en
Feedback
Ethio telecom Family

Ethio telecom Family

Open in Telegram

ይህ የኢትዮ ቴሌኮም ኢንተርናል ኮሙኒኬሽን የቴሌግራም ቻናል ነው፡፡

Show more
6 044
Subscribers
-124 hours
-17 days
-2530 days
Posts Archive
photo content

photo content

21 5th year telebirr Anniversary Kick off.jpg2.86 MB

21 5th year telebirr Anniversary Kick off.jpg2.86 MB

5th year telebirr Anniversary Kick off.jpg2.86 MB

ኩባንያችን ከብሪቲሽ ኢንተርናሽናል ኢንቨስትመንት ጋር የሀገራችንን የዲጂታል ሽግግር ለማፋጠን በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ውይይት አደረጉ የኩባንያችን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፍሬሕይወት ታምሩ
+4
ኩባንያችን ከብሪቲሽ ኢንተርናሽናል ኢንቨስትመንት ጋር የሀገራችንን የዲጂታል ሽግግር ለማፋጠን በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ውይይት አደረጉ የኩባንያችን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፍሬሕይወት ታምሩ ከዩናይትድ ኪንግደም የልማት ፋይናንስ ተቋም (BII) ከፍተኛ አመራሮች ጋር በሀገራችን ዲጂታል እና ዘላቂ መሠረተ ልማት ግንባታ ዙሪያ ስትራቴጂያዊ ውይይት አድርገዋል፡፡ በውይይቱም ዋና ሥራ አስፈፃሚያችን ኩባንያችን በክላውድ፣ በሰው ሠራሽ አስተውሎት፣ በቴሌብር እና በአረንጓዴ ኢነርጂ የታገዘ የተቀናጀ የዲጂታል ሥነ-ምህዳር በመገንባት የሀገሪቱን የዲጂታል ኢኮኖሚ እየመራ ስለመሆኑ በዝርዝር አብራርተዋል። የብሪቲሽ ኢንተርናሽናል ኢንቨስትመንት ልዑክ በበኩላቸው ኢትዮ ቴሌኮምን የዲጂታል ኢኮኖሚው ዋነኛ አንቀሳቃሽ ሞተር መሆኑን በመጥቀስ፤ በዩናይትድ ኪንግደም የሚደገፉ የኢንቨስትመንት ዕድሎችን ለመፍጠር እና የ"ቀጣዩ አድማስ፡ ዲጂታል እና ከዚያም ባሻገር 2028" ስትራቴጂን በጋራ ለማሳካት ያላቸውን ከፍተኛ ፍላጎት ገልጸዋል። በተለይም ሁለቱ ተቋማት አዳዲስ የኢኮኖሚ ዕድሎችን ለመፍጠር እና በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ መሠረተ ልማቶችን ለማስፋፋት በቅንጅት ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት አድርገዋል፡፡ ተጨማሪ፡- http://bit.ly/3QxqNXz

የኩባንያችን_ኤክስኩቲቭ_ማኔጅመንት_ቦርድ_የሚያዝያ_ወር_አፈጻጸም_ግምገማ_እና_በቁልፍ_ፋይናንሻል_መለኪያዎች.pdf2.81 MB

photo content

የኩባንያችን_ብራንድ_የደመቀበት_የ2018_የኢትዮ_ቴሌኮም_ታላቁ_ሩጫ_በጅማ_ተካሄደ!!.pdf7.31 MB

photo content

ውድ ቤተሰቦቻችን መልካም ቀን! መልካም የሥራ ሳምንት ይሁንላችሁ! #Monday #Ethiotelecom #telebirr #ZemenGEBEYA #EmpoweringEthiopia’sDigitalFuture&Bey
ውድ ቤተሰቦቻችን መልካም ቀን! መልካም የሥራ ሳምንት ይሁንላችሁ! #Monday #Ethiotelecom #telebirr #ZemenGEBEYA #EmpoweringEthiopia’sDigitalFuture&Beyond

የደቡብ_ደቡብ_ምስራቅ_ሪጅን_የተመሰረተበትን_አንደኛ_ዓመት_በተለያየ_መርሃግብር_በድምቀት_አከበረ!.pdf3.99 MB

photo content

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ በኢትዮጵያ የጣሊያን አምባሳደር ክቡር ሰም ፋብሪዚ ጋር የዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን ያለመ ስትራቴጂካዊ ውይይት አድርገዋል። ውይይቱ በኢትዮ
+4
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ በኢትዮጵያ የጣሊያን አምባሳደር ክቡር ሰም ፋብሪዚ ጋር የዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን ያለመ ስትራቴጂካዊ ውይይት አድርገዋል። ውይይቱ በኢትዮ ቴሌኮም እና በጣሊያን ኩባንያዎች መካከል የተጀመረውን ትብብር በማጠናከር፣ የሀገሪቱን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ለማፋጠንና ሁሉን አቀፍና አካታች የዜጎች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማሳካት ያለመ ነው። ቀደም ሲል ከጣሊያኑ አስኮት ኢነርጂ (Ascot Energy) ጋር የቴሌኮምና የዲጂታል ኃይል አጠቃቀምን እና የአረንጓዴ መሠረተ ልማት እንቅስቃሴዎችን ለማሳደግ በጋራ የተጀመሩ ተግባራትን ገምግመዋል። ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ከክቡር አምባሳደሩ ጋር በቴሌኮምና ዲጂታል መሠረተ ልማት ላይ የኃይል አስተማማኝነትን፣ የኦፕሬሽን ቅልጥፍናን እና የአካባቢ ጥበቃን የሚያሻሽሉ ዘላቂ ፕሮጀክቶችን በስፋት ለመተግበር በሚቻልባቸው ስትራቴጂዎች ዙሪያ መክረዋል። በተጨማሪም ከጣሊያኑ የልማት ፋይናንስ ተቋም (CDP) ጋር የተጀመረው ትብብር የተገመገመ ሲሆን፤ ይህም ለትላልቅ የዲጂታል መሠረተ ልማት እና ዘላቂ የኃይል ፕሮግራሞች የሚውል የፋይናንስ ድጋፍን በማረጋገጥ ላይ ያተኮረ ነው። እንዲሁም ከሌሎች የጣሊያን ኩባንያዎች ጋር ያለንን ግንኙነት ማስፋፋት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይም ውይይት ተደርጓል። በውይይቱ ወቅት ክቡር አምባሳደሩ ኢትዮ ቴሌኮም በኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ውስጥ ያለውን ቁልፍና ወሳኝ ሚና አድንቀው፤ በዘርፉ የሚገኙ ሌሎችም የጣሊያን ኩባንያዎች ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ቀጣይነት ያለው አጋርነት እንዲፈጥሩ የሚያደርጉትን ጥረት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።

✨🌍 ዓለም አቀፍ የመሬት ቀንን በልዩ ሁኔታ አክብረናል! ዛሬ የሚከበረውን ዓለም አቀፍ የመሬት ቀንን ምክንያት በማድረግ የሠራተኛ አምባሳደሮቻችን በእንጦጦ ፓርክ የሚገኙ እፅዋትን በመንከባከብና በማ
+6
✨🌍 ዓለም አቀፍ የመሬት ቀንን በልዩ ሁኔታ አክብረናል! ዛሬ የሚከበረውን ዓለም አቀፍ የመሬት ቀንን ምክንያት በማድረግ የሠራተኛ አምባሳደሮቻችን በእንጦጦ ፓርክ የሚገኙ እፅዋትን በመንከባከብና በማጽዳት ቀኑን በደመቀ ሁኔታ አክብረዋል። ኢትዮ ቴሌኮም የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብርን በንቃት በመቀላቀል፣ ባለፈው ዓመት ብቻ በሠራተኞቹ አማካኝነት ከ500,000 በላይ ችግኞችን በመላ ሀገሪቱ መትከሉ ይታወሳል። ከችግኝ ተከላው ባለፈም ለአካባቢ ጥበቃ ምቹ የሆኑ አረንጓዴ መሠረተ-ልማቶችን (Green Infrastructures) ማለትም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ መሙያ ጣቢያዎችን (EV Charging) እና በፀሐይ ኃይል የሚሰሩ የኔትወርክ ምሰሶዎችን (Solar poles) በማስፋፋት ላይ እንገኛለን። ለቀጣይ ትውልድ የምትመች አረንጓዴ ኢትዮጵያን ለመፍጠር የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥላለን! #EarthDay2026 #Ethiotelecom #NextHorizon #telebirr #telebirrSuperApp #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia

✨🌍 ዓለም አቀፍ የመሬት ቀንን በልዩ ሁኔታ አክብረናል! ዛሬ የሚከበረውን ዓለም አቀፍ የመሬት ቀንን ምክንያት በማድረግ የሠራተኛ አምባሳደሮቻችን በእንጦጦ ፓርክ የሚገኙ እፅዋትን በመንከባከብና በማ
✨🌍 ዓለም አቀፍ የመሬት ቀንን በልዩ ሁኔታ አክብረናል! ዛሬ የሚከበረውን ዓለም አቀፍ የመሬት ቀንን ምክንያት በማድረግ የሠራተኛ አምባሳደሮቻችን በእንጦጦ ፓርክ የሚገኙ እፅዋትን በመንከባከብና በማጽዳት ቀኑን በደመቀ ሁኔታ አክብረዋል። ኢትዮ ቴሌኮም የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብርን በንቃት በመቀላቀል፣ ባለፈው ዓመት ብቻ በሠራተኞቹ አማካኝነት ከ500,000 በላይ ችግኞችን በመላ ሀገሪቱ መትከሉ ይታወሳል። ከችግኝ ተከላው ባለፈም ለአካባቢ ጥበቃ ምቹ የሆኑ አረንጓዴ መሠረተ-ልማቶችን (Green Infrastructures) ማለትም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ መሙያ ጣቢያዎችን (EV Charging) እና በፀሐይ ኃይል የሚሰሩ የኔትወርክ ምሰሶዎችን (Solar poles) በማስፋፋት ላይ እንገኛለን። ለቀጣይ ትውልድ የምትመች አረንጓዴ ኢትዮጵያን ለመፍጠር የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥላለን! #EarthDay2026 #Ethiotelecom #NextHorizon #telebirr #telebirrSuperApp #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia

የኩባንያችን_ኤክስኩቲቭ_ማኔጅመንት_ቦርድ_የአራተኛውን_ሩብ_ዓመት_የአፈጻጸም_ጅማሮ_ላይ_ውይይት_አካሄደ!.pdf3.05 MB

photo content

ዋና_ሥራ_አስፈጻሚያችን_ግዙፍ_የኤሪክሰን_ኔትወርክ_ሰርክል_ማስፋፊያ_ፕሮጀክት_ይፋ_አደረጉ!.pdf1.47 MB

photo content