en
Feedback
የሐረሪ ህዝብ ክልል ምክር ቤት Harari People Regional Council

የሐረሪ ህዝብ ክልል ምክር ቤት Harari People Regional Council

Open in Telegram

የሐረሪ ክልል ምክር ቤት የስራ እንቅስቃሴ የሚያወጣቸውን አዋጅ፣ደንብና መመርያዎችን እንዲሁም የክልል ም/ቤቱ የሚያሳልፋቸውን የተለያዩ ውሳኔዎች እና ሹመቶችን በቅርበት በተከታታይ ያገኛሉ።

Show more
217
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
"መንግስት የሕዝቡን ኑሮ በማሻሻል በቁርጠኝት እየሰራ ነው" የተከበሩ ፈትሂ መሕዲ (ዶ/ር) መንግስት የሕዝቡን ኑሮ ለማሻሻል በቁርጠኝት እየሰራ ነው ሲሉ በፌደራል ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰላምና
+8
"መንግስት የሕዝቡን ኑሮ በማሻሻል በቁርጠኝት እየሰራ ነው" የተከበሩ ፈትሂ መሕዲ (ዶ/ር)
መንግስት የሕዝቡን ኑሮ ለማሻሻል በቁርጠኝት እየሰራ ነው ሲሉ በፌደራል ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰላምና ውጭ ግንኙነት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ የተከበሩ ፈትሂ መሕዲ (ዶ/ር) ገልፀዋል። የሀረሪ ክልል ህዝብን በፌደራል ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ከሸንኮር፣ ጀኔላ፣ ሐኪም እና አቦከር ወረዳ ነዋሪዎች ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይቱ ወቅት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰላምና ውጭ ግንኙነት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ዶ/ር ፈትሂ እንደገለፁት መንግስት የሕዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ባለፉት ጊዜያት የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ ስለመሆኑን ገልፀዋል፡፡ የሕዝቡ ሕይወት የተሻለ እንዲሆን በኢኮኖሚው ረገድም ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። የመድረኩ ተሳታፊ የነበሩት የአራቱ ወረዳ ነዋሪዎች የተለያዩ ጥያቄዎች በማንሳት የተወያዩ ሲሆን የመሠረተ ልማት ዝርጋታ ፣ ሙስና እንዲሁም የመልካም አስተዳደር ችግሮች መቅረፍ እንደሚገባ ገልፀዋል። መንግስት ስራ አጥነትን፣ የሰላም ጉዳይ፣ የኑሮ ውድነት እና ሌሎችም ችግሮች ላይ ትኩረት መስጠት እንዳለበት ገልፀዋል፡፡ ለጥያቄዎቹ ምላሽ የሰጡት የሀረሪ ጉባኤ ምክትል አፈ ጉባኤ ወ/ሮ አሚና አብዱልከሪም ችግሮችን እንዲፈቱ መንግስት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልፀው እንደዚህ አይነት መድረኮች ችግር ለመፍታት አስፈላጊ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ በመድረኩ የተነሱ ችግሮች መፍትሄ እንዲያገኙ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት የሚሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በክልሉ ምክር ቤት የህግ አስተዳደር እና ቤቶች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ ኢማን መሀመድ የሕዝቡ ጥያቄ በየደረጃው ምላሽ ያገኝ ዘንድ በትኩረት እንሰራለን ብለዋል።

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሐረሪ ክልል ተወካዮች ከህብረተሰቡ ከተውጣጡ አካላት ጋር ውይይት አካሄዱ **** በኢፌድሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሐረሪ ክልል ተወካዮች  ከህብረተሰቡ ከተውጣጡ አካላት ጋር ለስድስተኛ ዙር ውይይት አካሒደዋል። በውይይት መድረኩም የተለያዩ የህዝብ ጥያቄዎች ተንፀባርቀዋል። በምክር ቤቱ የአባላት ስነ ምግባር እና ደንብ መሰረት የምክር ቤት አባላት ከመረጣቸው ህዝብ ጋር በተለያዩ ጊዜያት እዲመክሩና የህዝብ ጥያቄዎችንም ለሚመለከተው አካል የማቅረብ ሃላፊነት እንዳለባቸው ይታወቃል። በዚህ መሰረት በዛሬው ዕለት የሐረሪ ክልልን ህዝብን በፌደራል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የወከሉ የምክር ቤት አባላት ከመረጣቸው ህዝብ ጋር ለድስተኛ ዙር ውይይት አካሂደዋል፡፡ በፌደራል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የክልሉን ህዝብ የወከሉት የተከበሩ ወይዘሮ ሰሚራ ዩሱፍ ላለፈው 3 አመት በየ ስድስት ወሩ በፌዴራል የፀደቁ አዋጅን ለህብረተሰቡ የማስገንዘብና  የህዝብ ጥያቄዎችን በየደረጃው ለሚመለከተው አካል አቅርቦ ምላሽ እንዲሰጡ የማድረግ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል። የፌደራል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል እና በምክር ቤቱ የሰላምና የውጭ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ የተከበሩ ዶክተር ፈትሂ መሃዲ ባለፈዉ 6 ወር በፌደራል ደረጃ የፀደቁ 46 ስምምነቶችና አዋጆችን  በጀጎል ምርጫ ክልል ለሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች አብራርተዋል ። መንግስት በቅርቡ በተገበረው የማክሮ ኢኮኖሚን ተከትሎ ለመንግሥት ሰራተኞች ይጨመራል የተባለው የደሞዝ ማሻሻያ በሚዲያ ቢሰራጭም በተጨባጭ አለማየታቸውን አንስተው በገበያው ላይ የሚታየው የገበያ ጭማሪ አሳሳቢ ደረጃ መድረሱን የመድረኩ ተሳታፊዎች ጠቁመዋል ። በክልሉ በኮሪደር ልማት እየተሰራ ያለው የቱሪዝም ስራ ህብረተሰቡንም ጎብኚዎችም ያስደሰተ ሆኖ ሳለ አሁንም ድረስ በክልሉ ያልተፈታ የሆቴል እና የእንግዳ ማረፊያ ችግር ሊፈታ እንደሚገባ ጠቁመዋል ። በክልሉ እየታየ ያለው የመብራት መቆራረጥ እና ከፍተኛ የሀይል መዋዠቅ ንብረቶች ላይ ጉዳት እያደረሰ  በመሆኑ መፍትሄ ሊበጅለት እንደሚገባ ገልፀዋል ። ተጀምረው ያላለቁ ተጠናቀውም አገልግሎት የማይሰጡ ለአብነት ተጀምሮ ያልተጠናቀቀ ኢማም አህመድ አለማቀፍ ስታዲየም፣ የተመረቀው ዳቦ ቤት ለታለመላቸው አላማ እንዲውሉ መሰራት እንደሚገባ ጠቁመዋል ። መንግስት ህብረተሰቡን በጤናው ዘርፍ ለመደገፍ ያዘጋጀው የጤና መድህን አስደሳች መሆኑን ጠቁመው ነገር ግን ከፍተኛ የመድሀኒት እጥረት በመኖሩ ፣ በማህበረሰብ አቀፍ መድሀኒት መሸጫ መደብሮች ውስጥም  ለማግኘት መቸገራቸውን አክለዋል። ሐረር ከዚህ ቀደም የምትታወቅበትን ስፖርት ፣ ኪነ ጥበብ ዘርፍ በአሁኑ ሰዓት የተቀዛቀዘ በመሆኑ ወጣቱ ከሱስ ተላቆ ከዘርፉ እንዲጠቀም በትኩረት መስራት እንደሚገባ ከመድረኩ ተነስቷል። ከዚህ ቀደም ተጠይቀው  ምላሽ የተሰጠባቸውን እንደ የመጠጥ ውሃ፣ በግለሰብ ተይዘው የነበሩ የትምህርት ቤት የመንግስት መሬት ማስመለስ ፣የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በህግ ተጠያቂ የማድረግ ስራዎች እና የተለያዩ የህዝብ ጥያቄዎች  ምላሽ ማግኘታቸውን በክልሉ ምክር ቤት በጀትና ፋይናስ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ ፈትሂያ ሳኒ ጠቁመዋል። ለወጣቱ የስፖርት ማዝወተሪያ ስፍራዎችን መንግስት በከፍተኛ ወጪ ማስገንባቱን ያነሱት በክልሉ ምክር ቤት ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ ደሊላ ዩሱፍ  ማዘውተሪያዎች በቂ ባይሆኑም ያሉትን በአግባቡ መጠቀም እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል ። በጤና ፣ በትምህርት ፣ በቱሪዝም ፣ በመልካም አስተዳደር ችግር፣ ስራ አጥነትን የመቀነስ እና መሰል ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል ። በፌደራል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሐረሪ ክልል ህዝብ ተወካዮች የተነሱ የህዝብ ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ በየደረጃው ላሉ የመንግስት መዋቅሮች እንደሚያቀርቡ መግለጻቸውን ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል ። **** የሐረሪ ክልል ምክር ቤት የሕዝብ ግንኙነትና የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት/ ➥ ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/hararicouncil/ ➥ ቴሌግራም:▸ https://t.me/hararicouncil_info ➥ ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/channel/ ➥ ትዊተር፦ https://twitter.com/hararicouncil ➥ ፍለከሪ፡-https://www.flickr.com/photos/harari people regional council/ ➥ ድረገጽ፦http://www.hararicouncil.gov.et/

የምክር ቤት አባላቱ ከህዝቡ የሚነሱትን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ጨምሮ ከመረጣቸው ነዋሪዎች የሚነሱ ችግሮችን ለመፍታት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገለፁ። *** የሐረሪ ክልል ተወካይ የኢፌድሪ ህዝብ
+6
የምክር ቤት አባላቱ ከህዝቡ የሚነሱትን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ጨምሮ ከመረጣቸው ነዋሪዎች የሚነሱ ችግሮችን ለመፍታት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገለፁ። *** የሐረሪ ክልል ተወካይ የኢፌድሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ከሐረሪ ክልል ምክር ቤት አባላት ጋር በመሆን ከመረጣቸው ህዝብ ጋር የውይይት መድረክ ያካሂዳሉ። የሐረሪ ክልል ተወካይ የኢፌድሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የተከበሩ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር) እና ክብርት ወ/ሮ ሰሚራ ሀጂ በዛሬው ዕለት ከሐረሪ ክልል ምክር  ቤት  ም/አፈ-ጉባኤ የተከበሩ አቶ ሃሪፍ መሀመድ ፣ የሀረሪ ጉባኤ ም/አፈ-ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ አሚና አብዱልከሪም ጨምሮ ከክልል ምክር ቤቱ የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች ጋር በመሆን ከመረጣቸው ህዝብ ጋር በሚያካሂዱት የመራጭ ተመራጭ የውይይት መድረክ ዙርያ ላይ ውይይት አካሂደዋል። የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በኢፌዴሪ ህገ-መንግስት አንቀፅ 55/17 ከተሰጡት ስልጣንና ተግባራቶች መካከል የህዝብ ውክልና ስራን መወጣት አንዱ ሲሆን በምክር ቤቱ የአሰራርና የአባላት ስነ-ምግባር ደንብ ቁጥር 6/2008ንዕስ አንቀፅ 1 እና 2 መሰረት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ከመረጣቸው ህዝብ ጋር በተለያዩ መንገዶች በመገናኘትና መድረክ በመፍጠር ከመራጩ ህዝብ ጋር የሚወያዩ መሆኑን ይገልፃል። የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ከሐረሪ ክልል ምክር ቤት አባላት ጋር በመሆን ከመረጣቸው የክልሉ ነዋሪዎች ጋር ውይይት በማድረግ ከህዝቡ የሚነሱትን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ጨምሮ ከመረጣቸው ነዋሪዎች የሚነሱ ችግሮችን ለመፍታት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገልፀዋል።

የሐረሪ ክልል ምክር ቤት ከፍተኛ አመራሮች እና ሰራተኞች የአንድ ጀንበር አረንጓዴ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር አከናወኑ።
+7
የሐረሪ ክልል ምክር ቤት ከፍተኛ አመራሮች እና ሰራተኞች የአንድ ጀንበር አረንጓዴ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር አከናወኑ።

የሐረሪ ክልል ምክር ቤት ጽህፈት ቤት የሰራተኞች ቅሬታና የአሰራር ስርዓት ክፍተቶችን ጨምሮ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ዙርያ ላይ ውይይት ተካሄደ። የሐረሪ ክልል ምክር ቤት ጽህፈት ቤቱ ሰራተኞች ከ
+3
የሐረሪ ክልል ምክር ቤት ጽህፈት ቤት የሰራተኞች ቅሬታና የአሰራር ስርዓት ክፍተቶችን ጨምሮ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ዙርያ ላይ ውይይት ተካሄደ።
የሐረሪ ክልል ምክር ቤት ጽህፈት ቤቱ ሰራተኞች ከም/ቤቱ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በክልል ምክር ቤት በጽ/ቤቱ የሰራተኞች ቅሬታና የአሰራር ስርዓት ክፍተቶችን ጨምሮ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ዙርያ ላይ ውይይት በዛሬው ዕለት የጋራ ውይይት መድረክ ተካሂዷል። የውይይቱ መድረኩን አስፈላጊነት ገለፃ በማድረግ ያስጀመሩት የክልል ምክር ቤቱ የሴቶች፣ህፃናትና ህግ አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ ኢማን መሀመድ ሲሆኑ የሰራተኞች ቅሬታና የአሰራር ስርዓት ክፍተቶችን ጨምሮ የመልካም አስተዳደር ችግሮች፣ ቅጥር፣ የደሞዝና ደረጃ እድገት አሰጣጥ እንዲሁም በአገልግሎት አሰጣጥ ሂደት ዙርያ ላይ የሚታዩ ችግሮች መርህ አልባ እንዳይሆኑ ያሉ ክፍተቶችን በመለየት አሰራሮችን ለማሻሻልና ለመቅረፍ እንዲያስችል መድረኩ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል። በውይይቱ ወቅት የሰራተኞች ቅሬታና የአሰራር ስርዓት ክፍተቶችን ጨምሮ የመልካም አስተዳደር ችግሮች በተመለከተ የታዩ ክፍተቶችን እና የሰራተኞች ቅሬታ ቀርበው ውይይት የተካሄደበት ሲሆን በአጠቃላይ በክልል ም/ቤት ጽ/ቤቱ ውስጣዊና ውጪያዊ ዕይታ ያሉ የመልካም አስተዳድር ግኝቶች ዙርያ ላይ የጽ/ቤቱ የሪፎርምና መልካም አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ የኋላእሸት በጋራ መድረኩ ገለፃ አድርገዋል። በውይይቱም የክልል ምክር ቤቱ የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች እና የጽ/ቤቱ ሰራተኞች አስተያየታቸውን የሰጡ ሲሆን በቀጣይ ያሉና የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮቹን ለመፍታት ስር ነቀል ለውጥ ለማምጣት በጋራ መስራት አስፈላጊ መሆኑንን በመድረኩ የጋራ አቋም በመውሰድ መድረኩ ተጠናቋል ። ****

የሀረሪ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ከነገ ጀምሮ ይካሄዳል የሀረሪ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 3ኛ ዓመት 6ኛ መደበኛ ጉባዔውን ከነገ ጀምሮ ማካሄድ እንደሚጀምር የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ አስታውቀዋል
የሀረሪ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ከነገ ጀምሮ ይካሄዳል
የሀረሪ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 3ኛ ዓመት 6ኛ መደበኛ ጉባዔውን ከነገ ጀምሮ ማካሄድ እንደሚጀምር የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ አስታውቀዋል። የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ሱልጣን አብዱሰላም በሰጡት መግለጫ ምክር ቤቱ ከነገ ጀምሮ ለሁለት ቀናት በሚያካሄደው ጉባኤ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ይመክራል ብለዋል። በዚህም የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት የ2016 ዓ.ም አፈጻጸም ሪፖርት እና 2017 እቅድ ቀርቦ ውይይት እንደሚደረግ ተናግረዋል። እንዲሁም የጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የ2016 የበጀት ዓመት ሪፖርት እና የ2017 እቅድ ቀርቦም ውይይት ይደረግበታል ብለዋል። በጉባኤው የክልሉ መስተዳድር የ2017 ዓ.ም የሥራ ዘመን ማስፈጸሚያ በጀት ላይ በመምከርም ያፀድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል። ምክር ቤቱ በሚያካሂደው ጉባኤ የተለያዩ ሹመቶችንም ያፀድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልፀዋል።

የሐረሪ ክልል ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ህገ-ወጥ ንግድን ለመከላከልና በኢንቨስትመንት ውጤታማ ተግባራትን ለማከናወን ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራ እንደሚገባ አስታወቀ። የሀረሪ ክልል ኢንተርፕራይዝ
+3
የሐረሪ ክልል ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ህገ-ወጥ ንግድን ለመከላከልና በኢንቨስትመንት ውጤታማ ተግባራትን ለማከናወን ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራ እንደሚገባ አስታወቀ።
የሀረሪ ክልል ኢንተርፕራይዝ እና ኢንዱስትሪያል ልማት ቢሮ የ2016 በጀት አመት ሪፖርት እና የ2017 በጀት አመት እቅድ ለቋሚ ኮሚቴው ሪፖርቱን ያቀረቡት የኢንተርፕራይዝና ኢንደስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማኤል ዩሱፍ እንደተናገሩት የ2016 በጀት ዓመት የተሻለ አፈፃፀም ያስመዘግባል። በገጠርና በከተማ ላሉ ስራ አጥ ዜጎች ግንዛቤና ስልጠና በመስጠት የሀገሪቱን ብልፅግና እውን ለማድረግ የስራ እድል ፈጥረዋል። የኢንዱስትሪ ልማት፣ ማዕድንና ኢነርጂ ኢንቨስትመንት እንዲሁም የአምራቾችና የምርት ኢንዱስትሪዎችን መተካት እና ገቢን ማሳደግ የውጭ ምንዛሪ ተፅእኖን ለመቀነስ ያስችላል ብለዋል። የአካል ጉዳተኞችንና ሲቶችን ማካተት እና ጥቅሞች ማረጋገጥ፣ የገበያ ትስስር በመፍጠር ረገድ፣ የዋጋ ንረቱን ለማረጋጋት አርሶ አደሮችንና ሻማቾቺን በቅዳሜና እሁድ ገበያ በቀጥታ በማገናኘት አበረታች ስራ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ዘመናዊ፣ ወቅታዊና ተደራሽ የሆነ የአሰራር ስርዓት ለመዘርጋት፣ ህገ-ወጥ ንግድን ህጋዊ ለማድረግ እና በነዳጅ ምርቶች ላይ አስፈላጊውን ቁጥጥርና ክትትል ለማድረግ ጥሩ ስራ መሰራቱን ተናግረዋል። የቋሚ ኮሚቴ አባላት በሪፖርቱ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡ ሲሆን በክልሉ ለመገናኛ ብዙኃን እየሰጡ ያለውን አገልግሎት በማስተዋወቅ በኩል ጉድለቶች መኖራቸውን ተናግረዋል። ስራ አጦችን የማጣራት እና ገበያ ተኮር ስልጠና ለመስጠት ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ብለዋል። በክልሉ የሚገኙ ሆቴሎች ፅዱና ማራኪ እንዲሆኑ፣ የመአድን ልማትና የኢንቨስትመንት ስራዎች ዉጤታማነት ላይ ትኩረት ሊደረግ ይገባል ብለዋል። የኢንተርፕራይዙና ኢንዱስትሪያል ልማት ቢሮ ኃላፊው በኢንቨስትመንት ላይ የሚፈለገውን ርምጃ ለመውሰድ ውሱን ሁኔታዎች መኖራቸውን ተናግረዋል። ከከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ጋር በቅንጅት በመስራት ከክልሉ ፍላጎት ጋር የሚሄዱ ኢንቨስትመንቶችን የማበረታት ስራ እንደሚሰሩ ተናግረዋል። የክልሉ ምክር ቤት የፋይናንስ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ጅብሪል ማመድ ለቢሮው ባስቅመጡት የትኩረት አቅጣጫ በ2017 በጀት አመትእቅድ ህገ ወጥ ንግድን በመቆጣጠር ከነዳጅ ጋር ተያይዞ አስፈላጊውን ቁጥጥርና ክትትል ማድረግ ላይ በትኩረት የተሻለ ስራ ሊሰራ ይገባል። በስራ እድል ፈጠራ ላይ አስፈላጊውን እቅድ አውጥቶ ከሚመለከታቸዉ አካላት ጋር እንዲሰራና በማዕድን ልማት የሌሎች ክልሎችን ልምድ እንዲወስድ አሳስበዋል።

Koreen dhaabbii mana marii gabaasa raawwii hojii waggaa bara bajataa 2016 fi karoora bara bajataa 2017 Kan Biiroo Misooma Int
+3
Koreen dhaabbii mana marii gabaasa raawwii hojii waggaa bara bajataa 2016 fi karoora   bara bajataa 2017 Kan Biiroo Misooma Intarpiraayizii fi Industirii naannoo Hararii gamaaggamee jira.
Koreen dhaabbii mana marii naannoo hararii gabaasa raawwii bara bajataa 2016 Kan Biiroo Misooma Intarpiraayizii fi Industirii naannoo Hararii qorachuun kallattii kaa'eera. Hojii misooma industirii, carraa hojii uumuu, misooma daldalaa akkasimas Investimantii albuudaa fi anniisa wajjiin walqabatee   hojiiwwan bara bajatichaatti raawwataman hogganaan biiroo misooma Intarpiraayizii fi Induustirii naannoo Hararii Obbo Usmaa'il bal'inaan dhiheessaniiru. Haaluma walfakkaatuun  karoorri   bara bajataa 2017 biirichaa  dhiyaateera. Damee albuudaa irratti xiyyeeffannoon hojjatamuu akka qabu, liqii deebisiisuu hojiin jalqabame cimee itti fufuu akka qabu, carraa hojii uumuu irratti akkasumas qaala'iinsa gabaa tasgabeessuuf ciminaan hojjatamuu akka qabu koree dhaabbii mana marichaa dhaamaniiru. Dhimmoota xiyyeeffannoo barbaadan galtee karoora 2017 godhachuun biirichi fooyyeessuu qabu irratti Walitti qabaan koree dhaabbii dhimma diinagdee Obbo Jibriil Mahammad kallattii xiyyeeffannoo kennaniiru.

Koreen dhaabbii mana marii gabaasa raawwii karoora waggaa bara bajataa 2016 fi toora xiyyeeffannoo karoora bara bajataa 2017
+2
Koreen dhaabbii mana marii gabaasa raawwii karoora waggaa bara bajataa 2016 fi toora xiyyeeffannoo karoora bara bajataa 2017 biiroo barnootaa naannoo Hararii gamaaggamee jira. ⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼ Adoolessa 5/2016 sagantaa waaree booda gaggeeffameen Koreen dhaabbii mana marii naannichaa gabaasa raawwii bara bajataa 2016 Kan Biiroo barnootaa naannoo Hararii irratti bal'inaan mari'achuun kallattii kaa'eera. Hogganaa Itti Aanaa   biiroo barnootaa naannoo Hararii Obbo Zakkariyaa Abdulaziiz  gabaasa raawwii  waggaa bara bajataa 2016 biirichaa kan  dhiyeessan yoo ta'u koreen dhaabbii mana marii naannichaa gabaasicha dhaggeeffachuun marii bal'aa taasiseera. Haaluma walfakkaatuun  kallattiin karoora   bara bajataa 2017 biirichaa  dhiyaateera. Dhimmoota mana keessa ka'aniif hogganaa itti aanaa  biiroo biiroo barnootaa naannoo Hararii Obbo Zakkariyaa Abdulaziiz ibsa kan itti yoo ta'u Yaada koree dhaabbii galtee hojii bara 2017  godhachuun kan hojjatan ta'uu himaniiru. Dhimmoota bara 2017 fooyya'uu qaban ilaalchisuun walitti qabduu koree dhaabbii dhimma hawaasummaa Aadde Daliilaa Yuusuf  kallattii xiyyeeffannoo kennaniin:- Qulqullina barnootaa irratti xiyyeeffannoon hojjatamuu akka qabu Manneen barnootaa dhuunfaa irratti hordoffii fi to'annoon ciminaan taasifamuu akka qabu Sagantaan barattoota nyaachisuu qulqullina barnootaa milkeessuuf gahee guddaa qaba waan ta'eef  xiyyeeffannoo itti kennamuu akka qabu kallattii kennaniiru. * Mana Marii Naannoo Hararii Daayrektoreetii Sub-Qunnamtii Uummata fi Komminikeshinii Oddeeffannoo Aaddaa adda Mana Marii Naannoo harari argachuudhaaf :- ➥ 𝐅𝐚𝐜𝐞𝐛𝐨𝐨𝐤 : https://www.facebook.com/hararicouncil/ ➥ 𝐓𝐞𝐥𝐞𝐠𝐫𝐚𝐦 : https://t.me/hararicouncil_info ➥ 𝐘𝐨𝐮𝐭𝐮𝐛𝐞  : https://www.youtube.com/channel/ ➥ 𝐓𝐰𝐢𝐭𝐭𝐞𝐫  : https://twitter.com/hararicouncil ➥ 𝐅𝐢𝐥𝐢𝐤𝐞𝐫 : https://www.flickr.com/photos/harari people regional council/ ➥ 𝐖𝐞𝐛𝐬𝐢𝐭𝐞 : http://www.hararicouncil.gov.et/

Gamaaggamni raawwii gabaasaa fi karoora seektaroota naannoo koree dhaabbii mana marii naannoo harariitiin gaggeeffamu akkuma
+3
Gamaaggamni raawwii gabaasaa fi karoora seektaroota naannoo koree dhaabbii mana marii naannoo harariitiin gaggeeffamu akkuma itti fufetti jira.
Sagantaa guyyaa har'aa waaree booda gaggeeffameen koreen dhaabbii mana marii naannichaa gabaasa raawwii bara bajataa 2016 kan biiroo misooma magaalaa fi konistiraakshinii naannoo hararii qoratee jira. Qophii pilaanii magaalaa,  kaartaa mirkaneessa qabiyyee lafaa, Ijaarsa seeraan alaa fi weerara lafaa ittisuu, nageenyaa fi kenniinsa tajaajila gamoo mirkaneessuu, kenniinsa heyyama ijaarsaa, hojiilee misooma manneenii fi konistiraakshinii mootummaa wajjiin walqabatee hojii bara bajataa 2016tti hojjataman hogganaa Itti Aanaa biiroo misooma magaalaa fi konistiraakshinii naannoo hararii Obbo Reeyis Yuusuf bal'inaan dhiheessaniiru. Biirichi bara 2017 tti bulchiinsa gaarii, qophii fi bulchiinsa laafaa, sirna kaadastaraa, to'annaa ijaarsaa cimsuu akkasumas  pirojektoota jalqabaman xumuruu toora xiyyeeffannoo godhachuun kan irratti hojjatu ta'uu ibsameera. Dhimmoota xiyyeeffannoo barbaadan irratti walitti qabaan koree dhaabbii dhimma diinagdee Obbo Jibriil Mahammad kallattii xiyyeeffannoo kaa'aniin:- Hanqina manneen jireenyaa naannoo keenyaa xiqqeessuuf  qaama dhimmi ilaallatu waliin ta'uun xiyyeeffannoon hojjatamuu akka qabu, Aanaalee baadiyyaa pilaaniin itti ragga'e bara 2017tti qabatamaan hojiirra ooluu akka qabu, Pirojektiilee kaappitaalaa buleeyyii jalqabamanii karatti hafan xumursiisuuf sochii cimaan taasifamuu akka qabu   akkasumas Hayyama ijaarsa manaa seera qabeessa kennuu irratti xiyyeeffannoon hojjatamuu akka qabu kallattii kennaniiru.
Mana Marii Naannoo Hararii Daayrektoreetii Sub-Qunnamtii Uummata fi Komminikeshinii Oddeeffannoo Aaddaa adda Mana Marii Naannoo harari argachuudhaaf :- ➥ 𝐅𝐚𝐜𝐞𝐛𝐨𝐨𝐤 : https://www.facebook.com/hararicouncil/ ➥ 𝐓𝐞𝐥𝐞𝐠𝐫𝐚𝐦 : https://t.me/hararicouncil_info ➥ 𝐘𝐨𝐮𝐭𝐮𝐛𝐞  : https://www.youtube.com/channel/ ➥ 𝐓𝐰𝐢𝐭𝐭𝐞𝐫  : https://twitter.com/hararicouncil ➥ 𝐅𝐢𝐥𝐢𝐤𝐞𝐫 : https://www.flickr.com/photos/harari people regional council/ ➥ 𝐖𝐞𝐛𝐬𝐢𝐭𝐞 : http://www.hararicouncil.gov.et/

Koreen Dhaabbii Mana Marii Naannoo Hararii gabaasa raawwii bara hojii 2016 kan Biiroo Abbaa Alangaa waliigalaa naannoo harari
+3
Koreen Dhaabbii Mana Marii Naannoo Hararii gabaasa raawwii bara hojii 2016 kan Biiroo Abbaa Alangaa waliigalaa naannoo hararii qoratee jira. **** Koreen dhaabbii mana marii naannichaa gabaasa raawwii bara bajataa 2016 kan biiroo Abbaa Alangaa waliigalaa naannoo hararii irratti bal'inaan mari'achuun kallattii kaa'eera. Ittigaafatamaan  Biiroo Abbaa Alangaa waliigalaa naannoo hararii Obbo Ayyuub Ahimad gabaasa raawwii  waggaa bara bajataa 2016 waajjira Abbaa Alangaa waliigalaa kan  dhiyeessan yoo ta'u koreen dhaabbii mana marii naannichaa gabaasicha dhaggeeffachuun marii bal'aa taasiseera Haaluma walfakkaatuun  kallattiin karoora   bara bajataa 2017 biirichaa  dhiyaateera. Yaadaa fi gaaffiilee mana keessaa ka'aniif komishiinarii komishiinii mana amala sirreessaa naannoo hararii Obbo Kaalid Nuuree fi hogganaan Biiroo Abbaa Alangaa waliigalaa naannoo hararii Obbo Ayyuub Ahimad ibsa itti laataniiru. Kallattii xiyyeeffannaa walitti qabduun  koree dhaabbii dhimma bulchiinsa seeraa, dub/ fi daa'im/ Aadde Imaan Mahammad kaa'aniin:- Seeroota fooyya'uu qaban kan sadarkaa wixinee irra jiran qaama dhimmi ilaallatuun raggaasisuuf sochiin godhamaa jiru gaarii ta'ullee ciminaan itti deemamuu akka qabu Tajaajila Abukaattoo ilaalchisee itti quufiinsa hawaasaa guddisuu irratti xiyyeeffannoon hojjatamuu akka qabu Hubannoo seeraa uumuu irratti ciminaan hojjatamuu akka qabu, Galmee malaammaltummaa irratti hojiin jalqabame gaarii ta'ullee ciminaan itti fufuu akka qabu kallattii kennaniiru.

Koreen Dhaabbii Mana Marii Naannoo Hararii gabaasa raawwii bara bajataa 2016 kan Biiroo galiiwwanii naannoo hararii qorate. *
+3
Koreen Dhaabbii Mana Marii Naannoo Hararii gabaasa raawwii   bara bajataa 2016 kan Biiroo galiiwwanii  naannoo hararii qorate. ** Koreen dhaabbii mana marii naannichaa gabaasa raawwii   bara bajatichaa biiroo galii naannoo hararii irratti mari'achuun kallattii kaa'eera. Humna galii sassaabuun cimsuun madda galii naannoo keenyaa bal'isuun, komii gibira kaffaltootaa furuun itti quufiinsa hawaasaa guddisuu irratti xiiqiin hojjatamuu akka qabu koreen dhaabbii dhaamaniiru. Yaadaa fi gaaffiilee mana keessaa ka'aniif hoggantuu Biiroo galiiwwanii  naannoo hararii Aadde Ikraam Abduqaadir akkasumas miseensonni manejmantii biirichaa ibsa itti laataniiru. Dhimmoota xiyyeeffannoo barbaadan irratti  dura teessuun koree dhaabbii  dhimma baajataa fi faayinaansii Aadde Fatihaa Saanii kallattii kennaniin:- Oditii taaksii ciminaan taasifamuu akka qabu, haqummaa gibiraa fi kenniinsa tajaajila gibira kaffaltoota ammayyeessuuf hojii dijitaalaayzeshinii cimuu akka qabu, Sirna sassaabbii galii fayyaaleessaa gochuun galiin naannichaa fooyya'uu akka qabu Dubartoota gahoomsuun gara hoggansaatti fiduu irratti jalqabbiin jiru gaarii ta'ullee kana caalaa fooyya'uu akka qabu kallattii xiyyeeffannoo kaa'aniiru.

Koreen dhaabbii mana marii gabaasa raawwii karoora waggaa bara bajataa 2016 fi karoora bara bajataa 2017 Biiroo Bulchiinsa Na
+6
Koreen dhaabbii mana marii gabaasa raawwii karoora waggaa bara bajataa 2016 fi karoora bara bajataa 2017 Biiroo Bulchiinsa Nagaa fi Nageenya Naannoo Hararii gamaaggamee jira. **** Koreen dhaabbii mana marii naannoo hararii  gabaasa raawwii karoora waggaa bara bajataa 2016 akkasumas karoora bara bajataa 2017 Biiroo Bulchiinsa Nagaa fi Nageenya Naannoo Hararii dhageeffachuun marii bal'aa taasiseera. Nageenya,  olaantummaa seeraa mirkaneessuu irratti, yakka ittisuu, hojiiwwan riifoormii ilaalchisee  hojiileen jajjabeessaa fi abdii namatti horu hojjatamuu koreen dhaabbii mana marichaa kan ibsan yoo ta'u dhimmoota fooyya'uu qaban irrattiis yaada fooyya'iinsaa kennaniiru. Yaadaa fi gaaffiilee mana keessaa ka'aniif hogganaan Biiroo Bulchiinsa Nagaa fi Nageenya Naannoo Hararii Obbo Toofiq Mahammad akkasumas miseensonni maanejmantii biirichaa ibsa laataniiru. Dhimmoota xiyyeeffannoo barbaadan irratti  kallattii xiyyeeffannoo  dura teessuun koree dhaabbii dhaabbii dhimma bulchiinsa seeraa fi dubartootaa Aadde Imaan Mahaammad kallattii xiyyeeffannoo  kaa'aniin:- Leenjii ijaarsa humnaa milishaa irratti ciminaan hojjatamuu akka qabu, Hirmaannaa tola ooltummaa wajjiin wal qabatee dargaggoonni naannoo keenyaa naannoo biraa deemanii hojii tola ooltummaa irratti akka bobba'an hojjatamuu akka qabu, Sirna kenniinsa tajaajila buufataalee poolisii irratti hojiin hordoffii fi to'annoo akkasumas galltee barbaachisu guutuu irratti  ciminaan hojjatamuu akka qabu, Poolisoota tiraafikii haaraa ilaalchisuun hojiin hojjatame gaarii ta'ullee leenjii ijaarsa humnaa yeroo yeroon kennuun cimuu akka qabu kallattii kennaniiru.

ለ26ኛው አለም አቀፍ የሀረር ቀን ለመሳተፍ ወደ ሀገር ቤት የገቡ ሁለተኛ ትውልድ ኢትዮጵያውያን በቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ አቀባበል ተደረገ 26ኛው ዓለም አቀፍ የሀረር ቀን በዓል ከሰኔ 27
+6
ለ26ኛው አለም አቀፍ የሀረር ቀን ለመሳተፍ ወደ ሀገር ቤት የገቡ ሁለተኛ ትውልድ ኢትዮጵያውያን በቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ  አቀባበል ተደረገ
26ኛው ዓለም አቀፍ የሀረር ቀን በዓል ከሰኔ 27 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ለ10 ተከታታይ ቀናት በተለያዩ ዝግጅቶች የሚከበር ሲሆን ይህንን መሰረት በማድረግ  የክልሉ ተወላጆች ከመላው ዓለም ወደ ሀገር ቤት እየገቡ ይገኛሉ::   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ( ዶ/ር)  ያደረጉት ሀገራዊ ጥሪ በመቀበል እንዲሁም በ26ኛው አለም አቀፍ የሀረር ቀን በዓል ላይ ለመሳተፍ ወደ ሀገር ቤት የመጡ ዲያስፖራዎች ቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ በፌደራልና በክልሉ መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች አቀባበል ተደርጎላቸዋል። በርካታ ሀረሪዎችና የሀረር ተወላጆች ሀገራዊውን ጥሪ በመቀበልና በ26ኛው አለም አቀፍ የሀረር ቀን ላይ ለመሳተፍ ከተለያዩ አለማት ወደ ሀገር ቤት የገቡ ሲሆን በሺዎች የሚቆጠሩ ደግሞ ወደ ሀገር ቤት እየተመሙ ይገኛሉ። በአቀባበሉ ላይም የሀረሪ ክልል ምክር ቤት አፈጉባኤ አቶ ሱልጣን አብዱሰላም ፣ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ዲኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የዴሞክራሲ ግንባታ ማእከል ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ካሊድ አልዋን፣ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ በላይነህ አቅናው ፣ የሀረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አብዱልሀኪም ኡመርን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በዛሬው እለት በቦሌ ዓለምአቀፍ አየር ማረፊያ የአቀባበል ስነ-ስርዓቱን በይፋ አስጀምረዋል።
የሐረሪ ክልል ምክር ቤት የሕዝብ ግንኙነትና የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት/ ወክታዊ እና ተከታታይ መረጃዎችን በቅርበት ለማግኘት Like & Share በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑን። ➥ ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/hararicouncil/ ➥ ቴሌግራም:▸ https://t.me/hararicouncil_info ➥ ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/channel/ ➥ ትዊተር፦ https://twitter.com/hararicouncil ➥ ፍለከሪ፡-https://www.flickr.com/photos/harari people regional council/ ➥ ድረገጽ፦http://www.hararicouncil.gov.et/ አብራችሁን ስለሆናችሁ ደስተኞች ነን.

በሀረሪ ክልል ለወረዳ ምክር ቤት አፈ-ጉባኤዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ፡፡

በሀረሪ ክልል ለወረዳ ምክር ቤት አፈ-ጉባኤዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ፡፡ በሐረሪ ክልል ምክር ቤት ጽህፈት ቤት አዘጋጅነት ለወረዳ ምክር ቤት አፈ-ጉባኤዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰቷል፡፡
+5
በሀረሪ ክልል ለወረዳ ምክር ቤት አፈ-ጉባኤዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ፡፡
በሐረሪ ክልል ምክር ቤት ጽህፈት ቤት አዘጋጅነት ለወረዳ ምክር ቤት አፈ-ጉባኤዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰቷል፡፡ ስልጠናውን ያስጀመሩት የሐረሪ ክልል ምክር ቤት ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ገዛኸኝ በቀለ የስልጠናው ዋና አላማ የወረዳ ምክር ቤት አፈ-ጉባኤዎች በተሰጣቸው ስልጣን ችግር ፈቺ የሆነ ውጤታማ ስራ ይሰሩ ዘነድ አቅማቸውን ለማጠናከር ነው ብለዋል፡፡ ከወረዳ አስፈፃሚ አካላት ጋር  ያለውን ግንኙነት ለማጠናክር በቀጣይ ትኩረት ተሰጥቶ የሚሰራ መሆኑን አክለው ገልፀዋል፡፡ የህብረተሰቡን የልማት እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በመመለስ አስተማማኝ ሰላም እና ልማት ለማረጋገጥ የወረዳ ምክር ቤቶች አፈ ጉባኤዎች ሚናቸውን መውጣት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል፡፡ የወረዳ ምክር ቤቶች እና አመራሮች የልማት እንቅፋት የሚሆኑ ችግሮችን ከመነሻ ለመፍታት ቁርጠኛ ሊሆኑ ይገባል ብለዋል፡፡ የስልጠና ተሳታፊ አፈ ጉባኤዎችም ያገኙትን ግንዛቤ ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡
የሐረሪ ክልል ምክር ቤት የሕዝብ ግንኙነትና የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት/ ➥ ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/hararicouncil/ ➥ ቴሌግራም:▸ https://t.me/hararicouncil_info ➥ ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/channel/ ➥ ትዊተር፦ https://twitter.com/hararicouncil ➥ ፍለከሪ፡-https://www.flickr.com/photos/harari people regional council/ ➥ ድረገጽ፦http://www.hararicouncil.gov.et/

በኦዲት ግኝቶች ዙሪያ ከ2013 እስከ 2015 ኦዲት አስደርገው መልስ ያልሰጡና በማስተካከያው ተቀባይነት ያጡ መስሪያ ቤቶች ጋር የሀረሪ ክልል ምክር ቤት አባላት በተገኙበት ውይይት ተካሄደ፡፡ ****
+3
በኦዲት ግኝቶች ዙሪያ ከ2013 እስከ 2015 ኦዲት አስደርገው መልስ ያልሰጡና በማስተካከያው ተቀባይነት ያጡ መስሪያ ቤቶች ጋር የሀረሪ ክልል ምክር ቤት አባላት በተገኙበት ውይይት ተካሄደ፡፡ ***** ማስረጃ ማቅረብ አለመቻል ጉዳዩን ወደ ሕግ ተጠያቂነት እንደሚወስደውም ተገልፃል፡፡ የሀረሪ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ሱልጣን አብዱሰላም በኦዲት ግኝቶች ዙሪያ ማስረጃ አለማቅረብ ጉዳዩን ወደ ጠቅላይ አቃቤ ህግ እንደሚመራ ተናግረዋል፡፡ የኦዲት ግኝቶችን ለማስተካከል መስራት እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡ የሀረሪ ክልል ምክር ቤት የበጀትና ፋይናንስ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ም/ሰብሳቢ ወይዘሮ አሚና አብዱልከሪም በበኩላቸው የወጡ ህጎችንና የወጡ መመሪያዎችን ተግባራዊ ማድረግ የሁላችንም ሀላፊነት ሊሆን ይገባል ብለዋል፡፡ የሀረሪ ክልል ምክር ቤት የሕግ ሴቶችን አስተዳደር ሰብሳቢ ወይዘሮ ኢማን አህመድ በበኩላቸው ምንም ምላሽ የማይሰጡ የተቋማቱ የፋይንናስ ሀላፊዎች እንዳሉ ገልፀው ይሄ ሊሻሻል እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡ ተጠያቂነትና ግልፀኝነት ለማስፈን የክትትል ስራ እንደሚሰራም ተናግረዋል፡፡ የሀረሪ ክልል ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ካሊድ አብዲ በበኩላቸው የመስሪያ ቤቶች አመራሮች ሀላፊነት ያለባቸው በመሆኑ በጀትን ተጠያቂነት ባለው መልኩ ስራ ላይ መዋሉን መከታተል ይገባል ብለዋል፡፡ የ2013 -2015 የክልሉ መንግስት ሒሳብ በትክክል እንዳልተዘጋም ተናግረዋል፡፡ የሀረሪ ክልል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዋና ኦዲተር አቶ አብዱልማሊክ በከር የአመራር ለውጥ በሚኖርበት ገዜ ርክክብ ሲደረግ ተጠያቂነትን ለማስፈን ትክክለኛው መንገድ ተከትሎ ርክክብ መደረግ እንዳለበት ተናግረዋል፡፡ በኦዲት ግኝቶች ዙሪያ 46 ተቋማት የተሳተፉ ሲሆን 18 የሚሆኑት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ ምንም ምላሽ ያልሰጡ 20 የሚጠጉ ሲሆን ተቀባይነት ያላገኙ ሶስት መስሪያ ቤቶች መሆናቸውንም ከመድረኩ ተገልፃል፡፡

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች እና አመራሮች በሐረሪ ህዝብ ክልል ምክር ቤት በመገኘት የምክር ቤቱን የአሰራር ሂደትና ተሞክሮዎች ዙርያ የልምድ ልውውጥ አካሄዱ። **** በክል
+9
የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች እና አመራሮች በሐረሪ ህዝብ ክልል ምክር ቤት በመገኘት የምክር ቤቱን የአሰራር ሂደትና ተሞክሮዎች ዙርያ የልምድ ልውውጥ አካሄዱ።  **** በክልል ምክር ቤቱ የህግ፣ ሴቶችና ህፃናት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሰቢ የተከበሩ ወ/ሮ ኢማን መሀመድ እና የክልል ም/ቤት ፅ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ገዝሃኝ በቀለ ለልምድ ልውውጡ ከድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ለመጡትን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች እና ከፍተኛ አመራሮችን እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት አቀባበል አድርገውላቸዋል። የተከበሩ ወ/ሮ ኢማን መሀመድ ለልዑካን ቡድኑ ባደረጉት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግራቸዉ ላይ እንደተናገሩት የሐረሪ ህዝብ ክልል ምክር ቤት ከአቻ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ጋር መልካም ተሞክሮዎችን ለመማማርና በሁለቱ ምክር ቤቶቹ መካከል ያለውን የስራ ግኑኝነት በተሻለ መናበብና ቅንጅታዊ አሰራር እንዲሁም የምክር ቤቶቹን ትስስር የሚያጠናክር መሆኑን በመግለፅ የልዑካን ቡድኑ ወደ ሐረሪ ህዝብ ክልል ም/ቤት በመምጣቱ በምክር ቤቱ ስም አክብሮታቸዉን ገልፀዋል። በመቀጠልም በም/ቤት ጽ/ቤቱ የህዝብ ግንኙነትና ኮምኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በአቶ ገመቺስ ዋቁማ የክልል ምክር ቤቱን አሰራር፣ አወቃቀርና አደረጃጀት ፤ የህግ አወጣጥ የአሰራር ሂደትን በተመለከተ፣ የክትትልና ቁጥጥር ሂደትና አሰራርን ጨምሮ የህዝብ ውክልና ማረጋገጥ እንዲሁም የም/ቤት ጽ/ቤቱን አጠቃላይ የአሰራር  ሂደት በተመለከተ ለልዑካን ቡድኑ ገለፃ አድርጓል። የድሬዳዋ አስተዳድር ምክር ቤት አባላት እና የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች የተሰጠውን ገለፃ መነሻ በማድረግ ሀሳብ አስተያየትና ጥያቄዎችን አቅርበዉ ሰፊ ውይይት አድርገዋል። በውይይቱ ለተነሱ አስተያየቶች አና ጥያቄዎች በክልል ምክር ቤቱ የህግ አማካሪ አቶ ሀምዲ መሀመድ እና በም/ቤቱ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ምላሽና ሰፊ ማብራሪያ ተሰጥተዋል። በመጨረሻም ሁለቱም ምክር ቤቶች ተባበረው ለሀገር ብልፅግና የጎላ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ ልምዶችን ለማጎልበት በቅንጅት መስራት እንደሚገባ ተጠቁሟል።