Ethio telecom Family
Open in Telegram
6 045
Subscribers
-124 hours
-17 days
-2530 days
Posts Archive
6 045
+4
የኩባንያችን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ጋር የሐዋሳን ከተማ ልማት ፕሮጀክት ለማፋጠን ያለመ ስትራቴጂካዊ ውይይት አደረጉ!
በዋና ሥራ አስፈጻሚያችን ፍሬሕይወት ታምሩ የተመራው የኩባንያችን ከፍተኛ ማኔጅመንት ቡድን፣ ከሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ እና ከከተማዋ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በከተማዋ እያስመዘገበችው የሚገኘውን ፈጣን የዲጂታል ዕድገት እንዲሁም የመጻኢ የቴክኖሎጂ ትስስርን ለማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ስትራቴጂካዊ ውይይት አካሂዷል።
ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ ኩባንያችን እያከናወናቸው የሚገኙ መጠነ ሰፊ የሪፎርም ሥራዎችን በማድነቅ፤ በተለይም የኢትዮጵያን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በማፋጠን ረገድ ኢትዮ ቴሌኮም እያበረከተ ለሚገኘው ቁልፍ ሚና እውቅና ሰጥተዋል፡፡
ክቡር ከንቲባው ቀደም ሲል በከተማዋ ለተከናወኑ የልማት ፕሮጀክቶች ኩባንያችን ላደረገው ሁለገብ ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበው፤ ሐዋሳ ከአዲስ አበባ በመቀጠል ዋነኛ የቱሪዝም እና የኮንፈረንስ መዳረሻ እንድትሆን ለማስቻል ያለመ አዲስ የሐዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ውጥን ይፋ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።
Read more
#ዲጂታል_ኢትዮጵያን_ዕውን_በማድረግ_ላይ!
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalEthiopia
#RealizingDigitalEthiopia #SmartCity #Hawassa #DigitalEthiopia
6 045
የኩባንያችን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ጋር የሐዋሳን ከተማ ልማት ፕሮጀክት ለማፋጠን ያለመ ስትራቴጂካዊ ውይይት አደረጉ!
በዋና ሥራ አስፈጻሚያችን ፍሬሕይወት ታምሩ የተመራው የኩባንያችን ከፍተኛ ማኔጅመንት ቡድን፣ ከሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ እና ከከተማዋ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በከተማዋ እያስመዘገበችው የሚገኘውን ፈጣን የዲጂታል ዕድገት እንዲሁም የመጻኢ የቴክኖሎጂ ትስስርን ለማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ስትራቴጂካዊ ውይይት አካሂዷል።
ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ ኩባንያችን እያከናወናቸው የሚገኙ መጠነ ሰፊ የሪፎርም ሥራዎችን በማድነቅ፤ በተለይም የኢትዮጵያን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በማፋጠን ረገድ ኢትዮ ቴሌኮም እያበረከተ ለሚገኘው ቁልፍ ሚና እውቅና ሰጥተዋል፡፡
ክቡር ከንቲባው ቀደም ሲል በከተማዋ ለተከናወኑ የልማት ፕሮጀክቶች ኩባንያችን ላደረገው ሁለገብ ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበው፤ ሐዋሳ ከአዲስ አበባ በመቀጠል ዋነኛ የቱሪዝም እና የኮንፈረንስ መዳረሻ እንድትሆን ለማስቻል ያለመ አዲስ የሐዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ውጥን ይፋ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።
Read more
#ዲጂታል_ኢትዮጵያን_ዕውን_በማድረግ_ላይ!
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalEthiopia
#RealizingDigitalEthiopia #SmartCity #Hawassa #DigitalEthiopia
6 045
የኩባንያችን_ኤክስኩቲቭ_ማኔጅመንት_ቦርድ_ሳምንታዊ_የአፈጻጸም_ክትትል_እና_በተለያዩ_ፕሮፖዛሎች_ላይ_ውይይት.pdf2.78 MB
6 045
ውድ ቤተሰቦቻችን መልካም ቀን! መልካም የሥራ ሳምንት ይሁንላችሁ!
#Monday #Ethiotelecom #telebirr #ZemenGEBEYA #EmpoweringEthiopia’sDigitalFuture&Beyond
6 045
ኩባንያችን_በሁዋዌ_ሰርክል_441_የኔትወርክ_ጣቢያዎችን_ለማዘመንና_ለማስፋፋት_የሚያስችል_ፕሮጀክት_በይፋ.pdf2.15 MB
6 045
የኩባንያችን_ኤክስኪዩቲቭ_ማኔጅመንት_ቦርድ_የበጀት_ዓመቱን_የ11_ወራት_የስራ_አፈጻጸም_በመገምገም፣_ የሰኔ.pdf2.69 MB
6 045
+9
እንኳን ደስ አላችሁ፤ እንኳን ደስ አለን!
ኢትዮ ቴሌኮም ባለአክሲዮኖቹ አክሲዮናቸውን በሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ መሸጥ፣ መግዛት እና ማስተላለፍ እንደሚችሉ በታላቅ ደስታ ያበስራል!
በዛሬው ዕለት የኩባንያችን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ፤ ኩባንያው አስፈላጊ ሕጋዊ አሠራሮችን በማሟላት ባለአክሲዮኖች በሁለተኛ ገበያ (ESX) አክሲዮኖችን መግዛት፣ መሸጥና ማስተላለፍ እንዲጀምሩ ዝግጁ ማድረጉን በይፋ አብስረዋል።
በተለይም ባለፉት ወራት በተከናወነ መጠነ-ሰፊ የማጣራት ሥራ ከ47,377 ባለአክሲዮኖች ውስጥ 45,366ቱ (95.8 በመቶ) ምዝገባቸውን በስኬት ማጠናቀቃቸውን ገልጸዋል። ይህም በገንዘብ ሲሰላ 3.04 ቢሊዮን ብር ዋጋ ያላቸው 10.1 ሚሊዮን አክሲዮኖች ለግብይት ዝግጁ መሆናቸውን ያረጋግጣል ብለዋል።
በዕለቱ የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ተዋናዮች በተገኙበት የአክሲዮን ግብይት ማስጀመሪያ የደወል ሥነ ሥርዓት የተከናወነ ሲሆን፣ የመጀመሪያው ግብይትም በሰነደ ሙዓለ ነዋይ ገበያው በይፋ ተከናውኗል።
ባለአክሲዮኖች አክሲዮናቸውን ለመሸጥም ሆነ ለመግዛት በመጀመሪያ በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ፈቃድ ከተሰጣቸው አገበያዮች ወይም የኢንቨስትመንት ባንኮች ዘንድ በመቅረብ የንግድ አካውንት መክፈት ይኖርባቸዋል።
በመጪው በጀት ዓመት የፋይናንስ ኦዲቱ እንደተጠናቀቀ በሚጠራው የባለአክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባኤ (AGM) ላይ የትርፍ ክፍፍል መጠን ተወስኖ ይፋ ይደረጋል። የባለቤትነት ድርሻቸውን ሂደት ያጠናቀቁ ባለአክሲዮኖች፤ የባለቤትነት መብታቸው ከያዝነው በጀት ዓመት መጀመሪያ ጀምሮ የሚጠበቅላቸው ይሆናል።
ለተጨማሪ መረጃ፦ https://bit.ly/4nROnuL
