en
Feedback
𝑹𝙖𝙢𝙖𝙨 𝑨𝑳-𝑯𝒂𝒏𝒂𝒏𝒊 (ራማስ)

𝑹𝙖𝙢𝙖𝙨 𝑨𝑳-𝑯𝒂𝒏𝒂𝒏𝒊 (ራማስ)

Open in Telegram

وَقُلْ جَاءَ الْحَقُّ وَزَهَقَ الْبَاطِلُ ۚ إِنَّ الْبَاطِلَ كَانَ زَهُوقًا በልም «እውነት መጣ ውሸትም ተወገደ፤ እነሆ ውሸት ተወጋጅ ነውና፡፡» 🎙 ራማስ ኢብኑ በድሩ 🍃

Show more
4 239
Subscribers
No data24 hours
-207 days
-9230 days
Posts Archive
#ጥቆማ ማንኛውም አይነት ከሸሪዓ ጋር የማይጋጩ የስራ ማስታወቂያዎችን በአንድ ፕላትፎርም ላይ ማግኘት ከፈለጉ Halal Jobsን ይቀላቀሉ! አዲስ ስራ ለሚፈልጉ፣ ስራ መቀየር ላሰቡና የተሻለ የስራ አማራጭ ለሚፈልጉ ሐላል ጆብስ ቤታቸው ነው። እንዲሁም ቀጣሪዎች የስራ ማስታወቂያቸውን በነፃ እንዲለቁበት በማሰብ የተዘጋጀ ፕላትፎርም ነው! ይወዳጁን! ይከታተሉን! ወዳጅዎንም ይጋብዙ! ያተርፉበታል! ቻናል👉  t.me/HalalJobsEth

በጣም አስቂኝ ክስተት አንብቡት የመን ውስጥ ዘማር የተባለ ቦታ ላይ አንድ መስጂድ ውስጥ የተከሰተ በጣጣጣም አስቂኝ ክስተት ነው 👍 አንብበው ሳይጨርሱ በሳቅ ሟቋረጥ ግን አይቻልም ¡¿ ይህ ክስተት እዚያው መስጂዱ ውስጥ ሰፈል አወል(የመጀመሪያው ሰፍ ) ላይ ቆሞ ሲሰግድ የነበረ አንድ ሰጋጅ ነው የሚያስተላልፍልን እናም ይህ ሰው እንዲህ ይለናል :- አንድ ሰው ይሞትና ተሰግዶበት ተቀበረ ከዚያም ከኢሻ ሶላት በኋላ ነእሹ (ጀናዛ መሸከሚያው) ሊመልሱት ይዘውት ወደ መስጂድ ሲመጡ ሰአት ሄዶ ስለነበር መስጂዱ ተዘግቷል ስለዚህ ኻዲሞች ለፈጅር ሶላት ሲመጡ እንዲያነሱት በሚል ጀናዛ መሸከሚያው ከመስጂዱ በር ከደረጃ ላይ ያስቀምጡታል ነገር ግን ሌሊት 9:30 ሰአት አካባቢ አንድ ሰውዬ ወደ መስጂድ ሲመጣ መስጂዱ ዝግ ሆኖ እና በረንዳው ተከፍቶ አገኘው የተወሰነ ቢጠብቅም መስጂዱን የሚከፍተው አጣ ብርዱ በጣም ሲበረታበት ዞር ብሎ ሲያይ ጀናዛ መሸከሚያው ከአጠገቡ አገኘ በውስጡም ብርድልብስ ነገር አለ እና ይህ ሰው አገኘሁ ብሎ ጀናዛ መሸከሚያው ውስጥ ብርድልብሱን ለብሶ ለጥ ብሎ እንቅልፉን ተኛ አባቴ ! በብርድ ደንዝዞ የነበረው ሰውነቱ ትንሽ ምቾት ሲያገኝ ነፍሱንም አያውቅ ለጥ ብሎ ተኝቶልሀል ክክክ ትንሽ እንደቆየ የመስጂዱ ኻዲም መጥቶ መሲጂዱ ሊከፍት ሲል በረንዳ ላይ ከነእሹ(ጀናዛ መሸከሚያው) ላይ የተኛ ሰውዬ ይመለከታል ከፈጅር በኋላ ሊሰገድበት ያመጡት ጀናዛ መሰለው ከኋላውም ሌሎች ሰዎች መጥቶ ግማሹ ሽንት ቤት ሌላው ውዱእ ሊያደርግ ይሄዳሉ ይህ በረንዳ ላይ ተኝቶ የሚያዩት ሰውዬ ( ጀናዛ) ደግሞ ሁሉም ቀድሞኝ የመጡ ሰዎች ሊሰገድበት ያመጡት ጀናዛ ነው ብሎ ያስባል በውስጡ በዚያ ላይ ፈጅር ነው ሰው ከእንቅልፉ ተነስቶ እየመጣ ነው ያለው ገና በደንብ ያልነቃ ህዝብ ነው ሊሰገድበት የመጣ ጀናዛ ይሆናል በማለት ተጋግዘው ወደ መስጂድ ኢማሙ ጋር ወደ ሚህራብ አስገቡት ክክክ ይህ ብርድ የቀጠቀጠው ሰውዬ ሲሸከሙት አያውቅ ተኝቷል ሰዎቹም የማን ይሁን ብለው አይጠይቁ ገና ከእንቅልፋቸው በደንብ አልነቁም እና ተሸክመው መስጂድ ውስጥ አስገቡት ፈጅር አዛን ብሎ ለመስገድ ወደ 50 የሚሆኑ ሰዎች ተሰበሰቡ 👌 ይህንን ታሪክ የሚያስተላልፍልን ሰው እኔም ከሰጋጆቹ አንዱ ነኝ የመጀመሪያው ሰፍ ላይ ነበርኩ ይላል ከፈርድ በኋላ ልንሰግድበት ጀናዛው ከፊት ተደርጎ የፈጅር ሶላት እየሰገድን ነው ክክክ ልክ ለሁለተኛው ረከአ ስንነሳ ጂናዛው ሲንቀሳቀስ አየሁ እንዴዴዴ አይኔ ነው ወይስ ምንድ ነው ብዬ አይኔን አበስኩ ጨፍኜም ገለጥኩ መንቀሳቀሱ ግን አልተወም በቃ እንቅልፍ አለቀቀኝም ይሆናል ብዬ አሰብኩ ነገር ግን ነእሹ በደንብ መንቀሳቀስ ጀመረ ያኔ መረባበሽና መፍራት ጀመርኩ ይህ የተኛው ሰውዬ ከብርድልብሱ ውስጥ ድንገት አንገቱ አውጥቶ ሰገዳችሁ ❓ ብሎ ጠየቀ ወ ያኔ ሁሉም ሰጋጆች ደንግጦ መተረማመስና መሮጥ ጀመሩ እኔም አጠገቤ ከነበረው በር ወጥቼ በባዶ እግሬ ሮጥኩኝ ወደ 1 ኪ.ሜ ያክል የሚርቀው ቤቴ በትንሽ ደቂቃዎች ደረስኩ ደግሞ ባዶ እግሬ መሆኔም የማውቀው ነገር የለም ኢማሙ( አሰጋጁንም ) ሳየው ደንግጦ መሬት ላይ ወድቋል ሌሎች ሰዎች ግማሹ ከግድግዳ ጋር ይጋጫል ሌላው ደግሞ ልክ እንደኔው በባዶ እግሩ ይሮጣል መስጂድ ውስጥ አንድ ሰው አልቀረም አሁንም ሌላኛው በጣጣጣም የሚያስቀው ክስተት ተከሰተ ያ ከሬሳ መሸከሚያ(ከነእሹ) ላይ ተኝቶ የነበረው ሰውዬ ሲነሳ ሰዎች ሲሸሹ ሲሮጡ ሲያይ ከኋላቸው ተከትሎ መሮጥ ጀመረ እናንተ ምን ሆናችሁ ነው ? ቂያማ ቆሞ ነው እንዴ ❓ እያለ ከኋላ ኋላቸው መሮጥ ጀመረ ክክክ ሰዎቹ ደግሞ ወደ ኋላቸው ሲዞሩ ይህ ሰውዬ እየተከተላቸው መሆኑ ያያሉ ያኔ ይብስባቸዋል ባለ በሌለ ሀይላቸው ይሮጣሉ በዚህ መልኩ ሁሉም ሰላታቸውን አቋርጠው ሮጡ ይለናል ቦታው ላይ የነበረ አንዱ ሰጋጅ መቼስ ይህንን አንብቦ በሳቅ ያልደከመ ይኖራል ? እኔ እንጃ በድጋሜ የተፖሰተ (®) ✅ ለማንኛውም ሼር ማድረግ ይቻላል https://t.me/FKR_ESKE_JENET

የኔ እህት ነገሮችን ለማሳካት ደፋ ቀና ትያለሽ ነገር ግን ምንም ጠብ የሚል ነገር የለ ይሆናል፤ ደስተኛ ሆንኩ ስትይ ያላሰብሽው ነገር መጥቶ ደስታሽን ያጠፋው ይሆናል ፤ ትክክለኛ የኔን ሰው አገኝሁ ብለሽ ሳታበቂ መከዳት ሊገጥምሽ ይችላል፤ ከሰዎች መጥፎ ባህሪ የተነሳ መግባባት አቅቶሽ ብቸኝነትን መረጥሽ ይሆናል፤ ሰኬትን ሰትናፍቂ በነገሮች አለመሳካት ተሰፋ ቆርጠሽ ይሆናል፤ ሰዎች ፊት እየሳቅሽ በውስጥሽ እንባ ታነቢ ይሆናል። ብዙ  ነገሮች ትሆኝ ይሆናል ........ ነገር  ግን ልብ በይ እህቴ አሏህ የሚወዳቸውን ባኖቹን ይፈትናል። ዞር ብለሽ እስኪ የነብያቶችን ታሪክ አዳምጭ አጥኝ ምን አይነት ችግር እንደደረሰባቸው ፤ምን አይነት መከራ እንዳዩ ፤ የሳሀባዎችን ፅናት አስታውሽ፤ ዱኒያ የመንገደኞች ግዜያዊ ማረፊያ ጥላ እንጂ የመጨረሻ ሀገራችን አይደለችም ። የመጨረሻውን አገርሽን ስንቅ ብቻ ያዥ። ዱኒያ የቱንም ያክል ብታምር  ጠፊ ናት። ''ብልጥ (ጮሌ) ብሎ ማለት ነፍሡን ሂሳብ የሚያደርግና ለአሄራ ቤቱ የሚለፋ ሰው ነው '' እናም ከጮሌዎቹ ሁኝ ጀግናየ !!! ሰላም ባንች ላይ ይሁን !!! 🤚 ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌ ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌┄┅┅┄┅✶🌹✶┅┄┅┅┄  🍃 https://t.me/FKR_ESKE_JENET

መውሊድ ቢድአ ነው፤ ቢድአ ሁሉ ጥመት ነው ፤ ጥምት  ሁሉ የእሳት ነው ተብሏል። ስለዚህ መውሊድ መጥፎ መሆኑ እየታወቀ የሚያከብር ያክብር የማያከበር አያክብር አይባልም። ሀቁን መናገር  ግዴታ ነው፤ መውሊድ አያጣላንም የሚሉ ኡስታዞች ሀቁን መናገር ሲያቅታቸው እና ጥቅማቸው  እንደይነካ ሰለሚፈልጉ ነው። ሀቁ ግን መጥፎውን መከልከል በመልካም ማዘዝ እንጂ መጥፎ ሲስራ እያዩ አያጣላንም አይደለም የሚባለው። አያጣላንም ማለት በተዘዋዋሪ መጥፎውን ብሰሩት ችግር የለውም እንደማለት ነው ። አሏህም  እንዲህ  ይለናል :- كُنتُمْ خَيْرَ أُمَّةٍ أُخْرِجَتْ لِلنَّاسِ تَأْمُرُونَ بِالْمَعْرُوفِ وَتَنْهَوْنَ عَنِ الْمُنكَرِ ........ ለሰዎች ከተገለጸች ሕዝብ ሁሉ በላጭ ኾናችሁ በጽድቅ ነገር ታዛላችሁ፤ ከመጥፎም ነገር ትከለክላላችሁ፤ ...... አሏህ ከመጥፎ ነገር ከልክሉ በጥሩ ነገር እዘዙ  እያለ ወዴት ነው ሀቁን ከመናገር የሚሸሸው ? መውሊድ  ቢድአ ነው በማለት ፈንታ አያጣለንም የሚባለው ??? ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌┄┅┅┄┅✶🌹✶┅┄┅┅┄ https://t.me/FKR_ESKE_JENET

ወዮ¡ የሙሀባው ምርቃና ከቁጥጥር ውጪ ሲሆን የምታሳየው ልዩ ከራማዊ አክሺን ይሄን ይመስላል .......ክክክ https://t.me/FKR_ESKE_JENET
ወዮ¡ የሙሀባው ምርቃና ከቁጥጥር ውጪ ሲሆን የምታሳየው ልዩ ከራማዊ አክሺን ይሄን ይመስላል .......ክክክ https://t.me/FKR_ESKE_JENET

መውሊድና ሰሜት ምን አገናኛቸው ? ይድረስ ለመውሊድ አክባሪዎች ❗️ ★ መውሊድ ማክበር በድናችን ቢድአ ከመሆኑንም ጋር  የተለያዩ ሽርክያቶች የሚሰሩበት የሽርክ ገብያ ነው! ብል ማጋነን አይሆንብኝም፡፡ ከመውሊድ ጋር በተያየዘ  በተለያዩ ግዜና ወቅቶች ቡዙ ነገር  ተብሏል ብዙም ተነግሮል፡፡ ሀቅን ለሚፈልግ ሰው በቂ በነበረ ነበር ,ግና ሰሜታዊትት አይናቸውን ከሸፈነው ቆይቶልና ሀቅን መገንዘብ ገደልን  በአይነ ስውርነት አንደ መውጣት ሆኖባቸዋል። ታዲያ እኛም የአላህ እዝነት ሰፊ ነውና  መፃፍችንን አላቆምንም ። አላህ ሱብነሁ ወተአላ እነዚያ ብዙ ግዜያትን ሀቅን ከመገንዘብ ወደ ኀላ ያሉ ሰዎችን  ሲገልፅልን እንዲህ ይለናል ✡إِنَّ الَّذِينَ كَفَرُوا سَوَآءٌ عَلَيْهِمْ ءَأَنذَرْتَهُمْ أَمْ لَمْ تُنذِرْهُمْ لَا يُؤْمِنُونَ✡خَتَمَ اللَّهُ عَلٰى قُلُوبِهِمْ وَعَلٰى سَمْعِهِمْ ۖ وَعَلٰىٓ أَبْصٰرِهِمْ غِشٰوَةٌ ۖ وَلَهُمْ عَذَابٌ عَظِيمٌ✡ እነዚያ የካዱት (ሰዎች )  ብታስፈራራቸም ባታስፈራራቸውም በነርሱ ላይ አኩል ነው አያምኑም  ✡ አላህ በልቦቻቸው ላይ በመስሚያቸውም ላይ አትሞባቸዋል በአይኖቻቸውም ላይ መሸፈኛ አለ ፡ ለነሱም ታላቅ ቅጣት አላቸው ፡፡ መውሊድ አንደሚታወቀው የተጀመረው በግብፅ በፋጢሚዪች ነው ፡፡ ከዚያ በፊት መውሊድ  አይታወቅም ይህ ከመሆኑ ጋር  አናንተ መጤ ናችሁ ሲሉ ይሞግታሉ! አላህ ያሳያችሁ መጤ የሚባሉት ሰዎች በድን ላይ ያመጡት ነገር ምን ይሆን ? እነሱ አዲስ አሰገኝተው ሲያበቁ በተቃራኒው ሲሞግቱ ስታዩ በርግጥም ገርሞ የሚገርም ነው፡፡ አላህ አይኖቻቸውን አትሞባቸዋል ያስብላል፡፡ ማን ነው መጤው (አዲሱ) ❓ ይህ ጥያቄ ይሰመርበት እነዚያ (ወሀብያ )የሚል ስያሜ የተሰጣቸው ወይስ መውሊድ አክባሪዎች  እንመልከት ወሀብዮች በድን ላይ ምንን አዲስ ተግባር ጨምረዋል ይመለስልን ? ለነገሩ መልሱ ለማንም አይሰወርም ምንም የተጨመረ አዲስ ነገር የለም "ጭማሪ በሙሉ (ቢድአ)  ሰለሆነ ቢድአ ደግሞ ጥመት መሆኑን ሰለተገነዘቡ አይጨምሩም ፡፡ ነገር ግን አዲስ መጤ አያሉ የሚሞግቱት አህባሽና ሱፍያ  አውነት የድሮ ናቸው ?  ይህ ግልፅ ነው አይደሉም ፡፡ ምክኒያትም መውሊድ የመጣው አሁን ነው ፡፡  ታዲያ እናንተ መጤ ሆናችሁ ሳለ  በምን ሚዛን ነው መጤወች የምትሉት ? አያችሁ ሰሜት መከተል ከመውሊድ ጋር ተገናኘ ይሉሀል ማለት ይህ ነው ፡፡ ለመሆኑ መውሊድ ይከበር ብለው የሚሞግቱት ለምን ይሆን ❓ -ነብያቺንን ሰለምንወድ -ሚስኪንን ለማብላት እነዚህ መልሶቻቸው በዋናነት ይጠቀማሉ ግና የእነሱ ስራ በተቃራኒው ነው ፡፡  በነብዩ ውዴታ ፈንታ ☞ ጭፈራ ዘፈን፤ ጫት                    ☞ ከአላህ ሌላ ማምለክን                   ☞ ወንድና ሴት መቀላቀልን የሚወዱ የጎታ ጨለማዎች ናቸው ፡፡ ምንም እንኳን በሀቅ ብታበራ ብርሀኑ የለም ብለው የሚሞግቱ ሰዎች ናቸው ፡፡ ተመልከቱ ሌለው ደግሞ ተነስቶ ሚስኪን ላበላ ይላል ኧረ ለመሆኑ ሚስኪኖች በአመት አንዴ ብቻ ነው እንዴ አብሉ የተባለው ? መቺስ ሀቅ ነው አወ  አትለኝም ፡፡ ታዲያ ለምን አንድ ቀን መረጣችሁ? ነብዩ በተወለዱበት ቀን ብቻ አብሉ የሚል ሰለሌለ ፡፡ ወሀብያ በሚል ሰም የሚጠሩት ሰዎች እውን መጤ ናቸውን ? ወሀብያ የሚለውን ሰያሜስ ማን አመጣው ? ወሀብያ የሚለው ሰያሜው የተወሰደው ሼክ ሙሀመድ አብዱል ወሀብ ከሚለው ከታላቁ ሼክ ነው ፡፡ የሰየሙትም ራሳቸው አህባሽና የሱፍያ አንጃወች ናቸው ፡፡( መውሊድ አክባሪዎች )  ታዲያ እኚህ ሼክ ሰማቸው ሙሀመድ ሆኖ ሳላ የአባታቸውን ስም መጠቀም ለምን አሰፈለገ  የሚል ጥያቄ ያስነሳል፡፡ አወ ሙሀመድያ የሚለውን ስም መጠቀም አይፈልጉም ለምን ነብያችንን ሙሀመድ  አለሂሙ ሰላት ወሰላምን እኖዳለን ብለው ስለሚሞግቱ ሰለዚህ ወሀብያ የሚለውን ሰያሜ መረጡ ። ግና አላህ ይህን መጥፎ ሰራቸውን አይቶ ወሀብ የሚለውን የአላህ ሰም ለአማኞቹ አደረገ ፡፡ አልሀምዱ ሊላህ ወሃብ  የላህ ሱብሀነ ወተአላ ስም ነው ፡፡ ማንም ማየትና አይቶ ማረጋገጥ ይችላል፡፡ ግና  መጀመሪያ ይህን ቢረዱ ኖሮ ወሀብያን ሳይሆን መሀመድያን በመረጡ ነበር ፡፡ ምንም አንኳን ስያሜውን (ወሀብያ ) ከእናንተ የመጣ ቢሆንም  አልሀምዱ ሊላህ ለአላህ ምስጋና ይገባው ! ወደሱ ስም አስጠጋን !! ለመሆኑ ሼኩ ምን አጥፍተው ነው ይህ ሁሉ የሚቀጠፍባቸው ❓ ይሰመርበት ሼኩ እንደሚታወቀው  የቢድአ ጠላትና ሸርክን በአለህ ቁርአንና ሀዲስ ከስሩ የነቀሉ  ታላቅ ሼክ ናቸው፡፡ ሼኩ ማስረጃቸውን ከቁርአን ከሀዲስ በመውሰድ  ነው  የሚናገሩት  ለዛም ነው ከሰሜታቸው ጋር ያልገጠመው ፡፡ ገና እኝህ ሼክ ከሰሜታቸው ጋር ሰላልተስማሙ በሳቸው ላይ መቅጠፉን ታያይዘውታል ፡፡ ቢሆንም አልሀምዱ ሊላህ ሰንቱ እውነትን አውቆ ተመልሶል የተቀሩትንም አላህ ሂዳያ ይስጣቸው ፡፡ ዛሬ መዉሊድ ያላከበረ ወሀብያ ነው ! በእናንተ አረዳድ ወሀብያ ደግሞ ለእናንተ ካፊር ነው ፡፡ ታዲያ እነዛ  ታላቅ ሳሀብዩቺ መዉሊድ አላከበሩም እነሱም ወሀብያ ናቸው? ይህን ከማለት በአላህ አንጠበቃለን ? ምክንያቱም በእናንተ አነጋገር መውሊድ ያላከበረ ወሀብያ ካፊር ነው ፡፡ ሰለዚህ እነ -አብ-በከር -ዑመር -ዑስማን -አሊይ -አስርቱ በጀነት የተበሰሩት ሰሀቦች -የነብዩ ሚስቶች አራቱ የመዝሀብ ባለቤቶች -አቡ ሀኒፍ -ኢማሙ ማሊክ -ኢማሙ  ሻፊኢ -ኢማሙ አህመድ ሙሀዲሶች -ቡኻሪ -ሙስሊም -ቲርሚዚ -ኢብኑ ማጃህ ከላይ የጠቀስኩልህ በሙሉ መውሊድ አያከብሩም ታዲያ እነዚህን ወዉሊድ ባለማክበራቸው ካፊር ልትላቸው ይሆን ? አላህ ይጠብቀን በርግጥም አላህ ልቦቻችሁን ዘግቶባችኀል! መቼም ካፊር ናቸው አትሉኝም አቃለሁ ታዲያ በምን ሚዛንህ መዝነህ ነው ? አንተ መውሊድ ካለከበርክ ካፊር ነህ የምትለው ፡፡ እነሱ አላከበሩም አላከብርም !!! አሏህ እንዲህም ይለናል፦ «وَمَن يُشَاقِقِ الرَّسُولَ مِن بَعْدِ مَا تَبَيَّنَ لَهُ الْهُدَىٰ وَيَتَّبِعْ غَيْرَ سَبِيلِ الْمُؤْمِنِينَ نُوَلِّهِ مَا تَوَلَّىٰ وَنُصْلِهِ جَهَنَّمَ ۖ وَسَاءَتْ مَصِيرًا» «ቅኑም መንገድ ለርሱ ከተገለጸ በኋላ መልክተኛውን የሚጨቃጨቅና ከምእመኖቹ መንገድ ሌላ የሆነን የሚከተል ሰው፣ (ከዚህ ዓለም) በተሾመበት (ጥመት) ላይ እንሾመዋለን (በመረጠው ላይ እንሾመዋለን!)፤ ገሀነምንም እናስገባዋለን፤ መመለሻይቱም ከፋች» ለእኛ የተመረጠልንና የተወደደልን እውነተኛ የሆነ ሁለንተናዊ ሙሉዕ እምነት እስልምና መሆኑን እንዲህ ሲል ይነግረናል፦ «الْيَوْمَ أَكْمَلْتُ لَكُمْ دِينَكُمْ وَأَتْمَمْتُ عَلَيْكُمْ نِعْمَتِي وَرَضِيتُ لَكُمُ الْإِسْلَامَ دِينًا ۚ » «ዛሬ ሃይማኖታችሁን ለእናንተ ሞላሁላችሁ። ጸጋዬንም በናንተ ላይ ፈጸምኩ። ለናንተም ኢስላምን ከሃይማኖት በኩል ወደድኩ።» አሏህ ሃይማኖታችሁን ሞላሁላችሁ እያለ አንተ ጎሏል ትላለህ ? በቃል ባትናገሩም ተግባራችሁ ይናገራል ። አሏህ የሞላውን ዲን ትተህ ምን ፍለጋ ነው መውሊድ የምታከብረው ? https://t.me/Ramas_alhanani

የትላንቱን ያህል ላንዋደድ እንችላለን የትላንቱን ያህል በልቦቻችን መካከል የነበረው መተሳሰር ያን ያህል ጠንካራ ላይሆን ይችላል። ብዙ አለመግባባቶች ተፈጥረዋል ። ተለያይተናል ተራርቀናል። ነገር ግን በመካከላችን የነበሩትን መልካም ጊዜ አንረሳም። ያሳለፍናቸውን እነዚያን ደግ ቀናት አንዘነጋም። ۚ وَلَا تَنسَوُا الْفَضْلَ بَيْنَكُمْ ۚ إِنَّ اللَّهَ بِمَا تَعْمَلُونَ بَصِيرٌ መካከላችሁም ችሮታን አትርሱ፤ አላህ የምትሠሩትን ሁሉ ተመልካች ነውና፡፡ ይላል አላህ (ሱብሀነ ወተአላ ) በቁርአን  ውስጥ። አንዳንድ  ሰወች አሉ ከወዳጆቻቸው ጋር በተፈጠሩ የተወሰነ አለመግባባቶች ብቻ ትላንት አብረው  እንዳልበሉ  አብረው  መልካም  ግዜያቶችን እንዳላሳለፋ ክብራቸው ላይ ሚረማመዱ ሚስጥራቸውን ባደባባይ የሚያሰጡ አንዳንድ ሰወች አሉ። ይሄ  ግን  ተገቢ አልነበረም። حتى لو كنت في فراق، كن جميلا በመለየት ውስጥ እንኳ ብትሆን ውብ ሁን ! እጂግ ከባዱ ነገር መለየት ነው ።ስትለይ እንኳን  ውብ ሁን። አልሃምዱሊላህ አላ ኒእመቱል ኢስላም !          ••●🍃🌹🍃●•• https://t.me/FKR_ESKE_JENET

تلاوة خاشعة🌷من سورة النساء .. 🍃 ራሀቱል ቀልብ 🍃 https://t.me/Ramas_alhanani

تلاوة خاشعة🌷من سورة النساء .. ራሀቱል ቀልብ 👇 https://t.me/Rahetulqelb

ማስታወቀያ ለ 👉ቻናል የሱና ቻናል ተደራሽነትና ተከታዮች ይጨምሩ ዘንዳ የቻናል ሊንክ መላክ ትችላላችሁ  ✍መስፈርት 1/ :- የሱና ቻናል ሊሆን ስለማጣራ ✍መስፈርት  2/:-  ከ1.5k member በላይ ✅ ከዛበታች ❌ ✍መስፈርት 3/:-  ቻናሉን አይቼ አሳውቃቹኋለሁ 👉 @twhidfirst1 👈 👉 @twhidfirst1 👈