Ethio telecom Family
Open in Telegram
6 045
Subscribers
-124 hours
-17 days
-2530 days
Posts Archive
6 045
የኩባንያችን_ኤክስኪዩቲቭ_ማኔጅመንት_የበጀት_ዓመቱን_ማጠቃለያ_ተግባራት_እና_የኢነርጂ_ኤፊሸንሲ_እና_ግሪን.pdf3.12 MB
6 045
ዋና_ሥራ_አስፈጻሚያችን_ለዓለም_አቀፍ_ስደተኞች_የዲጂታል_አካታችነት_እና_ተጠቃሚነት_ያላቸውን_ቁርጠኝነት.pdf2.20 MB
6 045
ውድ ቤተሰቦቻችን መልካም ቀን! መልካም የሥራ ሳምንት ይሁንላችሁ!
#Monday #Ethiotelecom #telebirr #ZemenGEBEYA #EmpoweringEthiopia’sDigitalFuture&Beyond
6 045
በአዲሱ_ቢሮ_ህንጻ_የስራ_ዝግጁነት_እና_በግንባታ_ላይ_ባሉ_ፕሮጀክቶች_አፈፃፀም_ዙሪያ_ውይይት_ተደረገ!.pdf2.82 MB
6 045
ኩባንያችን_በሰው_ሰራሽ_አስተውሎት_የታገዘ_እጅግ_ዘመናዊ_የኢንተሊጀንት_ኦፕሬሽን_ማዕከል_ይፋ_አደረገ!.pdf4.74 MB
6 045
+8
ኩባንያችን የቴሌኮም እና ዲጂታል ደኅንነትን ለማረጋገጥ ያለመ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ለፍትሕ ተቋማት ሰጠ
ኩባንያችን ኢትዮ ቴሌኮም የሀገሪቱን የዲጂታል ደኅንነት ለማስጠበቅ እና የቴሌኮም መሠረተ ልማቶችን ከጥቃት ለመከላከል እንዲቻል፣ ከተለያዩ የፍትሕ ተቋማት ለተውጣጡ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ሀገር አቀፍ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና በተለያዩ ከተሞች ሰጥቷል።
“የኢትዮ ቴሌኮም እና የፍትሕ ተቋማት ጥምረት ለዲጂታል ኢትዮጵያ ደኅንነት” በሚል መሪ-ቃል በድሬደዋ፣ በሐዋሳ እና በአዳማ ከተሞች በተካሄዱት በእነዚህ የሥልጠና መድረኮች ላይ ከፌዴራልና ከተለያዩ ክልሎች የተውጣጡ በአጠቃላይ 171 ዳኞች፣ አቃቤያነ ሕግና የፖሊስ አባላት ተሳትፈዋል።
የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናው ኩባንያችን የ3 ዓመት ስትራቴጂውንና የኢትዮጵያን የዲጂታል ሽግግር ለማፋጠን ከሚያደርገው ግዙፍ የ4ጂና 5ጂ ኔትወርክ መሠረተ ልማቶች ማስፋፊያ ባሻገር የእነዚህን መሠረተ ልማቶች ዘላቂነት ለማስቀጠልና የዲጂታል ሥነ-ምህዳሩን ደኅንነት ለማረጋገጥ ከፍትሕ አካላት ጋር ተቀናጅቶ መሥራት ወሳኝ በመሆኑ የተዘጋጀ ነው።
ሥልጠናው በዋናነት በዲጂታል ፋይናንስና በቴሌኮም ዘርፍ የሚፈጸሙ የማጭበርበር ወንጀሎችን ለመከላከል እንዲሁም በቴሌኮም መሠረተ ልማት ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን በሕግ አግባብ ለመቆጣጠር በሚቻልባቸው ስልቶች ላይ ያተኮረ ነው።
በሥልጠናው ላይ የተሳተፉ የፍትሕ ተቋማት ሀላፊዎችና ባለሞያዎች በበኩላቸው መድረኩ በቴክኖሎጂው ዘርፍ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን ለመረዳትና ተገቢውን የሕግ ምላሽ ለመስጠት ከፍተኛ ግንዛቤ የፈጠረላቸው መሆኑን የገለጹ ሲሆን የቴሌኮም መሠረተ ልማትን እንደ ሀገር ሀብት በመጠበቅና ወንጀሎችን በብቃት በመከላከል ረገድ ከኩባንያችን ጋር በቅንጅት ለመሥራት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል... Read More
6 045
+4
ኩባንያችን እና አፍሬክሲም ባንክ አህጉራዊ የዲጂታል ሽግግርን ለማፋጠን በሚያስችሉ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ላይ ተወያዩ
ኩባንያችን ከአፍሪካ ኤክስፖርት-ኢምፖርት ባንክ (Afreximbank) ከፍተኛ አመራሮች ጋር በዋና መሥሪያ ቤታችን ስትራቴጂካዊ ውይይት ያደረጉ ሲሆን ውይይቱ አዲሱን የምሥራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ ዳይሬክተር ሚስተር ሀምፍሬይ ንውጎን ለመቀበልና የዲጂታል ሽግግርን የሚያፋጥኑ የፋይናንስ አጋርነቶችን ለመፍጠር ያለመ ነው።
በመድረኩ ዋና ሥራ አስፈጻሚያችን ፍሬሕይወት ታምሩ የኩባንያችንን ስኬታማ የትራንስፎርሜሽን ጉዞ፣ ጠንካራ የፋይናንስ አፈጻጸምና ለሀገራዊ ዲጂታል ሽግግር እያበረከትን ያለውን ሚና ለባንኩ አመራሮች ያብራሩ ሲሆን ይህም ኩባንያችን ለማኅበረ-ኢኮኖሚያዊ ዕድገት እያበረከተ ያለውን ቁልፍ ሚና ያመላከተ ነው።
ውይይቱ የባንኩን አህጉራዊ የፋይናንስ አቅም ከኩባንያችን “ቀጣዩ አድማስ” ስትራቴጂ ጋር በማጣጣም ላይ ያተኮረ ሲሆን፤ እንደ ቴሌብር፣ ዘመን ገበያና ክላውድ አገልግሎቶች ያሉ የዲጂታል ሥነ-ምህዳር መፍትሔዎቻችን ላይ እንዲሁም ኩባንያችን ወደ ቀጣናዊ የቴክኖሎጂ ተቋምነት እያደረገ ያለውን ሽግግር የሚያስረዳ ነው።
የባንኩ ልዑክ በፋይናንስ አፈጻጸማችንና በቀጣናዊ የማስፋፊያ ግቦቻችን መደመማቸውን ገልጸው፤ ለረጅም ጊዜ የሚቆይ ስትራቴጂካዊ የፋይናንስ አጋርነት ለመፍጠር ጽኑ ፍላጎታቸውን ገልጸዋል።
ሁለቱም ተቋማት የዲጂታል መሠረተ ልማትን የሚያጠናክሩና አካታች አህጉራዊ ዲጂታል ኢኮኖሚን የሚገነቡ የፋይናንስ አማራጮችን ተግባራዊ ለማድረግ የተስማሙ ሲሆን ይህም በዲጂታል ሽግግር ጥረታችን ውስጥ ትልቅ ተስፋ የሚጣልበት ስትራቴጂካዊ እርምጃ መሆኑ ተመላክቷል።
6 045
+4
የኩባንያችን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ጋር የሐዋሳን ከተማ ልማት ፕሮጀክት ለማፋጠን ያለመ ስትራቴጂካዊ ውይይት አደረጉ!
በዋና ሥራ አስፈጻሚያችን ፍሬሕይወት ታምሩ የተመራው የኩባንያችን ከፍተኛ ማኔጅመንት ቡድን፣ ከሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ እና ከከተማዋ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በከተማዋ እያስመዘገበችው የሚገኘውን ፈጣን የዲጂታል ዕድገት እንዲሁም የመጻኢ የቴክኖሎጂ ትስስርን ለማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ስትራቴጂካዊ ውይይት አካሂዷል።
ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ ኩባንያችን እያከናወናቸው የሚገኙ መጠነ ሰፊ የሪፎርም ሥራዎችን በማድነቅ፤ በተለይም የኢትዮጵያን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በማፋጠን ረገድ ኢትዮ ቴሌኮም እያበረከተ ለሚገኘው ቁልፍ ሚና እውቅና ሰጥተዋል፡፡
ክቡር ከንቲባው ቀደም ሲል በከተማዋ ለተከናወኑ የልማት ፕሮጀክቶች ኩባንያችን ላደረገው ሁለገብ ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበው፤ ሐዋሳ ከአዲስ አበባ በመቀጠል ዋነኛ የቱሪዝም እና የኮንፈረንስ መዳረሻ እንድትሆን ለማስቻል ያለመ አዲስ የሐዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ውጥን ይፋ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።
Read more
#ዲጂታል_ኢትዮጵያን_ዕውን_በማድረግ_ላይ!
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalEthiopia
#RealizingDigitalEthiopia #SmartCity #Hawassa #DigitalEthiopia
