813
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
Repost from N/a
ውድ ሹፌሮቻችን መተግበሪያውን በማውርደ ከላይ በተዘረዘረው መስፈርት በሟሟላት የዋን ራይድ ቤተስብ ይሁኑ 🥳🥳🥳
ለበለጠ መረጃ
+251 930 85 86 87
+251 944 16 17 18
+251 955 16 17 18
+251 966 16 17 18
Official One Ride social media links
Facebook: https://www.facebook.com/rideinone
Instagram: https://www.instagram.com/rideinone
Telegram Group: http://t.me/rideinone
Telegram Chanel: http://t.me/rideinonee
Repost from 💡 የአብርሃም_ቤት ⛺️
#ከፍ_ዝቅ
ህይወት ዥዋ-ዥዌ
ኋላና ፊት ሆኖ ፥ በዝቶ መንቀላዎዝ
በመመላለስ ነው
በጀንበር የሚ'ጦዝ ።
ሞተው እስከሚያርፉ ፥ እስኪገላገሉ
በልቶ በማራገፍ
መኖር ይቀጥላል.... ሲሰፍሩ
ሲጎሉ !!
✍ #አብርሀም_ተክሉ
@Abrham_teklu
@Abrham_teklu
----አያሳጣን----
አያሳጣን አገር ሸምጋይ
መክረው ትውልድ የሚሰ'ሙ ፥ እቀ ሸንጎ የሚፈሩ
እናቶችም አያሳጣን
ሀደ ሲንቄ ፥ ለመድን ዋስ የሚጠሩ
አያሳጣን
ጳጳስ ፣ ኡስታዝ ፣ ፓስተር ፣ ቃሉ
እንደቋንቋው ፣ እንደ ዶግማው ፣ እንደ ውሉ
ላገር ባላ ፣ ላገር ካስማ ፣ ግብረ ገቡን የሚጥሉ
"አለ" ብለው ላመኑቱ
ለቤክ ብለው የሚገ'ዙ
ምእመኑን ከመሰይጠን ፥ ከእርኩሰቱ የሚያወግዙ ።
------------ አያሳጣን!! --------
ታዩት....የለ !
ቁርሾ ጋግረን ....በደም ቦካን
ከፋን ፣ ገማን ፥
ካካ ሆንን ፥ ሰይጣን እንኳን የማይነካን
በልቶ ማደር እየራቀን
አይወጥረን ... የግፍ ቁንጣን
ተኮላችን ላቀረበው
ጣረሞቱን የሚያባርር ፥ ባገር ይጢስ የሰላም 'ጣን
አያሳጣን
ሽማግሌ !
አያሳጣን
ሀደ ሲንቄ !
አያሳጣን
የእምነት አባት !
እኒህ ካሉ ምን .....ይጨንቃል !!!
ትውልዱ እንደው ገራገር ነው
ከቀደሙት...በበለጡት ይታረቃል !!!
እንጂማ
መካር ያሉት ምክር ጠፍቶት
ሸምጋይ ያሉት ሸንጎ ካጣ
በጡቶቷ ተገዝቶ...ልጅ በእናቱ ካልተቀጣ
አባት ያሉት ከጨከነ....ከባረከ መባላቱን
ተዉት...................................ወጣቱን !!!
11/12/2014
አብርሃም_ተክሉ
@Abrham_teklu
አኗኗር
ክ_ፋ_ት
እ
ር
ቃ
ን
ወ
ጣ
መልከ መልካም ሰይጣን ፥
ይሰየጥንበት ....ገሶ ጥርስ አወጣ
ዝርክርክ ተንኮሉ..
እንዳገር..እንደህዝብ ፥ ቱቢቱን አሰጣ ።
ልክ እንዳሁኑ
ተስፋ ከድር ቀጥኖ
ስጋ ተረት ሲኮን....ሲተካ በቆስጣ
ጉተናቢስነት ባመኑት ሲመጣ
አትደሳ ያለው....
ዘመኑ ሚዶ ነው...አገሬው መላጣ
ወይ ችግር አይነቅል
ወይ መልክ አያመጣ ።
አብርሃም ተክሉ
