን ወሕይወት ወኀይል ነሥአ ዘኢዚኣሁ…” (… አንድ የእግዚአብሔር ልጅ ከብርሃን የተገኘ ብርሃን ሕይወት ኀይል የሚኾን ርሱ እግዚአብሔር ባሕርዩ ያልነበረ ሥጋን ተዋሐደ) (ቅዱስ ቄርሎስ) ☞ “ወነአምን ቦቱ ከመ ውእቱ እግዚአብሔር ቃል ዘበአማን ወለድንግልሂ ንጽሕት ወላዲተ አምላክ ንሰምያ እመ እግዚአብሔር” (በእውነት ርሱ እግዚአብሔር ቃል እንደኾነ እናምንበታለን፤ አምላክን የወለደች ንጽሕት ድንግልንም የእግዚአብሔር እናት እንላታለን) (ቅዱስ ቄርሎስ) ☞ “ምንት ውእቱ ተሳትፎ በእሉ ከመዝ ዘእንበለ ከዊኖቱ ከማነ በሥጋ ወደም እምድንግል ቅድስት ወላዲተ እግዚአብሔር ማርያም እንዘ ውእቱ አምላከ ጽድቅ…” (በሥጋ ሰዎችን መምሰሉ ምንድን ነው? የባሕርይ አምላክ ሲኾን እግዚአብሔርን ከወለደች ከቅድስት ድንግል ማርያም በነሣው በነፍስ በሥጋ እንደ እኛ ሰው መኾኑ ነው እንጂ፤ ይኸውም ከአብ የተወለደ አካላዊ ቃል ነው፤ ለዘለዓለምም ከአብ ጋራ ትክክል ነው፤ በባሕርዩ ቀዳማዊ ነው፤ ልዕልና ባለው ጌትነት ርሱ ብቻውን ያበራል) (ቅዱስ ቄርሎስ) ☞ “ወከመዝ ንሕነ ነአምን ከመ ድንግል ቅድስት ኮነት ታኦዶኮስ (ቴኦቶኮስ) ዘውእቱ ወላዲተ እግዚአብሔር ብሂል ወሶበ ወለደቶ ለነ መንክረ ለዋሕድ ክርስቶስ በተሣትፎቱ ደመ ወሥጋ ከማነ” (እንደኛ ነፍስን ሥጋን በመዋሐዱ አንድ ክርስቶስ ድንቅ በሚያሰኝ ልደት በወለደችው ጊዜም ንጽሕት ድንግል ታኦዶኮስ (ቴኦቶኮስ) (Θεοτόκος,) እንደኾነች እናምናለን፤ ይኸውም እግዚብሔርን የወለደች ማለት ነው) (ቅዱስ ቄርሎስ) ☞ “ወኮነ ሰማይ ዓለመ ወዓለምሂ ሰማየ ወኮነ እግዚአብሔር ሰብአ በታሕቱ ወረሰዮ ለሰብእ ውስተ አርያም…” (ሰማይ ዓለም ኾነ፤ ዓለምም ሰማይን ኾነ፤ እግዚአብሔር ሰው ኾኖ በዚኽ ዓለም ተገኘ፤ ሰውንም በላይ በአርያም አደረገው፤ በሰማይ የሚቀርበው ምስጋና በዚኽ ዓለም ተደረገ፤ በአብ ዕሪና ያለ ርሱ በማርያም ክንድ ተይዞ ታየ፤ እግዚአብሔር አብ በማይመረመር ምስጢር ያለ እናት የወለደውን ማርያም በማይመረመር ምስጢር ያለ ዘርዐ ብእሲ በሥጋ ወለደችው) (ቅዱስ ሳዊሮስ) ☞ “ወካዕበ ይቤ እስመ እግዚአብሔር አስተርአየ ለሰብእ በተወልዶ ወመጽአ ኀበ ዕጓለ እመሕያው፤ ወዓዲ ይቤ ዝንቱ ውእቱ ቃለ እግዚአብሔር ዘኢይትገመር ዘሀሎ እምቅድመ ኲሉ መዋዕል ዘአልቦቱ ሥጋ ነሥአ ሎቱ ሥጋ” (ዳግመኛ እግዚአብሔር በመወለዱ ለሰው ተገለጠ፤ ወደ ሰውም መጣ አለ፤ ዳግመኛም የማይወሰን ከቀን ከዘመን አስቀድሞ የነበረ እግዚአብሔር ቃል ይኽ ነው፤ ሥጋ ያልነበረው ሥጋን ነሣ) (ቅዱስ ሱኑትዩ) ☞ “በፈቃደ አቡሁ ወረደ ኀበ ማርያም ተአንገደ በድንግልናሃ ንጹሕ እግዚአብሔር ተወልደ” (በአባቱ ፈቃድ ወረደ በማርያም ዘንድ እንግዳ ሆነ እግዚአብሔር በንጹሕ ድንግልናዋ ተወለደ) እንዲል ቅዱስ ዲዮስቆሮስ በቅዳሴው 🙏[ከኹለት አካል አንድ አካል፤ ከኹለት ባሕርይ አንድ ባሕርይ የኾንኽ አምላካችን ሥግው ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ፈጽመን እናመሰግንኻለን]🙏 [ከመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ] ✞የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያንን አስተምሮና ስርዓት የጠበቁ የተለያዩ መርሃ ግብሮች በየቀኑ ወደናንተ ይቀርባሉ፡፡ ለወዳጅዎ #Share በመድረግ የበረከት ተካፋይ እናድርጋቸው✞ ╭══•|❀:๑✞♡✞๑:❀|•══╮ @EOTC2921 @Orthodox2921 ╰══•|❀:๑✞♡✞๑:❀|•══╯

🌾✞ #የኢየሱስ_ክርስቶስ_እግዚአብሔርነት ✞🌾 ❖ የኢየሱስ ክርስቶስን እግዚአብሔርነት ትንቢትን በተናገሩ በቀደምት ነቢያት ፈንታ፤ በዓለሙ ኹሉ እግዚአብሔርነቱን በግልጥ ያስተማሩ ሐዋርያት ተተኩ፤ ከዚያም ምስጢሩን የሚያመሰጥሩ ሊቃውንት በሐዋርያት እግር ተተክተው የአምላካቸው የክርስቶስን እግዚአብሔርነት አምልተው አስፍተው አስተምረዋል፤ ይኽም ትምህርታቸው ጥልቅና ሰፊ ሲኾን በጥቂቱ ትምህርታቸው እነሆ፡- ☞ “ወአግሐዶ ዮሐንስ ወአጥመቆ በውስተ ዮርዳኖስ፤ ተመከረ በገዳም ወተዐውቀ ከመ እግዚአብሔር ውእቱ” (ዮሐንስ ገለጠው፤ በዮርዳኖስም አጠመቀው፤ በገዳም ተፈተነ፤ ርሱም እግዚአብሔር እንደኾነ ታወቀ) (ቅዱስ ሄሬኔዎስ) ☞ “ተሰቅለ በሕማመ ሥጋ ወሐይወ በኀይለ እግዚአብሔር ዘውእቱ መለኮቱ፤ ወወረደ ውስተ መትሕተ ዕመቀ ምድር ወጼወወ ነፍሳተ ሰብእ” (ለሥጋ በሚስማማ ሕማም ተሰቀለ፤ በእግዚአብሔርነቱ ኀይል ተነሣ፤ ይኸውም መለኮቱ ነው፤ ወደ ሲኦል ወርዶ ነፍሳትን ማረከ) (ቅዱስ ሄሬኔዎስ) ☞ “እግዚአብሔር ቃል ስለ እኛ እንደታመመ እግዚአብሔር ለእኛ ቤዛ እንደሞተ ብትሰማ፤ እኛ መለኮትን ከትስብእት ጋራ አንድ አካል አንድ ባሕርይ አድርገን ለእግዚአብሔርነቱ በሚገባ በዚኽ ባንድ ስም እንደምንጠራው ዕወቅ… የእኛ አምላክ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ በአብ ፈቃድ በግብረ መንፈስ ቅዱስም ከዳዊት ዘር ከእመቤታችን ማርያም ተፀነሰ” (ቅዱስ አግናጥዮስ) ☞ “ክርስቲያኖች በምድር ከሚኖሩ ሰዎች ኹሉ በልጠው እውነትን አገኙ፤ በመንፈስ ቅዱስም ተቀዳሚ ተከታይ የሌለው አንድያ ወልድን፤ የኹሉ ነገር ፈጣሪንና ሠሪን እግዚአብሔርን አወቁ” (አርስቲደስ) ☞ “እናንተ ግሪኮች እግዚአብሔር ከሰው ልጅ እንደተወለደ ስናስገነዝብ ስንፍናና እየተጫወትን ወይም ተርታ ነገር እየተናገርን አይደለም” (ቴሽያን ሶርያዊ) ☞ “የእግዚአብሔር ቃል ክርስቶስ ከአብ ጋር በህልውና ያለ፤ እኛንም ያስገኘ፤ አኹንም ይኸው ቃል ሰው ኾኖ ተገለጠ፤ ርሱ ብቻ እግዚአብሔርም ሰውም የኾነ እና የበጎ ነገራት ኹሉ ምንጭ ነው… በተዋሐደው ሥጋ ሲያዩት የተናቀ ቢኾንም እንደ እውነቱ ግን እጅግ ያማረ የተወደደ የተፈቀረ ነው፤ ኢየሱስ መድኀኒታችንና ኀጢአታችንን ይቅር ያለ ፈውሳችን የኾነ መለኮታዊ ቃል ሙሉ በሙሉ በርግጠኛነት በእውነት እግዚአብሔር ነው” (ቀሌምንጦስ ዘእስክንድርያ) ☞ “እግዚአብሔር ክርስቶስ የኹሉም ነገር አምላክ በመኾኑ ከሰው ዘር በመላ ኀጢአትን ጠራርጎ ዐጥቦ አሮጌውን ሰው ዐዲስ አድርጎታል” (ቅዱስ ሂፖሊተስ (አቡሊዲስ)) ☞ “ክርስቶስ ዕሩቅ ብእሲ ቢኾንማ “እውነተኛ አምላክ ብቻ የኾንኽ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይኽች የዘላለም ሕይወት ናት” በማለት ያስቀመጠውን ሕግ ለምን እንድናምን አደረገ? (ዮሐ ፲፯፥፫)፤ እግዚአብሔር መኾኑን እንድረዳው ባይፈልግ ኖሮማ ለምን “የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ” ብሎ ለምን አከለበት? ይኽም እንደ እግዚአብሔርነቱ እንድንቀበለው ነው፤ ይኽ ባይኾን ኖሮማ “የላክኸውን ሰው ኢየሱስ ክርስቶስን” ይለን ነበር፤ በርግጥ ግን ርሱ ይኽነን አላከለበትም፤ ወይም ክርስቶስ ራሱን ፍጹም ሰው ብቻ እንደኾነ አድርጎ አላቀረበልንም፤ ኾኖም ግን ርሱ ራሱ እግዚአብሔር እንደኾነ እንድንረዳው ፈልጎ ራሱን ከእግዚአብሔር አብ ጋር አስተካከለ እንጂ፤ በዚኽ መልኩ እንድረዳው ባይሻ ኖሮማ ራሱን በመነጠል ያቀርብ ነበር” (ኖቬሺያን) ☞ “ክርስቶስ እግዚአብሔር እንደኾነ የካደ ሰው የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ (መቅደስ) ሊኾን አይችልም” (ቆጵርያኖስ (ሲፕርያን ዘካርቴጅ (ዘቅርጣግና)) ☞ “የሕያው አካላዊ ቃል አባት አንድ እግዚአብሔር አለ፤ ርሱም ሕያው ጥበብ፣ ኀይልና ዘላለማዊ አካል ያለው፤ ፍጹም የኾነው ወልድን አካል ዘእምአካል ባሕርይ ዘእምባሕርይ የወለደ የአንድያ ልጁ የባሕርይ አባት ነው፤ አንድ ጌታ ከብቸኛው ከአብ የተገኘ ዋሕድ፤ ከእግዚአብሔር የተገኘ እግዚአብሔር፤ አባቱን በመልክ የሚመስለው በባሕርይ የሚተካከለው፤ ከሃሊው ቃል፤ የኹሉም ነገር መሠረትና ማጠቃለያ የኾነ ጥበብ ባለቤትና የፍጥረታት ኹሉ አስገኚያቸው፤ የእውነተኛው አብ እውነተኛ ልጅ ወልድ፤ ከማይታይ የተገኘ ኅቡእ፤ ኅልፈት ውላጤ ከሌለበት የተገኘ ኅልፈት ውላጤ የሌለበት፤ ከማይሞት የተገኘ ሕያው፤ ከዘላለማዊ የተገኘ ዘላለማዊ … እናም ወልድ ፈጽሞ አብን ወደ መኾን አይለወጥም፤ መንፈስ ቅዱስም ወልድን ወደ መኾን አይለወጥም፤ ግን ያለምንም ልዩነት እና ያለምንም ለውጥ በእግዚአብሔርነት የተካከሉት ሥላሴ ለዘለዓለም ይኖራሉ” (ቅዱስ ጎርጎርዮስ ገባሬ መንክራት) ☞ “እንግዲኽ የኾነ አንድ ቁጡ፤ የተናደደ እና የተደሰተ ሰው የእናንተ አምላክ ክርስቶስ እግዚአብሔር ነው? ብሎ ሊል ይችላል፤ በርግጥም ርሱ እግዚአብሔርና የተሰወሩት ኹሉ ኀይላት አምላካቸው ነው ብለን እንመልስለታለን” (አርኖቢዩስ) ☞ “ዝ ውእቱ ዘአጥፍኦ ለሞት ወሠዐሮ ለዲያብሎስ ዘምስሌሁ እዘዘ ሞት በትንሣኤሁ ባሕቲቱ እግዚአብሔር ዘኮነ ሰብአ ወአስተርአያ በአርአያ ብእሲ” (ሞትን ያጠፋው ከሙታን ተለይቶ በመነሣቱ የሞት ሥልጣን የነበረው ዲያብሎስን የሻረው ርሱ ነው፤ ሰው የኾነ በሰው ባሕርይ የተገለጠ እግዚአብሔር ነው) (ቅዱስ አትናቴዎስ) ☞ “ዝንቱ ዘበአማን እግዚአብሔር ወወልደ እግዚአብሔር ወውእቱ እግዚእ ቡሩክ ላዕለ ኲሉ…” (ርሱ በእውነት እግዚአብሔር ነው፤ የእግዚአብሔር ልጅ ነው፤ ከኹሉም በላይ የሚኾን የባሕርይ ገዢ ነው…) (ቅዱስ አትናቴዎስ) ☞ “ወውእቱ እግዚአብሔር ዘቦቱ ልደት በሥጋ በሕማማት ዲበ ዕፀ መስቀል ወመዊት ወትንሣኤ” (በሥጋ መወለድ በመስቀል መከራ መቀበል መሞት፣ መነሣት ገንዘቡ የኾነ ርሱ እግዚአብሔር ቃል ነው) (ቅዱስ ፊልክስ) ☞ “ተፈሥሒ ኦ ማርያም ምድር ቅድስት ዘበጽሐኪ እግዚአብሔር እንዘ ይጼዐን ዲበ ደመና ብሩህ ወቦአ ውስቴትኪ፤ ተፈሥሒ ኦ ማርያም ዘአስተርአየ እምኔኪ እግዚአብሔር ዘየዐርፍ በቅዱሳኒሁ፤ ተፈሥሒ ኦ ማርያም ዘሠምረ እግዚአብሔር ዘሀሎ እምቅድመ ዓለም ይትወለድ እምኔኪ ቃል ዘንሰግድ ሎቱ ምስለ አብ ወመንፈስ ቅዱስ” (እግዚአብሔር በብሩህ ደመና ኾኖ ወደ አንቺ የመጣ፤ በአንቺም ያደረ ምድር ቅድስት ማርያም ሆይ ደስ ይበልሽ፤ በቅዱሳን ዐድሮ የሚኖር እግዚአብሔር ቃል ከአንቺ ተወልዶ የተገለጠ ማርያም ሆይ ደስ ይበልሽ፤ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር የምንሰግድለት ቃል ከአንቺ ይወለድ ዘንድ ዓለም ሳይፈጠር የነበረ እግዚአብሔር አንቺን የወደደ ማርያም ሆይ ደስ ይበልሽ) (ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ)

#ኖላዊ_ትጉኅ Nolawi Teguh (Ethiopian Orhodox Tewahedo Mezmur) https://youtube.com/watch?v=h9_Ep2Nj01Y&feature=share

#ኖላዊ_ትጉኅ Nolawi Teguh (Ethiopian Orhodox Tewahedo Mezmur) https://youtube.com/watch?v=h9_Ep2Nj01Y&feature=share

🌾✞ #የምእመናን_አባት ✞🌾 የምእመናን አባት አገልጋይ የአምላክ ባለሟል መርቆሬዎስ/፪/ ተቀበለ ዛሬ/፬/ አክሊለ ሰማዕታት/፪/ ኧኸ

🌾✞ #ቅዱስ_መርቆሬዎስ ✞🌾 ቅዱስ መርቆሬዎስ ሰማእታዊው የእኛ አባት (2) ተዋህዶ ምሰሶ ሆንካት(2) ከእናትህ ማህፀን ቸሩ አምላክ ሲያስብህ(2) ለኢትዮጵያ ብርሃን አረግህ(2)

🌾✞ #መርቆሬዎስ ✞🌾 መርቆሬዎስ ትሩፈ ምግባር/2/ ትሩፈ ምግባር /4/ መርቆሬዎስ ትሩፈ ምግባር

🌾✞ #ሰላም_ለከ ✞🌾 ሰላም ለከ ኦ መርቆሬዎስ ዘሮሜ (፪) ሰማዕት ተጋድሎ (፫) ኮንከ ፈፃሜ (፪) #ትርጉም፦ የሮሜው ቅዱስ መርቆሬዎስ ሆይ ሰላም እልሃለሁ የሰማዕትነት ተጋድሎ ፈፃሚ ሆንክ

🌾✞ #መርቆሬዎስ ✞🌾 መርቆርዮስ /፬/ የችግሬ ደራሽ ና በፈረስ እንባዬን ልታብስ ፈጥነህ ድረስ //፪// ባስልዮስ ጎርጎሪዮስ ሰምሯል ልመናቸው ስዕሉ ዘለለ ታምራት አያችሁ እናንተን የረዳ መጥቶ በፈረስ ዛሬም ለኛ ይድረስ ይምጣ መርቆርዮስ #አዝ---✞✞✞----___---✞✞✞-- ዑልያኖስ ተገድሏል ሐይማኖት ይስፋፋል ብሎ መሰከረ መርቆሬዎስ ሃያል ገፀ ከላባቱ ባህርይ ቀየሩ እርሱን ለማገልገል ከእግሩ ስር አደሩ #አዝ---✞✞✞----___---✞✞✞-- ትካዜ ሀዘኔ ይርቃል ጭንቀቴ መርቆሬዎስ ሲመጣ ሲገባ ከቤቴ በፀሊም ፈረሱ እየገሰገሰ መርቆሬዎስ ወዳጄ ስጠራው ደረሰ #አዝ---✞✞✞----___---✞✞✞-- ስቃዩን ሊያረዝም ዳኪዎስ ወደደ ከጨለማ እስር ቤት ታስሮ ተወሰደ በጋለ ሹል ብረት መርቆሬዎስ ተወጋ ስሙ ተሰየመ ከሰማዕታት ጋ #አዝ---✞✞✞----___---✞✞✞-- አልፈራም መከራ አልፈራም ችግር መፍቅሬ አብ ካለ ያኘሎፓዴር ቂሳርያ እስር ቤት መርቆሬዎስ ታሰረ ወህኒ ቤቱ በራ እግዚአብሔር ከበረ #አዝ---✞✞✞----___---✞✞✞--

🌾✞ #የቅዱስ_መርቆሬዎስ_ሰማዕትነት ✞🌾 ኅዳር 25 ❖ ቅዱስ መርቆሬዎስ መካነ ልደቱ ቀጶዶቅያ ሲኾን ወላጆቹ በተወለደ ጊዜ ስሙን ፒሉፓዴር ብለውታል ትርጓሜውም “የአብ ወዳጅ” ማለት ሲኾን በመንፈሳዊ ትምህርት አጠንክረው አሳድገውታል፤ “ወተውህቦ ኀይል ዐቢይ ለቅዱስ መርቆሬዎስ ወተሰምዐ ዜናሁ በኲሉ ወተለዐለ እምሰብአ ቤተ መንግሥት” ይላል ❖ ታላቅ የድል አድራጊነት ኀይል እንደ ዳዊት፣እንደ ሶምሶን ተሰጥቶት ዜናው በኹሉ ቦታ ሲሰማ ከቤተ መንግሥት ሰዎችን ይልቅ ከፍ ከፍ ብሏል፤ በዚኽ ምክንያት ከ249-251 ዓ.ም. በጊዜው በነበረው ንጉሥ በዳኬዎስ ዘንድ በ17 ዓመቱ ጀምሮ ባለሟልነት አግኝቷል፡፡ ❖ ከዚያም በሮም ላይ የበርበር ሰዎች ተነሥተው የዳኬዎስን መንግሥት ሊወጉት መጡ፤ እጅግ ብዙዎችም ነበሩና ንጉሡ እጅግ ፈራ፤ ቅዱስ መርቆሬዎስ ግን እንደ ሶምሶን ኃይለ እግዚአብሔር ዐድሮበት “እግዚአብሔር ያጠፋቸው ዘንድ አለውና አትፍራ” አለው፡፡ ❖ “ወእምዝ ርእዮ ቅዱስ መርቆሬዎስ ለመልአከ እግዚአብሔር በውስተ ቀትል ወሰይፍ በሊኅ ውስተ እዴሁ” ይላል፤ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል በውጊያው ውስጥ የተሳለ ሰይፍ በእጁ ይዞ ተገልጦለት ሰይፉን በመስጠት “ጠላቶችኽን ድል ባደረግኽ ጊዜ ፈጣሪኽ እግዚአብሔርን ዐስበው” ብሎ ሰጥቶታል፤ አንዱ ራሱ ለውጊያ የያዘው ሰይፍ ኹለተኛም ከመልአኩ የተቀበለው ብሩህ ሰይፍ ነበርና በዚኽ ምክንያት “አበ አስይፍት” (የሰይፎች አባት) ተብሏል፤ ይኽም ሊታወቅ ኹለት ሰይፎች ይዞ ይሣላል፡፡ ❖ ከዚኽ በኋላ በ249 ዓ.ም ንጉሡ ዳኬዎስ ፈጣሪው ክርስቶስን ክዶ ለአርጤምስ ጣዖታት ዕጣን ሊያቀርብና በዓልን ሊያደርግ ወደዶ በዓልን ባደረገ ጊዜ ቅዱስ መርቆሬዎስ ግን ከርሱ ጋር አልወጣም፤ ቅዱስ ሚካኤልም ለቅዱስ መርቆሬዎስ ተገልጾ በአምላኩ በክርስቶስ ስም መከራን በትዕግሥት እንዲቀበል ነግሮታል። ❖ ንጉሡ ዳኬዎስም አስጠርቶት “ድልን ለሰጡን ለአማልክት ዕጣን ለማሳረግ ከእኔ ጋር ያልወጣኽ የእኔንስ ፍቅር ለምን ተውኽ” ብሎ ጠየቀው፤ በዚኽ ጊዜ ቅዱስ መርቆሬዎስ በንጉሡ ፊት ትጥቁንና ልብሱን ወርውሮ “ንጉሥ ሆይ ድልን የተቀዳጀነው በሰው እጅ በተሠሩ በነዚህ ደናቁርት ጣዖታት አይደለም፤ መልአኩን ልኮ ሰይፍን በሰጠኝ በጌታዬ በመድኃኒቴ ኢየሱስ ክርስቶስ ቸርነት እንጂ፤ አኹንም እኔ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስን አልክደውም ለረከሱ ጣዖታትም አልሰግድም” በማለት መለሰለት፡፡ ❖ ንጉሡም እጅግ ተቈጥቶ ርጥብ በኾኑ የሽመል በትሮችና እንዲደበደብና ከላም ቆዳ በተሠራ ጅራፍ እንዲገረፍ አዘዘ፤ ሥጋውንም በቢላዋ እየቆራረጡ ከበታቹ እሳት ሲያነዱ ከሰውነቱ ከወጣው ከብዙ ደም የተነሣ እሳቱ ጠፍቷል፡፡ ❖ ከዚያም ወደ እስር ቤት በጣሉት ጊዜ ጌታችን በዚያች ሌሊት ተገልጾለት ከሕመሙ ከስቃዩ ኹሉ ፈውሶታል። ከሓዲው ዳኬዎስም ቅዱስ መርቆሬዎስ ካለው ተወዳጅነት የተነሣ ሰዎች እንዳይነሡበት በመፍራት የቀጶዶቅያና የእስያ ክፍል ወደ ኾነች ወደ ቂሳርያ በብረት ማሠሪያ ታሥሮ እንዲላክና አንገቱ እንዲቆረጥ አዘዘ። ❖ ከዚያም ቅዱስ መርቆሬዎስ እጆቹን ዘርግቶ አምላኩ ክርስቶስ በገነት እንዲቀበለው ለመነ፤ ያን ጊዜ ጌታችን መላእክቱን አስከትሎ በታላቅ ግርማ ተገለጸለት፤ "የተመረጥክ ልጄ መርቆሬዎስ ሆይ ከቅዱሳን ጋር ወደ ዘላለማዊ ማረፊያኽ ና፤ ጸሎትኽ መልካም መዐዛ እንዳለው ዕጣን ወደ እኔ ዐረገ፤ የአንተ ስም በሚጠራበት ቤተ ክርስቲያን ኹሉ ተአምር ይደረጋል፤ በአንተ ምልጃ የሚማፀኑኝን አድናቸዋለው፤ የገድልኽን መጽሐፍ የሚጽፉ የሚያነቡ ስማቸውን በሕይወት መጽሐፍ እጽፈዋለሁ" ብሎ ቃል ኪዳን ገባለትና መርቆሬዎስን ባረከው። ❖ ቅዱስ መርቆሬዎስም በእጅጉ ተደስቶ በንጉሡ ትዕዛዝ አንገቱን ሊቆርጡ የተዘጋጁትን ፈጥነው እንዲፈጽሙ ለመናቸው፤ ከዚያም በጉልበቱ ተንበርክኮ "ጌታዬ ሆይ ኃጢአታቸውን አትቁጠርባቸው" ብሎ ልመናን ካቀረበ በኋላ ኅዳር 25 በ250 ዓ.ም. ከሓድያኑ ራሱን በተሳለ ሰይፍ ቈርጠውት በክርስቶስ ስም የሰማዕትነትን አክሊል በ25 ዓመቱ ተቀዳጀ። ❖ ያን ጊዜ ከበድኑ መዓዛው እንደ ሽቱና ዕጣን እጅግ ደስ የሚል ሽታ ይወጣ ነበር፤ ከበድኑና ከተቀበረበት ቦታ ብዙ ተአምራት ተደረጉ፤ በርካቶች ሕሙማን ተፈወሱ፤ የሰማዕታት ዘመን ካለፈም በኋላ በመላው ዓለም አብያተ ክርስቲያናት ታንጸውለታልና፡፡ እመቤታችን በግብጽ በደብረ ምጥማቅ ጉልላት ላይ ከግንቦት 21-25 ድረስ በተገለጠች ጊዜ ዐብረዋት ከሚመጡ ሰማዕታት ውስጥ ቅዱስ መርቆሬዎስ ነበረበት። ❖ ቅዱስ መርቆሬዎስ በፈጣን ተራዳኢነቱ የሚታወቅ ሲኾን ከሓዲው ዑልያኖስ ብዙ ክርስቲያኖችን በሚገድልበት ጊዜ ታላላቆች ሊቃውንት የነበሩትን ቅዱስ ባስልዮስና ቅዱስ ጎርጎርዮስ በአምላክ እናት ሥዕልና አጠገቧ በተሣለው በቅዱስ መርቆሬዎስ ሥዕል ፊት ቆመው ቢማፀኑ፤ እመቤታችን ሰማዕቱን አዝዛው ፈጥኖ ደርሶ ክርስቶስን የካደው ክርስቲያኖችን የሚፈጀው ዑልያኖስን ቀሥፎታል፤ ይኽም በመላው ዓለም በሚሣለው በሥዕሉ ላይ ይታያል ። ❖ ኢትዮጵያዊዉ ሊቅ አርከ ሥሉስም የቅዱስ መርቆሬዎስን ተጋድሎ በማዘከር፡- “ሰላም ለከ መርቆሬዎስ ዘሮም መስተጽዕነ ፈረስ ጸሊም አመ አንደዱ ታሕቴከ ውሉደ መርገም እምቅሡፍ አባልከ እንተ ውኅዘ ደም አርአያ ዝናም ብዙኅ አጥፍኦ ለፍሕም” (በጥቊር ፈረስ ላይ የተቀመጥኽ የሮም ሰው ለኾንኸው ለመርቆሬዎስ ሰላምታ ይገባኻል፤ የመርገም ልጆች ከሥርኽ እሳትን ባነደዱ ጊዜ ከተገረፈው ሰውነትኽ በብዙ ዝናብ አምሳል የፈሰሰው ደም ፍሙን አጠፋው) እያለ መስክሮለታል፡፡ ❖ ሊቁ አባ ጊዮርጊስም በተአምኆ ቅዱሳን መጽሐፉ ላይ፦ “ሰላም ለመርቆሬዎስ ሰማዕት ንጹሕ ድንግል ፈጻሜ ቃለ ወንጌል”፡፡ (የወንጌል ቃል የፈጸመ ለኾነ ለንጹሕ ድንግል ሰማዕት መርቆሬዎስ ሰላምታ ይገባል) በማለት አወድሶታል፨ [ተወዳጆች ሆይ ከበረከቱ ትሳተፉ ዘንድ በበዓሉ ዕለት የተራቡትን በመመገብ፤ የተጠሙትን በማጠጣት፤ የታመሙትን በመጠየቅ፤ ያዘኑትን በማጽናናት፤ በዓሉን በማክበር ታስቡት ዘንድ እመክራችኋለሁ የቅዱስ መርቆሬዎስ በረከት ይደርብን🙏 ✍በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ ✞ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያንን አስተምሮና ስርዓት የጠበቁ የተለያዩ መርሃ ግብሮች በየቀኑ ወደ እርስዎ ይቀርባሉ፡፡ ለወዳጅዎ #Share በመድረግ የበረከት ተካፋይ ያድርጓቸው ✞ ╭══•|❀:๑✞♡✞๑:❀|•══╮ https://t.me/EOTC2921 ╰══•|❀:๑✞♡✞๑:❀|•══╯

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን ETHIOPIAN ORTHODOX TEWAHEDO CHURCH የኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያንን ዶግማና ቀኖና የጠበቁ የነፍስ ስንቅ የምናገኝበት፦ ✍️"ማንም አንዳች የሚያውቅ ቢመስለው ሊያውቅ እንደሚገባው ገና አላወቀም" ፩ኛ ቆሮ. ፰፥፪ #ለተጨማሪ፦👇✞👇 http://facebook.com/EOTC2921 https://youtube.com/channel/UCk5CYu83D8pKtIrhI4nI0Qw https://t.me/EOTC2921

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን🙏 - Statistics & analytics of Telegram channel @eotc2921