የሁልባራግ ወረዳ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት
Open in Telegram
952
Subscribers
-124 hours
+27 days
No data30 days
Posts Archive
+1
ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተሠጠ ማሳሰቢያ፦
ከሻሸመኔ ወደ አዳሚቱሉ የሚሄደው የኃይ ማስተላለፊያ መስመር ላይ የጥገና ሥራ የሚከናወን በመሆኑ አርብ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ እስከ ሰኞ ሐምሌ 20 ቀን 2018 ዓ.ም ከንጋቱ 12 ሰዓት ድረስ በአሰላ፣ በአዳሚቱሉ፣ በቡታጅራ፣ በወራቤ፣ በቡኢ እና አካባቢው ኤሌክትሪክ ተቋርጦ ስለሚቆይ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ ከወዲሁ ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳስባለን፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል!!
(መረጃውን ያደረሰን የወራቤ ኤሌክትሪክ አገልግሎት መስጫ ማዕከል ነው)
በወረዳይ በባጀት ዘማኒ የትዌጠኑ ሙራድቸ በሱትከ በከሚሎት የአመ ሰበይ ተፈያጅነተ ጎት አሶት አቀተሌን -የሀምዳላይ ሽፈ
ቃግሜ 03/2018 ቶ.ኢ ሁልባራግ ተራከባት -ኬራቴ
በጉትለኜ ቶጲየ ቀፈት መንግስት በስልጤ ዞን ዩልባራግ ወረደ መቲንዳደሬ ቲያትዋስደይ የናረይ የክትበት ጋርቻ የ12ተ ወሬ የብል ተረሻት ሪፖርተ የዞፎፎ ዴረ ባውጄይ አያም ተከመላን።
https://www.facebook.com/share/1GCNxhZLpf/
የ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ሂደት ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ መጠናቀቁን ተከትሎ በሂደቱ የነበሩ ጥንካሬዎች እና ድክመቶች ተገምግመዋል።
https://www.facebook.com/100063683741222/posts/1673626364770139/?app=fbl
#ጥብቅ_ማስጠንቀቂያ!
ከሁልባራግ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት የተላለፈ የጥንቃቄ መልዕክት፦
በሁልባራግ ወረዳ በተለይም ኬራቴ ከተማ ላይ በምሽትም ይሁን በቀን ያለ ምንም በቂ ምክንያትና ያለ ህጋዊ ፈቃድ የሚደረገው የርችት መተኮስ ተግባር በማህበረሰቡ ላይ ከፍተኛ ድንጋጤና አላስፈላጊ ስጋት እየፈጠረ ይገኛል።
በመሆኑም የአካባቢን ሰላምና ጸጥታ በአስተማማኝ ሁኔታ ለማስከበር ሲባል ማንኛውም ግለሰብ በወረዳችን በቀንም ሆነ ከምሽቱ 12:00 ሰዓት በኋላ ርችት መተኮስ፣ አላስፈላጊ የሆኑ ሰልፎችን ማድረግና ግርግር መፍጠር የማይቻል መሆኑን ተቋሙ አስታውቋል።
ይህንን መመሪያ በመተላለፍ ርችት ሲተኩስ፣ ሀላፊነት የጎደለው ሰልፍና ግርግር ሲፈጥር በተገኘ ማንኛውም አካል ላይ ጥብቅ ህጋዊ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን የወረዳው ሰላምና ፀጥታ ፅ/ቤት ገልጿል።
የአካባቢያችንን ሰላም በጋራ እንጠብቅ!!
ግንቦት 16/2018 ሁልባራግ ኮሙኒኬሽን -ኬራቴ
ነግደ ለትቂበልነ!!
እንደሚታወቀው በሁልባራግ ወረዳ ባለፉት አመታት የተሰሩ የልማት ስራዎችና ፕሮጀክቶች የምረቃ መርሃ ግብር የፊታችን እሁድ ግንቦት 09/2018 በደማቅ ሁኔታ ይካሄዳል።
ለዚህ ፕሮግራም በርካታ እንግዶች ወደ ወረዳችን ስለሚመጡ የወረዳው ወጣቶችና አጠቃላይ ነዋሪዎች እንግዳ ተቀብላችሁ እንድታስተናግዱ የወረዳው አስተዳደር ጥሪውን ያቀርባል።
በዚህ መሰረትም ነገ ጧት የኬራቴ ከተማና አካባቢዋ ነዋሪዎች በሙሉ የሚሳተፉበት የፅዳት ዘመቻ ስለሚኖር ሁላችሁም አደባባይ በመገኘት እንድትሳተፉ በአክብሮት ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
ቡርደነ ጡሃረ ባሶት ነግዳዶነ ለትቂበልነ!!
የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች የምረቃ ፕሮግራም በሁልባራግ ወረዳ!👇👇👇
https://www.facebook.com/share/1bHdXha2KZ/
በዩንሴፍ የተራድኦ ድርጅት ድጋፍ የተገኘ ከ52,000 በላይ መጽሀፍ በሁልባራግ ወረዳ ለሚገኙ ትምህርት ቤቶች ተሰራጭቷል።
👇
https://www.facebook.com/share/1JDQ5UKT6S/
+9
በወረዳይ በላቶዋ በፈየ መቲንዳደሬ ጉለንተ የትጀመሩ ብልቸ በቀሬይ ሼሽት ወሪ በከሚሎት ዩመተይ ፈረጃተ ላትሪግጦት ጃድ ይትረሻን - የሁርሚ የሀምዳላይ ሽፈ
አምሌ 07/2018 ቶ.እ. ሁልባራግ ተራከባት - ኬራቴ
በጉትለኜ ቶጲየ ቀፈት መንግስት በስልጤ ዞን ዩልባራግ ወረደ ወባጀ ጋር የ4ለኜ ውርት የ52ኜ ሴረኜ ቡልሻከ ባውጄይ አያም በኬራቴ ከተመ አትዋሰዳን።
ዩልባራግ ወረደ ቡር አቲንዳደሪ የሁርሚ የሀምዳላይ ሽፈ በቡልሻኒ የባሉምኮ በወረዳይ በላቶዋ በፈየ መቲንዳደሬ ጉለንተ የትጀመሩ ብልቸ በቀሬይ ሼሽት ወሪ በከሚሎት ዩመተይ ፈረጃተ ላትሪግጦት ጃድ ይትረሻን ባሎን።
ቡር አቲንዳዳሪ በድባያም ቦባጀ ጋሪ የነቁይ የላቶዋ የፈየ መትንዳደሬ ሱልቸ በሱተ ጀዋበ ረከቦኔ ያመ ሰበይ ተፈያጅነት ያሰቶነኮ ሁልሚ ዬድበይማን አትኬዋኜ ቃምቸቸ ኢትቄርቢማነይ ሁለም ያሶነኮ ኢትረሻን ባሎን።
ዩልባራግ ወረደ ወባጀ ጋር ቡር አፈ ቡልሻን የሁርሚ የፍቃዱ እንዳለ በቡልሻኒ የባሉምኮ በሰ መቃምከ እነቆን የፈየ መቲንዳደሬ ምካትቸ እትፈቶነኮ ላሶት ዋ ቦረዳይ የትጀመረይ የላቶ ዋ የዴሞክራሲ ቅልቃዬ ላጀዲዶት ያትኬዋኚ ክ/ጋርቸ ያለይሙ አትዋጫት የሮሬ በውኖትከ ቁሚሮ ብለኒሙ ከውኖት ኢነብሪቢማን ባሎን፡፡
በቡልሸኒ ተዋሳጂላሎ ተነቁይ ሱልቸዋ ኡስባቦ ጉት በሉልነትም ቱንገዋ መትግራገቤ ክትበት ጋር፣ ታፊያ ድጋየ ዋቦት፣ቲርሰት ክትበት ጋር፣ ተመይዋ ሽፋ ክትበት ጋር፣ ተኮሬንቴ ተጃጂጎት አዘር፣ ታሽር ዋ ተገናምኒሙ አትኬዋኚ ክትበት ጋርቸ ቲንዛዛኔ ለነቁ ሱልቸ ዋ ኡስባቦ የክትበት ጋርቸ ወሻይብቸ ጀዋብ ዋ ማፍታቼ ታባኔ አትጋቦት አቀተሌን።
ከሁልባራግ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የተላለፈ የምስጋና መልዕክት‼️
የሁልባራግ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሽፋ ሀምዳላ በዛሬው ዕለት በመዲናችን ወራቤ ከተማ የሀገራዊ ለውጡን 8ኛ ዓመት አስመልክቶ በተካሄደው ዞናዊ የድጋፍ ሰልፍ ላይ በወረዳው ከሁሉም ቀበሌያት በመውጣት በንቃት የሰልፉ ተሳታፊ ለሆናችሁ በሙሉ ልባዊ ምስጋናዬን አቀርባለሁ ብለዋል።
የወረዳችን የሕዝብ ያሳየው ከፍተኛ ንቅናቄና ደማቅ ተሳትፎ ማህበረሰቡ በብልጽግና ፓርቲ ላይ ያለውን ጽኑ እምነትና ለለውጡ መንግስት ያለውን የማይነጥፍ ድጋፍ በተግባር ያሳየበት መሆኑንም አክለው ገልጸዋል።
የድጋፍ ሰልፉ ስኬታማ እንዲሆን በየደረጃው የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱ የወረዳ አመራር አካላት፣ ባለሃብቶች፣ የቀበሌ አመራሮች፣ የፀጥታ አካላት፣ የሚዲያ አካላት፣ ወጣቶች፣ ሽማግሌዎች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ ተሳታፊዎችን የሰልፉ ቦታ ላይ ለማድረስ የተሽከርካሪ ድጋፍ ላደረጋችሁ የተሽከርካሪ ባለንብረቶች፣ ሾፌሮች፣ በአጠቃላይ መላው የወረዳችን ማህበረሰብ ዞናዊ የድጋፍ ሰልፉ በስኬት ተጀምሮ እስኪጠናቀቅና ተሳታፊዎች ወደ ወረዳ በሰላም እንዲመለሱ ድጋፍ ያደረጋችሁ በሙሉ በወረዳው አስተዳደር ስም ምስጋናዬን አቀርባለሁ ብለዋል።
ሚያዝያ 19/2018 ሁልባራግ ኮሙኒኬሽን -ኬራቴ
ሞቶ ተገኝቷል❗️
ከስር የምትመለከቱት ግለሰብ በስልጤ ዞን ሁልባራግ ወረዳ አንጋሞ ዬዴ ቀበሌ አበሎሶ ወንዝ ላይ ሞቶ ተገኝቷል።
የሟቹን ማንነት የሚገልፅ መታወቂያም ሆነ ሌላ መረጃ ማግኘት ስላልተቻለ ሼር በማድረግ፣ ቤተሰቡን በማፈላለግ እንድትተባበሩን እንጠይቃለን።
አስክሬኑ በአሁን ሰዓት ሁልባራግ ፖሊስ ፅ/ቤት የሚገኝ ሲሆን ተጨማሪ መረጃ የወረደው ፖሊስ አዘዥ ረ/ኢ/ር ሰባሃዲን ሸውሞሎ 0916703040 ተጨመሪ 0920972838 ዋ/ኮርሚቻ መሀመድ በመደወል መግኘት ትችላላችሁ።
ወቅታዊ የጥንቃቄ መልዕክት‼️
በአንዳንድ የአጎራባች ዞኖችና አካባቢዎች ጅብ በሰው ልጆች ላይ አደጋ እያደረሰ በመሆኑ ሁሉም የማህበረሰባችን ክፍሎች ጥንቃቄ እንድታደርጉ እናሳስባለን።
በአሁኑ ወቅት በዳመና ምክኒያት ሳይመሽ ሊጨልም ስለሚችል ህፃናትም ሆነ አዋቂዎች የተለያየ ቦታ ሄደን ስንመለስ በጊዜ በመመለስ እንዲሁም የቤት እንስሳትንም ጭምር ከቤት ቅርበት ባለው ቦታ በማቆየት ጥንቃቄ እንድታደርጉ ስንል መልዕክታችንን ለማስተላለፍ እንወዳለን።
በተያያዘም በአሁኑ ወቅት የበልግ ወቅት ዝናብ እየዘነበ በመሆኑ የጎርፍ አደጋ ሊከሰት ስለሚችል የውሃ መውረጃ ቦዮችንና ቱቦዎችን በአግባቡ የመክፈት ስራ በመስራት ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል።
በሌላ በኩል ወንዞች ሲሞሉ ሰው የመውሰድ አደጋ ስለሚያስከትሉ በተለይ አላዋቂ የሆኑ ህፃናትን ብቻቸውን ወንዝ አቋርጠው እንዳይሄዱ በማድረግ አደጋውን መከላከል ያስፈልጋል ሲል የወረዳው ፖሊስ አሳውቋል።
መጋቢት 29/2018 ሁልባራግ ኮሙኒኬሽን -ኬራቴ
#ተራዘመ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ እስከ ሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም. መራዘሙን አሳውቋል።
ለሁልባራግ ወረዳ ነዋሪዎች በሙሉ፦
እንኳን የስልጤ ብሔር ራሱን በራሱ የማስተዳደር ህገ-መንግስታዊ መብቱ የተረጋገጠበት 25ኛ ዓመት የብር ኢዮቤልዮ በዓል ''የኡራግ አያም'' በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን!!
በዓሉ ከመጋቢት 22/2018 እስከ 23/2018 በወራቤ ከተማ በደማቅ ስነ-ስርዓት ይከበራል።
በመሆኑም መላው የወረዳችን ነዋሪዎች በዚህ ታላቅ በዓል ላይ እንድትሳተፉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ፤ አደረሰን!!
ሀበይ አጄጄሙ!!
የሁልባራግ ወረዳ አስተዳደር
ሰበር ዜና❗️
የ1447ኛው የሸዋል ወር ጨረቃ በሳውዲ አረቢያ ዛሬ ባለመታየቷ ኢድ አል ፊጥር በዓል መጋቢት 11/2018 ዕለተ አርብ ወይም ሸዋል 01/1447 ዓ.ል እንደሚከበር ተረጋግጧል።
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለኢድ አል-ፊጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ🙏
