ነጻ መንፈሳዊ የክርስቲያን መጽሐፍቶችንና ትምህርቶች ለማግኘት👈👇
“አምላክህ እግዚአብሔር መሐሪ አምላክ ነውና አይተውህም፥ አያጠፋህምም፥ ለአባቶችህም የማለላቸውን ቃል ኪዳኑን አይረሳም።” — ዘዳግም 4፥31
Show more1 650
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-230 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
ገንዘብ ሰዎችን ደስተኛ ያደርጋልን? ጤና ሰዎችን ደስተኛ ያደርጋልን? አያደርግም፡፡ ሰዎችን እውነተኛ ደስተኞች የሚያደርጋቸው የዘላለም ቤዛነት የሐጢያቶች ሁሉ ይቅርታ ብቻ ነው፡፡ ሰው ከውጭ ሲታይ ምንም ያህል ደስተኛ ቢመስል በልቡ ውስጥ ሐጢያት ካለበት ይህ ሰው ምስኪን ነው፡፡ ይህ ሰው በፍርድ ፍርሃት ውስጥ ይኖራል፡፡
የዳነ ሰው ቡቱቶ ቢለብስም እንኳን እንደ አንበሳ ደፋር ነው፡፡ በልቡ ውስጥ ሐጢያት የለም፡፡ ‹‹ጌታ ሆይ አመሰግንሃለሁ፡፡ እኔን ሐጢያተኛውን አዳንከኝ፡፡ እኔ ፍቅርህን ለመቀበል የተገባሁ አይደለሁም፡፡ ነገር ግን ስላዳንከኝ አመሰግንሃለሁ፡፡ እኔ ለዘላለም ከሐጢያቶች የዳንሁ ነኝ፡፡ ክብር ለእግዚአብሄር ይሁን!››
የዳነ ሰው በእርግጥም ደስተኛ ሰው ነው፡፡ በእርሱ የቤዛነት ጸጋ የተባረከ ሰው በእርግጥም ደስተኛ ሰው ነው፡፡
‹‹የዓለምን ሐጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሄር በግ፡፡›› ኢየሱስ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ስለወሰደ እኛ ሐጢያት የለብንም፡፡ እርሱ በመስቀል ላይ ደህንነትን ‹‹ፈጸመ፡፡›› የእናንተንና የእኔን ጨምሮ ሐጢያቶቻችን በሙሉ ‹በዓለም ሐጢያት› ውስጥ ስለተካተቱ ሁላችንም ድነናል፡፡ ( 1ኛ መፅሐፍ ስብከት 4)
ሰይጣን በተንኮሉ አሁንም ብዙዎችን ማሳቱን ቀጥሎአል። ወንድሞቼ የሰይጣንን ሐሳብ ላለመርሳት ሁሉጊዜ ልባችንን በእግዚአብሔር ቃል ላይ መትከል አለብን። ከውሃና ከመንፈስ ምንጭ ሁለ መጠጣትና መንፈሳችንን ማደስ አለብን። ያነ ሰይጣንን የሚናሸንፍበትን አቅም እናገኛለን። ያለበለዚያ በእርሱ ወጥመድ ውስጥ ተጠምደን እንወድቃለን። እንጠንቀቅ።
የመጥምቁ ዮሐንስ ማንነትና አገልግሎቱን አለማወቅ ለትልቅ መንፈሳዊ ኪሳራ ይዳርጋል።