ኢቅረእ ኢስላማዊ መፅሀፍት መሸጫ
Open in Telegram
ኢቅረእ ኢስላማዊ መፅሀፍት መሸጫ የተለያዩ ኢስላማዊ ይዘት ያላቸው መፅሀፎችን በተመጣጣኝ ዋጋ ካሉበት ቦታ እናደርሳለን🚙። አድራሻችን፦ ጎንደር እና አዲስ አበባ @Abuhafss ሰ.ቁ 0918290961 0920960367 0703290961
Show more510
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
አስላሙዓለይኩም
እጃችንን ላይ ሚገኙ መፅሀፍቶ
1 ራስን ፍለጋ ቁ2
2 ትርፋማው ንግድ
3 ዘረኝነት ይብቃ
4 ኢትዮጲያዊያን ሙስሊሞች እና የመጅሊስ ፈተና
5 በህዋት የጠለሸው መጅሊስ
6 ቁርአናዊ ዘይቤ
7 የዘር ካርድ
8 የሀገር ሰላም
10 አደጋ ያንዣበበት ትውልድ
11 የፍቅር በረከት
12 ቁርአን አይጋጭም
13 ጀነት መግባት ትፈልጋልህ
15 ከአሏህ ጋር
16 ሂክማ
17 የፍልስፍና ጥበባት እና እስልምና
18 ጣፋጭ ታሪኮች
19 ልብህን አስመልስ
20 ፍኖተ ጀነት
21ለውጥ
22 ሸህ አብዱልቃድር ጀይላን
23 ኢባደቱል ሙእሚኒን
25 የውቀት ሀይል በኢስላም ቀ.2
26 የስኬት ቁልፍ
27 ኑ ረሱልን እንውደድ
29 ኢብኑ ተይሚያ
30 ከአሏህ ጋር
31ስለ ኢስላም
33 የሁለት አለም ጀነት
34 ቢስሚከ ነህያ
@iqera
ፀጋህን አብዝተህ ቸርከኝ
እኔግን አመስጋኝ መሆን ከበደኝ
ፈተንከኝ ታጋሽ መሆን አቃተኝ
ባለማመስገኔ የሰጠህኝን ፀጋ አልወሰድክብኝም
ባለመታገሴም ችግሬንም አላረዘምክንኝም
ጌታየ ሆይ ! ቸርነት የሚታሰበው ቸር ከሆነው አምላክ ነው
ንፉግነትና ስስትማ የሰው ባህሪ ነው
ቸርነትህ ምንኛ በዛ !!!
@iqera
የሁለት ዓልም ጀነት ከሚለው መፅሃፍ የተወሰደ
አስላሙዓለይኩም
እጃችንን ላይ ሚገኙ መፅሀፍቶ
1 ራስን ፍለጋ ቁ2
2 ትርፋማው ንግድ
3 ዘረኝነት ይብቃ
4 ኢትዮጲያዊያን ሙስሊሞች እና የመጅሊስ ፈተና
5 በህዋት የጠለሸው መጅሊስ
6 ቁርአናዊ ዘይቤ
7 የዘር ካርድ
8 የሀገር ሰላም
9 ቀዷ ወል ቀደር
10 አደጋ ያንዣበበት ትውልድ
11 የፍቅር በረከት
12 ቁርአን አይጋጭም
13 ጀነት መግባት ትፈልጋልህ
15 ከአሏህ ጋር
16 ሂክማ
17 የፍልስፍና ጥበባት እና እስልምና
18 ጣፋጭ ታሪኮች
19 ልብህን አስመልስ
20 ፍኖተ ጀነት
21ለውጥ
22 ሸህ አብዱልቃድር ጀይላን
23 ኢባደቱል ሙእሚኒን
24 የውቀት ሀይል በኢስላም ቀ.1
25 የውቀት ሀይል በኢስላም ቀ.2
26 የስኬት ቁልፍ
27 ኑ ረሱልን እንውደድ
29 ኢብኑ ተይሚያ
30 ከአሏህ ጋር
31ስለ ኢስላም
32 ልብህን አስመልስ
33 የሁለት አለም ጀነት
34 ቢስሚከ ነህያ
@iqera
ሕይወት ለጨለመበት መብራት ሁን፣
መንገድ የጠፋበትን ምራ፣
መላ ለቸገረው አመላክተው፣
መፍትሄ ላጣ ጠቁመው፣
ሐዘን የገባዉን አበርታው፣
የደከመዉን ደግፈህ አንሳው፣
ወደኃላ የቀረዉን በተስፋ ሙላው፣
እህእ ...
ሰዉን ያክል የተከበረ ፍጡር አውላላ ሜዳ ላይ አትተወው፣
ከቻልክ እጁን ይዘህ አንሳው፣ ካልሆነም ምርኩዝህን አቀብለው፣ ወይም በዚህ በኩል ነው መሄጃው ብለህ በእጅህ አመላክተው፣ ካልሆነም መልካም ቃላትን ተባበረው፣ ካቃተህ ፈገግታን በመለገስ እርዳው።
የሚገርመው ይህ ሁሉ እና ተመሳሳዩ ድርጊት ምንዳ ያለው ሶደቃ ነው። እናም በርትተህ መጽዉት።
ሌሎችን ስናኖር እንኖራለን፣ ሌሎችን ስንደግፍ እንቆማለን፣ ለሌሎች ስናበራ ይበራልናል። ፈገግ በልና የሌሎችን ፈገግታ መልስ።
አትጨክኑ፣ ተደጋገፉ፣ ዱንያ ለነዋሪዎቿ ገር ትሆን ዘንድ ካላችሁ ነገር አትሰስቱ።
ተመልሰናል....
በእውነቱ ለላጤ ክረምት የሚከብደዉን ያህል ለኔም ያለናንተ መኖር ከባድ ነው።
ሰባሐል ኸይር ቤተሰብ!
https://t.me/MuhammedSeidAbx
@iqera
አስላሙዓለይኩም
እጃችንን ላይ ሚገኙ መፅሀፍቶ
1 ራስን ፍለጋ ቁ2
2 ትርፋማው ንግድ
3 ዘረኝነት ይብቃ
4 ኢትዮጲያዊያን ሙስሊሞች እና የመጅሊስ ፈተና
5 በህዋት የጠለሸው መጅሊስ
6 ቁርአናዊ ዘይቤ
7 የዘር ካርድ
8 የሀገር ሰላም
9 ቀዷ ወል ቀደር
10 አደጋ ያንዣበበት ትውልድ
11 የፍቅር በረከት
12 ቁርአን አይጋጭም
13 ጀነት መግባት ትፈልጋልህ
15 ከአሏህ ጋር
16 ሂክማ
17 የፍልስፍና ጥበባት እና እስልምና
18 ጣፋጭ ታሪኮች
19 ልብህን አስመልስ
20 ፍኖተ ጀነት
21ለውጥ
22 ሸህ አብዱልቃድር ጀይላን
23 ኢባደቱል ሙእሚኒን
24 የውቀት ሀይል በኢስላም ቀ.1
25 የውቀት ሀይል በኢስላም ቀ.2
26 የስኬት ቁልፍ
27 ኑ ረሱልን እንውደድ
29 ኢብኑ ተይሚያ
30 ከአሏህ ጋር
31ስለ ኢስላም
32 ልብህን አስመልስ
33 የሁለት አለም ጀነት
34 ቢስሚከ ነህያ
35 ያአፍቃሪወች አለም
@iqera
አስላሙዓለይኩም
እጃችንን ላይ ሚገኙ መፅሀፍቶ
1 ራስን ፍለጋ ቁ2
2 ትርፋማው ንግድ
3 ዘረኝነት ይብቃ
4 ኢትዮጲያዊያን ሙስሊሞች እና የመጅሊስ ፈተና
5 በህዋት የጠለሸው መጅሊስ
6 ቁርአናዊ ዘይቤ
7 የዘር ካርድ
8 የሀገር ሰላም
9 ቀዷ ወል ቀደር
10 አደጋ ያንዣበበት ትውልድ
11 የፍቅር በረከት
12 ቁርአን አይጋጭም
13 ጀነት መግባት ትፈልጋልህ
14 ጣፋጭ ታሪኮች
15 ከአሏህ ጋር
16 ሂክማ
17 የፍልስፍና ጥበባት እና እስልምና
18 ጣፋጭ ታሪኮች
19 ልብህን አስመልስ
20 ፍኖተ ጀነት
21ለውጥ
22 ሸህ አብዱልቃድር ጀይላን
23 ኢባደቱል ሙእሚኒን
24 የውቀት ሀይል በኢስላም ቀ.1
25 የውቀት ሀይል በኢስላም ቀ.2
26 የስኬት ቁልፍ
27 ኑ ረሱልን እንውደድ
28 ኢስላም ወርቃማ ስልጣኔ
30 ከአሏህ ጋር
31ስለ ኢስላም
32 ልብህን አስመልስ
33 የሁለት አለም ጀነት
34 ቢስሚከ ነህያ
35 ያአፍቃሪወች አለም
@iqera
ለማንበብ 30 ምክንያቶች
ለምን እናነባለን?
1- ዕውቀትን ለመጨመር እናነባለን፣
2- ጊዜን በአግባቡ ለመጠቀም እናነባለን፣
3- ከድብርት ለመገላገል እናነባለን፣
4- እቤት ቁጭ ብለን ዓለምን ለመዞር እናነባለን፣
5- ለመዝናናት ብለን እንነባለን፣
6- የማስታወስ አቅማችን እንዲዳብር እናነባለን፣
7- ትዝታን ለማምጣት እናነባለን፣
8- ሥራ ላለመፍታት እናነባለን፣
9- ከሥራ ፈቶቸ ለመላቀቅ እናነባለን፣
10- መንፈሳችን እንዲታደስ እናነባለን፣
11- ለመሳቅ እናነባለን፣
12- ለመተከዝና ለመቆዘም እናነባለን፣
13- ከሀሳብ ለማምለጥ እናነባለን፣
14- በሰው ቦታ ሆነን ራሣችንን ለማየት እናነባለን፣
15- ተስፋን ለመሰነቅ እናነባለን፣
16- ባህሪያችንን ለማሻሻል እናነባለን፣
17- አዲስ ነገር ፍለጋ እናነባለን፣
18- የሰዉን እይታና አመለካከት ለማሰስ እናነባለን፣
19- በምናብ ለመዞር እናነባለን፣
20- የራሳችንን ታሪክ ከሌላ ሰው ለመስማት እናነባለን፣
21- ከብቸኝነት ለመውጣት እናነባለን፣
22- ለመነሳሳትና ለመበርታት እናነባለን፣
23- ስህ,ተታችንን ለማረም እናነባለን፣
24- ያነበብነዉን ለማካፈል እናነባለን፣
25- ከእንቶፈንቶ ወሬ ለመራቅ እናነባለን፣
26- ሌሎች እንዲያነቡ ለመገፋፋት እናነባለን፣
27- አዳዲስ ሰዎችንና ሀሳቦችን ለማግኘት እናነባለን፣
28- ያለንበትን ሁኔታ ለመቀየር እናነባለን፣
29- የቀደመዉንና ያለፈዉን ትውልድ ለማነፃፀር እናነባለን፣
30- ለመገረም እናነባለን፣
31- ኢማናችንን ለማሳደግ እናነባለን፡:
@iqera
ይህ መጽሐፍ ነገ ያኛዉን ጀነት ከማግኘትህ በፊት የምድር ላይ ሕይወትህን ጀነት አድርገህ ኑር የሚል መልዕክት አለው፡፡ በአላህ ተደሰት፣ ክፍፍሉን ዉደድ፣ በሲሳዩ አመስግን ይላል፡፡ በዚህ መልኩ እሱ የወደደልህን ከወደድክ፤ ክፍፍሉን ካመሰገንግና ደስተኛ ከሆንክ ዛሬ ደስተኛ ሆነህ ትኖራለህ፤ ነገ ደግሞ አላህ ብሎልህ ጀነት ከገባህ ደግሞ ሌላ ደስታ ይጠብቅሃል ማለት ነው፡፡ ዛሬን በደስታ ከኖርክ ነገም ደስታን ከተጎናፀፍን በሁለቱም ጀነት ዉስጥ ኖርክ ማለት ነው፡፡ ከዚህ አንጻርም በምድር ላይ እንዴት ደስተኛ ሆኖ መኖር አንደሚቻል፤ ቀደምት ደጋግ የአላህ ባሮች ደስተኛ ሆነው ስለኖሩበት ሚስጢር ይጠቁመናል፡፡
አዘጋጅ – ኻሊድ አቡ ሻዲ
ትርጉም – ሙሐመድ ሰዒድ
የገፅ ብዛት ፡ 168
የታተመበት ዓመት ፡ ሚያዚያ 2010
@iqera
ይዘት ፡ መጽሐፉ በአጠቃላይ ሀሳቡ ከአላህ ጋር የመሆንን አስፈላጊነት ያወሳል። ከአላህ ጋር ሲሆኑ የተመኙት ሁሉ እንደሚሳካ፣ ምድራዊ ደስታም ሆነ አኺራዊ ስኬት እንደሚገኝ ይገልፃል። ከአላህ ጋር መሆን ሲባል ሁሌ እሱን በማሰብ በሃሳብ ሊሆን ይችላል፣ እሱን በማውሳትና በማወደስ ሊሆን ይችላል፣ እሱን በሁሉም ነገር ውስጥ በማስገባት ሊሆን ይችላል፣ በቃልም ሆነ በተግባር አላህን በማስታወስ ሊሆን ይችላል፣ በአምልኮ ተግባራት በመበርታት ሊሆን ይችላል … ሌላም ሌላ።
መጽሐፉ ከአላህ ጋር የተኖሩ የሕይወት ተሞክሮዎችን በማነሳሳት ከአላህ ጋር መኖር ለሕይወታችን ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ የሚያስታውስ ነው።
አዘጋጁ በመጽሐፉ ዉስጥ ከሁሉ ነገር ውስጥ ከአላህ ጋር የመሆንን ፋይዳን ይሰብካል፤ ያመላክታል፣ ይጠቁማል። አስተዋሽ ሲጠፋ፣ ሃሳብ ሲገባን፣ ሲደብረን፣ ስልችት ሲለን፣ ሲጨንቀን፣ ስንባክን… ይህን መጽሐፍ እንድናነሳም ይመክራል።
አዘጋጅ ፡ ሙሐመድ ሰዒድ
የገጽ ብዛት ፡ 152
የታተመበት ዓመት ፡ ታህሳስ 2013
ወደ ነቢያችን የአላህን መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ.) ዉዴታ የሚጣራ መጽሐፍ ነው፡፡ ከዉልደት እስከ ህልፈት የነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ.) የሕይወት ታሪክም በመጠኑ ተዳሶበታል፡፡ መጽፉ የኡስታዝ ኢንጂነር በድሩ ሑሴንን የሲዲ ሥራ መሠረት ያደረገ ነው፡፡
መጽሐፉ በዋናነት ለነቢያችን (ሰ.ዐ.ወ) ያለንን ፍቅር ልኬታ ይጠይቃል፡፡ በነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ሕይወት ያጋጠሙ እውነታዎችን የነበራቸውን ተዓምራት፣ ስብእናቸውን፣ ለሰው ልጆች እና ለፍጡራን የነበራቸውን ፍቅር በንዑስ ርዕሶች እየከፋፈለ ያስነብበናል፡፡ እኛ ተከታዮቻቸው ለነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ያለን ፍቅር ምን ያህል እንደሆነም ይጠይቃል፡፡ በመጠየቅ ብቻ ሳይወሰን ለምን ልንወዳቸው እንደሚገባም ምላሹን ይሰጣል፡፡ መጽሐፉ ሲዲውን ለተመለከቱም ሆነ ላልተመለከቱ ጥሩ ግንዛቤን የሚያስጨብጥ ነው፡፡
ቅንብር ፡ ሙሐመድ ሰዒድ
የገጽ ብዛት ፡ 91
የታተመበት ዓመት ፡ ሐምሌ 2002
@iqera
ሸይኽ ዐብዱልቃድር ጂላኒ ታላቅ የሱፊ ሸይኽና የሸሪዓ ሊቅ ናቸው፡፡ በዘመናዊ ዓለም አስተሳሰብና ምልከታም ያላቸው አሻራ በቀላሉ የሚታለፍ አይደለም፡፡ በመዝሀብ ሐንበሊ ሲሆኑ በመንፈሳዊ ፈለግ የነበራቸው የጠለቀ ስልት ኢትዮጵያን ጨምሮ በበርካታ የዓለማችን ሀገራት ዘወትር እንዲታወሱ አብቅቷቸዋል፡፡
የቁርአን ተፍሲርን ጨምሮ የበረከቱ መንፈሳዊ መዛግብትንም አበርክተዋል፡፡ አንድ የፓኪስታን ታላቅ ተመራማሪ ከሀያ ዓመታት በላይ ረዥም ምርምር ካደረገ በኋላ በአንድነት አዋቅሮ ለህትመት ያበቃልን ተፍሲራቸው በአጭር ጊዜ ከፍተኛ ተቀባይነት አግኝቷል፡፡ ይህ ተፍሲር በ2001 ዓ.ል ለአንባቢያን ደርሷል፡፡
የነበረውን ወርቃማ የኢስላም የጥበብና ስልጣኔ ዘመን ለመመለስ ይቻል ዘንድ የዚያን ዘመን ወርቃማ ሰዎች በመጠኑም ቢሆን በዚህ መጽሐፍ ተዳሷል፡፡
አዘጋጅ ፡ ሙሐመድ ዐሊ
የገጽ ብዛት ፡ 92
የታተመበት ዓመት ፡ 2009
እስልምና በየጊዜው በርካታ ተግዳሮቶችን አልፏል፡፡ በየዘመኑም ትንታግ በሆኑ ሊቃዉንቶቹ ታግዞ በርካታ መሰናክሎችን ተሻግሯል፡፡ በኢስላም ታሪክ ዉስጥ ትልቅ የዕውቀት እና የተሃድሶ አሻራ ትተው ካለፉ ሙስሊም ልሂቃን መካከል ሸይኽ ኢብኑ ተይሚያ አንዱ ናቸው፡፡ የርሣቸው አመለካከት መንገድና አስተምህሮ ዛሬም ድረስ ትልቅ ተጽእኖ አለው፡፡ ኢብኑ ተይሚያን ጠበቅ ባለ አቋማቸው ብዙዎች ቢቃወሟቸውም ስለ ታላቅ ምሁርነታቸው ግን ጠላቶቻቸው ጭምር ይመሰክሩላቸዋል፡፡ የኢማሙን የዕውቀት እና የትግል ሕይወት ጊዜ ወስደን ብንዳስስ በርግጥም በርሣቸው ላይ ይቀርቡ የነበረ ክሶች የተንሻፈፉ፣ የተጋነኑ አሊያም መሠረተ ቢስ መሆናቸውን እንረዳለን፡፡ ወጣቱ አሰላሳይ ሙሐመድ ዐሊ (ቡርሃን) የተዘጋጀው ይህ መጽሐፍ ሚዛናዊ በሆነ መልኩ የኢብኑ ተይሚያን ማንነትና ተጋድለዎን ይዳስሳል፡፡
አዘጋጅ ፡ ሙሐመድ ዐሊ
የገጽ ብዛት ፡ 168
የታተመበት ዓመት ፡ 2009
“ልብህን አስመልስ” በእንግሊዘኛው”Reclaim your Heart” በዓለም አቀፍ ደረጃ እጅግ ተወዳጅና ተነባቢ ከሆኑ መጽሐፍት መካከል አንዱ ነው፡፡ ጸሐፊዋ በበርካታ የዳዕዋ ዲስኩሮችና ስልጠናዎቿ በርካታ ተከታታዮች ያላት እንስት ነች፡፡ መጽሐፉ በዋነኛነት ትኩረቱን ያደረገው በራስ እነጻ እና ዳግም ግንባታ ላይ ነው፡፡ በጥልቀት ወደ ማስተዋል፣ ራስን ወደ መመልከትና ለመታደስ ወደ መዘጋጀት ይጋብዛል፡፡ ነገሮችን በማስተንተን ከውድቀትና ከተስፋ መቁረጥ በኋላ እንዴት መነሳት እንደሚቻል ይጠቁማል፡፡ ጸሐፊዋ ከነባራዊ ሁኔታዎችና ከተለያዩ ገጠመኞቿና ከራሷ ታሪኮች በመነሳት እንዴት ከዱንያዊ ትብታቦች መላቀቅ እንደምንችል፤ ቁርአናዊ እና ሐዲሳዊ አስተምህሮቶችን በማጣቀስ ብዙ ሐሳቦችን ታነሳለች፡፡
የመጽሐፉ ርዕስ፡ ልብህን አስመልስ
አዘጋጅ፡ ያስሚን ሙጃሒድ
ትርጉም፡ ሙሐመድ ረሺድ እና ሙሐመድ ሰዒድ
የገጽ ብዛት፡ 183
@iqera
ፍቅር አላህ (ሱ.ወ) ለሰው ልጆችና ለእንስሳትም ጭምር በተፈጥሮ የለገሰው ታላቅ ፀጋ ነው፡፡ ፍቅር በሰው ልጆች መካከል ብቻ የማይወሰን፣ ፈጣሪንና ተፈጥሮን ማፍቀርን ጭምር የሚያጠቃልል ኃያል ስሜትና ተግባር ሆኖ እያለ ብዙውን ጊዜ በተለይም በተቃራኒ ፆታዎች መካከል ያለው ተፈጥሯዊና ስሜታዊ መፈላለግ ብቻ ፍቅር ተደርጎ ሲቀርብ ይስተዋላል፡፡ ይህ እጅግ የተሳሳተ ግንዛቤና አቀራረብ ነው፡፡ በኢስላማዊ አስተምህሮ ግን ፍቅር ዘርፈ ብዙ ሲሆን የመጀመሪያውና ፍጹማዊ ፍቅር የውበትና የምልኡነት ምንጭ የሆነውን ታላቁን ፈጣሪ ማፍቀር ነው፤ ፍቅር ሁሉ ከዚህ ፍቅር ይመነጫል፡፡ መጽሐፉ በአጠቃላይ ስለ ፍቅር ምንነትና መገለጫዎች ያወሳል፡፡ ስለ ፍቅር አስደናቂ ወጎችም ይዳስሳል፡፡ ያላስተዋልናቸዉን ጎኖችም ያስመለክታል፡፡ መጽሐፉ ‹‹ረውደቱል ሙሒቢይን ወ ኑዝሀቱል ሙተቂይን›› የተሠኘው የታላቁ ዓሊም የኢማም ኢብኑ ልቀይም አልጀውዚይ ሥራ ነው፡፡ ተርጓሚው አሳጥሮና ጨምቆ ለአገራችን አንባቢያን በሚመች መልኩ አቅርቦታል፡፡
ዝግጅት ፡ ኢማም ኢብኑል ቀይም
ትርጉም ፡ ጁነይድ ዐብዱልመንናን
የገጽ ብዛት ፡ 127
የታተመበት ዓመት ፡ ሚያዚያ 2007
@iqera
ይህ መጽሐፉ አንድ ሙእሚን የግዴታም ሆነ ሌሎች በፈቃደኝነት የሚፈፀሙ የአምልኮ ተግባራትን በምን መልኩ በማረና ለራሱ ጥቅምን በሚያስገኙለት መልኩ መፈጸም እንዳለበትና እንደሚችል ይጠቁመናል፡፡ ግዴታዎች ለመወጣት ብቻ የምንፈጽማቸውን የአምልኮ ተግባራት ሳይሆኑ ትርጉማቸውና ዓላማቸው ምን እንደሆነ ያብራራልናል፡፡ አምላካችንን አላህን (ሱ.ወ.) ይበልጥ እንድናውቅም ዕድል ይሰጠናል፡፡ የረሳነውን ያስታውሰናል፡፡ ከተዘናጋንበትም ያነቃናል፡፡ በዋናነት የሚያጠነጥነው በሶላት፣ ሐጅ፣ ዚክር፣ ዱዓ፣ ቁርኣንና ፆም ዙርያ ነው፡፡
አዘጋጅ ፡ ዶ/ር ዐምር ኻሊድ
ትርጉም ፡ ሙሐመድ ሰዒድ
@iqera
መጽሐፍ በቁጥር አንድ እና ሁለት የተዘጋጀ ነው፡፡ በዕውቀት ዙርያ አስፈላጊ የሆኑ ሊታወቁም የሚገቡ በርከት ያሉ በተለያየ ርዕስ ዙርያ የሚያተኩሩ መረጃዎች በተደራጀ መልኩ የታጨቁበት ነው፡፡ ዕውቀት ምን ያህል ኃያል እና አስፈላጊ እንደሆነ ያሳያል፡፡ ሙስሊሙ ለዕውቀት ያለው አመለካከት ከፍ እንዲል ይወተዉታል፡፡
አዘጋጅ ፡ ሙሐመድ ዑመር አደም
የገጽ ብዛት ፡ ቁጥር አንድ 231 ገፆች
ቁጥር ሁለት 112 ገፆች
የታተመበት ዓመት ፡ 2007
@iqera
1. አጠገባቹህ ስላለው ሰው መጥፎ ከመናገር ታቀቡ
2. ሌሎችን በአጉል ጥርጣሬ ከመያዝ ታረሙ
3. ሹክሹክታና ሀሜትን አስወግዱ
4. ሀራም የሆን ነገር ከመመኘት ተቆጠቡ
5. ምንግዜም እውነታን ብቻ ተናገሩ
6. ምንግዜም ፈጣሪን አመስጋኝ ሁኑ
7. በገንዘብ መረዳት ያለባቸውን ሚስኪኖች ለማገዝ ቁርጥ አቋም ያዙ
8. በምድር በያዛቹሁት ስልጣን እና ሀይል ጨቋኞች አትሁኑ
9. አምስት ወቅት ስግደቶችን በአግባቡ ስለ መስገድ ብርቱ ሁኑ
10. የነብዩን ሱና ስለሚጠበቅ እና ስለመተግበር ታጋዬች ሁኑ
ሸይህ አብዱልቃድር ጀይላን ከሚለው መፀሀፍ
@iqera
አስላሙዓለይኩም
እጃችንን ላይ ሚገኙ መፅሀፍቶ
1 ራስን ፍለጋ ቁ2
2 ትርፋማው ንግድ
3 ዘረኝነት ይብቃ
4 ኢትዮጲያዊያን ሙስሊሞች እና የመጅሊስ ፈተና
5 በህዋት የጠለሸው መጅሊስ
6 ቁርአናዊ ዘይቤ
7 የዘር ካርድ
8 የሀገር ሰላም
9 ቀዷ ወል ቀደር
10 አደጋ ያንዣበበት ትውልድ
11 የፍቅር በረከት
12 ቁርአን አይጋጭም
13 ጀነት መግባት ትፈልጋልህ
14 ጣፋጭ ታሪኮች
15 ከአሏህ ጋር
16 ሂክማ
17 የፍልስፍና ጥበባት እና እስልምና
18 ጣፋጭ ታሪኮች
19 ልብህን አስመልስ
20 ፍኖተ ጀነት
21ለውጥ
22 ሸህ አብዱልቃድር ጀይላን
23 ኢባደቱል ሙእሚኒን
24 የውቀት ሀይል በኢስላም ቀ.1
25 የውቀት ሀይል በኢስላም ቀ.2
26 የስኬት ቁልፍ
27 ኑ ረሱልን እንውደድ
28 ኢስላም ወርቃማ ስልጣኔ
29 ኢብኑ ተይሚያ
30 ከአሏህ ጋር
31ስለ ኢስላም
32 ልብህን አስመልስ
33 የሁለት አለም ጀነት
34 ቢስሚከ ነህያ
35 ያአፍቃሪወች አለም
@iqera
