en
Feedback
Hadiya zone communication

Hadiya zone communication

Open in Telegram

This is Hadiya Zone Govern. Comm. official Telegram channel. For more updates please visit Hadiya zone government communication affairs department facebook page

Show more
1 071
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
በደቡብ ክልል የሀዲያ ብሔር ዘመን መለወጫ የ"ያሆዴ" በዓልን ጨምሮ የ10 ብሔር ብሔረሰቦች ባህል፣ታሪክና ሀገር በቀል ዕውቀቶች ዙሪያ የተዘጋጁ ጥናትዊ ጽሑፎች ታትመው ተመረቁ የብዝሃ ባህል ዕሴቶችን በጥናትና ምርምር አስደግፎ በመሰነድ ለትውልድ ለማስተላለፍ እየሰራ መሆኑን የደቡብ ክልል ባህል ቱሪዝም ቢሮ ገልጿል።

Repost from N/a
ሰኔ 6/2015 ዓ.ም ለሀገር ልማትና ዕድገት ሚና የሚያበረክቱ ብዝሃ ባህላዊ እሴቶችን በማጥናትና የተጠኑትን በማስተዋወቅ ወደ ኢኮኖሚ ፋይዳነት መቀየር ያስፈልጋል_የዘርፉ የስራ ኃላፊዎች ለሀገር ልማትና ዕድገት ሚና የሚያበረክቱ ብዝሃ ባህላዊ እሴቶችን በማጥናትና የተጠኑትን በማስተዋወቅ ወደ ኢኮኖሚ ፋይዳነት መቀየር እንደሚያስፈልግ በደቡብና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልሎች የሚገኙ የባህልና ቱሪዝም ኃላፊዎች ተናገሩ። የስራ ኃላፊዎቹ ይህን ያሉት የደቡብ ክልል ባህል ቱሪዝም ቢሮ ባካሄደው 4ኛ ዙር ክልላዊ የጥናትና ምርምር ጉባዔ ነው። በጉባኤው ቢሮው የ10 ብሔር ብሔረሰቦችን ባህል፣ታሪክና ሀገር በቀል ዕውቀቶች ዙሪያ ከተባባሪ አካላት ጋር ያዘጋጀውን ጥናትና ምርምር በማሳተም ለምረቃ አብቅቷል። የሀዲያ ዞን ባህል ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ ታምሬ ኤርሚያስ እንዳሉት ሀዲያ የራሱ የሆኑና ለዘመናት ጠብቆ ያቆያቸው በርካታ ታሪካዊ፣ ባህላዊ እሴቶችና ቅርሶች አሉት። ከእነዚህም ውስጥ የማይዳሰስ ቅርስ የሆነው " ያሆዴ" የሀዲያ የዘመን መለወጫ በዓል አንዱ ነው። በዓሉ በይበልጥ ለምቶ እንዲከበር በዓሉ በውስጡ አካትቶ ከያዛቸው ባህላዊ እሴቶች ስፋትና ፋይዳ አኳያ ባህላዊ የማክበሪያ ስፍራ ተገንብቶለት የአደባባይ በዓል እንዲሆን ከማስቻል ጀምሮ እንዲተዋወቅና በዓለም የማይዳሰስ ቅርስነት እንዲመዘገብ የጥናትና ምርምር ስራ ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። የጥናትና ምርምሩ 4 ዓመት የፈጀ መሆኑን የገለፁት ኃላፊው ታትሞ ለምረቃ በመብቃቱ የሀዲያ ህዝብ ለዘመናት ጠብቆ ያቆያቸውን ባህልና ታሪክ ለትውልድ ከማሸጋገር አኳያ አሻራ ጥሎ የሚያልፍ ነው ብለዋል። የጉራጌ ዞን ባህል ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ መሠረት አመረጋ በበኩላቸው የብሔር ብሔረሰቦች ታሪክ፣ ባህልና ቋንቋ በጥናትና ምርምር ተደግፎ ለአንባቢ ማብቃት ማለት ታሪክን ለትውልድ ማሸጋገር ማለት ነው። ኃላፊዋ አክለውም እነዚህ በመሰነድ ለንባብ እያበቁ ያሉ የጥናትና ምርምር ስራዎች እየተቀየሩና እየተዛቡ ያሉ ጉዳዮችን በመቀየር እውነታን ከማስጠበቅ ረገድ ጉልህ ሚና አላቸው ብለዋል። በዞኑ የሚገኙ ህዝቦች በስራና በቁጠባ ባህል በስፋት የሚታወቁ ቢሆኑም ጥናትና ምርምር ተደርጎባቸውና ተሰንደው ሌሎች ብሔር ብሔረሰቦች እንዲጠቀሙበት ብሎም ለትውልድ እንዲሸጋገሩ በቂ ስራ ተሰርቷል ማለት አይቻልም። ከዚህ ረገድ በክልሉ ባህል ቱሪዝም ቢሮና በጉራጌ ዞን የልማት ማህበር ትብብር ታትሞ ለንባብ የበቃው የጉራጌ የስራና የቁጠባ ባህል መጽሐፍ አጋዥ ነው ብለዋል። የደቡብ ኦሞ ዞን ባህል ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ ማሞ ካይሲ በዞኑ የማህበረሰቡ ባህላዊ እሴት የሆኑ የተለያዩ ተረትና ምሳሌያዊ ንግግሮች በጥናትና ምርምር ተደግፈውና ተሰንደው ለንባብ መብቃታቸውን ይናገራሉ። በዞኑ 16 ብሔረሰቦች መኖራቸውን የተናገሩት ኃላፊው አንዳንዶቹ ብሔረሰቦቹ እያሉ ቋንቋቸው የመጥፋት አደጋ የተደቀነባቸው ያሉ ብሔረሰቦች መኖራቸውን ይናገራሉ። ለአብነት የብራይሌ እና አንጎታ ብሔረሰብ ቋንቋ እየጠፉ አደጋ ያለ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው። በቋንቋና ሀገር በቀል ዕውቀቶች ላይ ትኩረት ያደረጉ ጥናትና ምርምሮች እነዚህ ቋንቋዎች እንዳይጠፉ ለመታደግ ያግዛል ነው ያሉት። በምሁራንና በዘርፉ ባለሙያዎች የሚደረጉ ጥናትና ምርምሮች በቀጣይ በስርዓተ ትምህርት ላይ የሚካተቱበት ሁኔታ ሊፈጠር ይገባል ሲሉ አስተያየት ሰጥተዋል። በደቡብ ክልል ባህል ቱሪዝም ቢሮ ጥናትና ምርምር ተደርጎና ተሰንዶ ለንባብ ከበቁት መጽሐፍት መካከል በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ውስጥ የሚገኘው የናኦ ብሔረሰብ ይገኝበታል። ክልሎቹ ከዚህ ቀደም በጋራ በነበሩበት ወቅት የተጀመረው የናኦ ብሔረሰብ ባህልና ታሪክ ተሰንዶ ለንባብ በቅቷል። የህዝቦች ታሪክ፣ ባህልና ቋንቋ ላይ ጥናትና ምርምር ማድረግ ብሎም ማስተዋወቅ ወሳኝ ነው ያሉት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ም/ኃላፊ አቶ አክሊሉ ለማ ይህ ካልሆነ ወደ መደብዘዝና መጥፋት ሊያመራ እንደሚችል ገልጸዋል። በመሆኑ ያልተጠኑ ብዝሃ ባህላዊ እሴቶችን በማጥናት የተጠኑትን በማስተዋወቅና ወደ ኢኮኖሚ ፋይዳነት መቀየር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል። የደቡብ ክልል በርካታ ብሔር ብረሰቦች መገኛ እንደመሆኑ መገለጫቸው ብዙ የሆኑ የብዝሀ እሴቶች ባለቤት ነው ያሉት የክልሉ ባህል ቱሪዝም ቢሮ ምክትልና የባህል ዘርፍ ኃላፊ አቡቶ አኒቶ። እነዚህ ሀገረሰባዊ ሀብቶች የክልሉን ብሎም የሀገር መልካም ገጽታ ከመገንባት ረገድ ያላቸው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል። ቢሮው የብሔር ብሔረሰቦችን ታሪክ፣ ቋንቋ፣ባህላዊ እሴቶችን፣ ሀገር በቀል እውቀቶችን ፣ የቱሪዝም ሀብቶችና ሌሎችንም ሳይንሳዊ መርህ በመከተል የማጥናት የማልማት ብሎም የማስተዋወቅና የመጠበቅ ኃላፊነት አለበት ብለዋል። በዚህም አሉታዊ መጤና ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን በማስቀረት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እንደሚሰራ ተናግረዋል። ከዚህ አንጻር በክልሉ የተለያዩ ስራዎች መሰራታቸውን የገለፁት አቶ አቡቶ በዓመቱ የ10 ብሔር ብሔረሰቦችን ብዝሃ እሴት በጥናትና ምርምር በማስደገፍ ብሎም በማሳተም ለምረቃ ማብቃቱን ገልጸዋል። የዘርፉ የስራ ኃላፊዎች በቀጣይም መሰል ጥናትና ምርምሮችን በማካሄድ ብሎም በመሰነድ የማስተዋወቅና የማልማት ስራዎች እንደሚሰሩ ጠቁመዋል። የሃዲያ ዞ/መ/ኮ

Repost from N/a
photo content
+6

photo content
+6

ለሀገር ልማትና ዕድገት ሚና የሚያበረክቱ ብዝሃ ባህላዊ እሴቶችን በማጥናትና የተጠኑትን በማስተዋወቅ ወደ ኢኮኖሚ ፋይዳነት መቀየር ያስፈልጋል_የዘርፉ የስራ ኃላፊዎች ሰኔ 6/2015 ዓ.ም (የሀዲያ ዞን መ/ኮ/ጉ/መምሪያ) ለሀገር ልማትና ዕድገት ሚና የሚያበረክቱ ብዝሃ ባህላዊ እሴቶችን በማጥናትና የተጠኑትን በማስተዋወቅ ወደ ኢኮኖሚ ፋይዳነት መቀየር እንደሚያስፈልግ በደቡብና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልሎች የሚገኙ የባህልና ቱሪዝም ኃላፊዎች ተናገሩ። የስራ ኃላፊዎቹ ይህን ያሉት የደቡብ ክልል ባህል ቱሪዝም ቢሮ ባካሄደው 4ኛ ዙር ክልላዊ የጥናትና ምርምር ጉባዔ ነው። በጉባኤው ቢሮው የ10 ብሔር ብሔረሰቦችን ባህል፣ታሪክና ሀገር በቀል ዕውቀቶች ዙሪያ ከተባባሪ አካላት ጋር ያዘጋጀውን ጥናትና ምርምር በማሳተም ለምረቃ አብቅቷል። የሀዲያ ዞን ባህል ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ ታምሬ ኤርሚያስ እንዳሉት ሀዲያ የራሱ የሆኑና ለዘመናት ጠብቆ ያቆያቸው በርካታ ታሪካዊ፣ ባህላዊ እሴቶችና ቅርሶች አሉት። ከእነዚህም ውስጥ የማይዳሰስ ቅርስ የሆነው " ያሆዴ" የሀዲያ የዘመን መለወጫ በዓል አንዱ ነው። በዓሉ በይበልጥ ለምቶ እንዲከበር በዓሉ በውስጡ አካትቶ ከያዛቸው ባህላዊ እሴቶች ስፋትና ፋይዳ አኳያ ባህላዊ የማክበሪያ ስፍራ ተገንብቶለት የአደባባይ በዓል እንዲሆን ከማስቻል ጀምሮ እንዲተዋወቅና በዓለም የማይዳሰስ ቅርስነት እንዲመዘገብ የጥናትና ምርምር ስራ ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። የጥናትና ምርምሩ 4 ዓመት የፈጀ መሆኑን የገለፁት ኃላፊው ታትሞ ለምረቃ በመብቃቱ የሀዲያ ህዝብ ለዘመናት ጠብቆ ያቆያቸውን ባህልና ታሪክ ለትውልድ ከማሸጋገር አኳያ አሻራ ጥሎ የሚያልፍ ነው ብለዋል። የጉራጌ ዞን ባህል ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ መሠረት አመረጋ በበኩላቸው የብሔር ብሔረሰቦች ታሪክ፣ ባህልና ቋንቋ በጥናትና ምርምር ተደግፎ ለአንባቢ ማብቃት ማለት ታሪክን ለትውልድ ማሸጋገር ማለት ነው። ኃላፊዋ አክለውም እነዚህ በመሰነድ ለንባብ እያበቁ ያሉ የጥናትና ምርምር ስራዎች እየተቀየሩና እየተዛቡ ያሉ ጉዳዮችን በመቀየር እውነታን ከማስጠበቅ ረገድ ጉልህ ሚና አላቸው ብለዋል። በዞኑ የሚገኙ ህዝቦች በስራና በቁጠባ ባህል በስፋት የሚታወቁ ቢሆኑም ጥናትና ምርምር ተደርጎባቸውና ተሰንደው ሌሎች ብሔር ብሔረሰቦች እንዲጠቀሙበት ብሎም ለትውልድ እንዲሸጋገሩ በቂ ስራ ተሰርቷል ማለት አይቻልም። ከዚህ ረገድ በክልሉ ባህል ቱሪዝም ቢሮና በጉራጌ ዞን የልማት ማህበር ትብብር ታትሞ ለንባብ የበቃው የጉራጌ የስራና የቁጠባ ባህል መጽሐፍ አጋዥ ነው ብለዋል። የደቡብ ኦሞ ዞን ባህል ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ ማሞ ካይሲ በዞኑ የማህበረሰቡ ባህላዊ እሴት የሆኑ የተለያዩ ተረትና ምሳሌያዊ ንግግሮች በጥናትና ምርምር ተደግፈውና ተሰንደው ለንባብ መብቃታቸውን ይናገራሉ። በዞኑ 16 ብሔረሰቦች መኖራቸውን የተናገሩት ኃላፊው አንዳንዶቹ ብሔረሰቦቹ እያሉ ቋንቋቸው የመጥፋት አደጋ የተደቀነባቸው ያሉ ብሔረሰቦች መኖራቸውን ይናገራሉ። ለአብነት የብራይሌ እና አንጎታ ብሔረሰብ ቋንቋ እየጠፉ አደጋ ያለ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው። በቋንቋና ሀገር በቀል ዕውቀቶች ላይ ትኩረት ያደረጉ ጥናትና ምርምሮች እነዚህ ቋንቋዎች እንዳይጠፉ ለመታደግ ያግዛል ነው ያሉት። በምሁራንና በዘርፉ ባለሙያዎች የሚደረጉ ጥናትና ምርምሮች በቀጣይ በስርዓተ ትምህርት ላይ የሚካተቱበት ሁኔታ ሊፈጠር ይገባል ሲሉ አስተያየት ሰጥተዋል። በደቡብ ክልል ባህል ቱሪዝም ቢሮ ጥናትና ምርምር ተደርጎና ተሰንዶ ለንባብ ከበቁት መጽሐፍት መካከል በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ውስጥ የሚገኘው የናኦ ብሔረሰብ ይገኝበታል። ክልሎቹ ከዚህ ቀደም በጋራ በነበሩበት ወቅት የተጀመረው የናኦ ብሔረሰብ ባህልና ታሪክ ተሰንዶ ለንባብ በቅቷል። የህዝቦች ታሪክ፣ ባህልና ቋንቋ ላይ ጥናትና ምርምር ማድረግ ብሎም ማስተዋወቅ ወሳኝ ነው ያሉት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ም/ኃላፊ አቶ አክሊሉ ለማ ይህ ካልሆነ ወደ መደብዘዝና መጥፋት ሊያመራ እንደሚችል ገልጸዋል። በመሆኑ ያልተጠኑ ብዝሃ ባህላዊ እሴቶችን በማጥናት የተጠኑትን በማስተዋወቅና ወደ ኢኮኖሚ ፋይዳነት መቀየር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል። የደቡብ ክልል በርካታ ብሔር ብረሰቦች መገኛ እንደመሆኑ መገለጫቸው ብዙ የሆኑ የብዝሀ እሴቶች ባለቤት ነው ያሉት የክልሉ ባህል ቱሪዝም ቢሮ ምክትልና የባህል ዘርፍ ኃላፊ አቡቶ አኒቶ። እነዚህ ሀገረሰባዊ ሀብቶች የክልሉን ብሎም የሀገር መልካም ገጽታ ከመገንባት ረገድ ያላቸው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል። ቢሮው የብሔር ብሔረሰቦችን ታሪክ፣ ቋንቋ፣ባህላዊ እሴቶችን፣ ሀገር በቀል እውቀቶችን ፣ የቱሪዝም ሀብቶችና ሌሎችንም ሳይንሳዊ መርህ በመከተል የማጥናት የማልማት ብሎም የማስተዋወቅና የመጠበቅ ኃላፊነት አለበት ብለዋል። በዚህም አሉታዊ መጤና ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን በማስቀረት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እንደሚሰራ ተናግረዋል። ከዚህ አንጻር በክልሉ የተለያዩ ስራዎች መሰራታቸውን የገለፁት አቶ አቡቶ በዓመቱ የ10 ብሔር ብሔረሰቦችን ብዝሃ እሴት በጥናትና ምርምር በማስደገፍ ብሎም በማሳተም ለምረቃ ማብቃቱን ገልጸዋል። የዘርፉ የስራ ኃላፊዎች በቀጣይም መሰል ጥናትና ምርምሮችን በማካሄድ ብሎም በመሰነድ የማስተዋወቅና የማልማት ስራዎች እንደሚሰሩ ጠቁመዋል። በይዲድያ ተስፋሁን

photo content
+3

የሀዲያ ብሔር ዘመን መለወጫ የ"ያሆዴ" በዓል ጥናታዊ ጽሑፍ ተመርቆ ለንባብ በቃ ሰኔ 6/2015 ዓ.ም (የሀዲያ ዞን መ/ኮ/ጉ/መምሪያ) ጥናታዊ ጽሑፉ የደቡብ ክልል ባህል ቱሪዝም ቢሮ በቡታጅራ ከተማ ባካሄደው 4ኛ ዙር ክልላዊ የጥናትና ምርምር ጉባዔ ነው ተመርቆ ለንባብ የበቃው። ጥናታዊ ጽሑፉም በደቡብ ክልል ባህል ቱሪዝም ቢሮ፣ በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲና በሀዲያ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ትብብር የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል። የደቡብ ክልል ባህል ቱሪዝም ቢሮ ባካሄደው 4ኛ ዙር የጥናትና ምርምር ጉባዔ የ10 ብሔር ብሔረሰቦች ባህል፣ታሪክና ሀገር በቀል ዕውቀቶች ዙሪያ ከተባባሪ አካላት ጋር ያዘጋጀውን ጥናትና ምርምር በማሳተም ለምረቃ አብቅቷል። ለምረቃ ከበቁት ውስጥ "ያሆዴ" የሀዲያ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል ጥናታዊ ጽሑፍ አንዱ ነው። ጥናታዊ ጽሑፉ የክብረ በዓሉ ምንነትና ታሪካዊ አመጣጥ፣ የያሆዴ አከባበር ስርዓትና ባህላዊ ክዋኔዎች፣ ትሩፋቶቹ እንዲሁም የቀጣይ አቅጣጫ መሠረት አድርጎ የተዘጋጀ ሲሆን እንደመነሻነትም የሀዲያ ታሪክ፣ባህል፣ ቋንቋና ባህላዊ አስተዳደር ስርዓት ተካቶበታል። በጥናታዊ ጽሑፉ በአዘጋጅነት ከተሳተፉት መካከል በዋቸሞ ዩኒቨርስቲ የማህበረሰብ ሳይንስ መምህርና ተመራማሪ አቶ መለሰ አቢዴ እንዳሉት ጥናታዊ ጹሑፉ በበዓሉ አከባበር ላይ ያሉ የመረዳዳት፣ የመጠያየቅን ጨምሮ ሌሎች ቱባ ባህላዊ እሴቶች ሳይደበዝዙ ለትውልድ እንዲሸጋገር የሚያስችል ነው። ከዛ ባሻገር ስለ ብሔሩ የዘመን መለወጫ ያሆዴ በዓል ሌሎች ተመራማሪዎች የተለያዩ የጥናትና ምርምር ስራዎችን እንዲሰሩ መነሻ በመሆን ያገለግላል ነው ያሉት። የሀዲያ ዞን ባህል ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ ታምሬ ኤርሚያስ በበኩላቸው ሀዲያ የራሱ የሆኑና ለዘመናት ጠብቆ ያቆያቸው በርካታ ታሪካዊ፣ ባህላዊ እሴቶችና ቅርሶች አሉት። ከእነዚህም ውስጥ የማይዳሰስ ቅርስ የሆነው " ያሆዴ" የሀዲያ የዘመን መለወጫ በዓል አንዱ ነው። በዓሉ በይበልጥ ለምቶ እንዲከበር በዓሉ በውስጡ አካትቶ ከያዛቸው ባህላዊ እሴቶች ስፋትና ፋይዳ አኳያ ባህላዊ የማክበሪያ ስፍራ ተገንብቶለት የአደባባይ በዓል እንዲሆን ከማስቻል ጀምሮ እንዲተዋወቅና በዓለም የማይዳሰስ ቅርስነት እንዲመዘገብ የጥናትና ምርምር ስራ ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። የጥናትና ምርምሩ 4 ዓመት የፈጀ መሆኑን የገለፁት ኃላፊው ታትሞ ለምረቃ በመብቃቱ የሀዲያ ህዝብ ለዘመናት ጠብቆ ያቆያቸውን ባህልና ታሪክ ለትውልድ ከማሸጋገር አኳያ አሻራ ጥሎ የሚያልፍ ነው ብለዋል። በቀጣይም መሰል ጥናትና ምርምሮችን በማካሄድ ብሎም በመሰነድ የማስተዋወቅና የማልማት ስራዎች እንደሚሰሩ ጠቁመዋል። ለምረቃ የበቃው የሀዲያ ዘመን መለወጫ የ ያሆዴ በዓል ጥናታዊ ጽሑፉ 147 ገጾች ያሉት ሲሆን 11 የዘርፉ ምሁራንና ባለሙያዎች በአዘጋጅነት፣ በአርታይነትና በአማካሪነት ተሳትፈዋል። በይዲድያ ተስፋሁን

ከተሞችን_በፕላን_በመምራት_ለዜጎች_ምቹ_ማድረግ_እንደሚገባ_ተገለጸ_ዘጋቢ፡_አለቃል_ደስታ_ከሆሳዕና_ጣቢያችን360p.mp410.85 MB

photo content

photo content
+9

ለተፈታኝ ተማሪዎች የስነ ልቦና ምክር አገልግሎት በመስጠት በሥነ ምግባር ተገንብተው በትምህርታቸው ከፍተኛ የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ የወላጅ ክትትል እና ድጋፍ እንደሚያስፈልግ እንዲሁም ተማሪዎችን ማብቃት የት/ቤት የመምህራን ብቻ ሳይሆን የወላጅም ኃላፊነት በመሆኑ በትምህርት ጥራት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለይቶ በሂደት ለመቅረፍ የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ትብብርን የሚጠይቅ በመሆኑ ኃላፊነታችንን እንወጣ ሲሉ መልክታቸውን አስተላልፈዋል። በካሳሁን አባይነህ

በዘንድሮው ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ዝግጅት እያደረግን ነው አሉ-- በሀዲያ ዞን የሊች ጎጎ ልዕቀት አዳሪ ት/ቤት ተማሪዎች ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ በ2015 ትምህርት ዘመን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የሚጠበቅባቸውን ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን በሀድያ ልማት ማህበር የሊች ጎጎ ልህቀት አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ገለፁ። የዞኑ ትምህርት መምሪያ የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ ብቁና ተወዳዳሪ ተማሪዎችን ለማፍራት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጾ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ፈተና ለሚወስዱ ተማሪዎች ከመደበኛ ትምህርት ውጪ የማጠናከሪያ ትምህርት በማዘጋጀት አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ ላይ እንደሆነም አስታውቋል፡፡ (ቀን05/9/2015 ዓ.ም ፤ የሀ/ዞ/የመ/ኮ/ጉ/መ) ተማሪ ሎምባሜ ለማ እና ተማሪ መልካሙ ፊሊጶስ በሀዲያ ዞን የሊች ጎጎ ልህቀት አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል ናቸው። ተማሪዎቹ ወደ ትምህርት ቤቱ የገቡት ከብዙ ተማሪዎች ጋር ተወዳድረው በተሰጠው የመግቢያ ፈተና የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ እንደሆነ ተናግረው የትምህርት ቤቱ ትምህርት አሰጣጥ ሀሳባችንን ከሚሰርቁና ከሚያዘናጉ ነገሮች ተነጥለን ሙሉ ትኩረታችንን በትምህርታችን ላይ ብቻ እንድናደርግ አስችሎናል ይላሉ። የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ተፈታኝ እንደመሆናቸው ከፍተኛ ውጤት ለማስመዝገብ በክፍል ከሚሰጠው ትምህርት፣ በግል ተነሳሽነት ከሚያደርጉት ጥረት ባሻገር በት/ቤቱ የማካካሻና ማጠናከሪያ መርሃ ግብር ተዘጋጅቶ ትምህርት እየተሰጣቸው መሆኑን ገልጸዋል። ተማሪዎቹ በግልና በህብረት ርስበርስ በመማማር ቅድመ ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ገልጸዉ ይህም ለፈተና ውጤት ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክትላቸውም ተናግረዋል። ተማሪዎቹ አያይዘውም ትምህርት ቤቱ ከተከፈተ አዲስ ቢሆንም አስፈላጊ ነገሮችን አቅም በፈቀደ መጠን ለማመቻቸት የሚያደርገው እንቅስቃሴ ጥሩ ሆኖ በቀጣይ በቤተ መጽሐፍት ተጨማሪ አስፈላጊ መፅሀፍትን ለሟሟላት ጥረት ሊደረግ ይገባል ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ መምህር ፀደቀ ነጋሽ በአዳሪ ትምህርት ቤቱ የሂሳብ ትምህርት አስተማሪ ናቸው። መምህር ፀደቀ በትምህርት ቤቱ ማስተማር ከጀመሩ አራት እንደሆናቸው ጠቅሰው በቆይታ ግዜያቸው የተማሪዎቹ የትምህርት አቀባበልና ያላቸው ፍላጎት እንዲሁም በየዓመቱ በክፍል የሚያስመዘግቡት ውጤት እየተሻሻለ መምጣቱን ተናግረዋል። አዳሪ ትምህርት ቤቱ በዘንድሮው የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን ለመጀመሪያ ጊዜ የሚያስፈትን እንደመሆኑ ተፈታኝ ተማሪዎቹ ከፍተኛ ውጤት ማስመዘገብ ይችሉ ዘንድ ከመደበኛ የመማር ማስተማር ሥራ ጎን ለጎን የማጠናከሪያና የማካካሻ ትምህርት በመስጠት አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል። ተማሪዎቹ አሁን ላይ ባላቸው ብቃትና ተነሳሽነት ቀሪ ጊዜያቸውን ባግባቡ ተጠቅመው በቂ ዝግጅት አድርገው በሚሰጠው አገር አቀፍ ፈተና ከፍተኛና የተሻለ ውጤት ሊያስመዘግቡ እንደሚችሉ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡ የልች ጎጎ ልህቀት አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር አቶ ተከተል ሱሞሮ በበኩላቸው ትምህረት ቤቱ በ2015 ዓመት ምህረት ለመጀመሪያ ጊዜ 36 ተማሪዎች የ 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና እንደሚያስፈትን ጠቁመው ተማሪዎቹም ከፍተኛና የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ለማስቻል ፤ ከመደበኛ ትምህርት ክፍለ ግዜ ከሚሰጠው ትምህርት ሰዓት ውጪ ከ 9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች የተመረጡ የትምህርት ይዘቶች ክለሳ፣ የቤተ ሙከራ ልምምድ ፣የቤተ መፅሐፍት ንባብ ምሽትን ጨምሮ ፣በማደሪያ ክፍላቸው የጥናት አደረጃጀት መፍጠር ፣የሞዴል ፈተና ትንተና፣ ሀገር አቀፍ ፈተናዎች ክለሳ እና ስነ ልቦናዊ ዝግጅት በመምህራን ልዩ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን አብራርተዋል ። ርዕሰ መምህሩ አክለው ተፈታኝ ተማሪዎች በራሳቸው የሚተማመኑ ብቁና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል ከመማር ማስተማሩ ተግባር በተጨማሪ በባለሙያ የተደገፈ የሥነ ልቦና ምክር አገልግሎትና የሕይወት ክህሎት ስልጠና እየተሰጣቸው መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ የሊች ጎጎ ልህቀት አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ከ 9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ሴት 30 ወንድ 155 በድምሩ 188 ተማሪዎችን እያስተማረ የሚገኝ ሲሆን በሂደት የቅበላ አቅሙን በማሳደግ የሚያስተምራቸው ተማሪዎችን ቁጥር በየዓመቱ በማሳደግ 8 መቶ ለማድረስ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት እየተሰራ እንደሆነ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።፡ የሀድያ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ክባሞ ዴታሞ በበኩላቸው እንደገለፁት በዞኑ በሚገኙ ሁሉም ትምህርት ቤቶች የመማር ማስተማር ሂደቱን ምቹና የተሻለ በማድረግ የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ ብሎም የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል ከዚህ ቀደም የተሰሩ ምርጥ ተሞክሮችን አጠናክሮ በማስቀጠል እንዲሁም የታዩ ጉድለቶችን ለይቶ ለመቅረፍ ከትምህርት ዓመቱ ዝግጅት ምዕራፍ ጀምሮ ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ በቅንጅት የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ ናቸው ብለዋል። ኃላፊው አያይዘውም በአሁኑ ወቅት በዞኑ በሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሚማሩ የ12 ኛ ክፍል ተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ፈተና ወስደው የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ከመደበኛ ትምህርት ውጪ የማጠናከሪያ ትምህርት መርሃ ግብር ተዘጋጅቶ ወደ ተግባር መገባቱን ገልፀው። ለዚህ ተግባር ውጤታማነት መምህራን ከመደበኛ ክፍለ ጊዜያቸው በተጨማሪ ተማሪዎች ባስመዘገቡት ውጤት መሰረት ለይተው በማስተማር እንዲደግፏቸው እየተደረገ ይገኛል ብለዋል። የመምሪያው ኃላፊ ዶ/ር ክባሞ ከርዕሰ ጉዳዩ ጋር አያይዘው እንደገለፁት የሊች ጎጎ ልህቀት አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤትን ከማደራጀትና ከማጠናከር አንፃር በአፈጻፀማቸው የተሻሉ መምህራንን ከሟሟላት ረገድ መምሪያው ርብርብ ያደረገ ሲሆን በቀጣይም ተጠናክሮ ተግባር መሆኑን ገልፀዋል። የሀድያ ልማት ማህበርም ከፍተኛ በጀት በመመደብ በጣም አስፈላጊ የሆኑ ቁሶችንን ለሟሟላት ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም እንዲሁ የክልሉ ትምህርት ቢሮ፣ ዋቸሞ ዩኒቨርስቲ የጃፓን መንግስት ድጋፍ ማድረጋቸውን የጠቀሱ ሲሆን ይህ ማለት ትምህርት ቤቱ አዲስ ከመሆኑ አኳያ አስፈላጊ ግብዓቶችን አሟልቶ ከማደራጀት አንፃር የሚጠበቀው ደረጃ ላይ ደርሷል ማለት አይደለም። ይልቁንም ያለውን ጥሩ ጅምር አጠናክሮ በማስቀጠል ረገድ ትኩረት ሰጥቶ ባለድርሻ አካላትን አሳትፎ መስራት እንደሚገባ አንስተዋል፡፡ የትምህርት ቤቱ ተማሪዎች አሁናዊ ብቃት ጥሩና የተሻለ በመሆኑ በቀሪው ጊዜ ተጨማሪ ዝግጅት አድርገው በሀገር አቀፍ ደረጃ ውጤት እንዲያስመዘግቡ በት/ቤቱ የተጀመረው የማጠናከሪያ፣ የማካካሻ ትምህርትና ሌሎች ተግባራት ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ብለዋል። የመምሪያው ኃላፊ በመጨረሻም በዞኑ በመደበኛ መርሃ ግብር ብቻ ከ 17 ሺህ በላይ የአስራ ሁለተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች መኖራቸውን ጠቁመው፤

photo content
+9

አንስተዋል፡፡ የትምህርት ቤቱ ተማሪዎች አህናዊ ብቃት ጥሩና የተሻለ በመሆኑ በቀሪው ጊዜ ተጨማሪ ዝግጅት አድርገው በሀገር አቀፍ ደረጃ ውጤት እንዲያስመዘግቡ በት/ቤቱ የተጀመረው የማጠናከሪያ የማካካሻ ትምህርትና ሌሎች ተግባራት ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ብለዋል። የመምሪያው ኃላፊ በመጨረሻም በዞኑ በመደበኛ መርሃ ግብር ብቻ ከ 17 ሺህ በላይ የአስራ ሁለተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች መኖራቸውን ጠቁመው፤ ለተፈታኝ ተማሪዎች የስነ ልቦና ምክር አገልግሎት በመስጠት በሥነ ምግባር ተገንብተው በትምህርታቸው ከፍተኛ የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ የወላጅ ክትትል እና ድጋፍ እንደሚያስፈልግ እንዲሁም ተማሪዎችን ማብቃት የት/ቤት የመምህራን ብቻ ሳይሆን የወላጅም ኃላፊነት በመሆኑ በትምህርት ጥራት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለይቶ በሂደት ለመቅረፍ የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ትብብርን የሚጠይቅ በመሆኑ ኃላፊነታችንን እንወጣ ሲሉ መልክታቸውን አስተላልፈዋል።

photo content
+2

ጥራት ያለው ትምህርት በማቅረብ ተወዳዳሪ ተማሪዎችን በማፍራት የልህቀት ማዕከል ለመሆን ራዕይ ሰንቆ እየሰራ እንደሚገኝ በሀድያ ልማት ማህበር (ሀልማ) የሊች ጎጎ ልህቀት አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ገለፀ የት/ቤቱን የስራ እንቅስቃሴ በዞኑ የሚገኙ የሀድያ ልማት ማህበር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የስራ ኃላፊዎች ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ተዟዙረው የተመለከቱ ሲሆን በትምህርት ቤቱ የስራ እንቅስቃሴ አበረታች መሠረታዊ ለውጦች በመኖራቸውን በቀጣይ አስፈላጊ ግብዓቶችን በማሟላት ለማጠናከር በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡም ተናግረዋል። ።።።።።ሆሳዕና፣ የሀድያ ዞን የመን/ኮ/ጉ/መ።።።።።። የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር አቶ ተከተል ሱሞሮ ለጉብኝቱ ተሳታፊዎች ባደረጉት ገለፃ ትምህርት ቤቱ ጥራት ያለው ትምህርት በማቅረብ ተወዳዳሪ ተማሪዎችን በማፍራት የልህቀት ማዕከል ለመሆን ራዕይ ሰንቆ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ጠቁመው የሊች ጎጎ ልህቀት አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በ 2012 ዓ.ም በዞኑ ከሚገኙ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎችን አዎዳድረሮ የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ 45 ተማሪዎችን ተቀብሎ በ 9ኛ ክፍል የመማር ማስተማር ሰራዉን በይፋ መጀመሩን አስታውሰው በዘንድሮው ዓመት ለመጀመሪያ ጊዜ 31 ወንድና 5 ሴት በድምሩ 36 ተማሪዎችን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን ለማስፈተን ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ገልፀው የትምህርት ቤቱን የተለያዩ ክፍሎችን የስራ እንቅስቃሴን ገለፃ በመስጠት ያስጎበኙ ሲሆን በመስክ ምከታው የትምህርት ቤቱን የአይሲቲ ትምህርት መስጫ ማዕከል፣ ዲጅታል ላይብረሪን፣ የሳይንስ ትምህርቶች ( የባይሎጂ፣ የፊዚክስና የኬሚስትሪ ) ቤተ ሙከራዎችን ፣ ቤተ መጽሐፍ፣ የተማሪዎች ማደሪያና መመገቢያ ሕንጻ ክፍሎችን፣ የትምህርት መርጃ ማዕከልን፣ መማሪያ ክፍሎችን፣ የተማሪዎች ክልኒክ፣ የአስተዳደር ቢሮዎችን፣ አጠቃላይ የትቤቱን ውስጣዊ አደረጃጀትና የስራ እንቅስቃሴን እንደሁም ግንባታቸው እየተካሄዱ የሚገኙ ሕንፃዎችን እና ሌሎች ተያያዥ ተግባራትን ተዟዙረው ምልከታ አድርገዋል፡፡ የጉብኝቱ ተሳታፈዎችም በትምህርት ቤቱ ተዟዙረው በተመለከቱት የስራ እንቅስቃሴ አበረታች መሠረታዊ ለውጦች በመኖራቸውን ገልፀው በቀጣይ አስፈላጊ ግብዓቶችን በማሟላት ለማጠናከር በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡ ገልፀው ምላሽ እንዲሰጣቸው የተወሰኑ ጥያቄዎችን አስተያየቶችን አቅርበዋል፡፡ ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የት/ቤቱ ር/መ/ር ምላሽና ማብራሪያ ሲሰጡ እንደገለፁት ትምህርት ቤቱ ምንም እንኳን አዲስ ቢሆንም የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ አጋዥ የሆኑ ነገሮች በሂደት ሊሟሉ የሚችሉ አንድ አንድ ክፍተቶች ቢያጋጥሙትም የተለያዩ አማራጭ ዘዴዎችን በመጠቀም ተገቢ የመማር ማስተማር ሂደትን በመተግበር በዕውቀትና ክህሎት የዳበሩ ስነ ምግባር የተላበሱ ብቁና ተወዳዳሪ ተማሪዎችን ለማፍራት ት/ቤቱ ከዞኑ አስተዳደር፣ ከሀድያ ልማት ማህበር፣ ከዋቸሞ ዩኒቨርስቲ፣ ከሆሳዕና መምህራን ትምህርት ኮሌጅ፣ ከጤና ሳይንስ ኮሌጅ፣ ከጃፖን መንግስት፣ ከዞኑ ትምህርት መምሪያ እና ሌሎች ከሚመለከታቸው መንግስታዊ ከሆኑና ካልሆኑ ድርጅቶች ባደረገው ቅንጅት ት/ቤቱን በአሰራር በአደረጃጀት በግብዓትና በሰው ኃይል በመደገፍ እንዲሁም በማጠናከር ረገድ ከተመሰረተ ጀምሮ ባለፉት ሶስት ዓመታት በርካታ ስራዎች መሰራታቸውንና እየተሰሩም እንደሆነ ተናግረው ለአብነትም ሲያብራሩ፡፡ ለአብነትም የጃፓን መንግስትና የዋቸሞ ዩኒቨርስቲ ዘመናዊ የአይሲቲና የትምህርት ማዕከልለና ዲጂታል ላይብረሪ መረጃ መሳሪዎችንና እንዲሁም ለሌሎች አገልልግሎት የሚውሉ ክፍሎችን አካትቶ የያዘ አንድ ዘመናዊ ሕንጻ ከ 4 ሚሊዮን በላይ ወጪ በማስገንባት 38 ኮምፒዩተሮችንና ሌሎች ግብዓቶችን በማሟላት ተማሪዎችና መምህራን እንዲጠቀሙበት መደረጉን፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ከጃፓን መንግስት በተገኘ 5 መቶ ሺህ ብር ድጋፍ የባይሎጂ፣ የኬሜስትሪና ፊዝክስ ትምህርት ዓይነቶች የቤተ ሙከራ /ላቦራቶሪ/ አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ ኬሚካሎችን ለማሟላት ጠረት የተደረ መሆኑን እንዲሁም ዋቸሞ ዩኒቨርስቲ፣ ሆሳዕና መምህራን ትምህርት ኮሌጅና ሆሳዕና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ቤተ ሙከራዎችን ለማደራጀት ያሚያግዙ የተለያዩ ግብዓቶችን በሟመዋላት ረገድ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል፡፡ የሀድያ ልማት ማህበር /ሀልማ/ የመማር ማስተማር ተግባር በይበልጥ ውጤታማ እንዲሆን አስፈላጊ ግብዓቶችን ለማሟላት በሚደረገው ጥረት ለድጂታል ላይብረሪው ብሎም ለአጠቃላይ ት/ቤቱ መማር ማስተማር ስራ እንዲያገለግል ከ 1 መቶ 30 ሺህ ብር በላይ ወጪ በማድረግ ብሮድ ባንድና ዋይ ፋይ ኢንተርኔት መስመር ተዘርግቶ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑ፡፡ እንዲሁም ልማት ማህበሩ ከ 1 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት በመመደብ መብራት በሚጠፋ ጊዜ የመማር ማስተማሩ ሂደት እንዳይደናቀፍ እንዲሁም ምሽት ላይ ተማሪዎች እንዳይቸገሩ በት/ቤቱ የሚገኙ ሕንፃዎችን በሙሉ ተደራሽ በማድረግ የመብራት አገልግሎት መስጠት የሚችል አቅም ያለው ትልቅ ዘመናዊ የመብራት ጀነሬተር ገዝቶ ላገልግሎት ማብቃቱ፤ ከዚህ በተጨማሪም ልማት ማህበሩ ቤተ መጽሐፍቱን ለማደራጀት በየግዜው የተለያዩ አጋዥ መጽሐፍትንና ሌሎች ግብዓቶችን በማሟላት የተማሪዎችን የምግብ የማደሪያና ሌሎች የትምህርት ወጪዎችን በመሸፈን ከፍተኛ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ የት/ቤቱ ርዕሰ መ/ር አብራርተዋል፡፡ የልማት ማህበሩ ሰራተኛ የሆኑት ዳኛ በቀለ ለሌ በበኩላቸው ትምህርት ቤቱ ተቀብሎ የሚያስተምራቸው ተማሪዎች በተመለከተ በሰጡት ገለፃ ት/ቤቱ በዞኑ ከሚገኙ ሁሉም ትምህርት ቤቶች 85 በመቶና ከዚያ በላይ ውጤት ያላቸውን ተማሪዎች በማወዳደር የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡትን ለይቶ ባለው ቦታ ልክ በዘጠነኛ ክፍል ተቀብሎ የሚያስተምር መሆኑን ጠቅሰው የአቀባበል ስርዓቱ ግልፅ ተገቢና ተቀባይነት ያለው ስራ እንዲሰራ የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ስራ በተቀመጠው የአራርና ደንብን መሰረት እየተሰራ እንደተመጣ አብራርተዋል፡፡ የሀድያ ልማት ማህበር ሀልማ ስራ አስኪያጅ አቶ አድነው ሎንሰቆ በመስክ ምልከታው ማጠቃለያ ላይ እንደገለፁት ማህበሩ የመንግስትን ክፋተቶች መሙላት በሚያስችሉ የትኩረት መስኮች በትምህርት፣ በጤና፣ በስራ እድል ፈጠራና በአካባቢ ጥበቃ አረንጓዴ ልማት ዘርፎች በመሰማራት የበኩሉን አስተዋፅኦ እያደረገ የሚገኝ የልማት ድርጅት መሆኑን ጠቁመዋል። የትምህርት ጥራትን ከማስጠበቅ አኳያ በዘርፉ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ ሲሆን የሊች ጎጎ የልህቀት አዳሪ ትምህት ቤት አንዱና ዋነኛው ተጠቃሽ በማለት የሊች ጎጎ የልህቀት አዳሪ ትምህርት ቤት የሀድያ ዞን አስተዳደርና የሀድያ ልማት ማህበር(ሀልማ) ትልቁና ቀጣይነት ያለው በዜጎች ላይ የሚሰራ የልማት ፕሮግራም ነው ሲሉ በመግለፅ ይህንኑም ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡

photo content