Ethio telecom Family
Open in Telegram
6 044
Subscribers
-124 hours
-17 days
-2530 days
Posts Archive
6 044
+4
ኩባንያችን ከብሪቲሽ ኢንተርናሽናል ኢንቨስትመንት ጋር የሀገራችንን የዲጂታል ሽግግር ለማፋጠን በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ውይይት አደረጉ
የኩባንያችን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፍሬሕይወት ታምሩ ከዩናይትድ ኪንግደም የልማት ፋይናንስ ተቋም (BII) ከፍተኛ አመራሮች ጋር በሀገራችን ዲጂታል እና ዘላቂ መሠረተ ልማት ግንባታ ዙሪያ ስትራቴጂያዊ ውይይት አድርገዋል፡፡
በውይይቱም ዋና ሥራ አስፈፃሚያችን ኩባንያችን በክላውድ፣ በሰው ሠራሽ አስተውሎት፣ በቴሌብር እና በአረንጓዴ ኢነርጂ የታገዘ የተቀናጀ የዲጂታል ሥነ-ምህዳር በመገንባት የሀገሪቱን የዲጂታል ኢኮኖሚ እየመራ ስለመሆኑ በዝርዝር አብራርተዋል።
የብሪቲሽ ኢንተርናሽናል ኢንቨስትመንት ልዑክ በበኩላቸው ኢትዮ ቴሌኮምን የዲጂታል ኢኮኖሚው ዋነኛ አንቀሳቃሽ ሞተር መሆኑን በመጥቀስ፤ በዩናይትድ ኪንግደም የሚደገፉ የኢንቨስትመንት ዕድሎችን ለመፍጠር እና የ"ቀጣዩ አድማስ፡ ዲጂታል እና ከዚያም ባሻገር 2028" ስትራቴጂን በጋራ ለማሳካት ያላቸውን ከፍተኛ ፍላጎት ገልጸዋል።
በተለይም ሁለቱ ተቋማት አዳዲስ የኢኮኖሚ ዕድሎችን ለመፍጠር እና በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ መሠረተ ልማቶችን ለማስፋፋት በቅንጅት ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት አድርገዋል፡፡
ተጨማሪ፡- http://bit.ly/3QxqNXz
6 044
የኩባንያችን_ኤክስኩቲቭ_ማኔጅመንት_ቦርድ_የሚያዝያ_ወር_አፈጻጸም_ግምገማ_እና_በቁልፍ_ፋይናንሻል_መለኪያዎች.pdf2.81 MB
6 044
ውድ ቤተሰቦቻችን መልካም ቀን! መልካም የሥራ ሳምንት ይሁንላችሁ!
#Monday #Ethiotelecom #telebirr #ZemenGEBEYA #EmpoweringEthiopia’sDigitalFuture&Beyond
6 044
+4
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ በኢትዮጵያ የጣሊያን አምባሳደር ክቡር ሰም ፋብሪዚ ጋር የዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን ያለመ ስትራቴጂካዊ ውይይት አድርገዋል።
ውይይቱ በኢትዮ ቴሌኮም እና በጣሊያን ኩባንያዎች መካከል የተጀመረውን ትብብር በማጠናከር፣ የሀገሪቱን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ለማፋጠንና ሁሉን አቀፍና አካታች የዜጎች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማሳካት ያለመ ነው።
ቀደም ሲል ከጣሊያኑ አስኮት ኢነርጂ (Ascot Energy) ጋር የቴሌኮምና የዲጂታል ኃይል አጠቃቀምን እና የአረንጓዴ መሠረተ ልማት እንቅስቃሴዎችን ለማሳደግ በጋራ የተጀመሩ ተግባራትን ገምግመዋል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ከክቡር አምባሳደሩ ጋር በቴሌኮምና ዲጂታል መሠረተ ልማት ላይ የኃይል አስተማማኝነትን፣ የኦፕሬሽን ቅልጥፍናን እና የአካባቢ ጥበቃን የሚያሻሽሉ ዘላቂ ፕሮጀክቶችን በስፋት ለመተግበር በሚቻልባቸው ስትራቴጂዎች ዙሪያ መክረዋል።
በተጨማሪም ከጣሊያኑ የልማት ፋይናንስ ተቋም (CDP) ጋር የተጀመረው ትብብር የተገመገመ ሲሆን፤ ይህም ለትላልቅ የዲጂታል መሠረተ ልማት እና ዘላቂ የኃይል ፕሮግራሞች የሚውል የፋይናንስ ድጋፍን በማረጋገጥ ላይ ያተኮረ ነው። እንዲሁም ከሌሎች የጣሊያን ኩባንያዎች ጋር ያለንን ግንኙነት ማስፋፋት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይም ውይይት ተደርጓል።
በውይይቱ ወቅት ክቡር አምባሳደሩ ኢትዮ ቴሌኮም በኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ውስጥ ያለውን ቁልፍና ወሳኝ ሚና አድንቀው፤ በዘርፉ የሚገኙ ሌሎችም የጣሊያን ኩባንያዎች ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ቀጣይነት ያለው አጋርነት እንዲፈጥሩ የሚያደርጉትን ጥረት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
6 044
+6
✨🌍 ዓለም አቀፍ የመሬት ቀንን በልዩ ሁኔታ አክብረናል!
ዛሬ የሚከበረውን ዓለም አቀፍ የመሬት ቀንን ምክንያት በማድረግ የሠራተኛ አምባሳደሮቻችን በእንጦጦ ፓርክ የሚገኙ እፅዋትን በመንከባከብና በማጽዳት ቀኑን በደመቀ ሁኔታ አክብረዋል።
ኢትዮ ቴሌኮም የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብርን በንቃት በመቀላቀል፣ ባለፈው ዓመት ብቻ በሠራተኞቹ አማካኝነት ከ500,000 በላይ ችግኞችን በመላ ሀገሪቱ መትከሉ ይታወሳል።
ከችግኝ ተከላው ባለፈም ለአካባቢ ጥበቃ ምቹ የሆኑ አረንጓዴ መሠረተ-ልማቶችን (Green Infrastructures) ማለትም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ መሙያ ጣቢያዎችን (EV Charging) እና በፀሐይ ኃይል የሚሰሩ የኔትወርክ ምሰሶዎችን (Solar poles) በማስፋፋት ላይ እንገኛለን።
ለቀጣይ ትውልድ የምትመች አረንጓዴ ኢትዮጵያን ለመፍጠር የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥላለን!
#EarthDay2026
#Ethiotelecom #NextHorizon #telebirr #telebirrSuperApp #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
6 044
✨🌍 ዓለም አቀፍ የመሬት ቀንን በልዩ ሁኔታ አክብረናል!
ዛሬ የሚከበረውን ዓለም አቀፍ የመሬት ቀንን ምክንያት በማድረግ የሠራተኛ አምባሳደሮቻችን በእንጦጦ ፓርክ የሚገኙ እፅዋትን በመንከባከብና በማጽዳት ቀኑን በደመቀ ሁኔታ አክብረዋል።
ኢትዮ ቴሌኮም የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብርን በንቃት በመቀላቀል፣ ባለፈው ዓመት ብቻ በሠራተኞቹ አማካኝነት ከ500,000 በላይ ችግኞችን በመላ ሀገሪቱ መትከሉ ይታወሳል።
ከችግኝ ተከላው ባለፈም ለአካባቢ ጥበቃ ምቹ የሆኑ አረንጓዴ መሠረተ-ልማቶችን (Green Infrastructures) ማለትም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ መሙያ ጣቢያዎችን (EV Charging) እና በፀሐይ ኃይል የሚሰሩ የኔትወርክ ምሰሶዎችን (Solar poles) በማስፋፋት ላይ እንገኛለን።
ለቀጣይ ትውልድ የምትመች አረንጓዴ ኢትዮጵያን ለመፍጠር የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥላለን!
#EarthDay2026
#Ethiotelecom #NextHorizon #telebirr #telebirrSuperApp #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
6 044
የኩባንያችን_ኤክስኩቲቭ_ማኔጅመንት_ቦርድ_የአራተኛውን_ሩብ_ዓመት_የአፈጻጸም_ጅማሮ_ላይ_ውይይት_አካሄደ!.pdf3.05 MB
