en
Feedback
Ashara Media - አሻራ ሚዲያ

Ashara Media - አሻራ ሚዲያ

Open in Telegram

የህዝብ ድምፅ

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Ashara Media - አሻራ ሚዲያ

Channel Ashara Media - አሻራ ሚዲያ (@ashara_media) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 77 494 subscribers, ranking 3 377 in the News & Media category and 428 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 77 494 subscribers.

According to the latest data from 09 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -105 over the last 30 days and by 215 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 17.39%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 13.16% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 13 464 views. Within the first day, a publication typically gains 10 190 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 61.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የህዝብ ድምፅ

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 10 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

77 494
Subscribers
+21524 hours
+1037 days
-10530 days
Posts Archive
ጠላት ይተማመንባት የነበረችውን በ12ኛ ዕዝ 71ኛ ክፍለጦር በዚህ መልኩ ድርምስምሷ ወጥቷል። ይህ የምትመለከቱት በለስ ቀንቶት ከተማረከው የጠላት ሠራዊት መካከል ጥቂቱ ነው።

ጠላት ይተማመንባት የነበረችውን በ12ኛ ዕዝ 71ኛ ክፍለጦር በዚህ መልኩ ድርምስምሷ ወጥቷል። ይህ የምትመለከቱት በለስ ቀንቶት ከተማረከው የጠላት ሠራዊት መካከል ጥቂቱ ነው። መረበኞች ነን መረጃ አጥማጆች! ቴሌግራም ገፃችን👉https://t.me/MerebMedia24

በዚህ አዲስ ዓመት መባቻ ላይ፣ በትግላችን ማዕከል የምናስባቸው እና የደማቸው ጥሪ የሚያስቆጣን ወገኖቻችን መኖራቸውን አንዘነጋም። ​በሃይማኖታቸው ምክንያት መከራና ሰቆቃ እየደረሰባቸው ያሉ የክርስትና እና የእስልምና እምነት ተከታዮች፣ ቤተ-እምነቶቻቸው ሲደፈሩ እና ሲቃጠሉ የታገሱት የመከራ ፅዋ ሞልቶ እየፈሰሰ ነዉ። ​በየማጎሪያው ያለ ፍርድ በበቀል እና በተረኝነት ስሜት የታጎሩ የፖለቲካ እና የማንነት እስረኞች፣ በማሰቃያ ክፍሎች ውስጥ አካላቸው የጎደለ እና ህይወታቸው ያለፈ ወገኖቻችን ፍትህ የማግኘት መብታቸውን ማስከበር የትግላችን አንዱ ግብ ነው። ​ በልማት ስም ከቀያቸው የተፈናቀሉ፣ ንብረታቸው የወደመባቸው፣ የአገዛዙን ጥቃት በመሸሽ ስደት ሀገር የሚሰቃዩ ወገኖቻችን ወደ ቀደመ ቀያቸው ተመልሰው በክብር እና በነፃነት የሚኖሩበት ሁኔታ እንዲፈጠር እንታገላለን። በመጨረሻም ትግላችን የህልውናችንን ዋስትና በብረት ማረጋገጥ ብቻ ሳይሆን፣ የሁሉም ብሔሮችና ብሔረሰቦች እኩልነት፣ ህግ የበላይነት እና ፍትህ የሰፈነባትን፣ የትኛውም ዜጋ በቋንቋው እና በማንነቱ የማይገፋባትን ከነባር ስልጣኔዋ፣ ታሪካ እና ባህሏ ያልተቃረነች ፍትሃዊ ኢትዮጵያን የመገንባት ስልታዊ ግብ አለው። ያለፈው አመት ለአማራም ሆነ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝቦች ወሳኝ የሆነ ዕድል ተፈጥሯል፤ የያዝነው አመት ደግሞ ይህን የትብብር ዕድል ተጠቅመን ህልውናችንን የምናረጋግጥበት፣ የጠላት የማጥፊያ አቅሞቹን ሰብረን በአሸናፊነት በአዲስ ፖለቲካዊ መድረክ ሀገርን ወደ ተሟላ እና ዘላቂ ሰላም ለማሸጋገር የምንሰራበት ይሆናል። በድጋሚ መልካም አዲስ ዓመት የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ

በሀገራችን በከፍተኛ የእርስ በእርስ መጠራጠር ብሎም መገፋፋት ውስጥ እንዲኖሩ ከፍተኛ ሴራ የተሰራባቸው ህዝቦች የጠላትን እንዲሁም የውጭ ሀይሎችን ጸረ ትብብር ጫና ተቋቁመው በአብሮነት ለመቆም መነሳት የአመቱ ብሎም የክፍለ ዘመኑ ትልቅ ድል ነው። በዚህም የህዝቦችን የተሳሰረ ዕጣ ፈንታ ከጋራ የህልውና ስጋት ባሻገር ለሀገር ግንባታ በጋራ መስራት የሚቻልበትን ፖለቲካዊ መደላድል ለመፍጠር ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል። በመሆኑም እንደ አማራ ሕዝብ ሁሉ ለሕልውናቸው፣ ለባህላቸው፣ ለማንነታቸውና ለፍትሕ የሚታገሉ ሌሎች የኢትዮጵያ ወንድምና እህት ሕዝቦች በጋራ መቆማቸውንና መተሳሰራቸውን የሚያውጁበት ታሪካዊ ወቅት ላይ እንገኛለን። ፬. በህዝባችን እና በሰራዊታችን ተጋድሎ የከሸፉት የአገዛዙ የስልጣን ማራዘሚያ ፕሮጀክቶች ያለፈው 2018 ዓ. ም ፖለቲካዊ መዋቅሩን በወታደራዊ አገዛዝ እየለወጠ ያለዉ ዘረ-ፈጁ አገዛዝ በምርጫ ስም ህጋዊ የጭፍጨፋ እውቅና እና ካርድ ለማግኘት እንዲሁም በብሔራዊ ምክክር ስም ግለሰባዊ ቅዠቶችን የብሔራዊ ምክክር ውጤት ለማድረግ በቢሊዬኖች የሚቆጠር ገንዘብን በማባከን በሰፊው የደከመበት ዓመት ነበር። ይሁን እንጅ የአማራ ህዝብን ጨምሮ መላው ኢትዮጵያዊ ባደረገው ተጋድሎ እና የነቃ እንቅስቃሴ ምክንያት አገዛዙ በምርጫ ስም ዓለምን ማታለል የማይችልበትን ይልቁንም ምርጫን ስልጣን ላይ ለመቆዬት የሚጠቀምበት የማጭበርበሪያ ስልት መሆኑን ማሳዬት ተችሏል። በምርጫም ሆነ በምክክር ስም የህልውና አደጋ የተደቀነበትን ህዝብ የህልዉና ጥያቄ ማዳፈን እንደማይቻል ተረጋግጧል። በመሆኑም ያለፈው ዓመት አገዛዙ ብሔራዊ አጀንዳወችን ለይስሙላ በማጉላት፣ ያልተደረገ ምርጫን እንደተደረገ በማስመሰል እንዲሁም በተጧጧፈ ጦርነት ውስጥ ሆኖ ብሔራዊ ምክክር በሚል ስም ስልጣንን ህጋዊ ቅቡልነት ያለው ለማድረግ ያደረጋቸው ሙከራወች ሙሉ በሙሉ የከሸፉበት መሆኑ በታሪክ የሚታወስ ነው። ይህ አዲስ ዓመት ተራ የዘመን መለወጫ ብቻ ሳይሆን የአማራን ህዝብ ከምድር ገጽ ለማጥፋት፣ ታሪኩን ለመደምሰስ፣ ሀብቱን ለመዝረፍ እና ስነ-ህዝባዊ አወቃቀሩን ለመቀየር በአገዛዙ የታወጀውን የዘር ማጥፋት ጦርነት በመመከት፣ የህዝባችንን ፍጹም አሸናፊነት የምናበስርበት ታሪካዊ ምዕራፍ እንዲሆን እየተመኘን ተከታዮችን ጥሪወች እናቀርባለን! ፩) ለመላው የአማራ ህዝብ:- አረመኔያዊውን ግፍና መከራ በትዕግስትና በጀግንነት እያሸነፍክ ላለኸው ኩሩ ሕዝባችን፣ አዲሱ ዓመት የሰላም፣ የፍትሕ፣ የዕረፍትና የታሪካዊ ክብርህ መመለሻ ዓመት እንዲሆንልህ ንቅናቄያችን ከትላንት በተሻለ መልኩ ደምና አጥንቱን ከስክሶ ህልውና እና ነጻነትን ለማስከበር ከምንጊዜውም በላይ ለመሥራት ቁርጠኛ መሆኑን ዛሬም እንደ ትላንቱ ያረጋግጣል። ስለሆነም የምታደርገውን ሁሉን አቀፍ ድጋፍና ደጀንነት ከምንግዜውም በላይ አጠናክረህ እንድትቀጥል ታሪካዊ ጥሪያችንን እናቀርባለን። የትኛውም ስትራቴጂም ሆነ ታክቲክ አንድነትን አያክለውም፤ አንድነትን የሚያሳጣ አማራጭ በምንም መመዘኛ ተገቢ፣ አስፈላጊ አለያም ጠቃሚ ሊሆን አይችልም። ህዝባዊ አንድነት፣ መዋቅራዊ አንድነት እና የአመራር አንድነት የትግላችን አይተኬ ስትራቴጂካዊ አቅሞቻችን ናቸው። በየትኛውም ጊዜ በተለይ ደግሞ በዚህ ወቅት አንድነትን የትግሉ ስትራቴጂካዊ አቅም መሆኑን ተረድተን አቅማችንን እንጠብቅ። ከዚህ በተቃራኒ የሆነ አካሄድ እና አሰላለፍ በጋራ እንታገል። አማራን በንዑስ ማንነት እና የጥቅም ትስስር በትኖ፣ የጀመረውን ዘር ማጥፋት በስኬት ለማጠናቀቅ ጠላት ከፋፍሎ ሊያጠፋን እየሰራ እንደሆነ ተረድተን አማራ ከብዙ አመታት በኋላ ያገኘውን ብሔራዊ አንድነት በጥንቃቄ ልንጠብቅ እና ከአቆርቋዥ ከፋፋዮች በጽናት ልንከላከለው ይገባል። በተጨማሪም አማራው የህዝብ እና የድርጅት አንድነት ባሳካበት አመት ህዝቡን ከከበባ እና ንጥልነት አውጥቶ በሀገር ውስጥ ካሉ ብሔራዊ ሀይሎች ጋር መተባበር መቻሉ ለአማራም፣ ለሌላውም ብሎም ለሀገር ትልቅ ዕድልን አስገኝቷል። ይህን መልካም ዕድል እና ተስፋ መንከባከብ ይገባል። ፪) ለአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ አመራርና አባላት፦ አማራ ተገፍቶ እና ተበድሎ የሚጠፋ ህዝብ ሳይሆን፣ በመከራ ውስጥ ታድሶ፣ የብረት ምሽግ ሆኖ የሚነሳ የጽናት አምድ ነው! የታጠቁ ድሮኖች፣ የተደረደሩ ታንክና መድፎች የተበላሹ የፕሮፓጋንዳ ማሽኖች የጊዜያዊ ጉልበት ምልክቶች እንጂ የህዝብን የእውነት እና የፍትህ ፍላጎት አይሰብሩም። የጠላቶቻችን ውድቀት ተቃርቧል፤ የብልፅግናን አገዛዝ አረመኔያዊ ጥቃት መክታችሁ፣ የሕዝባችሁን ሕልውና ለማስከበር በዱር በገደሉ የምታሳዩት የጀግንነት ታሪክ በአሁኑ ትውልድ ብቻ ሳይሆን፣ በመጪውም ትውልድ ዘንድ ታሪክ በወርቅ ቀለም የሚከትበው አኩሪ ገድል መሆኑን ለማሳሰብ እንወዳለን። አዲሱ 2019 ዓ.ም የሕዝባችንን ከሕልውና አደጋ አውጥተን፣ ነፃነት እና እኩልነትን የምናረጋግጥበት እንዲሁም ወንጀለኞችን ለፍርድ አደባባይ የምናቀርብበት የድል ዓመት እንዲሆን፣ ከምንጊዜውም በላይ ከፍተኛ አደራና ቃል-ኪዳናችንን የምናድስበት ዘመን እንዲሆን እንመኛለን። ፫) ለጸረ አገዛዝ ብሔራዊ ሀይሎች ካለፉት ስምንት አመታት የተማርነው ወሳኝ እውነት በተራ ለመበላት ወረፋ የምንጠብቅበት ጊዜ እና ሁኔታ ላይ አለመሆናችን ነው። እናም ሁሉም ህዝባዊ ሀይል ለህልውናው በአንድ የጋራ ጠላት ላይ በሁሉም ግምባር የቆመበት ምዕራፍ ለዚህ ለትውልዶች ለተደገሰው ጦርነት የመጨረሻው ምዕራፍ ነው፤ ለህዝቦች የአሸናፊነት ምዕራፍ። እናም ቀጣዩ አመት በትብብር አቅም የህልውና አደጋን በመመከት ጠላትን ጨርሶ በማስወገድ እልህ አስጨራሽ ተጋድሎ የምናደርግበት አመት ነው። ለዚህም የተጀመሩ መልካም የትብብር ተግባራትን በማስቀጠል፣ የጠላትን የፕሮፓጋንዳ ጥቃት ለመመከት በህዝባዊነት እንድንሰራ መልዕክታችንን ለማስተላለፍ እንወዳለን። የህዝቦችን እና የብሔራዊ ሀይሎች መልካም ግንኙነት ለጠላት ትልቅ አደጋ በመሆኑ ይህን ለማፍረስ የሚሰራቸውን ተግባራት ለመቀልበስ የህዝብን አቅም በጋራ መጠቀም ይገባል። ለዚህም የትብብሩን ተስፋዎች መንከባከብ የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ህዝቡ እና ሁሉም ብሔራዊ ሀይሎች በሁሉም ረገድ የጠላትን መግቢያ በሮች ለመድፈን የጋራ ርብርብ ልናደርግ ይገባል። ፬) ለአፍሪካውያንና ለመላው የዓለም ሕዝብ፦ በኢትዮጵያ ምድር እየተፈጸመ ያለውን አረመኔያዊ የሰብአዊ መብት ረገጣና የዘር ማጥፋት ወንጀል ዓለም በዝምታ ሊመለከተው አይገባም። የጭቁን ሕዝቦችን የነፃነት ድምፅና ትግል በሁሉም መስክ ሊደገፍ የሚገባዉ ነው። ​የአማራ ህዝብ የህልውና እና የፍትህ ጥያቄ ከዓለም አቀፍ ህጎች (IHL) እና ከህግ የበላይነት ጋር የተጣጣመ ነው። በምስራቅ አፍሪካ፣ በአፍሪካ ቀንድ እና በቀይ ባህር ቀጠና ዘላቂ መረጋጋት እና የንግድ መስመር ሰላም ሊመጣ የሚችለው የህዝባችን ሰብአዊ፣ ታሪካዊ እና ፖለቲካዊ መብቶች ሲከበሩ ብቻ ነው። ያልተረጋጋች ኢትዮጵያ ለቀጠናው ስጋት ናት፤ የህዝባችንን ትግል መደገፍ ደግሞ በቀጠናው ህጋዊነትን፣ ፍትህን እና ዘላቂ ሰላምን የመትከል ብቸኛው መንገድ ነው። በመሆኑም የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ሰላም እና መረጋጋትን የሚያውከውን የብልፅግና አገዛዝን ማስወገድ ለሰላማዊ የንግድ እና ፖለቲካ እንቅስቃሴ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን በማመን አገዛዙን ባለመደገፍ እና ለተጋድሏችን ዲፕሎማሲያዊ ድጋፍ በመስጠት የበኩላችሁን ድርሻ እንድትወጡ እንጠይቃለን። ፭) ለአገዛዙ የሰቆቃ ሰላባወች:-

አዲስ ዓመትን አስመልክቶ ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የተሰጠ መግለጫ መስከረም 01/ቀን 2019 ዓ.ም መላው የአማራ ህዝብ እና ኢትዮጵያዊያን፣ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ አመራርና አባላት፣ የብልፅግናን አገዛዝ በየግንባሩ የምትታገሉ ፀረ ብልፅግና ኃይሎች፣ አፍሪካውያን ወንድሞቻችንና ለመላው የዓለም ሕዝብ፤ ድርጅታችን የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) እንኳን ለ2019 ዓ.ም አደረሳችሁ፣ አደረሰን ይላል! ሀገራችን ኢትዮጵያ አዲሱን ዓመት እየተቀበለች ያለችው የቀውስ አገዛዙ በነደፈው የጥፋት ፕሮጀክት ምክንያት ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ምስቅልቅል ውስጥ ሆና ነው። የህዝባቸውን ህልውና ባስቀደሙ ብሔራዊ ኃይሎች እና በኢትዮጵያዊነት ላይ ሁለንተናዊ አደጋ በደቀነው የአገዛዙ ኃይል መካከል በሚደረግ ጦርነት ምክንያት በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ የእልቂት እና የቀውስ ምዕራፍ ውስጥ እንገኛለን። ከሀገራዊ ቀውሱ ባሻገር ብልፅግና በጎረቤት ሀገራት የውስጥ ሰላም ላይ ጭምር በደቀነው አደጋ ምክንያት የቀይ ባህር ከባቢን ጨምሮ የቀጣናው መልክዓ ፖለቲካ በዘላቂ አለመረጋጋት ውስጥ እንዲገባ ሆኗል። እንደ ሀገር ሙሉ ሉዓላዊነታችንን ለታዳጊ ኢምፔሪያሊስቶች በማከራዬት ኢትዮጵያን ተላላኪ መንግስት ያደረገው አረመኔያዊ አገዛዝ የሥልጣን ዕድሜውን ለማራዘም ብቻ የውስጥ ጦርነቶችን ከማፋፋም አልፎ፣ አደገኛ ቀጣናዊ ቀውሶችን እያወለደ አገሪቱን ወደማያባራ ቀጠናዊ ጦርነት በመምራት ወደ ጥልቁ ገደል ለመክተት እየተንደረደረ ይገኛል። ዘመኑ ባፈራቸው የቴክኖሎጂ መሣሪያዎች ሁሉ ንጹኃንን በድሮን መደብደብ፣ በታሪካዊ ከተሞችና በሃይማኖት ቦታዎች ላይ ከባድ መሣሪያ በመተኮስ፣ ኢትዮጵያዊያንን በማንነታቸው ማሳደድ፣ ማሰርና ማፈናቀል የአገዛዙ መገለጫዎች ከሆኑ ውለው አድረዋል። አገዛዙ የኢትዮጵያንን ማንነት እና ወጥ ስልጣኔ ምልክት የሆነውን ዘመን መለወጫን ጊዜን ለመለወጥ በምክክር ኮሚሽን ስም አጀንዳ በማድረግ ከኢትዮጵያዊ ማንነታችን እና ከታሪካችን ጋር የተጋጨ መሆኑንም አሳይቶናል። በተለይም በአማራ ህዝብ ላይ የተደቀነው ሁለንተናዊ የህልውና አደጋ ስሁት ትርክትን እና አጥፊ ፖሊሲዎችን እና ስልቶችን መነሻ ያደረገም ጭምር መሆኑ ይታወቃል። የአማራ ህዝብ ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር ያደረገውን ሰላማዊ ትግል እና የለውጥ ተስፋ እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ስልጣን ላይ የወጣው አገዛዝ የአማራን ሕዝብ ከምድረ-ገጽ ለማጥፋት ሁሉን አቀፍ ጦርነት እያደረገ ይገኛል። ለጨቋኞች ተንበርክኮ የማያውቀው የአማራ ሕዝብም የአገዛዙን የህልውና አደጋ ቀንበር ለመስበር በጽናት መራር ትግል እያደረገ ባለበት በዚህ ወቅት ዘርፈ ብዙ ድሎችንም ማስመዝገብ ችሏል። የጠላትን ወረራ በመመከት የተደረጉት ወታደራዊ ተጋድሎዎች በጦረኝነት ለወረራ የመጣውን ሰራዊት የውጊያ አቅም እና ሞራል በተደጋጋሚ መስበር ችለዋል። በዚህም የአማራ ህዝብ በመሪ ድርጅቱ አማካኝነት የገጠመውን የዘር ማጥፈት ጦርነት እየመከተ ይገኛል። ባለፈው አመት በተለያየ ቦታ የተገኘቱት የውጊያ ድሎች ባሻገር በተለይ በስልጠና ዘርፍ የታየው ሽህ ክንዶችን በአንዴ አሰልጥኖ ማስመረቅ የተቻለበት በመሆኑ በትግሉ ወቅት ትልቅ አቅም መጨመር ችሏል። ከእነዚህ እና መሠል ድሎች ባሻገር 2018 አመት ምህረት በአማራ ህዝብ ትግል ወሳኝ ስትራቴጂካዊ ድሎችም ተመዝግበዋል። ፩. የአፋብን ውልደት ትግሉ ባልተማከሉ አደረጃጀቶች ውስጥ መቆዬቱ የራሱ ታክቲካዊ ፋይዳ የነበረዉ ቢሆንም አቅምን የሚከፋፍል በመሆኑ የአደረጃጀት አንድነትን ማረጋገጥ ግዴታ ነበር። የአማራ ህዝብም በታሪኩ እና በትግል ሂደቱ መራር በሆነ መንገድ የተረዳው ተጨባጭ እውነት ቢኖር አንድነት መተኪያ የለሽ ስትራቴጂካዊ አቅም መሆኑን ነው። በአማራነት የመደራጀትና የመታገል ጉዳይ ግለሰባዊ እና ጠባብ ቡድናዊ ፍላጎትን፤ ትናንሽና መለስተኛ ቅራኔና ፀብን፥ ኩርፊያና ልዩነትን መተውና ለወል ፍላጎታችን መሰለፍን ይጠይቃል። ከትናንትም ሆነ ከዛሬ ነገሮቻችን መካከል መርጦ መዘንጋት እና ለይቶ ማንሳትን፣ ስለጋራ አማራዊ ፍላጎታችን በአንድ መስመር መሰለፍን ይጠይቃል። ይህንን የማይታበል ሀቅ በመቀበል የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ምስረታን ማሳካታችን የአመቱ ዋነኛ ፖለቲካዊ ስኬት ነበር። በዚህ ውስጥ የትግሉ ስትራቴጂካዊ አቅሞችን በማሰባሰብ እና በአንድ ድርጅታዊ ማዕቀፍ ስር ህልውናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ትግል ውስጥ ሁሉም አቅሞች እንዲውሉ ለማድረግ መድላድሉን መፍጠር ተችሏል። ይህም የአመቱ ስኬት ብቻም ሳይሆን በቀጣይ ጊዜያት ለሚያደርጋቸው ትግሎች ወሳኝ ስትራቴጂካዊ አቅም ሆኖ የሚቀጥል ነው። ፪. የዓለምን ትኩረት የሳበው ተጋድሏችን አፋብን ከምስረታው ማግስት በሁሉም ዕዞቹ ውስጥ ከትግሉ መነሻ ጀምሮ የነበረውን ህዝባዊ ድጋፍ የትግል ግለቱን ለማስቀጠል እንዲያስችል በሁሉም አካባቢዎች የተደረጉት ህዝባዊ መድረኮች ወሳኝ ህዝባዊ ንቅናቄ ፈጥረዋል። በነዚህ መድረኮች ህዝቡ በአጀንዳዎቹ ላይ የበለጠ ግልጸኝነት በመፍጠር፣ የትግሉን አላማ ለማሳካት ያለውን ቁርጠኝነት እና መነሳሳት ያሳየበት ነበር። በዚህም የአደረጃጀት አንድነቱን፣ ህዝባዊ ደጀኑን በአላማ በማስተሳሰር መሬት ላይ ይበልጥ መትከልና ማጽናት ተችሏል። ከዚህ በተጨማሪ የአማራ ህዝብ የትግልን አላማዎች በሀገር ውስጥ ብሎም በአለምአቀፍ ማህበረሰብ ዘንድ፣ በተመሳሳይ በአንድ ድምጽ በስፋት ማሰማት ተችሏል። ለአማራ ህዝብ ጥሪ ለወትሮው ጆሮ ባለመስጠት የምስክርነት እና የትርጓሜ ግፍ ሲፈጸምበት ቢኖርም ዛሬ ግን በተለያዩ ሀገራት፣ በተለያዩ ቋንቋዎች አማራ ለራሱ እውነት መመስከር ብሎም ማስረዳት ችሏል። በዚህም በአማራ ህዝብ ትግል ዙሪያ በተዛባ መልክ ተስፋፍተው የኖሩ ትርክቶችን ለማረም ጥቂት ዕድል ተገኝቷል። የአማራ ህዝብ መደመጥ በመቻሉም ህዝቡን ነጥሎ ለማጥቃት እና ለማስጠቃት ከዳግመ ጣሊያን ወረራ ጀምሮ የተተከሉ የጥላቻ ግምብ ለማፍረስ እና ጥርጣሬን አስወግዶ በህዝቦች መካከል መልካም ግንኙነት ለመፍጠር የሚያስችል ድልድይ እየተፈጠረም ይገኛል። ፫) የፖለቲካ ርዕደ መሬት የፈጠረው የትብብር ማዕቀፍ ዘረ ፈጁን አገዛዝ በማስወገድ በፋሽስታዊ ዕሳቤ ተተክሎ የኖረውን የትውልዶች ጦርነት በህዝባዊ ትግላችን መቀልበስ እና ህልውናን በዘላቂነት ማረጋገጥ አንደኛው ተልዕኳችን ነው። አማራን ለማጥፋት የተነሳው ዘረ ፈጅ አገዛዝ ሌሎች ህዝቦችንም በጉልበት ጨፍልቆ ከመግዛት አልያም ከመጥፋት ውጭ ሌላ አማራጭ አላስቀመጠም። ለዚህም እንዲመቸው የህዝቦች የጎንዮሽ መልካም ግንኙነት እንዲበላሽ እና ቅራኔወች እንዲሰፉ በሙሉ አቅሙ እየሰራ ይገኛል። ይሁንና እርስ በዕርስ እንዲተላለቁ የተደገሰላቸው ህዝቦች እና ብሔራዊ ሀይሎች የጥፋት ትርክት እና ሴራን አክሽፈው፣ ለህልውናቸው ሲሉ የጋራ ጠላትን በጋራ ለመታግል መግባባታቸዉን የሚያውጁበት የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ደርሰዋል። በየትኛውም የዓለም ማዕዘን ተከስተው የነበሩ ፀረ-ህዝብ አገዞች የተገረሰሱት የጋራ እጣ ፋንታን በሚጋሩ ፀረ ጭቆና የትግል ኃይሎች ነው። ይህ መሠረታዊ እውነት ህዝባዊ አላማን አንግበው በሚታገሉ ብሔራዊ ሕዝባዊ ኃይሎች መካከል ያሉትን ልዩነቶች ተቀራርበው እንዲሰሩ አስችሏል። በእርግጥም እንኳንስ የሁሉም ህዝቦች ብሎም ሀገር የህልውና አደጋ ውስጥ ወድቀው አይደለም፤ የአንድ ማህበረሰብ የህልውና አደጋ ብቻዉን ህዝባዊ ኃይሎች እንዲተባበሩ የሚያስገድድ በቂ ምክንያት ነው።

እነ ክርስቲያን ታደለ እና ከ600 በላይ ታራሚዎች ከጠባቡ ወደ ሰፊው እስር ቤት ወጥተው ወደ ሰፊው አስር ቤት ወጥተዋል። እንኳን በህይት አገኘናችሁ
እነ ክርስቲያን ታደለ እና ከ600 በላይ ታራሚዎች ከጠባቡ ወደ ሰፊው እስር ቤት ወጥተው ወደ ሰፊው አስር ቤት ወጥተዋል። እንኳን በህይት አገኘናችሁ

በመረሐቤቴ አውራጃ ሰፊ ሕዝባዊ መድረኮች እና የአደረጃጀት ሥራዎች መካሔዱ ተገለፀ!! ጳጉሜ 05/2018 ዓ.ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መረሐቤቴ አውራጃ በሚገኘው ሞረትና ጅሩ ወረዳ ሰፊ ሕዝባዊ መድረኮች እና የአደረጃጀት ሥራዎች በተሳካ ሁኔታ መካሄዳቸውን የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ መርሀ-ቤቴ ስምሪት ቡድን አስታወቀ። በመድረኮቹ ወቅት መሠረቱ ሕዝብ የሆነው የፋኖ ፖለቲካዊ ትጥቅ ትግል ከማህበረሰቡ ጋር በየዕለቱ በመወያየት ላይ ሲገኝ፣ በቀበሌዎች አዳዲስ ድርጅታዊ አሠራሮችንና መዋቅሮችን የማስፋፋት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ገለፁ። የአገዛዙን ፀረ-አማራነት ጉዞ በመመከት፣ በፋኖ አሠራርና መርህ መሠረት ማህበረሰቡን በክላስተርና በአውራጃ ደረጃ በማደራጀት ወደ አንድ የተቀናጀ አደረጃጀት የማምጣት ሥራ በቋሚነት እየተሠራበት እደሚገኝ አክለው ገልፀዋል። በሞረትና ጅሩ ወረዳ ከተከናወኑ ሰፊ የሕዝባዊ መድረክ እና የአደረጃጀት ሥራዎች መካከል የ"አብዲናጎ ክላስተር "እና "የውሎ ክላስተር" በርካታ ቀበሌዎችን በማቀናጀት አደረጃጀቶች የተዘረጉ ሲሆን፣ ከሕልውና ትግሉ ጎን ለጎን የሕዝቡን የመልካም አስተዳደር ችግሮች በሲቪል አስተዳደሩ በኩል በተሳካ መልኩ እዲፈቱ የሚያስችል ተሠርቷል ብለዋል። በተካሄዱት ሕዝባዊ መድረኮች በየደረጃው ያሉ የድርጅቱ አመራሮች፣ በተለይም የዕዝና የኮር አመራሮች የተገኙ ሲሆን፣ አመራሮቹ ከማህበረሰቡ ለተነሱ አስተያየቶችና ጥያቄዎች አዎንታዊ ምላሽ በመስጠት፤ ከወቅታዊ ሁኔታዎች አኳያ ሰፊ ዝርዝር ጉዳዮች ላይ በመወያየት ቀጣይ የትግል አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል። በዚህም መሠረት አባት አርበኞች በአደረጃጀታቸው፣ ወጣቶች ደግሞ ወደ ስልጠና ማዕከላት እየገቡ በመሰልጠን የብልፅግናን አገዛዝ በጋራ ሊታገሉ እንደሚገባ መግባባት በመድረኩ የተሳተፉት የመላው ማህበረሰብ አባላት በትግሉና በአፋብን ሁሉን አቀፍ ውሳኔዎች መደሰታቸውን ገልጸዋል። በመጨረሻም የዕዙ የስምሪት ቡድን፣ የአማራ ሕዝብ የትግሉ ዋና ባለቤት በመሆኑ በሚችለው አቅም ሁሉ በቁርጠኝነት አስተማማኝ ደጀን ሆኖ ሊታገል እንደሚገባ በመጠቆም መድረኮቹ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቃቸውን አሳውቋል። " ክብር ለተሰውት ሰማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

የአፄ ዓምደ ጽዮን ኮር በሸዋ ጠቅላይ ግዛት የፈፀመው ተጋድሎ፤ጠላት ላይ ከፍተኛ ሰብዓዊና ወታደራዊ ኪሳራ አስተናገደ!! ጳጉሜ 05/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው 5ኛ ዕዝ፣ አፄ ዓምደ ጽዮን ኮር ከተጉለትና ቡልጋ እስከ መርሀቤቴ አውራጃዎች ባደረጉት ቆራጥ ተጋድሎ፣ የጠላትን ወራሪ ኃይል በመደምሰስ ከፍተኛ ወታደራዊና ሰብዓዊ ኪሳራ ማድረሳቸውን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን አስታወቀ። ጠላት በሁለት ታላላቅ ግንባሮች ማለትም በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ ሳሲት ክላስተር እንዲሁም በመርሀቤቴ አውራጃ ሚዳና ሬማ ክላስተር ለዘረፋ ተግባር የተንቀሳቀሰው የአገዛዙ 112ኛ እና 101ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር እንዲሁም 105ኛ ኮማንዶ ክፍለ ጦር ከአርበኞች ጦር ሰራዊት ጋር በተደረገ የተቀናጀ ውጊያ ከባድ ኪሳራ ማስተናገዱ ተገለፀ። በሳሲት እና በመርሀቤቴ ግንባሮች የተመዘገቡ ድሎች ከጳጉሜ 03/2018 ዓ.ም ጀምሮ በሳሲት ቀጠና በተደረገው ውጊያ፤ የንጉስ ሣህለ ሥላሴ ክፍለ ጦር ልዩ ቦታው ብርቃ በተባለ ስፍራ በፈጸሙት የጨበጣ ውጊያ በ112ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሲያደርሱ፤ በተመሳሳይ ሳሲት ክላስተር የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር በተቀናጀ ውጊያ ይሕንኑ መፈፀማቸው ተገልጿል። በሌላኛው ግንባር ትላንት ከጳጉሜ 04/2018 ዓ.ም ጀምሮ በመርሀቤቴ አውራጃ ሚዳና ሬማ ክላስተር በተካሄደው ተጋድሎ፣ አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር በሬማ ከተማ ዘልቀው በመግባት የ101ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር አመራርን አስደናቂ እርምጃ መውሰዳቸው ተገለፀ። እንዲሁም በአዝማና ይጎቢያ ቀበሌ በተደረገው ውጊያ ከ12 በላይ የሚሆኑ የዘራፊ ቡድኑ አባላት ሲደመሰሱ፣ በቀጠናው በተካሄደው እልህ አስጨራሽ ውጊያ የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ሻለቆች፣ የኮሉ ብርጌድና የካራምሽግ ብርጌድ አርበኞች በትብብር ወራሪውን ኃይል መምታታቸው ተረጋግጧል። የሀገር መከላከያ ሰራዊት ነኝ ብሎ፡ አጥፊና ዘራፊ ቡድን ከሳሲት ክላስተር ከ8 በላይ የአርሶ አደሮችን በሬዎችን በመዝረፍ፣ በጥቅሉ ከ15 በላይ ኩንታል ጤፍና ስንዴ እህል በአስገዳጅ መዋጮ መዝረፉ ሲገለፅ፣ በተመሳሳይ በሚዳና ሬማ ክላስተርም መጠነ ሰፊ የዝርፊያ ወንጀል መፈጸሙን የኮሩ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ክፍል አስታውቋል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

photo content
+2

የስርዓቱን መፍረስ የተረዱ አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ 305ኛ ጎቤ መልኬ ኮርን ተቀላቅለዋል! ጳጉሜ 4/13/2018 ዓ.ም ከሁሉም አቅጣጫ በመፍረስ ላይ የሚገኘው የአገዛዙ መዋቅር አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ 305ኛ ጎቤ መልኬ ኮርን በመቀላቀል ላይ ይገኛል። 1.አቶ ጠጁ መኮነን ==ሰላም አስከባሪ 2.አቶ አሰፋ አስቀኔ=== ሰላም አስከባሪ 3.ኢ/ር ገ/ማርያም ሃጎስ ==የአዳኛገር ጫቆ ወረዳ ፓሊስ መምሪያ ስንቅና ትጥቅ ኃላፊ የነበረ ከማዕከላዊ አርማጭሆ ወረዳ ማሰሮ ደንብ ከተማ እና ካዳኛገር ጫቆ ወረዳ ነጋዴ ባህር ከተማ በመክዳት ኮሩን የተቀላቀሉት አባላቱ በአማራ ህዝብ ላይ የሚደርሰዉን ግፍ እና በደል በመረዳት ለደሞዝ ብለን የራሳችን ህዝብ ከሚጨፈጭፍ ስርዓት ጋር መተባበር እራስን እንደማጥፋት ይቆጠራል ያሉት አባላቱ ከዚህ በፊት የበደልነዉን ህዝባችንን ለመካስ ከነ ሙሉ ትጥቃችን ተመልሰናል ብለዋል ሲል መረጃውን ያደረሰን የኮሩ ህዝብ ግንኙነት ነው። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ !

photo content
+1

የብልፅግናው ጦር እየፈረሰ ፋኖን እየተቀላቀለ ይገኛል! የምኒልክ ዕዝን መብረቃዊ ምት መቋቋም ያቃተው የአገዛዙ ጦር ከመዋጋት ይልቅስ በሰላም እጅ መስጠትን እየመረጠ ይገኛል። በሰሜን ወሎ ዞን ደጋማ አካባቢዎች የወረዳ ከተማዎች ላይ ብቻ ተወሽቆ የሚገኘው የስርዓቱ ቀለብተኛ ወታደር የ16ኛ ኮርን ምትሃታዊ ገድል ምት መቋቋም አልቻለም። በዚህም በዛሬው እለት አንድ ዘመናዊ የሞርተር መነፀርን ጨምሮ ጥቁር ክላሽን በመያዝ 16ኛ ኮር 163ኛ ክፍለጦርን ተቀላቅሏል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ 16ኛ ኮር ቃል አቀባይ ጷግሜ፦ 05/ 2018 ዓ/ም

photo content
+4

የአባት አርበኞች ጦር አደረጃጀቱን በማዘመን "ምኒልክ አርበኞች ክፍለ ጦር" በሚል ስያሜ በተጉለት በይፋ መመስረቱ ተገለፀ!! ጳጉሜ 05/2018 ዓ.ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ተጉለት አውራጃ ሲንቀሳቀስ የቆየው የአባት አርበኞች ጦር አደረጃጀቱን በማዘመንና በማጠናከር "ምኒልክ ክፍለ ጦር" በሚል ስያሜ በይፋ መመስረቱ የተጉለት ቀጠና ስምሪት ቡድን አስታወቀ። ክፍለ ጦሩ ይፋ በተደረገበት በዚህ መድረክ ላይ የዕዝ፣ የኮር እንዲሁም የክፍለ ጦር አመራሮች በተገኙበት ሲመሠረት፤ አደረጃጀትን በማዘመን እና የድርጅቱን የፖለቲካ ትጥቅ ትግሉን በማስረፅ አባት አርበኞቹ ለአካባቢው ሠላምና ደሕንነት እዲያረጋግጡ ታልሞ መዋቀሩ ተገለፀ። በውይይቱ ወቅት አመራሮቹ እንዳመለከቱት፤ የአማራ ህዝብ የገጠመውን የህልውና አደጋ ለመመከትና ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት የአደጋውን ዘርፈ-ብዙነት መረዳት ተገቢ በመሆኑ፣ ለዚህም ዕድሜው ለትግል የደረሰ የህብረተሰብ ክፍል በሙሉ ባለው አቅም መታገል እንደሚኖርበትና፣ ትግሉም በዋናነት ቀጥተኛ ጥቃት እያደረሰ ባለው አገዛዝ ላይ ብቻ መነጣጠር እንዳለበት አስምረውበታል። በሌላ በኩል አርበኞቹ በሰጡት አስተያየት፤ አሁን ያለው አገዛዝ በይፋ እድጠፋና ባወጀበት፣ ንብረታችን እዲወድም በዘመተበት፣ በስልታዊ መንገድ ወጣቱ በጦርነት እዲማገድ፣በጥቅም ማባበያ ሚሊሻና አድማብተና እያለ ትውልዱን እያመከነ በመሆኑ፤ ይሕንን የህልውና አደጋ ለመመከት ብቸኛውና የመጨረሻው አማራጫችን በተባበረ ክንድ አገዛዙን ማስወገድ ነው ሲሉ አቋማቸውን አስቀምጠዋል። ሆኖም በርካታ ጀግኖችን አቅፎ በአባት አርበኞች አደረጃጀት ሲታገል የቆየው የተጉለት አውራጃ ጦር፣ የታጋዮቹን ፍላጎት መነሻ በማድረግና የትግሉን ህልውና ለማስቀጠል ሲባል አደረጃጀቱን ማዘመን አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ "ምኒልክ አርበኞች ክፍለ ጦር" በሚል ስያሜ መመስረቱን አስታውቀዋል። አደረጃጀቱ በማደጉ የተደሰቱት የምኒልክ አርበኞች ክፍለ ጦር አባላት በበኩላቸው፤ የተካሄደው የምክክር መድረክ በትግል ሂደቱ ላይ የነበሩ ብዢታዎችን ያጠራ መሆኑን ገልጸው፣ እንደ ቀደምት አባቶቻችን በመታገል የሸዋ ምድር የድል መቋጫ እንድትሆን የድርሻችንን ለማበርከት ዝግጁ ነን ሲሉ አረጋግጠዋል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

photo content
+2