en
Feedback
ዶ/ር ምህረት ደበበ

ዶ/ር ምህረት ደበበ

Open in Telegram

በዚህ ቻናል የተለያዩ የሳይኮሎጂ ምክሮች እና ሀሳቦች ይነሳሉ፡፡ ✔የሳይኮሎጂ ምክር ✔አጫጭር ታሪኮች ✔የታዋቂ ሰዎች አጫጭር አባባሎች <<...ካመለጠ ትናንት ያልመጣ ነገ ይሻላል። በእጅ ያለ ዛሬ ግን ከሁሉም ይበልጣል።...>>

Show more
3 458
Subscribers
-224 hours
+87 days
-1230 days
Posts Archive
ሁለት ሰዎች በአንድ ሆስፒታል ክፍል ውስጥ አልጋ ይዘው ተኝተዋል፡፡ ሁለቱም በጠና ታመው በአምላክ እጅ ተይዘዋል። አንደኛው ሳንባው የቋጠረውን ውሀ ለማድረቅ ሲባል ለሰአታት ያህል አልጋው ላይ ቁጭ እንዲል ይደረጋል ከመስኮት አጠገብ ነው። ሌላኛው ህመምተኛ ደግሞ በተቃራኒው ለሰአታት በጀርባው እንዲተኛ ይደረጋል። እነዚህ ህሙማን በቆይታቸው ብዙ ተጨዋውተዋል። ስለ ቤተሰቦቻቸው፣ ስለ ኑሯቸው፣ በወታደር ቤት ስለሰጡት አገልግሎት፣ የእረፍት ጊዜያቸውን የት እንደሚያሳልፉ... ወዘተ አውርተዋል። ከመስኮት አጠገብ ያለው ህመምተኛ ቁጭ በሚልበት ሰአት ወደ ውጭ እየተመለከተ ሁሉን ነገር በጀርባ ለተኛው:ሰው ይገልጽለታል። በሚያማምሩ ዛፎች የተከበበ ሀይቅ ይታየኛል ... በሀይቁ ላይ ዳኪዬዎች ይዋኛሉ...... ህጻናት ደግሞ ከወረቀት የሰሩትን መርከቦች በሀይቁ ዳርቻ በማስቀመጥ ይጫወታሉ... ፍቅረኛሞች በአንድ እጆቻቸው አበባ በሌላው ደግሞ ተቃቅፈው ሀይቁን ይዞራሉ .. ከሀይቁ ባሻገር ውብ የሆነ ከተማ ይታየኛል ህፃናቶችም በደስታ ይቦርቃሉ " በማለት ዘወትር የሚያየውን ሁሉ በሚያምር አገላለፅ ይተርክለታል! ... በዚህ አይነት ሁኔታ ሳምንታት አለፉ አንድ ማለዳ ነርስዋ ገላቸውን ልታጥብ ውሀ ይዛ መጣች። ከመስኮት አጠገብ ያለው የተቀመጠው በሽተኛ ግን በህይወት አልነበረም። በጣም ደነገጠች። ጓደኛውም እንዲሁ አዘነ። ነርስዋ አስከሬኑን በቶሎ እንዲያነሱ ሰዎች ሌሎች ነርሶችን ጠርታ አዘዘቻቸቸው! ያ ብቻውን የቀረው በጀርባው የተኛው በሽተኛ አልጋውን ከመስኮቱ አጠገብ እንዲወስዱለት ጠየቀ። ወሰዱለት። ሟች የነገርውን በሙሉ በመስኮት ለማየት በጣም ቸኩሏል። ቀና ብሎ ወደ ውጭ ተመለከተ። ከመስኮቱ ባሻገር ያለው ጥቁር ቀለም የተቀባ ግድግዳ ብቻ ነው። ደነገጠ!!! "ምን ሆንክ?" አለቸው ነርሰዋ። "ሰዉዬው ብዙ አስደሳች ነገሮችን በዚህ መስኮት አሻግሮ ይመለከት ነበር" አላት። "ኧረ ሰዉዬው ማየት የማይችል አይነስውር ነበር" ስትል በመገረም መለሰችለት፡፡ ልብ የሚነካ ነገር.. ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ። ለካስ እሱን ለማስደሰትና የመኖር ተስፋ ለመስጠት ነበር ያን ሁሉ ነገር ፈጥሮ የሚያወራው። አንዱን ለማጠንከር ወይም ለማበርታት የኛ ጥንካሬና ብርታት አስፈላጊ ነው። ለሰወች ደግ ነገር በማድርግ የተጨነቀ አምሮአቸውን እረፍት እንስጠው:: 😘@mihret_debebe 😘 😍@mihret_debebe 😍 ❤️❤️@mihret_debebe❤️❤️ 💚💛❤️

ግመልን ስትጠይቅ ቀበሮነትህን አትርሳ ግመሉ ወንዙን እንደተሻገረ ቀበሮውም ለመሻገር መጣና ስለወንዙ ጥልቀት ለማወቅ ከወንዙ በወድያኛው ዳር ያለውን ግመል ጠየቀው። ግመሉም ጥልቀቱ ጉልበት ድረስ እንደሆነ ነገረው። ቀበሮውም ጉልበት ድረስ ከሆነማ አያሰምጠኝም በማለት ለመሻገር ወደ ወንዙ ገባ። በሚያሳዝን ሁኔታ ወንዙ ያሰምጠው ጀመረ። ይሄኔ ቀበሮው ግመሉ እንደሸወደው ተረዳና እንደምንም ተፍጨርጭሮ ወደ ነበረበት ተመለሰ፤ ራሱንም ከሞት አተረፈ። ይሄኔ በንዴት ጮክ ብሎ "አንተ ያምመሀልን? ጥልቀቱ ጉልበት ድረስ ነው አላልክምን?" አለው። ግመሉም "አዎና! ታዲያ በራሴ ጉልበት ነው እንጂ ያልኩህ ባንተ ጉልበት መች አልኩህ?" በማለት መለሰለት። ቀበሮው በልምድ የቀደመውን አካል መጠየቁ ትክክል ቢሆንም የግመሉን ማንነት መርሳቱ ግን ስህተት ነበር። ግመሉም ልምዱን ማካፈሉ ትክክል ቢሆንም የቀበሮውን ማንነት ግን መርሳት አልነበረበትም። ሁለት ሰዎች ሲነጋገሩ እንደየራሳቸው ተሞክሮ ቢነጋገሩም የአንዱ ልምድ ለሌላው መፍትሔ ሊሆን ግድ አይደለም። ባይሆን የአንደኛውን የህይወት ልምድ ለሌላኛው መጥፊያው ሊሆን ይችላልና ጥንቃቄ ማድረጉ ግድ ይላል። ለምሳሌ አንድ ሁለት ሴቶች አረብ ሀገር ሰርተው ተመልሰው ውጤታማ ቢሆኑ ሁሉም አረብ ሀገር የሄደ ሰው ውጤታማ ይሆናል ማለት አይደለም፡፡ ስለዚህ የሰዎችን የህይወት ተሞክሮ ወደ እራሳችን ህይወት አምጥተን ለመትግበር ስንዘጋጅ ማስተዋልና ጥንቃቄ አይለየን፡፡ 😘@mihret_debebe 😘 😍@mihret_debebe 😍 ❤️❤️@mihret_debebe❤️❤️ 💚💛❤️

የጉብዝና ጊዜ 👉ሰው ህፃን ሳለ እና በእርጅናው ገዜ የሚመራው በስሜታዊነት ነው። ምክንያቱ ደግሞ ሁለቱ የእድሜ ክልሎች ላይ ስንደርስ ከማይንዳችን ይቀልጡን መስራት የሚጀምረው ስሜታዊ የሆነው የአይምሮአችን ክፍል ስለሆነ ነው። ህፃናት ለስሜታቸው እና ለፍላጎታቸው በጣም ቅርብ ናቸው። ምክንያቱም የማገናዘብ አቅማቸው በዛ ሰአት መስራት ስለማይጀምር ነው። በእርጅና ወቅት ደግሞ ምክንያታዊ የሆነው የአይምሮ ክፍል እየደከመ ስለሚመጣ ነው። 👉በጉብዝናህ ጊዜ ግን ሁለቱንም የአይምሮ ክፍል መጠቀም ትችላለህ። ስሜታዊውንም ምክንያታዊውንም። በነዚህ ወቅት ላይ በስትክክል የምትጠቀመው ከሆነ እና ከነቃህበት በስተርጅናህ ጊዜ የተስተካከለ ህይወት ትመራለህ። የጉብዝና ወቅት የሚባለው የወጣትነህ ጊዜ ነው። በዚህ የወጣትነት ጊዜ ሶስት ትላልቅ ሀይሎች አሉህ፦ 🕤 ሙሉ እና በምንም ያልተያዘ ጊዜ አለህ። በዚህ የወጣትነህ ጊዜ ላይ የህይወትህን ሙሉ ፕሮግራም የምትሰራበት ነው። 💪 ሌላኛው በምንም ያልተነካ እና ንፁህ የሆነ አቅም አለህ። ጉልበትህን የምታከማችበት እና መጠቀም የምትጀምርበት ምርጡ ጊዜህ ነው። በዚህ ጊዜ ልክ እንደጉንዳኖች በበጋው ወቅት ለክረምት የሚሆን ምግብ የምትሰበስብበት አቅም ይኖርሀል። 👱‍♂ ውበት ይኖርሀል። የምትፈካበት የምትደምቅበት እና ለብዙዎች የምትታይበት ወቅት ነው። ውበትህ በራሱ የነገህን የምትገነባበት አንደኛው መሳሪያ ሲሆን ያለጊዜው እና ያለቦታው ካዋልከው ነገህን በፀፀት እንድትሞላው ከሚያደርጉህ ከህይወት በረከቶችህ መሀከል አንደኛው ነው። 🧠 ሌላኛው እና ዋነኛው ደግሞ አይምሮህ ሲሆን እንድታስብበት እና ከላይ የጠቀስኳቸውን የህይወት በረከቶች እንዴት መጠቀም እንዳለብህ የሚመራህ ነው። አንድ መርከብ የቱንም ያህል ግዙፍ ቢሆን የሚመራው ግን ትንሽ የሆነችው መሪ ናት። አንተም የቱንም ያህል ግዙፍ ብትሆን ሀብት ቢኖርህ ውበት ብታከማች ያለ አይምሮህ የምትኖር ከሆነ ተራ ነው የምትሆነው። 🔴ስለዚህ በጉብዝናህ ጊዜ የተሠጡህን እነዚህን በረከቶች በጊዜው በወጣትነት ትጠብቃቸው እና በአግባቡ ትጠቀምባቸው ዘንድ ምክሬ ነው። መልካም ቀን😘😘😘 😘@mihret_debebe 😘 😍@mihret_debebe 😍 ❤️❤️@mihret_debebe❤️❤️ 💚💛❤️

አዲስነት የጊዜ ጉዳይ ሳይሆን የራስ ለውጥ ነው 👉 አዲስ የሚባለው ነገር ወይ ከመጀመሪያው ያልነበረ ወይም ደግሞ የነበረው እንደአዲስ ሲታደስ ነው። የጊዜ አዲስ የለውም። ለምን መሠላችሁ ሰዎች በጊዜ ውስጥ ያልፋሉ እንጂ ጊዜ በሰው ውስጥ አያልፍም። ይህ ማለት ጠዋት ስትነሡ ጊዜ ይኖራል። ጊዜ የሚኖረው እኔ ዮናስ እስካለው ብቻ ነው። እኔ ከሞትኩ ጊዜ የሚባል ነገር የለም። ይሄ እውነታ ነው።አንድ ነገር የሚኖረው እናንተ እስካላችሁ ብቻ ነው። 👉 ስለዚህ የጊዜ አዲስ የለውም። አዲስ የሚሆንም ነገር የለም። አዲስ ከሆናችሁ አዲስ የምትሆኑት እናንተ ናችሁ። እሱንም የሀሳብ ለውጥ ካመጣችሁ ነው። አዲስ የምትሆኑት የትላንታችሁን ስለምትረሱት ሳይሆን በትላንታችሁ ውስጥ መኖር ስታቆሙ ነው። እንዳንዳንዶች አዲስ የሆነ ማንነት ገንቡ ምናምን ብዬ አልሰክስም። ምክንያቱም ምንም ምትገነቡት አዲስ ማንነት ስለሌላችሁ ነው። 👉ሰው በዉስጡ ያለውን ማንነት ነገሮች ሲስተካከሉ እና ሀሳቡ ሲሻሻል እያስተካከለ ይጠቀመዋል እንጂ አዲስ የሚፈጥረው ምንም አይነት ማንነት የለውም። 👉 ስለዚህ ምንም አዲስ የሚባል አመትም ሆነ ቀን የለም። ይሄ ካልተዋጠልህ ሳትወድ በግድህ በውሀ ታወራርደዋለህ። አንድን ነገር አዲስ የሚያደርገው ያንተ መኖር ብቻ ነው። 👉በነገራችን ላይ የእድሜህንም ቁጥር ያወከው ሰዎች በሠጡህ የጊዜ አቆጣጠር ተጠቅመህ እንጂ ሌላ ነገር አይደለም። ከዛም ሰው 80 አመት ሲሞላው የመሞቻ ጊዜው እንደደረሰ ታስብ እና ሞት ሞት ይሸትሀል ከዛም ትሞታለህ። 👉የገጠር ሠዎችን አይተሀቸው ታውቃለህ እድሜያቸውን አያቁትም ቀኑንም አይቆጥሩም በቃ ዝም ብለው ይኖራሉ። ሚገርመው ቶሎ አለመሞታቸው ነው።😂😂 ምክንያቱም አያቁማ ሰው በስንት እድሜው እንደሚሞት። ስለዚህ አያስቡም። አንተ ግን ትቆጥራለህ የቆጠርካት ላይም ከአፈር ትቀላቀላለህ። 👉ስለዚህ ባትጃጃሉ መልካም። በተቻላችሁ መጠን አዲስ ዘመን ስለመጣ እቅድ አታውጡ🙏🙏🙏 ይሄ በአል እረፈስኪያልፍ እቅድ አታውጡ። ጊዜው ይለፍ ከዛም ታወጣላችሁ። መልካም ቀን እወዳችሁዋለው❤❤❤ 😘@mihret_debebe 😘 😍@mihret_debebe 😍 ❤️❤️@mihret_debebe❤️❤️ 💚💛❤️

ለሠው የምትሠጠው ትልቁ ስጦታ 👉በዘመንህ እንደዚህ እመን ፈጣሪ በጣም ከወደደህ ሰው ይሠጥሀል። ሰው ደግሞ እራሱን ይሠጥሀል። እራስን መስጠት ማለት ምን መሠላችሁ ፦ አንድን ሰው ስትወዱት የኔ የምትሉት ምንም ነገር ሳይኖር እራሳችሁን ሳትሠስቱ ትሰጡታላችሁ። አለምን የሠራት ፈጣሪ የሠው ልጆች ሁሉ በሀጥያት ሲበላሹ ዝም አላለም እራሱን በሠው አምሳል ገልጦ ክብሬን ምናምን ሳይል ወደ ምድር መጣ። ክብሩን ተወው። አየህ ለምትወደው ሰው የምትደብቀው ክብር የለህም። በምትወደው እና በሚወድህ ሰው መካከል ግንኙነታችሁ እራቁት መሆን መቻል አለበት። እራቁት የሆነ ነገረ አይደበቅም ሁሉም ነገሩ ይታያል። የህይወትህን የሆነ ክፍል እየደበክ ፍቅረኛህን ወይም ፍቅረኛሽን አፈቅረዋለው ወይም አፈቅራታለው ብትል የውሸት ነው። 👉 ለምትወደው ሠው የምትሠጠው ስጦታ ራስን ከሆነ ይሄ ነገር በእራቁትነት ይገለጣል። አብሶ ለፍቅረኛሞች እና ለባለትዳሮች የምመክራችሁ ትልቁ ምክር ይሄ ነው ፦ በምትወዱት እና በምታፈቅሩት ሰው መሀከል የኔ የምትሉት ነገር እንዳይኖራችሁ። ታድያ ይሄ ነገር መሆን ያለበት በአንድ ሠው በኩል ባለ መዋደድ ብቻ ሳይሆን በሁለቱም አካላት መሀከል ባለው መዋደድ ላይ ይመሠረታል። 👉ፍቅር ማለት እራቁትነት ነው። ህፃን ልጅ እራቁቱን ሲሆን የሚደብቀው አካል የለውም። የሚገርመው ያ ህፃን ነፃነቱን የሚያገኘው እራሱ እራቁቱን ሲሆን ነው። ይሄ ብቻ አይደለም እራቁቱን በመሆኑም አያፍርም። እውነተኛ ፍቅርም ልክ እንደዚሁ ነው። እራቁቱን በመሆኑ ነፃነት ይሠማዋል። የኔ የምትሉት ሚስጥር አይኑራችሁ። አትደባበቁ። 👉ትልቁን ስጦታችሁን ለምተሰወዱት ሰው ስጡ። እራቁታችሁን ሁኑ። እወዳችሁዋለው መልካም ቀን ይሁንላችሁ❤️❤️❤️ 😘@mihret_debebe 😘 😍@mihret_debebe 😍 ❤️❤️@mihret_debebe❤️❤️ 💚💛❤️

በቅንነት ሼር ያድርጉ "ሰው ማለት እኮ የትዝታውና የትውስታው ድምር ነው። ሕይወት የመርሳትና የማስታወስ ሚዛን ናት። መርሳት ያለብንን መርሳት ሲያቅተን ሕይወታችን ይመሳቀላል... ደግሞ ማስታወስ ያለ
በቅንነት ሼር ያድርጉ "ሰው ማለት እኮ የትዝታውና የትውስታው ድምር ነው። ሕይወት የመርሳትና የማስታወስ ሚዛን ናት። መርሳት ያለብንን መርሳት ሲያቅተን ሕይወታችን ይመሳቀላል... ደግሞ ማስታወስ ያለብንን የሕይወት ልምዶች ጠቃሚ ሰዎችና ነገሮች ከረሳን ...የእኛነታችን መለያና የስብእናችን ድንበር ይጠፋና ሌላ ሰው እንሆናለን።" ከሌላሰው መፅሃፍ ገፅ 285 የተወሰደ። 😘@mihret_debebe 😘 😍@mihret_debebe 😍 ❤️❤️@mihret_debebe❤️❤️ 💚💛❤️

በአንድ ወቅት አንዱ ስብሐትን ይጠጋውና "ጋሽ ስብሐት ጽሁፎችህ ተወዳጅነት አላቸው። በተለይ ወጣቶች በብዛት ያደንቁሃል። ለምን መጽሀፍትህን ሁሉም በነፃ የሚያገኙበትን መንገድ አናመቻችም?" ስብሐት "
በአንድ ወቅት አንዱ ስብሐትን ይጠጋውና "ጋሽ ስብሐት ጽሁፎችህ ተወዳጅነት አላቸው። በተለይ ወጣቶች በብዛት ያደንቁሃል። ለምን መጽሀፍትህን ሁሉም በነፃ የሚያገኙበትን መንገድ አናመቻችም?" ስብሐት "በጣም ደስ ይለኛል" ልጁ ደስታውን ከፊቱ ላይ ለመደበቅ እየታገለ፦ "በቃ ስራዎችህ የህዝብ እንዲሆኑ የሚያስፈልገውን የህግ ሰነድ አርቅቄ እመጣለሁ" ከጥቂት ቀናት በኋላ ልጁ ከሰነዱ ጋር ወደ ስብሐት መጣ። ስብሐት ሰነዱን ተቀብሎ በሚገባ አነበብ። ሃሳቡ ሲጨመቅ ስብሐት የፃፋቸውን ሁሉም ልብወለዶች እንዲሁም ለዘመናት የከተባቸው እልፍ መጣጥፎች ባለቤትነት በፍቃዱ ለአንድ አሳታሚ ድርጅት ማስተላለፉን ይገልፃል። ልጁ የአሳታሚ ድርጅቱ ባለቤት ነው። ስብሐት በሰነዱ ላይ ያሉትን ሁሉንም መጠይቆች ሞላ። ስም አድራሻ የመሳሰሉትን። በዚህ መሐል ልጁ ምራቁ እየተዝረበረበ ነው። በአእምሮው ምንም ሳይሰራ የሚያገኘውን ገንዘብ እያሰላ ነው። ይህንን ከሰማይ የወረደለትን መና እየቆጠረ ነው። ከሰከንዶች በኋላ ያልለፋበት ብዙ ሺህ ብር ኪሱ ይገባል። ስብሐት በተረጋጋ ስሜት ሁሉንም መረጃ ሲያስገባ ከቆየ በኋላ ልክ የፊርማው ቦታ ሲደርስ ይህንን በአማርኛ ፃፈ፦ "FUCK YOU"😌 😘 😘 😍 😍 ❤️❤️❤️❤️ 💚💛❤️

በአንድ ወቅት አንዱ ስብሐትን ይጠጋውና "ጋሽ ስብሐት ጽሁፎችህ ተወዳጅነት አላቸው። በተለይ ወጣቶች በብዛት ያደንቁሃል። ለምን መጽሀፍትህን ሁሉም በነፃ የሚያገኙበትን መንገድ አናመቻችም?" ስብሐት "
በአንድ ወቅት አንዱ ስብሐትን ይጠጋውና "ጋሽ ስብሐት ጽሁፎችህ ተወዳጅነት አላቸው። በተለይ ወጣቶች በብዛት ያደንቁሃል። ለምን መጽሀፍትህን ሁሉም በነፃ የሚያገኙበትን መንገድ አናመቻችም?" ስብሐት "በጣም ደስ ይለኛል" ልጁ ደስታውን ከፊቱ ላይ ለመደበቅ እየታገለ፦ "በቃ ስራዎችህ የህዝብ እንዲሆኑ የሚያስፈልገውን የህግ ሰነድ አርቅቄ እመጣለሁ" ከጥቂት ቀናት በኋላ ልጁ ከሰነዱ ጋር ወደ ስብሐት መጣ። ስብሐት ሰነዱን ተቀብሎ በሚገባ አነበብ። ሃሳቡ ሲጨመቅ ስብሐት የፃፋቸውን ሁሉም ልብወለዶች እንዲሁም ለዘመናት የከተባቸው እልፍ መጣጥፎች ባለቤትነት በፍቃዱ ለአንድ አሳታሚ ድርጅት ማስተላለፉን ይገልፃል። ልጁ የአሳታሚ ድርጅቱ ባለቤት ነው። ስብሐት በሰነዱ ላይ ያሉትን ሁሉንም መጠይቆች ሞላ። ስም አድራሻ የመሳሰሉትን። በዚህ መሐል ልጁ ምራቁ እየተዝረበረበ ነው። በአእምሮው ምንም ሳይሰራ የሚያገኘውን ገንዘብ እያሰላ ነው። ይህንን ከሰማይ የወረደለትን መና እየቆጠረ ነው። ከሰከንዶች በኋላ ያልለፋበት ብዙ ሺህ ብር ኪሱ ይገባል። ስብሐት በተረጋጋ ስሜት ሁሉንም መረጃ ሲያስገባ ከቆየ በኋላ ልክ የፊርማው ቦታ ሲደርስ ይህንን በአማርኛ ፃፈ፦ "FUCK YOU"😌 😘@mihret_debebe 😘 😍@mihret_debebe 😍 ❤️❤️@mihret_debebe❤️❤️ 💚💛❤️

«ልጅ ሆኜ ነብሴን እጅግ ደስ የሚላት ጢቢ፣ ጢቢ ስጫወት ነበር። ጎረምሳ ሆኜ ነብሴን እጅግ ደስ የሚላት ሴት ልጅን ሳቅፍ ነበር።ዛሬ አርጅቼ ነብሰን እጅግ ደስ የሚላት ልጂ ስትስቅ ሳይ ነው። አሁን እነዚህን ሶስት እኔዎች ሳስተያያቸው እን ድ ሰው ናቸው?..... እኔ ሽማግሌውስ አንድም፣ አራትም ብሆን ይኸው እዚህ አለሁ፡፡ ያ እኔ የምለው ልጅና ያ እኔ የምለው ጎረምሳ ግን የት ሄዱ? የኔ ትውስታ ውስጥ ከልጅየውም ከጎረምሳውም ከብዙ በጥቂቱ እንደ ፊልም ተቀርፆ ይገኛል እንጂ እነሱ ግን የሉም።.» #ጋሽ ስብሀት ...እግረ መንገድ 😘@mihret_debebe 😘 😍@mihret_debebe 😍 ❤️❤️@mihret_debebe❤️❤️ 💚💛❤️

በአንድ ወቅት አንዱ ስብሐትን ይጠጋውና "ጋሽ ስብሐት ጽሁፎችህ ተወዳጅነት አላቸው። በተለይ ወጣቶች በብዛት ያደንቁሃል። ለምን መጽሀፍትህን ሁሉም በነፃ የሚያገኙበትን መንገድ አናመቻችም?" ስብሐት "
በአንድ ወቅት አንዱ ስብሐትን ይጠጋውና "ጋሽ ስብሐት ጽሁፎችህ ተወዳጅነት አላቸው። በተለይ ወጣቶች በብዛት ያደንቁሃል። ለምን መጽሀፍትህን ሁሉም በነፃ የሚያገኙበትን መንገድ አናመቻችም?" ስብሐት "በጣም ደስ ይለኛል" ልጁ ደስታውን ከፊቱ ላይ ለመደበቅ እየታገለ፦ "በቃ ስራዎችህ የህዝብ እንዲሆኑ የሚያስፈልገውን የህግ ሰነድ አርቅቄ እመጣለሁ" ከጥቂት ቀናት በኋላ ልጁ ከሰነዱ ጋር ወደ ስብሐት መጣ። ስብሐት ሰነዱን ተቀብሎ በሚገባ አነበብ። ሃሳቡ ሲጨመቅ ስብሐት የፃፋቸውን ሁሉም ልብወለዶች እንዲሁም ለዘመናት የከተባቸው እልፍ መጣጥፎች ባለቤትነት በፍቃዱ ለአንድ አሳታሚ ድርጅት ማስተላለፉን ይገልፃል። ልጁ የአሳታሚ ድርጅቱ ባለቤት ነው። ስብሐት በሰነዱ ላይ ያሉትን ሁሉንም መጠይቆች ሞላ። ስም አድራሻ የመሳሰሉትን። በዚህ መሐል ልጁ ምራቁ እየተዝረበረበ ነው። በአእምሮው ምንም ሳይሰራ የሚያገኘውን ገንዘብ እያሰላ ነው። ይህንን ከሰማይ የወረደለትን መና እየቆጠረ ነው። ከሰከንዶች በኋላ ያልለፋበት ብዙ ሺህ ብር ኪሱ ይገባል። ስብሐት በተረጋጋ ስሜት ሁሉንም መረጃ ሲያስገባ ከቆየ በኋላ ልክ የፊርማው ቦታ ሲደርስ ይህንን በአማርኛ ፃፈ፦ "FUCK YOU"😌 😘@mihret_debebe 😘 😍@mihret_debebe 😍 ❤️❤️@mihret_debebe❤️❤️ 💚💛❤️

ብንስማማስ ???!!! እንዲህ የሚል ከጥንት ጀምሮ የሚታወቅ የአይሁዳውያን ተረት አለ፡- አንዲት በጣም የተራበች ድመት ከአንድ ሱቅ ስጋ ሰረቀች፡፡ ያንን ሌብነቷን የተመለከተ አንድ ውሻ ነበረና እኩል
ብንስማማስ ???!!! እንዲህ የሚል ከጥንት ጀምሮ የሚታወቅ የአይሁዳውያን ተረት አለ፡- አንዲት በጣም የተራበች ድመት ከአንድ ሱቅ ስጋ ሰረቀች፡፡ ያንን ሌብነቷን የተመለከተ አንድ ውሻ ነበረና እኩል ካላካፈልሽኝ አጋልጥሻለሁ አላት፡፡ ድመቷ መካፈል ስላልፈለገች መጣላት ጀመሩ፡፡ ሁለቱ በነበራቸው ጸብ ማንም ማሸነፍ ስላልቻለና ጸቡ ማቆሚያ ስላጣ የስጋው ሽታ ስቧት የመጣች በአካባቢው የነበረችን አንዲት ቀበሮ ጠሩና እንድትዳናኛቸው ጠየቋት፡፡ ቀበሮዋ፣ “ከምትጣሉ ስጋውን እኩል ተካፈሉ” የሚልን ቀላል ምክር ለገሰቻቸው፡፡ በምክሩ ሁለቱም በመስማማታቸው ድመት ስጋውን ለሁለት ቆርጣ ለውሻ አካፈለች፡፡ ሆኖም ውሻው፣ የተሰጠው ድርሻ አናሳ እንደሆነ በማሰብ ጸቡን አላበርድ አለ፡፡ በዚያን ጊዜ ቀበሮ የስጋውን መጠን በማስተካከል ሰበብ ከድመት ድርሻ ላይ ደህና አድርጎ በመቦጨቅ ዋጥ በማድረግ ውሻን አስደሰተና ለማስተካከል ሞከረ፡፡ አሁን ደግሞ ድመት የእሷ በመቀነሱ ምክንያት፣ “የውሻ ድርሻ በዝቷል” በማለት ጸቡን አላበርድ አለች፡፡ አሁንም ቀበሮ ድመትን ለማስደሰት በሚል ሰበብ ከውሻው ድርሻ ላይ ጠቀም ያለ መጠን ቦጨቅ በማድረግ ዋጥ አደረገ፡፡ አሁን ደግሞ ውሻ እንደገና የእሱ ማነሱን ሲያይ የድመት በዝቷል፣ ከዚያም ቀበሮ ድርጊቱን ሲደጋግም ድመት ደግሞ የውሻ በዝቷል ሲባባሉ፣ ቀበሮ ከዚህም ከዚያም ሲቀናንስ ስጋውን ጨረሰውና ድመትና ውሻ ምንም ሳይደርሳቸው ባዶ ቀሩ ይባላል፡፡ ተጣልተን ሁሉን ከምናጣ ተስማምተን ግማሽ ማግኘቱና አብሮ መኖሩ አይሻለንም? 😘@mihret_debebe 😘 😍@mihret_debebe 😍 ❤️❤️@mihret_debebe❤️❤️ 💚💛❤️

አለቅነት ወይስ አገልጋይነት? ለመሪዎች . . . የአንዲት አነስተኛ ከተማ ከንቲባ በአካባቢው በነበረ አንድ ጉባኤ ከተሳተፉ በኋላ በነበረው የምሳ ዝግጅት ላይ በመሳተፍ ላይ ናቸው፡፡ የተዘጋጀው የዶሮ ምሳ በሰው ቁጥር ልክ በመሆኑ ከአንድ ዶሮ በላይ መውሰድ አይቻልም ነበረና ምሳ ጨላፊዋ ለእያንዳንዱ ተጋባዥ አንድ አንድ ዶሮ በመጨለፍ በየሳህኑ ላይ ታደርጋለች፡፡ ከንቲባው፣ “ተጨማሪ ዶሮ ሳህኔ ላይ አድርጊ” አሏት፣ ኮራ በማለት፡፡ አስተናጋጇም፣ “ይቅርታ፣ ለአንድ ሰው አንድ ዶሮ ብቻ ስለተዘጋጀ መውሰድ የሚፈቀደውም ያንንው ብቻ ነው” አለቻቸው፣ በትህትና፡፡ ከንቲባው ደጋግመው ፍላጎታቸውን ትእዛዝና ጥያቄ በተቀላቀለበት ድምጽ ቢነግሯትም እሷ ግን ደጋግማ ያንኑ መልስ ነገረቻቸው፡፡ በመጨረሻም፣ “ለመሆኑ ማን እንደሆንኩኝ ታውቂያለሽ? የዚህ አካባቢ አለቃ እኮ ነኝ” አሏት፣ አሁንም ኮራ ባለ ድምጽ፡፡ ምግብ አቅራቢዋም የነበራትን አክብሮትና ትህትና ሳትለቅ፣ “ልክ ነው፣ እርሶ የዚህች ከተማ አለቃ ነዎት፣ እኔ ደግሞ የዚህ የዶሮ ምሳ ዝግጅትና አቅርቦት ባለአደራ ነኝ፡፡ ስለዚህ የሚፈቀደው አንድ ነው” አለቻቸው፡፡ ከንቲባው ከዚህ በፊት በነበራቸው “የአገልጋይነት አመራር” (Servant Leadership) ስልጠና ላይ የሰሟቸውና እስካሁን ብዙም ያልተጠቀሙባቸው መርሆች ትዝ አላቸውና ዝም አሉ፡፡ ከመርሆቹ ዋና ዋናዎቹ እነዚህ ነበሩ፡- 1. አገልጋይ መሪ (Servant Leader) ከራሱ በፊት የሚመራውን ሕዝብ ያስቀድማል፡፡ 2. አገልጋይ መሪ (Servant Leader) ስልጣኑን በሄደበት ሁሉ ካለአግባብ አይጠቀምም፡፡ 3. አገልጋይ መሪ (Servant Leader) ባለው ስልጣን ተጠቅሞ ከሕግ በላይ ለመሆን አይሞክርም፡፡ Leadership or servitude? For leaders. . . The mayor of a small town is attending a luncheon after attending a local congregation. The prepared chicken lunch was so large that no one could take more than one chicken, and the chef would chop one chicken for each guest and put it on each plate. "Put more chicken on my plate," the mayor said proudly. The hostess said politely, "Sorry, only one chicken is prepared for one, and that's the only one allowed." The mayor repeatedly told her in a mixed voice, but she kept telling him the same thing over and over again. Finally, he said, “Do you know who I am? I'm the boss of this area, ”she said proudly. The waiter did not lose her respect and humility, saying, “That's right, you are the mayor of this city, and I am in charge of the preparation and delivery of this chicken lunch. So one thing is allowed. ” The mayor remembered the principles he had heard in his previous "Servant Leadership" training, which he had not yet used, and remained silent. Here are some of the key points: 1. The Servant Leader puts the people before him. 2. The Servant Leader does not abuse his authority wherever he goes. 3. Servant Leader does not use his authority to try to be above the law. Leaders fall - Have a good server leadership era! መሪዎች፡- መልካም የአገልጋይ መሪነት ዘመን ይሁንላችሁ! 😘@mihret_debebe 😘 😍@mihret_debebe 😍 ❤️❤️@mihret_debebe❤️❤️ 💚💛❤️

መገፋትን ለጥቅም ማዋል! (“የመገፋት ሕመም” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ መጽሐፍ ውስጥ የተወሰደ) በጓደኝነት፣ በቤተሰብ፣ በፍቅር ግንኑነትና በመሳሰሉት ማሕበራዊ ግንኙነቶች ውስጥ የመገፋትን፣ የመገለልንና ያለመፈለግን ልምምድ በምትቀምስበት ጊዜ የሁኔታውን መልካም ጎን ለማየትና ወደፊት ለመዝለቅ የሚከተሉትን ሃሳቦች እንደመነሻ መጠቀም ትችላለህ፡፡ • አንዳንድ ጊዜ በሰዎች መገፋትህ ከእነዚያ ከሚገፉህ አላስፈላጊ ሰዎችና ሁኔታዎች የምትለይበትና የምትጠቀምበት ብቸኛ መንገድ ሊሆን እንደሚችል ማሰብ፡፡ • አንዳንድ ጊዜ አንዱ ሰው ስለገፋህ ሌላ የተሻለ ሰው፣ አንዱ ተቋም ስላገለለህ ሌላ የተሻለ ተቋም . . . የምታገኝበት ብቸኛ መንገድ ሊሆን እንደሚችል ማስታወስ፡፡ • አንዳንድ ጊዜ በመገፋት ውስጥ በተደጋጋሚ ስታልፍ ምናልባት ካለአግባብ የምትገፋበት አጉል ባህሪይ ሊኖርህ ስሚችል ራስህን እንድትጠይቅና ያንን አጉል ባህሪይ ለመለወጥ የምትችልበትን መንገድ መጀመር፡፡ አዎን! የመገፋትን ልምምድ ወደመልካም መለወጥ ይቻላል! 😘@mihret_debebe 😘 😍@mihret_debebe 😍 ❤️❤️@mihret_debebe❤️❤️ 💚💛❤️

ሁለቱ የአመራር “ንጥረ-ነገሮች” ለመሪዎች . . . በማንኛውም የአመራር ሂደቶችና መስኮች ውስጥ ሁለት አይነት መሪዎች አሉ፡፡ የመጀመሪያዎቹ የተጽእኖ መሪዎች ሲሆኑ፣ ሁለተኛዎቹ ደግሞ የሹመት መሪዎች ናቸው፡፡ 1. የተጽእኖ መሪዎች፡፡ የተጽእኖ መሪዎች ምንም እንኳን መደበኛ በሆነ መልኩ እውቅናና ሹመት ባይሰጣቸው ካላቸው ስነ-ምግባር፣ ዲሲፕሊን፣ እውቀት፣ የሰው-ለሰው ግንኙነት፣ ማሕበራዊ ብልህነት የተነሳ በአካባቢው ሰው ላይ መልካምን ተጽእኖ የሚያመጡ ሰዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ሰዎች ወደ ሹመት ስልጣን የማይመጡበት በርካታ ምክንያቶች ሊኖሩ ቢችሉም ባሉበት ሆነው ግን የሚያመጡት ተጽእኖ ይህ ነው አይባልም፡፡ 2. የሹመት መሪዎች፡፡ የሹመት መሪዎች በሁለት መልኩ ወደዚያ ሹመት ሊመጡ ይችላሉ፡፡ አንዳንዶቹ ከላይ በተጠቀሰው መልኩ ትክክለኛ የተጽእኖ ሰው መሆናቸው ታይቶ ወደሹመት ሊመጡ ይችላሉ፡፡ ሌሎቹ ግን ምንም አይነት የመልካም ተጽእኖ ባህሪይ፣ ዲሲፕሊንም ሆነ የአመራር ብቃት ባይኖራቸውም በአጉል ብልጠት፣ በወገናዊነትና በመሳሰሉት ትክክለኛውን ሂደት በተጣረሰ መልኩ ወደ መሪነት ሊመጡ ይችላሉ፡፡ ማንኛውም መሪ ከሁሉም በፊት ሊያሳስበው የሚገባው በሰዎች ላይ መልካም ተጽእኖ አምጪ የመሆኑ ጉዳይ ነው፡፡ ያንን እርግጠኛ ከሆነ በኋላ ሹመት ባያገኝም እንኳን ባለው መልካም ተጽእኖን የማሳደር አቅም ወደፊት መቀጠል ይችላል፡፡ ሆኖም፣ በመልካም ተጽእኖው የታወቀው ሰው እውቅናንና ሹመትን ቢያገኝ ያለው መልካም ነገር ወደሰዎች በተቀላጠፈ ፍጥነትና መደበኛ በሆነ መንገድ እንዲደርስ ሊያደርገው እንደሚችል ማሰብ ጥሩ ነው፡፡ መሪዎች፡- አመራር የሚጀምረውም ሆነ የሚቀጥለው በመልካም ተጽእኖ መሆኑን አውቃችሁ በቅድሚያ ለእርሱ ስትሰሩ ሌላው ጊዜውን ጠብቆ እንደሚመጣ አትዘንጉ፡፡ The two "elements" of leadership For leaders. . . There are two types of leaders in any leadership process. The first are influential leaders, and the second are appointed leaders. 1. Influence leaders. Influential leaders, even if they are not formally recognized and appointed, are people who make a positive impact on the community because of their morals, discipline, knowledge, human relationships, and social intelligence. There may be many reasons why these people do not come to power, but that is not the case. 2. Appointment leaders. Appointment leaders can come to that appointment in two ways. Some may be appointed to the position of having the right influence. Others, however, may come to the fore in a way that violates the right process, such as ingenuity, partisanship, and so on, without any positive influence, discipline or leadership skills. The main concern of every leader is to make a difference. Once he is convinced of that, he will continue to be able to make a difference, even if he is not appointed. However, it is good to think that if a person who is known for his influence is well-known and well-appointed, he will be able to reach people quickly and efficiently. Leaders' Leadership: Remember that leadership begins and ends with a positive impact. 😘@mihret_debebe 😘 😍@mihret_debebe 😍 ❤️❤️@mihret_debebe❤️❤️ 💚💛❤️

ዓመተ ምህረት  ያደጉ ያልናቸው - አቅምን እስኪያጡ፣ በሚያስፈራ ጅራፍ - ተገርፈው ሲቀጡ። እኛም በፍርሃት - አያድርስ በማለት፣ ከእጃችን እንዳይጠፋ - የያዝነው በረከት። እንዴት እናቆየው - እስከነ ማማሩ፣ የቤታችን ግርማ - ሳይበላሽ ክብሩ? ዓይናችን እያየ - ጨረቃን የነኩ፣ በእሳት ሆነም በጎርፍ - ታመውም ሲለኩ። ወረርሽኝም መጥቶ - ጉልበት አሳይቶ፣ ተጠበብኩ ያሉትን - ቦታ አሳጥቶ። በወሬ መስታዎት - ተደንቀን ያየነው፣ በጆሮአችን ደርሶ - ቀርበን የሰማነው። ሆኖ ነው ያገኘነው - ነገሩ የረቀቀ፣ ደካማው እንዲማር - ብርቱ እየወደቀ። ጥልቅ መልዕክት አለው - ለደካማዎቹ፣ እንደ ኢትዮጵያ ላሉ - ለታዳጊዎቹ። ያሳያታል ይኸው - አቅሟን እየለካ፣ ደቋሽ ክንዱን ትቶ - በአርጩሜ እየነካ። ብርቱን የመታበት - ውሃና እሳቱ፣ ሳይለቅባት አዝኖ - እልፍ በማለቱ። ዓመት ጨመረላት - ውበቷን አድንቃ፣ የማን እንደሆነች - የያዛትን አውቃ። ካለችበት ቅዠት - ወጥታ ተመልሳ፣ እራሷን እንድታይ - ምህረቱን ለብሳ። የአዲስ ዓመት መምጣት - በቤትዋ ታወጀ፣ ውበቷ በአደይ - ደምቆ ተዘጋጀ። ልጆቿም እንደ እርሷ - እንዲታዩ አምረው፣ እንቁጣጣሽ አሉ - በየቤቱ ዞረው። ሁለት ሺህ አስራ ሶስት - ዓመቶች አለፉ፣ ደግና ክፉውን - ታሪክ ሁሉ ጻፉ። አዲስ ዓመት ብላ - ልትጠብቅ ልጆቿን፣ እንዳትወድቅ ስታጥፍ - የተዘረጉ እጆቿን። አዲስ ዕድሜ አግኝታ - ጉዞዋን ቀጠለች፣ ንስሀ እንድትገባ - የምህረት ዓመት - አዲስ ተቀበለች።

ሰውና አዲስ አመት ፀሐይ እዛው ቆማ - ምድር እየዞረች፣ ምሽትና ቀኑን - እየወረወረች፣ አለች እስከዛሬ - ዕድሜ እየነገረች። እሱም በማንጋጠጥ - ፀሐይ ወጣች ብሎ፣ ደጋግሞ ስላያት - የሀሳብ መስመር ስሎ፣ ሶስትመቶ ስልሳ አምስት - ሰንሰለት ቀጥሎ። አደይ ብቅ ስትል ያንን - አስተውሎ። አንድ ዙር ማድረጓን - መለየትን ችሎ፣ ምልክት አረጋት - በየዓመቱ መጥታ፣ ስላስጀመረችው - አዲስ ዓመት ሰጥታ። እርሱ ግን አንድ ቦታ - እዛው ተቀምጦ፣ እራሱን ሳያድስ - ከልብ ተለውጦ። ይቆጥረዋል ቀኑን - ዕድሜውም ይገፋል፣ የተሰጠው ጊዜ - ሳያውቅበት ያልፋል። አደይ ግን አክብራ - ቀጠሮ ጠብቃ፣ እየተመለሰች - በየዓመቱ ደምቃ። መታየቷ አልቀረም - የሰው ልጅ ችግሩ፣ እርሱ ሳይታደስ - ለእርሷ መዘመሩ። ምናለበት እሱም - አብሯት ተለውጦ፣ ኑሮውን ቢያሳምር - እንደ እሷ አጊጦ። ሰው ግን አላወቀም - አሁንም ያረፍዳል፣ ላባከነው ጊዜ - በአዲስ ዓመት ያብዳል። የያዘው አባዜን - ሱሱን ሳይጥል ታግሎ፣ አሮጌው ውስጥ ሆኖ - አዲስ መጣ ብሎ። አደባባይ ወጥቶ - መደገስ ያበዛል፣ በአዲሱ መልሶ - አሮጌ ይገዛል።

ችግር! - የእምቅ ብቃትህ ብቸኛ መውጫው ቀዳዳ! “ያልገደለኝ ነገር ሁሉ ያጠነክረኛል” ይላል ምንጩ ያልታወቀ የከረመ አባባል፡፡ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ለማለፍ ፈቃደኛ እስካልሆንክ ድረስ የብቃትህን ጥግ ሳታውቀው ታልፋለህ፡፡ የሰው አቅሙና ብቃቱ የሚወጣው በሚያልፍበት አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ነው፡፡ ብዙ ሰዎች አሁን ከድሮው ሕይወታቸው የተሻለ ኑሮን እየኖሩና የአሁኑ ዘመን ከበፊቱ በብዙ እጥፍ እየበለጠ እንኳን፣ “ድሮ ቀረ!” ሲሉ የሚደመጡት የበፊቱ አስቸጋሪ ዘመን በጊዜው ፈትኗቸው ቢሆንም እንኳን ተደብቆ የነበረውን እምቅ ብቃታቸውንና ድብቅ ብርታታቸውን እንዳወጣው ያውቃሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች ዛሬ የሆኑትን የሆኑት፣ ዛሬ የሚችሉትን የቻሉት፣ ዛሬ የገባቸው ነገር የገባቸው . . . ከእነዚያ ፈታኝ፣ ነገር ግን ድንቅ አመታት የተነሳ እንደሆነ ውስጣቸው ያውቀዋል፡፡ አንዳንድ ሰዎች አስቸጋሪ ሁኔታዎች ሲገጥማቸው የበለጠ እያዳበሩ የሚሄዱት “ችሎታ” ከዚያ ሁኔታ፣ ስፍራ፣ ግንኑነት … የመሸሽን ችሎታ ብቻ ነው፡፡ ስለዚህ ግሩም የሆኑ “የሽሽት ባለሞያዎች” ወደመሆን ያድጋሉ፡፡ የስራና የትምህርት ዘርፍ ከበድ ሲላቸው እየለወጡ ውስጣቸው ግን ሳይለወጥ፣ የትዳር ሕይወት ችግር ይዞ ሲመጣ የትዳር ጓደኛን እየቀየሩ ባሪያቸው ግን ሳይቀየር፣ መንደር፣ ሰፈርና ሃገር አልመች ሲላቸው እየለወጡ አመለካከታቸው ግን ሳይለወጥ እንደነበሩ ይኖራሉ፡፡ ምን ያህል አስገራሚ ብቃት እንዳለህ ማንም ሰው አያውቀውም፣ አንተው ራስህ እንኳን በቅጡ አታውቀውም፡፡ ይህንን ብቃትህን የሚያወጣው ጉዳይ “ችግር” ይባላል፡፡ ይህ ችግር የሚባል ነገር በሁለት ይከፈላል፣ 1) አስፈላጊ ችግርና፣ 2) አላስፈላጊ ችግር፡፡ አስፈላጊው ችግር የተለመደውን የሕይወት መስክ ይዘህ ስትጓዝ በተመሳሳይ ሁኔታ የሚያልፍ ሰው ሁሉ የሚጋራው ችግር ነአትፍቀድለት፡፡ችግር ከመሸሽ ይልቅ ስትጋፈጠው የውስጥህ ብቁ ማንነት ይወጣል፡፡ አላስፈላጊ ችግር በእኛው የጥበብ ጉድለትና የተሳሳተ ውሳኔ የሚመጣው አይነት ችግር ነው፡፡ ይህን ችግር ሽሸው፣ እንዳይከሰትም የምትችለውን ሁሉ አድርግ፡፡ ሆኖም፣ አንዴ ከተከሰተ ግን ከስህተትህ ተማር፣ ውጤቱንም ተጋፈጥ እንጂ ለመደባበቅና ለመሸሽ አትሞክር፡፡ ዛሬ የምታልፍበት ችግር ነገ በብዙ ብቃት የምትወጣበት አስገራሚ እድል እንጂ ዛሬ የምትደክምበት ሁኔታ እንዲሆን አትፍቀድለት፡፡ 😘@mihret_debebe 😘 😍@mihret_debebe 😍 ❤️❤️@mihret_debebe❤️❤️ 💚💛❤️

ለዝግጅት እረፍት የለም! ከምንም ነገር ማረፍ ትችላለህ፣ ነገ ሕይወት ለሚያቀብልህ ፍልሚያዎች የመዘጋጀትን ጉዳይ አስልክቶ ግን ለአንድ ቀን እንኳን ማረፍ አትችልም፡፡ በየቀኑ ራስን ማዘጋጀት፣ ማሰልጠንና እየበሰሉ መሄድ የግድ ነው፡፡ የኦሊምፒክ ውድድር የሚመጣው በየአራት አመቱ ነው፣ የስፖርተኞቹ ልምምድና ዝግጅት ግን በየቀኑ ነው፡፡ ፈተና የሚመጣው በሴሚስተሩና በአመቱ መጨረሻ ነው፣ የተማሪዎቹ ጥናትና ዝግጅት ግን በየቀኑ ነው፡፡ ጦርነት የሚመጣው አንዳንድ ጊዜ ነው፣ የአንድ ሃገር የውትድርና ስልጠናውና ዝግጅቱ ግን በየቀኑ ነው፡፡ የግል ሕይወት ፈተናው የሚመጣው አልፎ አልፎ ነው፣ በአመለካከትና በስሜት ጽንአት የማደግ ዝግጅቱ ግን በየቀኑ ነው . . . የቀረውን የዝግጅትና የፍልሚያ መስክ ዝርዝር አንተ ቀጥልበት፡፡ በሕይወትህ የሚገጥሙህን ግጥሚያዎችና ፍልሚያዎች የማሸነፍህን ወይም የመሸነፍህን ጉዳይ ከሚወስኑ ዋና ዋና ነገሮች መካከል አንዱ ቀድመህ የመዘጋጀትህና ያለመዘጋጀትህ ጉዳይ ነው፡፡ የብዙ ሰዎች ሕይወት ለወደፊት የሕይወት ግጥሚያና ፍልሚያ የተዘጋጀ አይደለም፡፡ ስለሆነም፣ ሁኔታው አፍጥጦ ሲመጣ ነው መፍትሄ ለማግኘት መሯሯጥ የሚጀመሩት፡፡ ሳይዘጋጁ መፋለም ያለው ችግር በስልጠና ራሱን ያላዘጋጀ ማንነት ፍልሚያ ሲመጣ አቅም ከማጣቱም ባሻገር ለምክርና ለድጋፍም ዝግጁ አለመሆኑ ነው፡፡ በዝግጅት ያልዳበረው ደካማ ማንነቱ ችግሩ በድንገት ሲመጣ ከሚከተለው መደናገር ጋር ተደምረው ውስጡን ያዝሉታል፣ አቅም ያጥረዋል፣ ግራ ይጋባል፣ ነገን መጋፈጥ ያስጠላዋል . . . ፡፡ ነገ የሚኖርህ ማሕበራዊ ሕይወት፣ የፍቅርና የትዳር ሕይወት፣ የባለሞያነት ሕይወት . . . ፍልሚያን ይዘው እንደሚመጡ በማወቅ ዛሬ መዘጋጀትህን አትርሳ፡፡ “እንዴት ልዘጋጅ?” ካልክ ለመንደርደሪያ የሚከተሉትን ተጠቀምባቸው . . . • አንብብ! አድምጥ! ሰልጥን! • በተለያዩ ችግሮች ውስጥ ስታልፍ ከሁኔታው ባለመሸሽ ለትምህር ልቦናን በመክፈት ትምህርት አጠራቅም፡፡ • የሌሎችን ስኬትና እድገት ለቅንአትና ለፉክክር ሳይሆን ለመነሳሳት ተጠቀምበት፡፡ • የሌሎችን ስህተትና ውድቀት ለፍርድና ለወሬ ሳይሆን ለትምህርት ተጠቀምበት! ከምንም ነገር እረፍ በየቀኑ ከመዘጋጀት ግን በፍጹም አትረፍ! 😘@mihret_debebe 😘 😍@mihret_debebe 😍 ❤️❤️@mihret_debebe❤️❤️ 💚💛❤️

ጠቃሚ ሀሳቦች ====+====+====+====+====+====+ 👉 እንደገቢህ ሁኔታ በየሳምንቱ ወይም በየወሩ የተወሰነ ገንዘብ አስቀምጥ መጠኑ አያሳስብም ዋናው መቆጠብህ ነው። 👉 የቤተሰቦችህን ምክር ስማ በቀኑ በመጨረሻም ስለአንተ መልካም በመመኘት ብኜቹ እነሱ ሆነው ታገኛቸዋለህ 👉 ጓደኞችህን ተጠንቅቀህ ምረጥ አንተ የአከባቢህ ውጤት ነህ 👉 ጥቂቶች ብቻ የሚካኑበት ክህሎት ስለሆነ ብቻህን መሆንን እና እራስህን መቻልን ተለማመድ 👉 እራስህን አስተምር አንብብ አሁንም አንብብ፣ ጤናህን ጠብቅ፣ አካልህን ተመልከተው ሌሎች እንዲወዱህ አትጠብቅ በመጀመሪያ አንተ ራስህን ውደድ 😘@mihret_debebe 😘 😍@mihret_debebe 😍 ❤️❤️@mihret_debebe❤️❤️ 💚💛❤️

😘@mihret_debebe 😘 😍@mihret_debebe 😍 ❤️❤️@mihret_debebe❤️❤️ 💚💛❤️
😘@mihret_debebe 😘 😍@mihret_debebe 😍 ❤️❤️@mihret_debebe❤️❤️ 💚💛❤️