cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ዐቂደቱል ሙወሒዲን

✉ በዚህ ቻናል በአሏህ ፍቅድ የቁርኣን አንቀጾች ፥ የረሱል ሰለሏሁ ዐለይሒ ወሰለም ሐዲሶች ፥ የሠለፎች አሳር ፥ የአኢማዎች ትምህርት ይቀርብበታል፡፡ ኢንሻ አሏህ ፡፡ ✉

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
344
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

💥 الدكتور القرضاوي كافر بفتواه هذه ☝️باتفاق علماء المذاهب، ومن لم يكفّره بعد العلم بالحال فهو كافر مثله (ترقبوا قليلا)!!
Show all...
Show all...
حكم من تبين له غير الإسلام دينا بعد إستعمال العقل والتدبر│ الشيخ يوسف القرضاوي

ስለ *አል-ኸጣእ* የሚያቀርቡት ሹብሃ አላለቀም፡፡ ኢንሻ አሏህ፡፡ ለዛሬ ይህ ይብቃን፡፡ ነገ አሏህ ከፈቀደ በሌላ ፅሁፍ እንገናኛለን፡፡ ሰሞኑ አድራሻ ስለምቀይር ሌላም አዲስ የቴሌግራም ቻናል መክፈቴ አይቀርም፡፡ በዚህ ግቡ ፥ በዛ ግቡ ስል እንዳትሰላቹ ለማለት ኖ፡፡ ወጀዛኩሙሏሁ ኸይራ
Show all...
🅾 (2) የሙርጂኣዎች ማደናገርያ የቁርኣን አንቀጾችና እና በሽርክ/ኩፍር ዑዝር ቢል-ጀህል... በአሏህ ስም ፅሁፌን እጀምራለሁ፡፡ በአሽረፈል ኸልቅ ረሱል(ﷺ) ላይ የዘወትር ራህመትና ውዳሴ ይውረድ፡፡ •ሙርጂኣዎች ስለ *አል-ኸጣእ* የተነገሩ የቁርኣን አንቀፆች ጥቅል ትርጉም ነው ያላቸው በማለት በሽርክና በኩፍር ላይ ዑዝር ቢልጀህል አለ ለማለት ማሥረጃ አድርገው ሲጠቅሱ እናያለን፡፡ በዚህ ክፍል ልክ በመጀመርያ ክፍል እንዳየነው *አልኸጣእ* የተባለው ኩፍርና ሽርክ እንዳልተፈለገበት ከቁርኣን ማሥረጃ እንገልፃለን፡፡ አሏህ እንዲህ ብሏል ፦ 9:65 «በእርግጥ ብትጠይቃቸው «እኛ የምንዘባርቅና የምንጫወት ብቻ ነበርን» ይላሉ፡፡ «በአላህና በአንቀጾቹ፣ በመልክተኛውም ታላግጡ ነበራችሁን» በላቸው፡፡» ( وَلَئِن سَأَلْتَهُمْ لَيَقُولُنَّ إِنَّمَا كُنَّا نَخُوضُ وَنَلْعَبُ ۚ قُلْ أَبِاللَّهِ وَآيَاتِهِ وَرَسُولِهِ كُنتُمْ تَسْتَهْزِئُونَ ) التوبة (65) 9:66 «አታመካኙ፤ ከእምነታችሁ በኋላ በእርግጥ ካዳችሁ፡፡ » ይህ የቁርኣን አንቀፅ *አል-ኸጣእ* ወይም ስህተት ሁሉ ዑዝር እንደሌለውና ቀስድ ያለበት ስህተት እስከሆነ ድረስ ሰውዬ የሚሠራው ነገር እንደሚያከፍረው ባያውቅም እንኳን እንደሚከፍር ማሥረጃ ይሆናል፡፡ ሙፈሲር ታላቁ ኢማም ኢብን ጀሪር (አሏህ ይዘንለት) የዚህ ቁርኣን መልዕክት የወረደበት ምክንያት ሲጠቅስ እንዲህ ብሏል ፦ " ከዘይድ ቢን አስለም እንደዘገበው አንድ ሙናፊቅ (በውጩ ኢስላም ግልፅ የሚያደርግ ውስጡ ግን የካደ) ሰው ነበር፡፡ የተቡክ ዘመቻ ጊዜ ለዐውፍ ቢን ማሊክ እንዲህ አለው ፦ እነዚህ አንባቢዎቻችን¡ ሆዳም የሆኑ፥ አንደበታቸውም ውሸታም የሆኑ ፥ ጠላትን በሚገጥሙ ጊዜ ፈርተው የሚያፈገፍጉ" ብሎ (በሶሃቦች ላይ ያላግጥ ጀመር)፡፡ ዐውፍም እንዲህ አለው "በርግጥም ዋሽተሐል፡፡ ሄጄ ለረሱል (ሰለሏሁ ዐለይሒ ወሰለም) ይህን እነግራቸዋለሁ አለው፡፡ዐውፍም ለረሱል(ﷺ) ሊነግራቸው ሄደ፡፡ ሆኖም ቁርኣን ቀድሞት ወርዷል፡፡ የዘገባው ባለቤት ዘይድም እንዳለው "ዐብዱሏህ ቢን ዑመር እንዲህ ብሏል ፦ ወደሰውዬ(ሙናፊቁም) ተመልክቻለው፡፡ ከረሱል ﷺ ግመል ገመድ ጋር ታስሮ ድንጋዮችም እየመቱት ይጎትቱታል፡፡ እሱም እንዲህ እያለ ዑዝሩ ያቀርባል ፦ «እኛ የምንዘባርቅና የምንጫወት ብቻ ነበርን» ይላሉ፡፡ የአሏህ መልዕክተኛ ﷺ ደግሞ 9:66 «አታመካኙ፤ ከእምነታችሁ በኋላ በእርግጥ ካዳችሁ፡፡ » እያሉ ይመልሱላቸዋል፡፡ •ሙርጂኣዎች አንድ ሙሥሊም ነኝ የሚል ሰው ኩፍር ላይ ቢወድቅ *ኩፍር ላይ እንደወደቀ ተነግሮት ፥ ተብራርቶለት እንቢ ካለ ነው የሚከፍረው* ይላሉ፡፡ አሏህና መልዕክተኛው ﷺ ግን እነዚህ ሙሥሊም ነኝ የሚሉ ሰዎች በሰሩት ኩፍር ምንም ዑዝር አልሰጧቸውም፡፡ እስቲ መጀመርያ በዲን ማላገጥ ኩፍር እንደሆነ ይነገራቸውና ከዚያ እንቢ ካሉ ይከፍራሉ አልተባለም፡፡ 9:66 «አታመካኙ (ዑዝር አታቅርቡ) ፤ ከእምነታችሁ በኋላ በእርግጥ ካዳችሁ፡፡ » ነው የተባሉት፡፡ ስለዚህ ስለ *አልኸጣእ* የሚናገሩ የቁርአንም ይሁን የሃዲስ ማሥረጃዎች በሁሉም ነገር ላይ የተሳሳተ ሰው ዑዝር ቢልጀህል አለው ማለት አይደለም፡፡ ቢሆንማ ይኸው 2 የቁርኣን አንቀጾች ጠቅሰናል፡፡ ሁሉም ስህተት ዑዝር እንደማይሰጥበት፡፡ •ሌላው ኩፍር በራሱ ከነዚህ ጥቅል የሆኑ *አልኸጣእ* ላይ ማግራራት እንዳለ ከሚጠቁሙ ማሥረጃዎች ተነጥሎ የወጣ መሆኑ እንረዳለን፡፡ ኢንሻ አሏህ ይቀጥላል፡፡ ☑️ወቢላሂ አትተውፊቅ ✍ አቡ ሙሥሊም ነኝ፡፡ •ቴሌግራም @Anti_Murjia
Show all...
🅾(1) የሙርጂኣዎች ማደናገሪያ የቁርኣን አንቀፆች እና በሽርክ/ኩፍር ዑዝር ቢል-ጀህል.... በአሏህ ስም ፅሁፌን እጀምራለሁ፡፡ በረሱልﷺ ላይ ዘወትር ሰላም እና እዝነት ይውረድ፡፡ አሏህ በቁርኣን እና ረሱል ሰለሏሁ ዐለይሒ ወሰለም በሐዲሳቸው እንዳስተማሩን በአሏህ የሚያጋራ ሰው የሚሠራው ስራ ሽርክ እንደሆነ ባያውቅም እንኳን *ሙሽሪክ* ይሆናል፡፡ ነገርግን ሙርጂኣዎች ዘንድ *ሙሥሊም* ነው ብለው የተለያዩ ማደናገርያ አንቀጾችን እያመጡ ነው፡፡ ከዚያ ውስጥ ጥቂቱ እንመልከት፡፡ ሙርጂኣዎች ከሚጠቅሷቸው አንቀጾች መካከል:- 2:286 " አላህ ነፍስን ከችሎታዋ በላይ አያስገድዳትም፡፡ ለርስዋ የሠራችው አላት፡፡ በርስዋም ላይ ያፈራችው (ኀጢአት) አለባት፡፡ (በሉ)፡- ጌታችን ሆይ! ብንረሳ (إِن نَّسِينَا) ወይም ብንስት( أَخْطَأْنَا ) አትያዘን፤ (አትቅጣን)፡፡ " ይላል፡፡ [ رَبَّنَا لَا تُؤَاخِذْنَا إِن نَّسِينَا أَوْ أَخْطَأْنَا ۚ رَبَّنَا ] البقرة (286) ፨ እንዲሁም ከሚያመጡት ማደናገርያ አንቀፅ ሌላኛ ይህ ነው፡፡👇 ۚ وَلَيْسَ عَلَيْكُمْ جُنَاحٌۭ فِيمَآ أَخْطَأْتُم بِهِۦ وَلَٰكِن مَّا تَعَمَّدَتْ قُلُوبُكُمْ ۚ وَكَانَ ٱللَّهُ غَفُورًۭا رَّحِيمًا 33:5 " በእርሱ በተሳሳታችሁበት ነገርም በእናንተ ላይ ኀጢአት የለባችሁም፡፡ ግን ልቦቻችሁ ዐውቀው በሠሩት (ኀጢአት) ነው፡፡ " አህዛብ፡5 ከሐዲስ የሚያመጡት ማደናገርያ ደግሞ «رفع عن أمتي الخطأ والنسيان وما استكرهوا عليه» "ከዑመቴ ላይ ስህተት ፥ መርሳት ፥ እና የተገደዱበት ነገር ከነሱ ተነስቶላቸዋል፡፡ " እነዚህ የመሣሠሉ አንቀጾችና ሐዲሶች ጃሒል ሆነው በአሏህ የሚያጋሩ ሰዎችን *ሙሥሊሞች* ናቸው ለማለት ማሥረጃ ነው አሉ፡፡ ፨መልሳችን:- እነሱ እንደሚሉት "እነዚህ (ሩኽሳዎች የሚጠቁሙት ) አንቀጾች ጥቅል መልዕክት የያዙ ናቸው፡፡ ስለሽርክ የመጡ ጥቅል አንቀጾች በነዚህ አንቀጾች የተገደሉ ይሆናሉ ብለው ሞገቱ፡፡ ➊ እነዚህ አንቀጾች የሚያስተላልፉት መልዕክት በጥቅሉ አይደለም የምንረዳው፡፡ በቁርኣን ፥ በሃዲስ ፥ በኢጅማዕ ፥ በሶሃቦች ግንዛቤ ፥ ከነሱ በኋላም በመጡ ዑለማዎች ንግግር ማሥረጃ አድርገን ጥቅል መልዕክት እንደሌላቸው ነው የምንረዳው፡፡ እነዚህ ስለ ስህተት የሚናገሩ አንቀጾች ጥቅል መልዕክት እንደሌላቸው ከሚጠቁሙ ማሥረጃዎች አንዱ አሏህ እንዲህ ብሏል ፦ 49፡2 " እናንተ የማታውቁ ስትኾኑ ሥራዎቻችሁ እንዳይበላሹ (ተከልከሉ)፡፡ ٍ أَن تَحْبَطَ أَعْمَٰلُكُمْ وَأَنتُمْ لَا تَشْعُرُونَ ፨ እነዚህ ሙርጂኣዎች አንድ ሰው የሚሠራው ስራ ሽርክ መሆኑ ተነገሮት ፥ አውቆ ፥ ከዚያ እንቢ ካለ እንጂ አይከፍርም ሲሉ ነበር፡፡ አሏህ (ሱ.ወ) ግን ከነሱ የተበለሸ ዐቂዳ በተቃራኒ *አንድ ሰው ምንም በማያውቀው መልኩ ስራ ሁሉ ውድቅ እንደሚሆንበት እየነገረን፡፡ * በሙርጂኣዎች ዐቂዳ ደግሞ አንድ ሰው የማያውቅ ከሆነ ስራውም ሁሉ ውድቅ አይሆንም ፥ ሰውዬውም ከፍሯል አይባልም፡፡ ስለዚህ ይህ አቋም በግለጽ ቁርኣንን ይጋጫል፡፡ •ከዚህ በፊት አንድ ሙሥሊም የሆነ ሰው ጃሒል ሆኖ በሚሠራው ስራ አይቀጣም ፥ ሙሽሪክም አይባሉም ሲሉ ነበር፡፡ አሏህ ግን አንድ ሙሥሊም የሆነ ሰው ምንም በማያውቀው በኩል ስራው ሁሉ ውድቅ እንደሚሆንበት ይነግረናል፡፡ ዑዝር ቢኖር ኖሮ ይህ ሰው ባላወቀው ነገር ስራው ሁሉ ውድቅ ባልተደረገበት ነበር፡፡ ሌላው ስራ ሁሉ ውድቅ የሚሆነው ያ የሰራው ስራ *ኩፍር* ሲሆን ነው፡፡ • ሼይኹል ኢስላም ኢብን ተይሚያህ (ረሂመሁሏህ) እንዲህ ብሏል፦ والحبوط الكلي لا يكون إلا بالكفر ، كما أن غفران الذنوب جميعها لا يكون إلا بالتوبة وهذا من أصول أهل السنة. «ስራን ሙሉ በሙሉ ውድቅ የሚሆነው ኩፍር ላይ ከሆነ ብቻ ነው፡፡ ልክ አጠቃላይ ወንጀልን ምህረት የሚገኘው በተውበት እንጂ በሌላ እንዳልሆነ ሁሉ ነው፡፡ ይህ ከአህሉ ሱና መሠረቶች ነው፡፡» 📚ዑዝር ቢልጀህል፡213 (ከሳሪም አልመሥሉል) ፨ ይህ የኢብን ተይሚያ ንግግር የሚጠቁመው የአንድ ሰው መልካም ስራው ሙሉ በሙሉ ውድቅ የሚሆነው በኩፍር ነገር ብቻ ነው፡፡ ልክ ወንጀልን ሁሉ ምህረት የምናገኘው በተውበት እንደሆነው፡፡ ታድያ ሙርጂኣዎች አንድ ሰው ሳያወቅ በሠራው ስራ አይቀጣም ፥ አይከፍርም ሲሉ አልነበር? ይህ አሏህ በግልፅ እንዲህ ብሏል ፦ 49፡2 " እናንተ የማታውቁ ስትኾኑ ሥራዎቻችሁ እንዳይበላሹ (ተከልከሉ)፡፡ ሱረቱል ሑጁራት:2 ይኸው አሏህ በግልፅ *የማታውቁ ስትሆነ* እያለ ነው፡፡ ይህ ማለት ጃሒል ሁናቹህ ማለት ነው፡፡ •ይህ አንቀጽ በግልፅ ስለ *አል-ኸጠእ* የመጡ አንቀጾች ኩፍር ነገር እንደማያካትቱ የሚያስረዳን ነው፡፡ ✉ሁለተኛው ማሥረጃችን ቀጥሎ ይቀርባል፡፡ ☑️ወቢላሂ አትተውፊቅ ✍አቡ ሙሥሊም •ቴሌግራም👉 @Anti_Murjia
Show all...
→ ኢማም ወኪዕ ቢን ጀራህ (ረሂመሁሏህ) [ 196 ዓመተ ሂጅሪያ የሞተ ) ከታላላቅ የሐዲስ ሊቃውንቶች አንዱ ነው፡፡ እንዲህ ብሏል ፦ قال أهل الإيمان : لا يجزئ قول إلا بعمل وبعقد. /ذم الكلام:١١٨٥ « የኢማን ባለቤቶች እንዲህ ብለዋል *ንግግር ብቻውን በስራና በቀልብ እምነት እንጂ አያብቃቃም፡፡ » 📚አልጃሚዕ ፊ ኩትቢ አልኢማን፡1/23 ሙርጂኣዎች ተግባርን ከኢማን በማሥወጣት ላይ የተጠመዱ ሲሆን ከዚህ ቢድዐ የሆነ እምነታቸው ጋር *ተክፊር* በተመለከተ ደግሞ በቀልብ ኢስቲህላል ካላደረገ አይከፍርም የሚሉ ደጃሎች ናቸው፡፡ እንጠንቀቅ፡፡ ☑️ @Anti_Murjia ☑️
Show all...
የአህሉ ሱና ዐቂዳና መንሐጅ *ተክፊር* ብለው የሚያጠለሹ ሙርጂኣዎች መታገል ይኖርብናል፡፡ በዚህ ጠቃሚ የሆነ ነገሮች የሚያጋራኝ ሁሉ እቀበላለሁ፡፡
Show all...
እሱ የፃፋቸው ፅሁፎች ደርሰውኛል፡፡ ግን ከአንዳንድ ስራዎች ጋር መሽጉል ስለምሆን ኢንሻ አሏህ በቅርቡ እያንዳንዷ ግልፅ ትደረጋለች፡፡ አንድ ነገር ለመፃፍ ኪታቦችና የዑለሞች ተቅሪራት ማየት ስለሚያስፈልግ ታገሱኝ፡፡ ኢንሻ አሏህ፡፡
Show all...
ውይይቱም ያቋረጥኩት ሙሂቡዲን አንድ ነገር ላይ ችክ ብሎ ንግግርን የማሳጣት ሂደት ስለሚሄድ ነበር የተውኩት እንጂ እሱ አህሉ ሱና የሚረታበት ማሥረጃ አምጥቶ አልነበረም፡፡ ሊያመጣም ስለማይችል፡፡ ምናልባት የሙርጂኣዎች ሹብሃ የማይረዳ ሰው ሊያታልል ይችላል ፡፡ ኢንሻ አሏህ እያንዳንዷ ትብራራለች፡፡
Show all...
የሙሂቡዲን አጨብጫቢዎች ምን ያህል ሙፍሊስ እንደሆኑ ይበልጥ የተረዳሁት [ በኡስታዝ ሙሂቡዲንና በወንድም አቡ ሙሥሊም መካከል የተደረገ ውይይት ] ብለው የሆኑ ፅሁፎች እያሰራጩ ነው፡፡😆 ለመሆኑ የትኛው ውይይት ነው እንዲህ ቀባብተው የሚያሰራጩት? ሲጀመር ገና አፉፍ ላይ የተቋረጠ ውይይት እንዴት *ያደረጉት ውይይት ተብሎ ይነዛል? አዑዙቢላህ ወሏህ ጀህሚይ ኢኽዋንዮች ሆይ! በማሥረጃ ድርቅ የተመታ ሌጣ መንሐጃሁ ለማሠማመር ብትጥሩም አይሳካላቹም፡፡ በማሥረጃ ብትንትኑ እናወጣዋለን፡፡
Show all...