cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking ÂŤAccept allÂť, you agree to the use of cookies.

avatar

🇪🇹Ethiopia🇪🇹🇪🇹 News🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹

True Breaking News

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
153Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ዶ/ር አብርሃም በላይ ለኢድ አልፈጥር በዓል የእንኳን አደረችሁ መልዕክት አስተላለፉ --------------------------------- ግንቦት 05/2013 (ዋልታ) - የትግራይ ክልል ግዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር አብርሃም በላይ ለህዝበ ሙሰሊሙ እንኳን ለ1ሺህ 442ኛው የኢድ አልፈጥር በአል በሰላም አደረሳችሁ ብለዋል። ይህን በአል ስናከብር አንድነታችን ይበልጥ የምናጠናክርበትና በተለያዩ ቦታዎች የተፈናቀሉ ወገኖች የምናግዝበት በአል ሊሆን ይገባል ብለዋል። በተጨማሪም የተቸገረን በመርዳትና በመተሳሰብ መሆን አለበት ብለዋል ዶ/ር አብርሃም በላይ በመልእክታቸው፡፡
Show all...
ብሔራዊ ቡድኑ የማበረታቻ ሽልማት እና እውቅና ሊበረከትለት ነው -------------------------------------------- ግንቦት 04/2013 (ዋልታ) - የኢትዮጵያ ወንድ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን ከ8 አመት በኋላ ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፉን ተከትሎ በመንግስት እና በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አማካኝነት የእውቅና እና ሽልማት ሊበረከትለት መሆኑን የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ኮምሽነር አቶ ኤሊያስ ሽኩር እና የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ በጋራ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ አስታወቁ፡፡ ብሄራዊ ቡድኑ ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፉን ተከትሎ በወቅቱ በተለያዩ ምክንያቶች የሽልማት እና የማበረታቻ ፕሮግራም ባይካሄድም የሀገራችን ህዝቦች በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች አደባባይ በመውጣት በከፍተኛ ድምቀት የጀግና አቀባበል በማድረግ ደስታቸውን እንደገለፁ ኮምሽነሩ በመግለጫቸው አንስተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ወንዶች እግር ኳስ ብሄራዊ ቡድን ለ33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በማለፉ ሀገርንና ህዝብን በማኩራታቸው እና በቀጣይ ባለው አፍሪካ ዋንጫም ሆነ በሌሎች ውድድሮች ላይ ተፎካካሪ ሆኖ እንዲቀርብ የዝግጅት ስራ ለመስራት ዓላማ ተደርጎ የተዘጋጀ ፕሮግራም እንደሆነ ታውቋል፡፡ ብሄራዊ ቡድኑ ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ለስፖርቱ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ፣ መነቃቃትን የፈጠረ ቢሆንም ቀጣይነት እንድኖረው ታዳጊ ወጣቶች ላይ መስራት እና ኤሊት ስፖርተኞችን በጥራትና በስፋት ማዘጋጀት ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ የገለፁት ኮምሽነሩ ብሄራዊ ቡድኑ ቀጣይ ባሉት ውድድሮች ላይ ጠንካራ እና ተፎካካሪ እንዲሆን የወዳጅነት ጨዋታዎችን ጨምሮ ሀብት ተመድቦ ... https://www.facebook.com/489211707826282/posts/4275772712503477/
Show all...
ሙስሊሙ ማኅበረሰብ ከረመዳን ጾም በኋላም መልካምና በጎ ነገር ማድረጉን እንዲያስቀጥል ተጠየቀ ----------------------------------- ግንቦት 05/2013 (ዋልታ) - የደብረታቦር ከተማ ሙስሊም ማኅበረሰብ የ1 ሺህ 442ኛውን ኢድአልፈጥር በዓልን በቴዎድሮስ አደባባይ በሶላትና በእስላማዊ ትምህርቶች አክብሯል፡፡ በእለቱ በእንግድነት የተገኙት የደብረታቦር ከተማ ከንቲባ መሰረት ወንዴ ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት እስልምናና ክርስትና ሃይማኖቶች ለበርካታ ዓመታት አብረው ተከባብረው የኖሩ መሆናቸውን አስታውሰዋል። ይህንን መልካም እሴት ላቆዩን አባቶቻችን ክብር ይግባቸዋልም ብለዋል፡፡ ከንቲባው እስልምና ማለት ሰላም ማለት መሆኑን ጠቅሰው ኢትዮጵያ ከተጋረጠባት ችግር እንድታልፍ ሕዝበ ሙስሊሙ ዱኣ (ጸሎት) እንዲያደርግ ጠይቀዋል፡፡ በበዓሉም የሶላት ሥነ ሥርዓትና ሌሎች አስተምህሮዎች ተከናውነዋል፡፡ በበዓሉ ለሕዝበ ሙስሊሙ ሃይማኖታዊ ትምህርት የሰጡት የሃይማኖቱ ዳኢ (አስተማሪ) ሸህ አብዱል ሃዲ ሁሴን ከእስልምና መሰረቶች ውስጥ አንዱ ጾም መሆኑን ጠቅሰው በጾም ወቅት እዝነት፣ መረዳዳት፣ ያለው ለሌለው ማካፈልና በጎ ስራ መስራት ከፈጣሪ ጋር የሚያስታርቅ ነው ብለዋል፡፡ ሙስሊሙ ማኀበረሰብ ከሮመዳን ጾም በኋላም መልካምና በጎ ነገር መስራትን አጠናክሮ በመቀጠል ከአላህ ምንዳውን ለማግኘት ሃይማኖቱን መኖር እንዳለበት አሳስበዋል፡፡ (ምንጭ፡- አሚኮ)
Show all...
ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ የቢላሉል ሐበሽን ማዕከል ጎብኙ ------------------------- ግንቦት 05/2013 (ዋልታ) - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአዲስ አበባ የኢትዮጵያ ጥንታዊ እስላማዊ ቅርሶች መገኛ የሆነውን ቢላሉል ሐበሺ የማህበረሰብ ሙዚየምን ዛሬ ጎብኝተዋል፡፡ ማዕከሉ የኢትዮጵያውያንን ችግሮች ለመፍታት፣ ድኾችን ለመርዳትና ዕውቀትን ለማስፋፋት የሚያደርገው ጥረት አድንቀዋል። በተለይም የረዥም ዘመናት ታሪክ ያለውን የኢትዮጵያን እስልምና ቅርሶች ለማሰባሰብና ለትውልዱ ለማሳየት የተመሠረተው ሙዝየም በከተማችን ሊጎበኙ ከሚገባቸው ቦታዎች አንዱ ነው ሲሉም ገልፀዋል። ተቋሙ ከዚህ የበለጠ ነገር ለኢትዮጵያ እንደሚሠራም እምነቴ ነው ሲሉ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው አስፍረዋል።
Show all...