en
Feedback
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን🙏

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን🙏

Open in Telegram

የኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያንን ዶግማና ቀኖና የጠበቁ የነፍስ ስንቅ የምናገኝበት፦ ✍️"ማንም አንዳች የሚያውቅ ቢመስለው ሊያውቅ እንደሚገባው ገና አላወቀም" ፩ኛ ቆሮ. ፰፥፪ #ለተጨማሪ፦👇✞👇 https://www.youtube.com/EOTC2921 https://www.facebook.com/eotc2921 https://www.tiktok.com/@eotc2921 https://www.instagram.com/eotc2921

Show more
4 374
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
🌾✞ #ሐይማኖትኪ_አድኀነተኪ ✞🌾 ✝️"ከፈሪሳውያንም አንድ ከእርሱ ጋር ይበላ ዘንድ ለመነው፤ በፈሪሳዊው ቤትም ገብቶ በማዕድ ተቀመጠ። እነሆም በዚያች ከተማ ኃጢአተኛ የነበረች አንዲት ሴት፤ በፈሪሳዊው ቤት በማዕድ እንደ ተቀመጠ ባወቀች ጊዜ፥ ሽቱ የሞላበት የአልባስጥሮስ ቢልቃጥ አመጣች። በስተ ኋላውም በእግሩ አጠገብ ቆማ እያለቀሰች በእንባዋ እግሩን ታርስ ጀመረች፥ በራስ ጠጕርዋም ታብሰው እግሩንም ትስመው ሽቱም ትቀባው ነበረች። ✝️የጠራው ፈሪሳዊም አይቶ፦ ይህስ ነቢይ ቢሆን፥ ይህች የምትዳስሰው ሴት ማን እንደ ሆነች እንዴትስ እንደ ነበረች ባወቀ ነበር፥ ኃጢአተኛ ናትና ብሎ በልቡ አሰበ። ኢየሱስም መልሶ፦ ስምዖን ሆይ፥ የምነግርህ ነገር አለኝ፡ አለው። እርሱም፦ መምህር ሆይ፥ ተናገር፡ አለ። ለአንድ አበዳሪ ሁለት ተበዳሪዎች ነበሩት በአንዱ አምስት መቶ ዲናር ነበረበት በሁለተኛውም አምሳ። የሚከፍሉትም ቢያጡ ለሁለቱም ተወላቸው። ✝️እንግዲህ ከእነርሱ አብልጦ የሚወደው ማንኛው ነው ስምዖንም መልሶ፦ ብዙ የተወለቱ ይመስለኛል፡ አለ። እርሱም፦ በእውነት ፈረድህ፡ አለው። ወደ ሴቲቱም ዘወር ብሎ ስምዖንን እንዲህ አለው፦ ይህችን ሴት ታያለህን? እኔ ወደ ቤትህ ገባሁ፥ ውኃ ስንኳ ለእግሬ አላቀረብህልኝም፤ እርስዋ ግን በእንባዋ እግሬን አራሰች በጠጕርዋም አበሰች። አንተ አልሳምኸኝም፤ እርስዋ ግን ከገባሁ ጀምራ እግሬን ከመሳም አላቋረጠችም። አንተ ራሴን ዘይት አልቀባኸኝም፤ እርስዋ ግን እግሬን ሽቱ ቀባች። ✝️ስለዚህ እልሃለሁ፥ እጅግ ወዳለችና ብዙ ያለው ኃጢአትዋ ተሰርዮላታል፤ ጥቂት ግን የሚሰረይለት ጥቂት ይወዳል። እርስዋንም፦ ኃጢአትሽ ተሰርዮልሻል፡ አላት። ከእርሱም ጋር በማዕድ ተቀምጠው የነበሩት በልባቸው፦ ኃጢአትን እንኳ የሚያስተሰርይ ይህ ማን ነው? ይሉ ጀመር። ሴቲቱንም፦ እምነትሽ አድኖሻል፤ በሰላም ሂጂ፡ አላት።" ✍️ሉቃስ ፯፥፴፮-፶ 🙏አቤት አምላክ ሆይ! የፈሪሳዊቷን ዓይነት ንፁህ ዕምነት አድለን። አሜን🙏

🌾✞ #መልክዐ_ኪዳነ_ምሕረት ✞🌾 🌾ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘአስተማልዎ በኮከብ፤ ሶበ ብርሃኖ ተከድኑ ጽልሙታነ ራእይ ሕዝብ፤ ኪዳነ አምላክ ማርያም ወተስፋ መድኀኒት ዘዐርብ፤ ተናዘዘ ብኪ አኮኑ ሕሊ
🌾✞ #መልክዐ_ኪዳነ_ምሕረት ✞🌾 🌾ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘአስተማልዎ በኮከብ፤ ሶበ ብርሃኖ ተከድኑ ጽልሙታነ ራእይ ሕዝብ፤ ኪዳነ አምላክ ማርያም ወተስፋ መድኀኒት ዘዐርብ፤ ተናዘዘ ብኪ አኮኑ ሕሊና ቀዳማይ አብ፤ አመ እምገነቱ ተሰደ በኃዘን ዕፁብ፡፡ 🌾ሰላም ለአእዛንኪ እለ ተበሥራ ኪዳነ፤ እም አፈ ፈጣሪ ወልድኪ ዘባሕርየኪ ተከድነ፤ አምሕለኪ ማርያም ከመ ኢታርእይኒ ደይነ ፤ እንበለ ምግባር ባሕቱ እመ ኢይጸድቅ አነ ፤ ቦኑ ለከንቱ ኪዳንኪ ኮነ፡፡ 🌾ሰላም ለእራኅኪ ተመጣዌ ኅብስት ወማይ፤ ሶበ ያመጽኡ ለኪ መላእክተ ሰማይ ፤ እንዘ ሀሎኪ ማርያም በመቅደሰ ኦሪት ዐባይ፤ ይትወከፍ ሊተ ኪዳንኪ ከመ መሥዋዕተ ሠርክ ኅሩይ፤ ለእመ ኅፍነ ማይ አስተይኩ ለጽሙዕ ነዳይ። አንቲ ውእቱ ተስፋሁ ለአዳም ፤ አመ ይሰደድ እምገነት፡፡🙏

✞✞✞ #ጾመ_ነቢያት_የገና_ጾም ✞✞✞ 🌾✞ ኅዳር 15 ይጀምራል ✞🌾 ✔ጾመ ነቢያት በየዓመቱ ከኅዳር ፲፭ ቀን ጀምሮ እስከ በዓለ ልደት ዋዜማ ድረስ የሚጾም፤ ከሰባቱ አጽዋማት መካከል አንደኛው ጾም ነው፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ዓለምን ለማዳን ሲል የሰውን ሥጋ ስለ መልበሱ፤ ወደ ግብጽ ስለ መሰደዱ፤ በባሕረ ዮርዳኖስ ስለ መጠመቁ፤ በትምህርቱ ብርሃንነት ጨለማውን ዓለም ስለ ማብራቱ፤ ለሰው ልጆች ድኅነት ልዩ ልዩ መከራን ስለ መቀበሉ፤ ስለ መሰቀሉ፣ ስለ ሞቱ፣ ትንሣኤው፣ ዕርገቱና ዳግም ምጽአቱ በየዘመናቱ የተነሡ ቅዱሳን ነቢያት በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝተው ትንቢት ተናግረዋል፤ ትንቢቱ ደርሶ፣ ተፈጽሞ ለመመልከትም ‹‹አንሥእ ኃይለከ ፈኑ እዴከ፤ ኃይልህን አንሣ፤ እጅህን ላክ›› እያሉ በጾም በጸሎት ተወስነው አምላክ ሰው የሚኾንበትን ጊዜ በቀናት፣ በሳምንታት፣ በወራትና በዓመታት እያሰሉ ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡ ✔ይህ ጾም የእግዚአብሔርን ሰው መኾን ሲጠባበቁ የኖሩት የነቢያት ትንቢትና ጸሎት በጌታችን መወለድ ፍጻሜ ያገኘበት ወቅት በመኾኑ ‹‹ጾመ ነቢያት (የነቢያት ጾም)›› እየተባለ ይጠራል፡፡ ✔ለአዳም የተነገረው የድኅት ተስፋ ስለ ተፈጸመበትም ‹‹ጾመ አዳም (የአዳም ጾም)›› ይባላል፡፡ ስለ እግዚአብሔር ሰው መኾን በስፋት ትምህርተ ወንጌል የሚሰጥበት ወቅት በመኾኑም ‹‹ጾመ ስብከት (የስብከት ጾም)››፤ የጾሙ መጨረሻ (መፍቻ) በዓለ ልደት በመኾኑ ደግሞ ‹‹ጾመ ልደት (የልደት ጾም)›› በመባል ይታወቃል፡፡ እንደዚሁም ‹‹ጾመ ሐዋርያት›› ይባላል፡፡ ✔ቅዱሳን ሐዋርያት ‹‹በዓለ ትንሣኤን ዐቢይ ጾምን ጾመን እናከብረዋለን፤ በዓለ ልደትንስ ምን አድርገን እናከብረዋለን?›› በማለት ነቢያት የጾሙትን ከልደተ ክርሰቶስ በፊት ያለውን ጾም ጾመዋልና፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ይህ ጾም ‹‹ጾመ ፊልጶስ (የፊልጶስ ጾም)›› ተብሎ ይጠራል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ፊልጶስ በአፍራቅያና አውራጃዋ ዅሉ እየተዘዋወረ በጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ወንጌልን በማስተማር፣ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን በማድረግ ብዙዎችን ወደ አሚነ እግዚአብሔር ሲመልስ ቆይቶ ትምህርቱን በማይቀበሉ የአፍራቅያ ሰዎች አማካይነት በሰማዕትነት ዐርፏል፡፡ ✔ደቀ መዛሙርቱ ሥጋውን ሊቀብሩ ሲሉም ስለ ተሰወረባቸው የሐዋርያውን ሥጋ ይመልስላቸው ዘንድ ሱባዔ ይዘው፣ በጾም በጸሎት ተወስነው በለመኑት ጊዜ እግዚአብሔር ልመናቸውን ተቀብሎ በ፫ኛው ቀን መልሶላቸው ሥጋውን (አስከሬኑን) በክብር አሳርፈውታል፡፡ ደቀ መዛሙርቱ የሐዋርያውን ሥጋ ካገኙ በኋላ እስከ ጌታችን ልደት ድረስ ጾመዋል፡፡ ስለዚህም ጾመ ነቢያት ‹‹ጾመ ፊልጶስ›› እየተባለ ይጠራል፡፡ ከዚሁ ዅሉ ጋርም ወልደ አምላክ ክርስቶስን በግብረ መንፈስ ቅዱስ እንደምትፀንሰው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ካበሠራት በኋላ እመቤታችን ‹‹ሰማይና ምድር የማይወስኑትን አምላክ ፀንሼ ምን ሠርቼ እወልደዋለሁ?›› በማለት ጌታችንን ከመውለዷ አስቀድማ ጾማዋለችና ይህ ጾም ‹‹ጾመ ማርያም›› በመባልም ይታወቃል፡፡ ✔በአጠቃላይ በዚህ በገና ጾም ነቢያትም ሐዋርያትም ጾመው በረከት አግኝተውበታል፡፡ እኛ ምእመናንም እንደ እነርሱ በረከትን እናገኝ ዘንድ ይህንን ጾም መጾም እንደሚገባን የቤተ ክርስቲያን አባቶች ሥርዐት ሠርተውልናል፡፡ ✔በዚህም መሠረት የነቢያት፣ የሐዋርያት፣ የጻድቃንና የሰማዕታት አምላክ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ከቅዱሳን ነቢያትና ሐዋርያት በረከት እንዲያሳትፈን፤ መንግሥቱንም እንዲያወርሰን ዅላችንም በዚህ በጾመ ነቢያት ወቅት በጾም በጸሎት ተወስነን እግዚአብሔርን ልንማጸነው ይገባል፡፡ #ምንጭ፦ ፍትሐ ነገሥት ንባቡና ትርጓሜው፣ አንቀጽ ፲፭፤ ጾምና ምጽዋት፣ ዲያቆን ቃኘው ወልዴ፤ ገጽ ፵፯ -፶፡፡ 🙏ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር🙏 ✞ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያንን አስተምሮና ስርዓት የጠበቁ የተለያዩ መርሃ ግብሮች በየቀኑ ወደ እርስዎ ይቀርባሉ፡፡ ለወዳጅዎ #Share በመድረግ የበረከት ተካፋይ ያድርጓቸው ✞ ╭══•|❀:๑✞♡✞๑:❀|•══╮ https://t.me/EOTC2921 ╰══•|❀:๑✞♡✞๑:❀|•══╯

➋ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በባህር ሲጓዙ የተጨነቁትን የተራዳበት ዕለት ነው። በአንድ ዘመን ብዙ ሰዎች ከግብፅ አውራጃ መጥተው ወደ ባሕር ማዶ ሄዱ፡፡ ከባሕሩም በደረሱ ጊዜ በመርከብ ላይ ተሳፍረው ከየብሱ ጥቂት በራቁና ወደ ባሕሩ መካከል በደረሱ ጊዜ ጽኑ ነፋስ ተነሳባቸው ለመስጠም እስኪ ደርሱ ድረስ፡፡ የማዕበሉ ሞገድ እየጨመረ እየጸና ከፍ አለ፡፡ ታላቅም ማዕበል መጥቶ ሊገለብጣቸው ደረሰ፡፡ ፍጹም ጥፋትና ክፉ ሞት እንደ መጣባቸው ባዩ ጊዜ ጽኑ ሐዘን ያዛቸው፡፡ የሚያድናቸው የሚያጽናናቸው አጥተው ተስፋ ቆረጡ፡፡ ያን ጊዜ እንዲህ ብለው ጮኹ፡፡ ‹‹የመላእክት አለቃቸው ግሩም ገናና የምትሆን ሚካኤል ሆይ የተአምራትና የይቅርታ መልአክ ነህና፡፡ ልዑል ቸርነቱን የሚገልጥብህ መልአክ ሆይ! እግዚአብሔር ፍቅሩን የሚያስታውቅብህ መልአክ ሆይ ወደኛ ተመልከት እርዳን፡፡ የተጨነቅን እኛን አድነን፡፡ ከመጣብን ሞትና ጥፋት እንድን ዘንድ ስለኛ ወደ ፈጣሪህ ወደ ፈጣሪያችን ወደ እግዚአብሔር ለምንልን፡፡ አሁን የሞት መጋረጃ ዓይናችንን ሸፍኖታልና፡፡ ፍጹም የጥፋት ጥላንም አይተናታልና›› ብለው በፍጹም ልቦናቸው ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፡፡ ✔በመርከብ ውስጥ ያሉት ሁሉ ጽኑ ለቅሶ እያለቀሱ መራራ እንባ እያፈሰሱ ጮኹ፡፡ ከባሕር ጽኑ ማዕበል ከሞት ያድናቸው ዘንድ ያን ጊዜ በዚያች ሰዓት እግዚአብሔር የልቦናቸውን ሐዘንና ልመናቸውን ሰማቸው፡፡ ያን ጊዜም ይረዳቸው ዘንድ ቸር መልአኩን ሚካኤልን ላከላቸው የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ከሰማይ ወረደ መርከቡን በእጁ ይዞ ሳበው፡፡ ✔በመርከቡ ውስጥ ያሉትንም ወደ የብስ አወጣቸው፡፡ በደኅናቸው ተሻገሩ፤ ክፉ ነገር ጥቂትስ እንኳ ፈጽሞ አላገኛቸውም፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም ገናና የሆነ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ልመናውና አማላጅነቱ ፈጽሞ ይጠብቀን፡፡ ከጽኑ ጠላት እጅ በክንፎቹ ጋርዶ ይሰውረን፡፡ ➌ በዓለ ሲመቱ ለቅዱስ ሚካኤል በዚህ እለት መላእኩ ቅዱስ ሚካኤል የመላእክት አለቃ ሆኖ የተሾመበት እለት ነው፡፡ ✔መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል ኢያሱ ወልደ ነዌ ሕዝቡን እየመራ በኢያሪኮ አጠገብ ሳለ ዐይኑን አንሥቶ ቢመለከት እነሆም የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ የያዘ ሰው በፊቱ ቆሞ አየ። ወደ እርሱም ቀርቦ «ከእኛ ወገን ወይስ ከጠላቶቻችን ወገን ነህን?» አለው። እርሱም «እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ነኝ አሁንም ወደ አንተ መጥቻለሁ» ብሎታል። ኢያ ፭፥፲፫-፲፭። ይኽንንም ሐዋርያው ቅዱስ ይሁዳ «የመላእክት አለቃ ሚካኤል» በማለት መስክሮለታል ይሁዳ ፩፥፱። ✔ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ በደሴተ ፍጥሞ በግዞት ሳለ በተመለከተው ራእይ ሃላፊያትና መጻእያት ተገልጠውለት ስለነበረ «በሰማይም ሰልፍ (ጦርነት) ሆነ፤» ካለ በኋላ «ሚካኤልና መላእክቱም ዘንዶውን ተዋጉት ዘንዶውም ከነሠራዊቱ ተዋጋቸው። አልቻላቸውምም ከዚያም በኋላ በሰማይ ቦታ አልተገኘላቸውም። ዓለሙን ሁሉ የሚያስተው ዲያቢሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ዘንዶ እርሱም የቀደመው እባብ ተጣለ ወደ ምድርም ተጣለ መላእክቱም (የዘንዶው ሠራዊት) ከእርሱ ጋር ተጣሉ፤» ብሏል። ራእ ፲፪፥፯-፱።ዳን ፲ ፡፲፫ " ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ" የመላእክት አለቃ መሆኑን መስክሯል፡፡ በሌላ በኩል ቅዱስ ዳንኤል ፲፪፥፩ እንዲህ ይላል፦ «በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው (በአማላጅነት በተራዳኢነት የሚቆመው) ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል ሕዝብም በምድር ከተፈጠረ ጀምሮ እስከዚያ ዘመን ድረስ እንደ እርሱ ያለ ያልሆነ የመከራ ዘመን ይሆናል፤» ብሏል። ዩሐንስ በራእዩ ፩ ፡ ፲፰ ያየው "ታላቅ ስልጣን ያለው ሌላ መላእክ ሲወርድ አየሁ ከክብሩም የተንሳ ምድር በራች" ብሎ የመላእኩን ክብረ ተናግሯል የመላእክት አለቃ መሆኑን መስክሯል፡፡ ➍ እስራኤልን ከግብፅ እየመራ ወደ ሀገራቸው ያስገባበት ዕለት የሚታሰብበት እለት ነው፡፡ ከባርነት ቤት ከግብፅ የወጡትን ሕዝብ እግዚአብሔር ቀኑን በደመና ዓምድ ሌሊቱን ደግሞ በብርሃን ዓምድ መርቷቸዋል እስራኤል ዘሥጋን በመንገዳቸው ሁሉ የጠበቃቸው መና ከሰማይ ያወረደላቸው ተአምራትን ያደረገላቸው ማርና ወተት ወደምታፈስሰው ርስታቸው የመራቸው በደመና መጋረጃ የጋረዳቸውበክንፎቹም የሸፈናቸው መጋቤ ብሉይ የተባለ ቅዱስ ሚካኤል ነው። መላእኩ በዚሁ እለት የሰራውን ድንቅ ስራ እንመሰክራለን፡፡ ✔ኅዳር አሥራ ሁለት ቀን በየዓመቱ በማኅሌት እና በቅዳሴ የምናከብረው በዓለ ሹመቱን በማሰብ ቴዎብስታ ዱራታዎስ ያደረገው ታምረ እና በባህር የተጨነቁትን ያዳነበት በማሰብ ነው። ሌላው እና ዋንኛው የምናከብረው ይህ ለእስራኤል ዘሥጋ የተደረገውን የበለጠው ደግሞ እስራኤል ዘነፍስ ለምንባል ክርስቲያኖች ይደረግልናል። ☞ሰለማይንገር ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን፡፡ የቅዱስ ሚካኤል ምልጃና ጠብቆቱ ፍቅርና ርህራሄው በእኛ በልጆቹ ላይ አድሮ ለዘላለም ይኑር አሜን፡፡ 🙏ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር🙏

🕊✞ #ኅዳር_ሚካኤል ✞🕊 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ኅዳር 12 እንኳን ለታላቁ መልአክ ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል አመታዊ ክብረ በአል በሰላም አደረሰን፦ ✉ለምንድን ነው የቅዱስ ሚካኤል ክብረ በዓል ወር በገባ በ12 የሚከበረው የሚታሰበው? ✉ህዳር 12 የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ምን ምን ያደረገበት እንየሆነ እንመለከታለን። #ሚካኤል ማለት በዕብራይስጥ ቋንቋ ሚ-መኑ' ካ-ከመ' ኤል- አምላክ ማለት ሲሆን በአንድነት ሲነበብ መኑ ከመ አምላክ (እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው) ማለት ነው፡፡ ይህ ታላቅ መልአክ ዮሐንስ ወንጌላዊ በራዕዩ ‹‹በእግዚአብሔር ፊት የሚቆሙትን ሰባቱን መላእክት አየሁ›› ብሎ ከተናገረላቸው መላእክት ውስጥ የሚመደብ ሲሆን የሰባቱም ሊቃነ መላእክት አለቃ እንዲሆን እግዚአብሔር መርጦ ሹሞታል፡፡ ይህ ታላቅ መልአክ ያደረጋቸው የሠራቸው እጅግ ብዙ የሆኑ ተአምራት አሉት፡፡ ✔ስለዚህ ስለ ታላቁ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ክብር፤ ጠባቂነትና አማላጅነት ከአባቶቻቸው የተማሩትን በኑሮአቸው ያዩትን አባቶቻችን ጽፈዋል፡፡ ስለ ቅዱስ ሚካኤል ከጻፉት አባቶች መካከል የተወሰኑትን ለመጥቀስ ያክል፡- + ዮሐንስ አፈወርቅ + ኤዎስጣቴዎስ ዘአንፆኪያ + ቅዱስ መቃርዮስ + ቅዱስ ያሬድ + አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ + የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ አባዲማቴዎስ ናቸው፡፡ ✔እኛም የአባቶቻችንን አንደበት አንደበታችን አድርገን በኅዳር 12 ክቡር ገናና የሆነ ቅዱስ ሚካኤል ካደረጋቸውና ከሠራቸው ብዙ ተአምራት ውስጥ የተወሰኑትን በመልአኩ ተረዳኢነት እንዲህ ብለን እንናገራለን አንጽፋለን፡፡ ❖የቅዱስ ሚካኤል ክብረ በዓል ለምን ወር በ12 ይከበራል? ✔በእስክንድርያ ሀገር ውስጥ ‹‹ሳተርን›› (ዙሐል) የተባለ ቤተ ጣዖት ነበራቸው። ይህን የንግስት ክሌዎፓትራ በእስክንድርያ (በግብፅ ) ‹‹ሳተርን›› (ዙሐል) ለሚባለው ጣዖት ቤተ ጣዖት ያሰራችለት እርሷ እንደሆነቸ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ ፡፡ ✔ይህ ቤተ ጣዖት እስከ እስክንድርያው ፓትርያርክ እለ እስክንድሮስ /312- 326/ ዘመን ድረስ ነበር፡፡ እለ እስክንድሮስ ሊያጠፋው ሲነሣ ሕዝቡ ከልቡ ገና የአምልኮ ጣዖት ስላልጣፋ 18 ፓትርያርኮች ያልነኩትን አንተ ለምን ታፈርስብናለህ ብለው ተቃወሙት፡፡ እለ እስክንድሮስም ሕዝቡን መክሮና አስተምሮ የሳተርን በዓል ይውልበት በነበረው በ12 ነው። እስክንድሮስም ስአስተምሮ የሳተርን አጠፋው። ሕዝብ በ12 በገባ ሳተርን›› (ዙሐል) እናከብር ነበር አንተ እርሱን አጠፋህብን ሰለዚህ የለመድነው እንዳይቀር አንድ ነገር አድርግልን አሉት እስክንድሮስም በ12 የቅዱስ ሚካኤልን በዓል እንዲያከብሩ አውጆ ቤተ ጣዖቱንም በቅዱስ ሚካኤል ስም ሰይሞ ቤተክርስቲያን አደረገው፡፡ ከዚህ በኋላ በቅዱስ ሚካኤልም ስም አብያተ ክርስቲያናት መታነጽ ጀመሩ በዓሉ በዚህ ቀን እንዲከበር ተወስኗል፡፡ ✔ይህ ወደ እኛ የመጣው እስክንድሮስ ካረፈ በኋላ ቅዱስ አትናቴዎስ በተሾመ ጊዜ አባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን (ፍሬምናጦስ) ከኢትዮጵያ ሀገር ተልከው በእስክንድርያ ሀገር ጵጵስና ይዘው ሲመጡ ቅዱስ አትናቴዎስ ወር በገባ 12 የቅዱስ ሚካኤል በዓል እንዲያከብሩ አስተምሯቸው አንድ ሕዝብ በ12 የቅዱስ ሚካኤልን በአል ሲያከብሩ እግዚአብሔር ሲያመሰግኑ ተመልክተው ይህ ወደ ሀገራችን ወደ ኢትዮጵያ ይዘው መተዋል አባቶቻችንም ወር በገባ 12 የቅዱስ ሚካኤል በዓል እንዲ ዘከር እንዲከበር እንዲቀደስ በፍትሐ ነገስ ሥርዓት ሰርተውልናል። ❖ህዳር 12 የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ምን ምን ያደረገበት ነው? ✔ህዳር 12 የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ምን ምን ያደረገበት እንየሆነ እንመለከታለን፡፡ ➊ቅዱስ ዱራታዎስ ቴዋብለት (ቴውብስታ) ቤት የተገለጠበት ቤታቸውን የባረከበት ዕለት ነው። እንዲህም ሆነ የእግዚአብሔር ወዳጅ የሆነ ስሙ ዱራታዎስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፡፡ የሚስቱም ስም ቴዋብለት ነው፡፡ እነርሱም ሁልጊዜ ያለ ማቋረጥ የዚህን የከበረ መልአክ የሚካኤልን የበዓሉን መታሰቢያ ያረጉ ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ በሀገር ውስጥ ችግር በሆነ ጊዜ ገንዘባቸው አለቀ፡፡ በዚህም የተነሳ ለመላእክት አለቃ ለቅዱስ ሚካኤል ለበዓሉ መታሰቢያ የሚያደርጉትን አጡ፡፡ ዱራታዎስም ሽጦ ለበዓሉ መታሰቢያ ያደርገው ዘንድ የእርሱን ልብስና የሚስቱን ልብስ ይዞ ወጥቶ ሄደ፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በታላቅ መኮንን አምሳል ለዱራታዎስ ተገለጠለት፤ ቅዱስ ሚካኤልም ዱራታዎስን ወደ በጎች እንዲሔድና በእርሱ ዋስትና በአንድ ዲናር አንድ በግ እንዲወስድ አዘዘው፤ ሁለተኛም ወደ ዓሣ አጥማጅ ሔዶ አንድ ዓሣ እንዲወስድ አዘዘው፡፡ መልአኩም ወደ ቤት ሳይደርስ የዓሣውን ሆድ እንዳይቀድ አስጠነቀቀው፡፡ ወደ ባለ ስንዴም እንዲሔድና የሚሻውን እንዲሁ በእርሱ ዋስትና እንዲወስድ አዘዘው ዱራታዎስም ቅዱስ ሚካኤል እንዳዘዘው አደረገ፡፡ ✔ወደ ቤቱም በተመለሰ ጊዜ በረከትን ሁሉ ቤቱ ተመልቶ አገኘው፤ እጅግም አደነቀ፤ የዚህንም የከበረ መልአክ የበዓሉን መታሰቢያ እንዳስለመደው አደረገ፡፡ የተራቡ ድሆችን ሁሉንም ጠርቶ መገባቸውና ወደ ቤታቸው አሰናበታቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ለዱራታዎስና ለሚስቱ ቅዱስ ሚካኤል ለሁለተኛ ጊዜ ተገለጠላቸው ዱራታዎስንም የዓሳውን ሆድ እንዲሰነጥቅ አዘዘው፤ በሰነጠቀውም ጊዜ ሦስት መቶ የወርቅ ዲናር በዓሳው ሆድ ተገኘ፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም ዱራታዎስንና ቴዋብስታን እንዲህ አላቸው፡፡ ‹‹ከዚህ ዲናር ወስዳችሁ ለባለ በጉ ለባለ ዓሳውና ለባለ ስንዴው ዕዳችሁን ክፈሉ የቀረውም ለፍላጎታችሁ ይሁናችሁ፤ እግዚአብሔር አስባችኋልና በጎ ሥራችሁን መስዋዕታችሁን ምጽዋዕታችሁን በዚህ ዓለም አሳመረላችሁ፡፡ በኋላኛውም መንግስት ሰማያትን አዘጋጅቶላችኋል፡፡›› ብሎ ባርኳቸው ከእንርሱ ተሰወረ። •••••• #ይቀጥላል•••••

#የቁስቋም_ክብር_በኢትዮጵያ_ቀደምት_ሊቃውንት ኅዳር ፮ https://t.me/EOTC2921 ❖ ከ3 ዓመት የስደት ውጣ ውረድ በኋላ የአምላክ እናት ልጇ አምላካችን ክርስቶስን ይዛ አረጋዊ ዮሴፍና ሰሎሜን አስከትላ ከመዐዲ ወደ ላዕላይ ግብጽ በጀልባ ደግሞ ከካይሮ በስተደቡብ 320 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በላዕላይ ግብጽ በምትገኘው ወደ ደብረ ቊስቋም ገብተው በመንገድ ጒዞ ካገኛቸው ድካም 6 ወር ከ10 ቀናት ዐርፈዋልና ኅዳር 6 በደመቀ መልኩ በዓሏ ይከበራል፡፡ ❖ በደብረ ቁስቋም ሳሉ ጨካኙ ሄሮድስ እንደሞተ የጌታ መልአክ በግብፅ ለዮሴፍ በሕልም ታይቶ "የሕፃኑን ነፍስ የፈለጉት ሞተዋልና ተነሣ፥ ሕፃኑን እናቱንም ይዘኽ ወደ እስራኤል አገር ኺድ" ብሎታል (ማቴ 2፡19-20)። ❖ ይኽቺን ጌታ ከእናቱ ጋር ያረፈባትን የተቀደሰች ቦታን ጌታችን ባርኳት ወደ ናዝሬት ተመልሰዋል። ጌታችን ካረገ ከብዙ ዘመን በኋላ በኅዳር ስድስት ቀን “አስተጋብኦሙ እግዚእነ ለሐዋርያቲሁ ቅዱሳን ውስተ ዝንቱ ደብረ ቊስቋም ወቀደሰ ታቦተ ወቤተ ክርስቲያን ወሠርዐ ቊርባነ ወመጠዎሙ ሥጋሁ ቅዱሰ ወደሞ ክቡረ” ይላል (በዚኽ በደብረ ቊስቋም ቅዱሳን ሐዋርያቱን ሰበሰባቸው ታቦትንና ቤተ ክርስቲያንንም አክብሮ የቊርባን መሥዋዕትንም ሠርቶ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ሰጥቷቸዋል) ይላል፡፡ ❖ በዚኽ ምክንያት ደብረ ቁስቋምን የእስክንድርያ ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት በግብጽ የመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን ይሏታል፤ የግብጽ ኦርቶዶክስ ምእመናን በእጅጉ የሚወዷት የቁስቋም ገዳም ስትኾን በ1993 ዓ.ም. ላይ እመቤታችን በገዳሙ ተገልጣ እንደነበር ይናገራሉ፤ በዚኽችም ገዳም 100 መነኮሳት ይገኙበታል፤ ከቦታዋ ክብር የተነሣ "ዳግሚት ቤተልሔም" ይሏታል፤ በገዳሙም በቅዱሳት መጻሕፍት የተመላ ታላቅ ቤተ መጻሕፍት አለ፨ ❖ በጌታ በተባረከችው ይኽቺ ቦታ ላይ በ3ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ላይ ቅዱስ ጳኩሚስ ገዳምን የገደመ ሲኾን፤ የእስክንድርያ 23ኛ ፓትርያርክ ቴዎፍሎስ በታናሿ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ምትክ ታላቅ ቤተ ክርስቲያን ለመሥራት ባሰበ ጊዜ እመቤታችን ተገልጻለት የልጇ የክርስቶስ ትሕትናው በገዳሙ እንዲታሰብበት ባለበት እንዲኾን ነግራዋለች። ❖ ከኢትዮጵያ መሪዎች ውስጥ ቁስቋምን በእጅጉ ያስቡት የነበሩት ከ1723-1748 ዓ.ም. የነገሡት የዐጼ በካፋ ሚስት እቴጌ ምንትዋብ ሲኾኑ የእመቤታችን የስደቷና ቁስቋም የመቀመጧን ነገር ኹሌ የሚያስቡ ንግሥት ነበሩ፤ እመቤቴ ልጇን ይዛ ከሀገሯ ወጣ ብላ ቁስቋም እንደቆየች እኔም ከከተማው ወጣ ብዬ መቀመጥ እሻለሁ ብለው 5ት ኪሎ ሜትር ከጎንደር ከተማ ርቀው በአንድ ሺሕ የኢትዮጵያ የግንባታ ጠበብት የእመቤታችን የቁስቋም ቤተ ክርስቲያንን ሲያሠሩ 500ው ቆመው ስሕተቶችን በመንገር ያስገነቡ ነበር። ❖ ንግሥት ምንትዋብ የእመቤታችንን ስደት በማሰብ ዕንባቸውን ያፈሱ የነበሩ ንግሥት ሲኾኑ የእመቤታችን ስደቷን አስበው የፈቃድ ጾም የኾነውን ጾመ ጽጌን መጾም የጀመሩ ንግሥት ርሳቸው እንደነበሩ ሊቁ ዶክተር ሥርግው ይገልጻሉ። ❖ በርካቶች የኢትዮጵያ ሊቃውንት እመቤታችን ከልጇ ጋር ወደ ቊስቋም የመግባቷን ነገር የጻፉ ሲኾን ለምሳሌም አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በሰዓታት መጽሐፉ ላይ በስፋት ሲዘረዝረው፡- [“በሊዓ ሕፃናት ሶበ ኀለየ ሄሮድስ አርዌ ሰማይ ምስለ ዮሴፍ አረጋይ ነገደት ቊስቋመ ናዛዚተ ሐዘን በብካይ”] (የሰማዩ አውሬ ሄሮድስ ሕፃናትን መብላት ባሰበ ጊዜ፤ ከሐዘንና ከልቅሶ የምታረጋጋ ማርያም ከአረጋዊዉ ዮሴፍ ጋራ ወደ ቊስቋም ኼደች (ተሰደደች)) ❖ “አሥረጸት ማርያም አክናፈ ረድኤት አምሳለ ዖፍ ለዐሪገ ቊስቋም ህየ ከመ ትትዐቀብ ዘመነ ወአዝማነ ወመንፈቀ ዘመን በከመ ይቤ መጽሐፍ” (ማርያም ወደ ቊስቋም ተራራ ለመውጣት እንደ ዎፍ የረድኤት ክንፎችን አበቀለች በመጽሐፍ እንደተናገረ በዚያ በዘመንና በዘመናት በዘመን እኩሌታም ትጠበቅ ዘንድ) ❖ “ብጽዐን ለኪ ኦ ደብረ ቊስቋም እምኲሎን አድያም እምናዝሬት እስከ ቤተልሔም ዘተጸወነ ላዕሌኪ መድኀኔ ኲሉ ዓለም” (ከናዝሬት እስከ ቤተ ልሔም ካሉ አውራጆች ኹሉ የዓለም ኹሉ መድኀኒት ወደ አንቺ የተጠጋ የቊስቋም ተራራ ሆይ ክብር ይገባሻል) ❖ “በቃለ ውዳሴ ጥዑም ይደሉ ሰላም ለዕበይኪ ፍጹም አድባረ ቊስቋም ማኅደረ ልዑል ዘአርያም” (በአርያም ያለ የልዑል ማደሪያው የኾንሽ የቊስቋም ተራራ ሆይ ፍጹም ለሚኾን ክብርሽ በሚጣፍጥ የምስጋና ቃል ሰላምታ ማቅረብ ይገባል) በማለት ዘርዝሮ ጽፎላታል፡፡ ❖ ቅዱስ ያሬድም ቅድስት ድንግል ማርያም ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስን ይዛ በስደቷ ወቅት በደብረ ቊስቋም ስለማረፏ በድጓው ላይ ሲጽፍ፡- “መንግሥቱ ሰፋኒት ዘእምቅድመ ዓለም ወልደ ቅድስት ማርያም ኀሠሠ ምእራፈ ከመ ድኩም ንጉሥ ዘለዓለም ግሩም እምግሩማን ብርሃነ ሕይወት ዘኢይጸልም ኀደረ ደብረ ቊስቋም” (ቅድመ ዓለም የነበረች ጌትነቱ ምልእት ስፍሕት የኾነች የቅድስት ድንግል ማርያም የባሕርይ ልጅ የዘለዓለም ንጉሥ ሲኾን እንደ ደካማ ማረፊያን ፈለገ፤ ከግሩማን ይልቅ ግሩም፤ የማይጨልም የሕይወት ብርሃን ርሱ በደብረ ቊስቋም ዐደረ) ❖ “መንክር ወመድምም ዘተገብረ በደብረ ቊስቋም መንክር ወመድምም ዘይሴባሕ በአርያም አምላክ ፍጹም ኀደረ ውስቴቱ መድኀኔ ዓለም ዘሀሎ እምቅድም ኀደረ ውስቴቱ ለዝንቱ ደብር ዘአብ ቃል ምስለ እሙ ድንግል ደመና ቀሊል” (በደብረ ቊስቋም የተደረገው የሚያስደንቅ እና የሚያስገርም ነው፤ በአርያም የሚመሰገን ፍጹም የባሕርይ አምላክ መድኀኔ ዓለም በውስጡ ዐደረ፤ ቅድመ ዓለም የነበረ የአብ አካላዊ ቃል ፈጣን ደመና ከተባለች ከድንግል እናቱ ጋር በዚኽ ደብር በውስጡ ዐድሯል) በማለት መስክሮላታል፡፡ ❖ እኔም ለወንጌል አገልግሎት ወደ ግብጽ ኼጄ በነበረ ጊዜ እመቤታችን ልጇን ይዛ ከስደት ስትመለስ ከአረጋዊ ዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር ከድካም ያረፉበት ይኽቺን ቅድስት ቦታ ገዳመ ቁስቋምን ስረግጣትና ጌታችን ከእናቱ ጋ የተቀመጡበት ዋሻ ውስጥ ገብቼ የተቀደሰችውን ቦታ ስስማት መጀመሪያ ያሰብኩት ቅዱሱ አባት አባ ጽጌ ብርሃን በማሕሌተ ጽጌው ላይ፦ “ተአምረ ግፍእኪ ለአርእዮ እምገጸ ሄሮድስ መስቴማ አመ ጐየይኪ ማርያም በሐዊረ ፍኖት እለ ደክማ ምስለ እግረ ጽጌኪ ልምሉም ኀበ አእጋርኪ ቆማ ለምድረ ገዳምኪ ቅድስት ቊስቋም ስማ እምፈተውኩ በጺሕየ በሰጊድ እሰዓማ” (ማርያም የግፍሽን ተአምር ለመግለጥ ከጠላት ሄሮድስ ፊት በሸሸሽ ጊዜ ከለመለመች ከልጅሽ እግር ጋር መንገድን በመኼድ የደከሙ እግሮችሽ የቆሙባት ስሟ ቊስቋም የተባለ የተቀደሰች ገዳምሽን እኔም ደርሼ ብሳለማት እመኛለሁ እወዳለሁ) በማለት የጸለያት ጸሎትን ነበር፡፡ 🙏♥ የእመቤታችን በረከት ይደርባችኊ፤ ቦታዋን ያላያችሁ ለመሳለም ኹላችኹንም ያብቃችሁ እላለሁ፡፡♥🙏 ✍ከመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ

አዳዲስ ዝማሬዎችን ማግኘት የምትፈልጉ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተወዳጅነትን ያፈራው የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮች የተሰኘውን ከ30k በላይ ተከታይ ያለውን የቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ። ቻናላችንን ሲቀላቀሉ ሙሉ የማኅቶት ቲዩብ ዝማሬዎችን በውስጡ ያገኛሉ። ታዲያ ምን ትጠብቃላቹ ከስር Open የሚለውን ነክታችሁ Join አድርጉ። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 ▧▧▧▧   ▧ ▧ ▧  ▧▧▧▧  ▧▨       ▨ ▧      ▧   ▧     ▧  ▨           ▧ ▧      ▧ ▧      ▧   ▧ ▧ ▧  ▧▧▨▧  ▨   ▨    ▨ ▧      ▧   ▧          ▧           ▧     ▧  ▨ ▧▧▧▧   ▧          ▧▨▧▨  ▨       ▧▧ .

አዳዲስ ዝማሬዎችን ማግኘት የምትፈልጉ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተወዳጅነትን ያፈራው የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮች የተሰኘውን ከ30k በላይ ተከታይ ያለውን የቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ። ቻናላችንን ሲቀላቀሉ ሙሉ የማኅቶት ቲዩብ ዝማሬዎችን በውስጡ ያገኛሉ። ታዲያ ምን ትጠብቃላቹ ከስር Open የሚለውን ነክታችሁ Join አድርጉ። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 ▧▧▧▧   ▧ ▧ ▧  ▧▧▧▧  ▧▨       ▨ ▧      ▧   ▧     ▧  ▨           ▧ ▧      ▧ ▧      ▧   ▧ ▧ ▧  ▧▧▨▧  ▨   ▨    ▨ ▧      ▧   ▧          ▧           ▧     ▧  ▨ ▧▧▧▧   ▧          ▧▨▧▨  ▨       ▧▧ .

አዳዲስ ዝማሬዎችን ማግኘት የምትፈልጉ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተወዳጅነትን ያፈራው የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮች የተሰኘውን ከ30k በላይ ተከታይ ያለውን የቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ። ቻናላችንን ሲቀላቀሉ ሙሉ የማኅቶት ቲዩብ ዝማሬዎችን በውስጡ ያገኛሉ። ታዲያ ምን ትጠብቃላቹ ከስር Open የሚለውን ነክታችሁ Join አድርጉ። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 ▧▧▧▧   ▧ ▧ ▧  ▧▧▧▧  ▧▨       ▨ ▧      ▧   ▧     ▧  ▨           ▧ ▧      ▧ ▧      ▧   ▧ ▧ ▧  ▧▧▨▧  ▨   ▨    ▨ ▧      ▧   ▧          ▧           ▧     ▧  ▨ ▧▧▧▧   ▧          ▧▨▧▨  ▨       ▧▧ .

አዳዲስ ዝማሬዎችን ማግኘት የምትፈልጉ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተወዳጅነትን ያፈራው የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮች የተሰኘውን ከ30k በላይ ተከታይ ያለውን የቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ። ቻናላችንን ሲቀላቀሉ ሙሉ የማኅቶት ቲዩብ ዝማሬዎችን በውስጡ ያገኛሉ። ታዲያ ምን ትጠብቃላቹ ከስር Open የሚለውን ነክታችሁ Join አድርጉ። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 ▧▧▧▧   ▧ ▧ ▧  ▧▧▧▧  ▧▨       ▨ ▧      ▧   ▧     ▧  ▨           ▧ ▧      ▧ ▧      ▧   ▧ ▧ ▧  ▧▧▨▧  ▨   ▨    ▨ ▧      ▧   ▧          ▧           ▧     ▧  ▨ ▧▧▧▧   ▧          ▧▨▧▨  ▨       ▧▧ .