en
Feedback
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን🙏

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን🙏

Open in Telegram

የኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያንን ዶግማና ቀኖና የጠበቁ የነፍስ ስንቅ የምናገኝበት፦ ✍️"ማንም አንዳች የሚያውቅ ቢመስለው ሊያውቅ እንደሚገባው ገና አላወቀም" ፩ኛ ቆሮ. ፰፥፪ #ለተጨማሪ፦👇✞👇 https://www.youtube.com/EOTC2921 https://www.facebook.com/eotc2921 https://www.tiktok.com/@eotc2921 https://www.instagram.com/eotc2921

Show more
4 374
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
🕊✞ #እሳተ_ጽርሑ 🕊✞ እሳተ ጽርሑ ማይ ጠፈሩ ደመና መንኮራኩሩ ለመድኃኔዓለም ትርጉም፦ አዳራሹ እሳት ጣራውም ውሃ የመድኃኔዓለም ሠረገላው ደመና ነው፡፡

🕊✞ #ይትፌሳሕ 🕊✞ ይትፌሳሕ ሰማይ በልደቱ ወትትሐሰይ ምድር በጥምቀቱ ለመድኃኔዓለም ሶበ ሶበ ይወርድ ወልድ ውስተ ምጥማቃት ትርጉም፦ ሰማይ በልደቱ ይደሰታል ምድርም በመድኃኔዓለም ጥምቀት ትደሰታለች ወልድ ወደ መጠመቂያው በወረደ ጊዜ፡፡

🕊✞ #መጽአ_ቃል 🕊✞ መጽአ ቃል ፬ መጽአ ቃል/፪/ እም ደመና ዘይብል ዝንቱ ውእቱ ወልድየ ዘአፈቅር ሎቱ ስምዕዎ/፪/

🕊✞ #ወረደ_ወልድ 🕊✞ ወረደ ወልድ/፫/ እም ሰማያት ውስተ ምጥማቃት ትርጉም፦ ወልድ ከሰማያት ወርዶ ወደ መጠመቂያው ገባ፡፡

🕊✞ #ሖረ_ኢየሱስ 🕊✞ ሖረ ኢየሱስ/፪/ እም ገሊላ/፫/ ኀበ ዮሐንስ ሄደ ኢየሱስ/፪/ ከገሊላ/፫/ ወደ ዮሐንስ

🕊✞ #ወረደ ወልድ 🕊✞ ወረደ ወልድ/፫/ እም ሰማያት ውስተ ምጥማቃት ትርጉም፦ ወልድ ከሰማያት ወርዶ ወደ መጠመቂያው ገባ፡፡

🕊✞ #ኢየሱስ_ሖረ ✞🕊 ኢየሱስ ሖረ ሀገረ እሴይ ዮሐንስ አጥመቆ በማይ/፪/ ትርጉም፦ ኢየሱስ ወደ እሴይ ሀገር ሄደ ዮሐንስም በውሃ አጠመቀው

🕊✞ #እግዚኡ_መርሐ ✞🕊 እግዚኡ መርሐ ዮርዳኖስ አብጽሐ ወበህየ ዮሐንስ ወበህየ ፍፁመ ተፈስሐ/፪/ ጌታውን መራና ዮርዳኖስ አደረሰው በዚያችም ቀን ዮሐንስ በዚያችም ቀን ፈፅሞ ደስ አለው።

🕊✞ #በዕደ_ዮሐንስ ✞🕊 በዕደ ዮሐንስ ተጠምቀ ኢየሱስ ናዝራዊ/2/ ሠማያዊ/4/ሠማያዊ ኢየሱስ ናዝራዊ/2/ #አዝ•••••••✞✞✞••••••• አዳም ያጠፋውን ልጅነት ሊያስመልስ በሠላሳ ዘመን ተጠመቀ ኢየሱስ እርሱ አምላክ ሢሆን ፈጥሮ የሚገዛ ወረደ ወደምድር እንዲሆነን ቤዛ #አዝ•••••••✞✞✞••••••• ሊያጠፋው አቅልጦ እንደ አምላክነቱ እረግጦ ሊሠርዝ እንደ ሠውነቱ የፍጥረቱ ጌታ በዮርዳኖስ ቆሟል የእዳውን ፅህፈት በስልጣኑ ሽሯል #አዝ•••••••✞✞✞••••••• የአንድነት ሶስትነት ተገልጧል ምስጢሩ በዕደ ዮሐንስ ተጠምቆ መምህሩ አብም በደመና ለልጁ መስክሯል በአምሳለ ርግብ መንፈስ ቅዱስ ወርዷል #አዝ•••••••✞✞✞••••••• ሲነገር እንዲኖር የእርሱ ትህትና ለዓለም እንዲገለጥ የባሪያው ልዕልና ተጠማቂው ሄደ ወደ አጥማቂው አምላክ የሠራልን ስርዓቱ ይህ ነው #አዝ•••••••✞✞✞•••••••

፠  ✞✞✞ የልደት ሥርዓተ ማኅሌት ✞✞✞  ፠  እንኳን ለብርሃነ ለደቱ በሰላም አደረሳችሁ!!! ፩.  ነግሥ / ለአፃብዒክሙ / ሰላም ለአፃብዒክሙ እለ እምአጽፋር ኢይትሌለዩ፤ ለቤትክሙ ሥላሴ ዘኢየሐልቅ ንዋዩ፤ አመ አብዓልክሙ ሰብአ ድኅረ አንደዮ ጌጋዩ፤ ዘኢርእዩ እምቅድመ ዮም መላእክተ ሰማይ ርእዩ፤ ወአግብርተ ሰብእ መላእክት ተሰምዩ ። ዚቅ፦ ርእይዎ ኖሎት አእኰትዎ መላእከት ፨ ለዘተወልደ እማርያም እምቅድስት ድንግል ፨ ዮም ሰማያዊ በጎል ሰከበ። ወረብ፦ ርእይዎ ኖሎት ርእይዎ ኖሎት አእኰትዎ መላእከት፤ ዮም ሰማያዊ በጎል ሰከበ ለዘተወልደ እምቅድስት ድንግል። ፪ .  ነግሥ / ለልደትከ / ሰላም ለልደትከ ኦ አማኑኤል፤ ዘቀዳሚ ወዘደኃሪ ብሉየ መዋዕል፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘአብ ቃል፤ እፎ እፎ አግመረተከ ድንግል፤ ወእፎ እንዘ አምላክ ሰከብከ በጎል። ዚቅ፦ በጎል ሰከበ በአጽርቅት ተጠብለለ ፨ ውስተ ማኅፀነ ድንግል ኀደረ ፨ እፎ ተሴሰየ ሐሊበ ከመ ሕፃናት ። ወረብ፦ በጎል ሰከበ በአጽርቅት ተጠብለለ ኀደረ ማኅፀነ ድንግል፤ እፎ ተሴሰየ ተሴሰየ ሀሊበ ከመ ሕፃናት ተሴሰየ። ፫. ለዝክረ ስምከ / መልክአ ኢየሱስ / ሰላም ለዝክረ ስምከ ስመ መሐላ ዘኢይሔሱ፤ ዘአንበረ ቅድመ እግዚአብሔር በአትሮንሱ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ለዳዊት ባሕርየ ከርሡ፤ አክሊለ ስምከ እንዘ ይትቄጸል በርእሱ፤ አህጉረ ፀር ወረሰ ኢያሱ። ዚቅ፦ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ፨ ንሰብክ ወልደ እምዘርዓ ዳዊት ዘመጽአ፨ ወተወልደ በሥጋ ሰብእ፨ እንዘ ኢየዓርቅ እመንበረ ስብሐቲሁ፨ ውስተ ማኅፀነ ድንግል ኃደረ  ሥጋ ኮነ ወተወልደ፨ ትጉሃን የአምኑ ልደቶ ፨ ወሱራፌል  ይቀውሙ ዓውዶ፨ መጽአ ይቤዝወነ ውስተ ዓለም ፨ የሀበነ ሰላመ ፨ ጋዳ ያበውኡ ቍርባነ። ወረብ፦ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ንሰብክ ወልደ እምዘርዓ ዳዊት፤ ወተወልደ በሥጋ ሰብእ። ፬. ለአጽፋረ እዴከ / መልክአ ኢየሱስ / ሰላም ለአጽፋረ እዴከ ዘኅበሪሆን ጸዓዳ፤ በምግባር ወግእዝ እለ ይትዋሐዳ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ምስፍና አባሉ ለይሁዳ፤ ለመንግሥትከ ሰፋኒት እንዘ ይትመሐለሉ ዐውዳ፤ ሰብአ ሰገል አወፈዩ ጋዳ። ዚቅ፦ አንፈርዓፁ ሰብአ ሰገል አምኃሆሙ ፨ አምጽኡ መድምመ ፨ ረኪቦሙ ሕጻነ ዘተወልደ ለነ። ወረብ፦ አንፈርዓፁ ሰብአ ሰገል አንፈርዓፁ ሰብአ ሰገል፤ አምኃሆሙ አምጽኡ መድምመ። ፭. እምኲሉ ይኄይስ / መልክአ ኢየሱስ / እምኵሉ ይኄይስ በሥላሴከ ተአምኖ፤ ወበወላዲትከ ተማኅፅኖ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ እምቤተ መንግሥት ወተክህኖ፤ ተሰብኦተከ እመቦ ዘያስተሐቅር መኒኖ፤ ያንኰርኵር ታሕተ ደይን ግዱፈ ከዊኖ። ዚቅ፦ ወካዕበ ተማኅፀነ በማርያም እምከ፨ እንተ ይእቲ እግዝእትነ፨ ወትምክሕተ ዘመድነ በወሊዶተ ዚአከ። ወረብ፦ ትምክሕተ ዘመድነ ትምክሕተ ዘመድነ በወሊዶተ ዚአከ፤ ይእቲ እግዝእትነ እግዝእትነ ማርያም ድንግል። ፮. ኦ ዝ መንክር / ማኅሌተ ጽጌ / ኦ ዝ መንክር በዘዚአኪ አምሳል፤ ኮከበ ትንቢት ዘቦቱ መልክአ ሕጻን ሥዑል፤ ሠረቀ ያርኢ ተአምርኪ ድንግል፤ ወመርሖሙ ለሰብአ ሰገል እምርኁቅ ደወል፤ ጽጌኪ ኀበ ሀሎ ይሰክብ በጎል። ዚቅ፦ ወኖሎት በቤተልሔም አንከሩ እምዘርእዩ ወሰምዑ ሰብአ ሰገል ፨ ርእዮሙ ኮከበ መጽኡ እምርኁቅ ብሔር ፨ ከመ ይስግዱ ለወልድኪ ወይግነዩ ለኪ። °༺༒༻°  አንገርጋሪ  °༺༒༻° ሃሌ ሉያ ዮም ፍሥሐ ኮነ፤ በእንተ ልደቱ ለክርስቶስ፤ እምቅድስት ድንግል፤ ውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ፤ ዘሎቱ ሰብአ ሰገል ሰገዱ ሎቱ፤ አማን መንክር ስብሐተ ልደቱ። °༺༒༻°  አመላለስ °༺༒༻° ዮም ፍሥሐ ኮነ በእንተ ልደቱ ለክርስቶስ፤ እምቅድስት ድንግል ድንግል ውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ። °༺༒༻°  እስመ ለዓለም  °༺༒༻° ተወልደ ኢየሱስ በቤተልሔም ዘይሁዳ ፨ አዋልደ ጢሮስ አሜሃ ይሰግዳ ፨ ሰብአ ሰገል አምጽኡ ሎቱ ጋዳ ፨ ወይትኃሠያ አዋልደ ይሁዳ። °༺༒༻°  አመላለስ °༺༒༻° ተወልደ ኢየሱስ በቤተ ልሔም በቤተ ልሔም ዘይሁዳ በቤተ ልሔም፤ አዋልደ ጢሮስ አሜሃ ይሰግዳ አሜሃ ይሰግዳ በቤተልሔም። °༺༒༻°  ዕዝል °༺༒༻° በጎል ሰከበ በአጽርቅት ተጠብለለ፤ ውስተ ማኅጸነ ድንግል ኀደረ፤ ዮም ተወልደ እግዚእ ወመድኅን ቤዛ ኵሉ ዓለም። ምልጣን፦ በጎል ሰከበ በአጽርቅት ተጠብለለ፨ እግዚእ ወመድኅን ፨ ቤዛ ኲሉ ዓለም ዮም ተወልደ ፨ ቤዛ ኲሉ ዓለም ዮም ተወልደ። አመላለስ፦ ቤዛ ኵሉ ዓለም ዮም ተወልደ፤ ቤዛ ኵሉ ዓለም ዮም ተወልደ። °༺༒༻°  አቡን በ፩ ሃሌ °༺༒༻° ዮም በርህ ሠረቀ ለነ ፨ ሰማይ ወምድር ዘኢያገምሮ ማኅጸነ ድንግል ፆሮ ፨ እንዘ አምላክ ውእቱ ኀደረ ወተገምረ ውስተ ማኅፀነ ድንግል ፨ ኮነ ሕጻነ ንዑሰ ዘአልቦ መምሰል ተወልደ ፨ ፀሐየ ጽድቅ ሠረቀ። °༺༒༻°  ዓራ  °༺༒༻° ለዘተወልደ እምቅድስት ድንግል ፨ ምንተ ንብሎ ናስተማስሎ ለመድኃኒነ ፨ አርዌ ገዳምኑ አንበሳ ወሚመ ከራድዮን ፨ ዖፍ ጸዓዳ ንጉሥ አንበሳ ፨ እምዘርዓ ዳዊት ዘመጽአ። °༺༒༻°  ሰላም  °༺༒༻° ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ፨ ንሰብክ ወልደ እምዘርዓ ዳዊት ዘመጽአ ፨ ወተወልደ በሥጋ ሰብእ ፨ እንዘ ኢየዓርቅ እመንበረ ስብሐቲሁ ፨ ውስተ ማኅፀነ ድንግል ኀደረ  ሥጋ ኮነ ወተወልደ ፨ ትጉሃን የአምኑ ልደቶ ፨ ወሱራፌል  ይቀውሙ ዓውዶ ፨ መጽአ ይቤዝወነ ውስተ ዓለም ፨ የሀበነ ሰላመ ፨ ጋዳ ያበውኡ ቍርባነ። ✞✞✞✞✞✞✞༒ ተፈጸመ ༒✞✞✞✞✞✞✞ © ፍሬ ማኅሌት

➍✝#ኃያል ኃያልነት የበሕርይ ገንዘቡ ነው "ኀይሉ ለአብ ወጸጋ ለአህዛብ…”የአብ ኃሉ እርሱ ነው ለአህዛብም ጸጋን የሚሰጥ “ እነዳለ መጽሐፈ ኪዳን፡፡ መንግሥትህ ያንተ ናትና ኃይል ምስጋና ክብር ለዘላለሙ” ማቴ 6፥13 በኃይሉ ኃይለኛው ቤት ገብቶ ዕቃዉን ሊነጥቀዉ እንዴት ይቻላል።ማቴ 12፥29👉“ክርስቶስም ስለ እናንተ አይደክምም /ደካማ/አይደለም ነገር ግን በእናንተ ኃለኛ ነው በድካም ተሰቅሏልና ነገር ግን በእግዚአበሔር /በእግዚአብሔር/ኃይል በሕይወት ይኖራል 1ኛ ቆሮ 13፥3-5 👉“የእግዚአብሔር ጥበብ የሆነው ክርስቶስ ነው” 1ቆሮ 1፣24-26 ሰዎች ይህንን የእግዚአብሔር ኃይል አላወቁም ነበር። 👉“የእግዚአብሔርን ኃይል አታዉቁም እና ትስታለችሁ” ማቴ 22፥22 ➎✝#አምላክ ➏✝#የዘላለም_አባት ➐✝#የሰላም_አለቃ { ትንቢተ ኢሳያስ (ምዕራፍ 9፥6:7) } 👉"ሕፃን ተወልዷልና ወንድ ልጅም ተሰቶናልና አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል፡ ስሙም ድንቅ መካር ሀያል አምላክ፡ የዘላለም አባት የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል፡ ለአለቆች ሰላምን ለዕርሱም ህይወትን አመጣለሁና፡ ከዛሬ ጀሞሮ እስከ ዘልአለም ድረስ በፍርድና በፅድቅ ያፀናውና ይደግፈው ግዛቱ ታላቅ ይሆናል፡ በዳዊት ዙፋን መንግስቱም ትፀናለች ለሰላሙም ፍፃሜ የለውም። የእግዚአብሔር ቅንነት ይህንን ያደርጋል።" 🌾🌾🌾🙏🙏🙏🌾🌾🌾 ውድ የተዋሕዶ ቤተሰቦች የሆናችሁ የእናቱ የእናታችን የቅድስተ ቅዱሳን የንጽሕይተ ንጹሐን የድንግል ማርያም የዓሥራት የአደራ ልጆች የሆናችሁ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን። በዓሉ፦ 🕊የሰላም 😁የደስታ 👩‍❤️‍👨የፍቅር 🧖‍♂የጤና 👨‍👩‍👧‍👦የመተሳሰብ 🐥የመተዛዘን 🌾የበረከት 🌽የእረድኤት ⛪️የስኬት 🌻የቅንነት ይሆንልን ዘንድ የፈጣሪ ቅዱስ ፈቃዱ ይሁን አሜን!!! ✞ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያንን አስተምሮና ስርዓት የጠበቁ የተለያዩ መርሃ ግብሮች በየቀኑ ወደ እርስዎ ይቀርባሉ፡፡ ለወዳጅዎ #Share በመድረግ የበረከት ተካፋይ ያድርጓቸው ✞ ╭══•|❀:๑✞♡✞๑:❀|•══╮ https://t.me/EOTC2921 ╰══•|❀:๑✞♡✞๑:❀|•══╯

🌾✞ #ሕፃን_ተወልዶልናልና ✞🌾 በስመ አብ ወወለወድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን 👉ልደታትን ስንመለከት ብዙ አሉ፦ ልደተ አዳም ከምድር፣ ልደተ ሔዋን ከአዳም ፣ልደተ ሙታን ከመቃብር፣ ልደተ ሕፃናት ከእናታቸው ማህፀን የሚጠቀሱት ናቸው፡፡የእነዚህ ሁሉ ልደት ለራሳቸው እንጂ ለእኛ አይደሉም። 👉#ህፃን_ተወለልዶልናልና የሚለው ግን ለእኛ ነው፡፡ የአምላክን መወለድ ብዙ ነቢያት በብዙ ሕብረ ትንቢት ተናግረዋል በብዙ ሕብረ አምሳል መስለዋል፡፡ 👉ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር በብዙ አይነትና በብዙ ጎዳና ለአባቶቻችን በነቢያት ተናግሮ ሁሉን ወራሽ ባደረገው ዳግምም ዓለማትን በፈጠረበት በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን።ዕብ፡1፥1 በብዙ ሕበረ አምሳል በብዙ ሕብረ ትንቢት እግዚአብሔር ከተናገረባቸው ነቢያት አንዱ ኢሳይያስ ነው። ኢሳይያስ ከነቢያት ወንድሞች በተለየ መልኩ የአምላክን ሰው መሆን የተናገረ ነቢይ ነው። መወለዱን፣ስሙን፣ከማን እነደሚወለድ ፣ለሰው ልጆች ያደረገውን የቤዛነት ስራ መከራ መቀበሉን ፣በጎል መወለዱን በግልፅ ከተናገሩ የተነሳ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ወንጌላዊ ነቢይ የሚል ቀጽል ሰጥተው ይጠሩታል፡፡የትንቢት መጽሐፉንም ደረቅ ሐዲስ በማለት ሰይመውታል፡፡ይህም ማለት ስለክርስቶስ መወለድ በምሰሌ ያይደለ በቀጥታ የተናገረ በመሆኑ ነው ለምሳሌ የሚከተሉትን ማየት ይቻላል፡፡ 👉"ጌታ ምልክት ይሰጣችኋል እነሆ ድንግል ትጸንሳለች ወንድ ልጅንም ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።"ኢሳ፡7፥14 ከላይ ባጭሩ እንዳየነው ከማን እንደምትወልድ ስሙን ማን አንደሆነ በግልጽ እስቀምጧል፡፡ 👉"በስድስተኛው ወር ገብርኤል መላክ ከእግዚአብሔር ዘንድ ተላከ ከዳዊት ወገን የሆነ ስሙ ዮሴፍ ለሚባል ሰው ከታጨች ከድንግል ዘንድ የዚህች ድንግል ስሟ ማርያም ነው"ሉቃ፡1፥26 በማለት ወንጌለዊው ገልጧል። 👉"በነቢይ ከጌታ ዘንድ እነሆ ድንገል ትፀንሳለች ወንድ ልጅም ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤል ይሉታል የተባለውን ይፈጸም ዘንድ ይህ ሁሉ ሆኗል ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ነው። ማቴ፡1፥22 ኢሳይያስ "ሕፃን ተወልዶልናል" ብሎ ለእኛ መዳን የተወለደው ነገረን ቀጥሎም ወንድ ልጅ ተሰጥቶናል።" ይላል። ሥጋውን በልተን ደሙን ጠጥተን መድኃኒት ለሆነን እንደመጣ ሊያሳይ፡፡ ከዚህ በመቀጠል እርሱን ለመግለጥ የተጠቀማቸው ቃላት በጣም የሚደንቁ ናቸው፡፡ #ስሙ_ድንቅ_መካር_ኃያል_አምላክ_የዘላዓለምአባት_የሰላምአለቃ በሚሉ #ሰባት ቃላት ገልጾታል ቁጥሩ በእብራዊያን ዘንድ ፍጹም ነው። ከላይ ኢሳይያስ የተጠቀማቸው ሰባት ቃላት ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው መሆኑን የሚያስረዱ ናቸው፡፡ ሕፃን ብሎት ነበር ሕፃን የሚለው ስም ታህታዊ ማንም በሥጋ የወለደ ሰው ሲወለድ የሚጠራበር ነው ፡፡ ሰው መሆኑን ለመግለጥ ሕጻን አለው አምላክነቱን ለማስረዳት ስሙም ብሎ ጀምሮ በሰባት ቃለት አስረድቶናል፡፡ ➊✝#ስሙ ስለ ስሙ ቅዱሳት መጻፍት ሲናገሩ ኢየሱስ ፣አማኑኤል፣ ክርስቶስ ፣መድኃኔዓለም የሚባሉት ስመ ስጋዌ ናቸው። ሰው በመሆኑ የተጠራባቸው ኢየሱስ፦ማለት መድሐኒት ማለት ነው፡፡ አማኑኤል፦ማለት እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ነው። ከእኛ ጋር፦ ሲባል ከስጋችን ሥጋ ከደማችን ደምን ነስቶ ሰው የሆነ አምላክ ማለት ነው። ክርስቶስ፦ማለት መሲህ ፣ሹም፣ንጉሥ ፣አለቃ ማለት ነው፡፡ መድኃኔዓለም፦ማለት የአለም መድኃኒት የዓለም ቤዛ ደሙን አፍስሶ ሥጋውን ቆርሶ በደሙ ዓለምን የዋጀ ማለት ነው፡፡ 👉"ልጅም ትወልዳለች እርሱም ሕዝቡን ከኃጢያታቸው ያድናቸዋልና ስሙን ኢየሱስ ትለዋለች" ማቴ፡1፥21 👉"ክርስቶስ የሚባል መሲሕ እንዲመጣ አውቃለሁ እርሱ በመጣ ጊዜ ሁሉን ይነግረናል አለችዉ ኢየሱስም የምትናገሪዉ እርሱ እኔ ነኝ አላት።"ዮሐ፡1፥42 👉"እኛ ራሳችን ሰምተነዋል አርሱም በእውነት ክርስቶስ የዓለም መድኃኒት እንደሆነ እናውቃለን።"ዮሐ፡4፥42 ከላይ የተመለከትናቸው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ስሙንና ግብሩን የሚገልጡ ናቸው፡፡ ትርጉሙ ከተግባር ጋር የተያያዘ ነውና ይህንን ነው ኢሳይያሰ “ሕፃን ተወለደልን” በማለት የተነገረለት ኢሳይያስም ሕጻን ብሎ የጠራዉ ሰዉ ሲሆን አምላክነቱ አልተለወጠምና አምላክነቱን መግለጥ የሚችሉ ቃላት ከስሙ ጀምሮ ተጠቅሟል ስሙ አዳኝ ነው። 👉"አቤቱ በስምህ አድነኝ።"መዝ፡53፥1 👉ስሙ ቅዱስ ነው፤ እርሱ ለእኔ ታላቅ ስራ አድርጎል እና ስሙም ቅዱስ ነው።"ሉቃ 1፥50 👉ስሙ፦ አጋንንትን ይገዛል "አጋንንት በስምህ ተገዙልን።"ሉቃ 10፥17 👉ያመኑትን እነዚህን ምልክቶች ይከተሏቸዋል በስሜ አጋንትን ያወጣሉ እባቦችን ይይዛሉ የሚያሰክር መርዝ ቢጠጡ አይገድላቸውም።ማር 16፥17 👉ስሙ፦ ስግደት የሚገባው ነው ?"እግዚአብሔር/እግዚአብሔርነቱ/ ያለልክ ከፍ ከፍ አድርገው ከስምም ሁሉ በላይ ያለዉን ስም ሰጠው ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ ለኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይንበርከኩ ዘንድ።" ቆላ 2፥9-11 👉ስሙ፦ ምስጋና ይገባዋል 👉"በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ ስምህ ይቀደስ.."ማቴ 6፥9 ➋✝#ድንቅ ድንቅ፦ማለት ቃል እነደሚገባው አድርጎ የማይገልጠዉ ቃላት ላጣንለት ነገር የምንጠቀመዉ ነዉ በህቱም ድንግልና ተጸንሶ በህቱም ድንግልና መወለዱን ሲደንቅ የሚኖር ነውና በኪሩቤል ላይ የሚገለጥ ስጋን ለብሶ መወለዱን የማይወስነዉ መወሰኑ የማይዳሰሰው መዳሰሱ የማይታየው መታየቱ የማይጨበጠው እሳተመለኮት በጨርቅ መጠቅለሉ በጎል መጣሉ የሚደንቀን ነው እነኳን ለኢሳይያስ ለመላእክትም ድነቅ ነው። ሰማይ ዙፋኑ የሆነ አምላክ በትህትና መገለጡ ድሆች እንኳ ባልተወለዱበት የከብቶቸች በረት መወለዱ ድንቅ ነው፡፡ 👉"በልዎ ለእግዚአብሔር ግሩም ግብርከ"(እግዚአብሔርን ስራህ ድንቅ ነው በሉት) መዝ፡65፥3 ሕፃናትን በእናታቸው ማህጸን የሚጠብቃቸው ሕጻን ሆነ ይህ እንዴት አይደንቅ 👉"ስራህ ድንቅ ነው ነፍሴም እጅግ ታዉቀዋለች።"መዝ 138፥12 በላይ በሰማይ በኪቤል ጀርባ በምድር በእናቱ እቅፍ መታየቱ ድንቅ ነው? "ግንበኞች የናቁት ድንጋይ እርሱ የማእዘን ራስ ሆነ ይህም ከጌታ ዘንድ ሆነ ለዓይናችን ድንቅ ነው።"መዝ 117፥22 ማቴ 22፥42 ➌✝#መካር ሰው ለመሆን መወሰኑን በልብ የመከረውን በነብያት ያናገረውን ያን የፈጸመ ምክረ ከይሲን በምክሩ የሻረ ዲያብሎስን ያሣፈረ በልቡ ጥበብ ከሰው ልጆች በተለየች ምክሩ አዳምን ነጻ ያወጣ መካር ነው፡፡👉"ግሩም ምክሩ እምጎለመኸያው (ምክሩ ከሰው ልጆች ይልቅ ልዩ ነው)"መዝ 65፥5 በዚህ በልዩ ምክሩ ዲያብሎስ የመከራቸውን የነፍስና የስጋ ተዋህዶ በሥጋ ተወለደ ይህ የዲያብሎስን ስራ ያፈርስ ዘንድ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ። 1ኛ ተሰ 3፥7👉"ውዕቱ ጥበቡ ወምክሩ ያድኅነነ መጸአ (እርሱ የአብ ጥበቡና ምክሩ ሊያድነን መጣ)" ይለዋል ቅዱስ ያሬድ፤

#ጌታችን_ስለተወለደባት_ምሽት_ሶርያዊው_ቅዱስ_ኤፍሬም_አንዲህ_አለ፦ 🌾🌾🌾🙏✞🙏🌾🌾🌾 👉‹‹ይህች ምሽት ንጹሕ የሆነውና እኛን ሊያነጻን የመጣው (አምላክ) የተገለጠባት ንጽሕት ምሽት ናት፡፡ ጆሮአችን ንጹሕ ይሁን ፤ ዓይኖቻችንም ወደ ንጹሕ ነገር ይመልከቱ ፤ የልባችን ስሜት ቅዱስ ይሁን! ንግግራችንም አክብሮትን ይሞላ! 👉ይህች ምሽት የዕርቅ ምሽት ናት ፤ ስለዚህ ማንም ሰው ወንድሙን ተቆጥቶ እንዳያስቀይም! ይህች ምሽት ለዓለም ሁሉ ሰላምን ያስገኘች ምሽት ስለሆነች ማንም ሰው አይሸበርባት፡፡ ይህች ምሽት የደግነት ምሽት ስለሆነች ማንም ሰው ክፉ አይሁን! ይህች ምሽት የትሕትና ምሽት ናትና ማንም ሰው እንዳይታበይባት! 👉ይህች ምሽት የደስታችን ቀን ስለሆነች የበደሉንን አንበቀልባት! የበጎ ፈቃድ ቀን ናትና የጭካኔ ቀን አናድርጋት! የጸጥታ ቀን ናትና በቁጣ የምንነድባት ቀን አናድርጋት! ዛሬ እግዚአብሔር ወደ ኃጢአተኞች የመጣበት ቀን ነው ፤ ስለዚህ ጻድቅ ሰው በኃጢአተኞች ላይ አይኩራባቸው! ዛሬ እጅግ ባለጠጋ የሆነው አምላክ ስለ እኛ ደሃ የሆነበት ቀን ነው፤ ስለዚህ ሀብታም ሰው ድሆችን ወደ ገበታው ይጥራቸው፡፡ 👉ዛሬ ያልጠየቅነውን ሥጦታ የተቀበልንበት ዕለት ነው፡፡ ስለዚህ እጆቻቸውን ዘርግተው እየጮኹ ለሚለምኑን ሰዎች የእርዳታ እጃችንን እንዘርጋ! የዛሬዋ ዕለት ለጸሎቶቻችን የሰማያትን በር ከፍታልናለች ፤ እኛም ይቅርታን ለሚጠይቁን ሰዎች በራችንን እንክፈት! ዛሬ አምላክ የሰውነትን ማኅተም በራሱ ላይ አተመ ፤ ሰውም የአምላክነትን ማኅተም ተጎናጸፈ!›› #የገና_አባት (ቅዱስ ኒቆላዎስ) ለድኆች ሥጦታ ይለግስ የነበረ ቅዱስ አባት ነው። ታሪኩም በስንክሳር ታኅሣሥ 10 ላይ ተጽፎአል። "የገና ዛፍ ባሕላችን አይደለም እነርሱ ክረምታቸውን የሚያስታውሱበት ነው ከእኛ ጋር አይገጥምም" "የተወለደውን ክርስቶስ የበዓሉ ማዕከል እንዳናደርግ ያደርገናል" ማለት ትክክለኛ ነገር ነው። Pagan Origin (የባዕድ አምልኮ መነሻ) አለው ብሎ ጣዖት አምልኮ ነው ማለት ግን ከገደብ ያለፈ ድምዳሜ ነው። በከዋክብት ያመልኩ የነበሩት የጥበብ ሰዎች በሚያመልኩት ነገር ወደ ክርስቶስ ተጠርተዋል ፣ የዙሐል ጣዖት ይከበርበት የነበረውን ዕለት ከክርስትና በኋላ በእስክንድርያ የቅዱስ ሚካኤል በዓል ቀን ሆኗል። 👉የራሳችንን የገና ባሕላዊ አከባበሮች የገና ጨዋታን ፣ ቀጤማ መጎዝጎዝ የመሳሰሉትን ማክበር ይገባናል። ከዚያ ውጪ በክርስትና መንፈስ እስከተቃኘና የጌታን በበረት መወለድ ፣ የሰብአ ሰገልን ጉዞ ፣ ከዋክብቱን ፣ የመላእክትን ዝማሬ ፣ የእረኞችን ደስታ ፣ የሰብአ ሰገልን እጅ መንሻ የሚያሳይ እስከሆነ ድረስ የኛ ባሕል ያልሆነውን ሁሉ ጣዖት ነው ብሎ ማንቋሸሽ ፣ የሚያምር ነገርን ሁሉ ማውገዝ ያስመስላል። ቅዱስ ኒቆላስም የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የምትዘክረው ቅዱስ ስለሆነ አጋጣሚውን ጻድቁን ለማስተዋወቅም ልንጠቀምበት ይገባል። ሥጦታም የምንሠጣጠው የሰብአ ሰገልን ሥጦታ መነሻ አድርገን ሲሆን ልግስናውን ለነዳያን ብናደርገው የበለጠ በረከት እንቀበልበታለን። ✍በዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ✞🌾 🕊 #ቅዱስ_ተክለ_ሃይማኖት_ሐዋርያዊ 🕊 ታኅሳስ  ፳፬ [24] 🌾✞ #ልደት መልካም ዛፍ መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን የወለዱት ደጋጉ ጸጋ ዘአብ  ካህኑና  እግዚእ ኃረያ ናቸው። እርሱ በክህነቱ እርሷ በደግነቷ በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ ፍሬን ሰጥቷቸዋል:: በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ ቢደርስባቸው  ቅዱስ ሚካኤል ጸጋ ዘአብን ከሞት እግዚእ ኃረያን ከትድምርተ አረሚ [ ከአረማዊ ጋብቻ ] አድኗቸዋል። በኋላም የቅዱሱን መወለድ አብስሯቸዋል። አቡነ ተክለ ሃይማኖት የተጸነሱት መጋቢት 24, 1196 ዓ/ም ሲሆን የተወለዱት ታሕሳስ 24, 1197 ዓ/ም ነው። በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት ተገልጸዋል። ቤታቸውም በበረከት ሞልቷል። 🌾✞ #ዕድገት የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው "ፍሥሃ ጽዮን " ይሰኛል። ይሕንን ስም ይዘው አባታቸው ጸጋ ዘአብን ተከትለው አድገዋል። በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን [ብሉያት ሐዲሳትን] ተምረዋል። በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል። ዲቁና ከወቅቱ ዻዻስ አባ ጌርሎስ  ተቀብለዋል። 🌾✞ #መጠራት አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮን ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ ተሰማ። የክብር ባለቤት  ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላእክት እያመሰገኑ በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ። የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ፤ " ከዛሬ ጀምሮ ስምህ ተክለ ሃይማኖት [ ተክለ ሥላሴ ] ይሁን። አራዊትን ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ። ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ" ብሎ በግርማ ዐረገ። ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ ጊዜ በኋላሰዓትን አላጠፉም። ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ ይዘው ቤታቸው እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ። 🌾✞ #አገልግሎት ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዻዻሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል አገልግሎትን ጀመሩ። በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ [ ጽላልሽ ] አካባቢ ብቻ በ ፲ ሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው አጠመቁ። ያን ጊዜ ኢትዮዽያ ፪ መልክ ነበራት። ፩. ዮዲት [ ጉዲት ] በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽዕኖ ወደ ደቡብ አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዷል ወይም በባዕድ አምልኮ ተጠምዷል። ፪. ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር። ግማሹ ሃገር በጨለመበት ወቅት የደረሱት  ሐዲስ ሐዋርያ አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ። ሕዝቡን መሣፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው ማርያኖችን [ ጠንቁዋዮችን ] አጥፍተዋል። 🌾✞ #ገዳማዊ_ሕይወት ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮዽያን ከማብራታቸው ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል። እርሳቸው ከሁሉ የተሻሉ ሳሉም በ ፫ ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል። እነዚህም በአቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ለ፲፪ ዓመታት በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ ገዳም ለ ፯ ዓመታት በደብረ ዳሞ ከአቡነ ዮሐኒ  ጋር ለ ፯ ዓመታት በአጠቃላይ ለ፳፮ ዓመታት አገልግለዋል በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ በኋላም ወደ ምድረ ሽዋ ዞረሬ ተመልሰው በአንዲት በዓት ውስጥ ለ ፳፪ ዓመታት ቆመው ጸልየዋል። በተሰበረ እግራቸውም ፮ ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለ ፯ ዓመታት ጸልየዋል። 🌾✞ #ስድስት_ክንፍ ኢትዮዽያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከኢትዮዽያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት መካናት ተባርከዋል። ጻድቁ ምድረ እሥራኤል  የገቡት በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ: እያስተማሩና እያሳመኑ ነበር። የወቅቱ ሊቀ ዻዻሳት አባ ሚካኤል  ጋርም ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ በኋላ ነው ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ እንባቸው ይፈስ ነበር። ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም። 🌾✞ በገሃድ፦ - በቤተ መቅደስ ብስራቱን - በቤተ ልሔም ልደቱን - በቤተ ዮሴፍ ግዝረቱን - በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን - በቤተ አልዓዛር ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር። - የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል ወደሆነው  ቀራንዮ ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ ቢመለከቱት ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ። በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ  እመቤታችን ድንግል ማርያም ፈጥና ደርሳ ጻድቁን ወደሰማይ አሳረገቻቸው። 🌾✞ በዚያም፦ - የብርሃን ዐይን ተቀብለው - ፮ ክንፍ አብቅለው - የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው - ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው - ከ፳፬ቱ ካህናተ ሰማይም ተደምረው - ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው - "ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል። 🌾✞ #ተአምራት የጻድቁ ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው:: - ሙት አንስተዋል - ድውያንን ፈውሰዋል - አጋንንትን አሳደዋል - እሳትን ጨብጠዋል - በክንፍ በረዋል - ደመናን ዙፋን አድርገዋል - ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን መሥርተዋል። በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕጻናት አብረው ኑረዋል። በዘመናቸው ሰይጣን ታሥሯልና። 🌾✞ #ዕረፍት ጻድቅ ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን ሆነው መከራን በብዙ ተቀብለው አእላፍ ፍሬን አፍርተው በተወለዱ በ፺፱ ዓመት ከ ፰ ወር ከ ፩ ቀናቸው ነሐሴ ፳፬ በ1296 ዓ/ም ዐርፈዋል። ጌታ ድንግል ማርያምና ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል። ፲ ትውልድ የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል። የጻድቁ አባታችን ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት የቅድስናና የክብር ስሞች፦ ፩. ተክለ አብ፤ ተክለ ወልድ፤ ተክለ መንፈስ ቅዱስ ፪. ፍስሐ ፅዮን ፫. ሐዲስ ሐዋርያ ፬. መምሕረ ትሩፋት ፭. ካህነ ሠማይ ፮. ምድራዊ መልዐክ ፯. እለ ስድስቱ ክነፊሁ [ባለስድስት ክንፍ] ፰. ጻድቅ ገዳማዊ ፱. ትሩፈ ምግባር ፲. ሰማዕት ፲፩. የኢትዮዽያ መነኮሳት አለቃ ፲፪. ፀሐይ ዘበፀጋ ፲፫. የኢትዮዽያ ብርሃኑዋ ፲፬. ብእሴ እግዚአብሔር [የእግዚአብሔር ሰው] ፲፭. መናኒ ፲፮. ኤዺስ ቆዾስ [እጨጌ] እነዚህ የአባታችን ስሞች እንደዘመኑ ሰው ለመሞጋገስ የወጡ ሳይሆኑ ሁሉም በትክክል ሥራዎቹንና ለቤተ ክርስቲያን የሆነላትን የሚያዘክሩ ናቸው። እንኳን ለአባታችን ለቅዱስ ተክለ ሐይማኖት የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ !!!

የአምላክ እናት ድንግል ማርያም ሆይ እወድሻለሁ። ድንግል ሆይ አንቺን የሰደበ ሰው እንዴት ይኖራል፤ አይኖርም እንጂ። ምክንያቱም በልጅሽ የፍርድ መጽሐፍ ላይ እናት አባቱን የሰደበ ሰው ይሙት ይላልና፤
የአምላክ እናት ድንግል ማርያም ሆይ እወድሻለሁ። ድንግል ሆይ አንቺን የሰደበ ሰው እንዴት ይኖራል፤ አይኖርም እንጂ። ምክንያቱም በልጅሽ የፍርድ መጽሐፍ ላይ እናት አባቱን የሰደበ ሰው ይሙት ይላልና፤ ታዲያ የአምላክን እናት ሰድቦማ እንዴት ይኖራል? አባ ፅጌ ድንግል

🌾✞ #በእምነታቸው_ዳኑ ✞🌾 https://t.me/EOTC2921 በእምነታቸው ዳኑ ከዚያ ነበልባል /፪/ አናንያ አዛርያ ሚሳኤል /፪/ ናቡከደነፆር ጨካኙ ንጉስ በባቢሎን ሀገር ጣዖት የሚያነግስ እያለ ስገዱ አማኙን ሲያምስ ወጣቶች ተነሱ በቅናት መንፈስ #አዝ ለሰራኸው ጣዖት አንሰግድም እያሉ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ልባቸውን ሞሉ የፈጠረን አምላክ ያድነናል ሲሉ አናንያ አዛርያ ሚሳኤል /፪/ #አዝ ነበልባል ነዲዱ እንዲያቃጥላቸው በጭካኔ መንፈስ አስወረወራቸው ገብተው ሲጸልዩ እቶን ሳይነካቸው መልአኩን ልኮ አበረደላቸው ገብርኤል /፪/ በመስቀሉ #አዝ እንደ ሦስቱ ህፃናት በእምነት ለሚቆው መልአኩን ይልካል እግዚአብሔር ሲረዳው እሳቱም ይበርዳል መልአኩ ሲነካው ገብርኤል /፪/ በመስቀል #አዝ 🎤ሊቀ መዘምራን ዓባይ አጥሌ

#እንደ_አናንያ ✞የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያንን አስተምሮና ስርዓት የጠበቁ የተለያዩ መርሃ ግብሮች በየቀኑ ወደናንተ ይቀርባሉ፡፡ ለጓደኞቻችን #Share በመድረግ የበረከት ተካፋይ እናድርጋቸው✞ ╭══•|❀:๑✞♡✞๑:❀|•══╮ @EOTC2921 ╰══•|❀:๑✞♡✞๑:❀|•══╯