ታሪካዊ ፎቶዎች 📷 📼
Open in Telegram
ይህ የታሪካዊ ፎቶዎች ኦፊሻል ቻናል ነው ታሪክን መዘከር ትልቅነት ነው ትውልድንም ያንፃል ‼️ Officeal channel 📡 》t.me/ @Tarikawi_potowech https://t.me/+3SO18mqWX_tiOWE0 #የጦር_ሜዳ_ውሎ https://t.me/joinchat/AAAAAFUFiN1N7T13DEKhAQ 👉 ለአስተያየትዎ @Eyoha_Bot
Show more735
Subscribers
+124 hours
-17 days
+3530 days
Posts Archive
Adigrat, Axum, Dessie, Gonder, Harar, Mekele, Welliso & Wendo-Guenet in 1937/1938 G.C
ኢትዮጵያ በ1930/1931 ዓ.ም
Deutsche Fotothek Photographic Archive
http://www.deutschefotothek.de/documents/de
Adigrat, Axum, Dessie, Gonder, Harar, Mekele, Welliso & Wendo-Guenet in 1937/1938 G.C
Ethiopia in 1930/1931 ም
German Photo Library Photographic Archive
http://www.deutschefotothek.de/documents/de
Translated from German
@Tarikawi_fotowech
@Tarikawi_fotowech
አዲስ አበባ ለገሀር ባቡር ጣቢያ - 1969/1970 ዓ.ም
Addis Abeba Railway station back in 1977/1978
Hubert Tabutiaux Photograph/Jean-Pierre Crozet's Franco-Ethiopian Railway Photo Collection:
https://www.train-franco-ethiopien.com/photos_cfe/gare_addis_cfe/images/image/26%20Place%20De%20La%20Gare%20Addis-abeba%201977.JPG
@Tarikawi_fotowech
በህዳር 14 ቀን የተረሸኑት ባለስልጣናት የተለያየ የክስ ቻርጅ የቀረበባቸው ነበር በዚህም መሰረት
ሀ. ‹‹ኃይላቸውን ከህግ አግባብ ውጭ ተጠቅመዋል›› በሚል ውንጀላ የተገደሉ ባለስልጣኖች ባለስልጣኖች (‹‹Gross
Abuse of Power››)
1. ፀሃፌትዕዛዝ ጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተወልድ
2. ልዑል አስራተ ካሳ
3. እንዳልካቸው መኮንን
4. ራስ መስፍን ስለሺ
5. አቶ አበበ ረታ
6. ሌተናል ኮሎኔል ታምራት ይገዙ
7. አቶ አካለወርቅ ሀብተወልድ
8. ዶ/ር ተስፋዬ ገብረእግዚዕ
9. አቶ ሙላቱ ደበበ
10. ደጃዝማች ሰለሞን አብርሃ
11. ደጃዝማች ለገሰ በዙ
12. ደጃዝማች ሳህሉ ድፋዬ
13. ደጃዝማች ወርቅነህ ወልደአማኑኤል
14. ደጃዝማች ክፍሌ እርገቱ
15. ደጃዝማች ወርቁ እንቁሥላሴ
16. ደጃዝማች አዕምሮሥላሴ አበበ
17. ደጃዝማች ከበደ ዓሊ ወሌ
ለ. ‹‹ስልጣናቸውን ከህግ አግባብ ውጭ ተጠቅመዋል›› በሚል ውንጀላ የተገደሉ ባለስልጣኖች (‹‹Gross Abuse of
Authority››)
1) አቶ ነብየልዑል ክፍሌ
2) ኮሎኔል ሰለሞን ከድር
3) አፈንጉስ አበጀ ደባልቅ
4) አቶ ይልማ አቦዬ
5) አቶ ተገኝ የተሻወርቅ
6) አቶ ሰለሞን ገብረማርያም
7) አቶ ኃይሉ ተክሉ
ብላታ አድማሱ ረታ
9) ልጅ ኃይሉ ደስታ
10) ፊታውራሪ አመዴ አበራ
11) ፊታውራሪ ደምስ አላምረው
12) ፊታውራሪ ታደሰ እንቁሥላሴ
13) ሌተናል ጄኔራል አብይ አበበ
14) ሌተናል ጄኔራል ከበደ ገብሬ
15) ሌተናል ጄኔራል ድረሴ ዱባለ
16) ሌተናል ጄኔራል አበበ ገመዳ
17) ሌተናል ጄኔራል ይልማ ሽበሽ
18) ሌተናል ጄኔራል ኃይሌ ባይከዳኝ
19) ሌተናል ጄኔራል አሰፋ አየን
20) ሌተናል ጄኔራል በለጠ አበበ
21) ሌተናል ጄኔራል ኢሳያስ ገብረሥላሴ
22) ሌተናል ጄኔራል አሰፋ ደምሴ
23) ሌተናል ጄኔራል አበበ ኃይለማርያም
24) ሜጀር ጄኔራል ስዩም ገድለጊዮርጊስ
25) ሜጀር ጄኔራል ጋሻው ከበደ
26ኛ) ሜጀር ጄኔራል ታፈሰ ለማ
27) ሪር አድሚራል እስክንድር ደስታ
28) ብርጋዴር ጄኔራል ሙሉጌታ ወልደዮሐንስ
29) ብርጋዴር ጄኔራል ግርማ ዮሐንስ
30) ኮሎኔል ያለምዘውድ ተሰማ
31) ኮሎኔል ጣሰው ሞጆ
32) ኮሎኔል ይገዙ ይመኔ
33) ሻለቃ ብርሃኑ ሜጫ
34) ካፒቴን ሞላ ዋቅኬኔ
ሐ. ‹‹የእርስ በእርስ ጦርነት ለመቀስቀስ በተሸረበ ደባ እና ታላቁን የለውጥ እንቅስቃሴ ለመግታት በተደረገ አሻጥር›› በሚል ክስ
ተወንጅው የተገደሉ
1. ካፒቴን ደምሴ ሽፈራው
2. ካፒቴን በላይ ጸጋዬ
3. ካፒቴን ወልደዮሐንስ ዘርጋው
4. ላንስ ኮርፖራልተክሉ ኃይሉ
5. ወታደር በቀለ ወልደጊዮርጊስ
መ). ‹‹ለመስሪያ ቤት የተገባን ቃል ኪዳን ባለመጠበቅ እና በጦር ኃይሉ ውስጥ ክፍፍል ለመፍጠር ሙከራ ማድረግ›› በሚል ክስ ተወንጅለው የተገደሉ
1). ሌተናል ጄኔራል አማን ሚካኤል አንዶም
2). ሌቴናል ጄኔራል ተስፋዬ ተክሌ
3). ጁኒየር ኤርክራፍትማን ዮሐንስ ፍትዊ
✍ ገዳዮቹ...
በየትኛውም ስርአት ወታደር የበላይ አለቃውን ትዕዛዝ የመቀበል ሙያዊ ግዴታ እንዳለበት የታወቀ ቢሆንም አንዳንድ ግዜ ደግሞ
ከሙያዊ ግዴታ ይበልጥ የህሊና ጥያቄን ማዳመጥ ተገቢ ሳይሆን አይቀርም። ሊገድል የመጣን መግደል አንድ ነገር ሆኖ እራሱን ለመከላከል እድሜ ጤናና ሁኔታው ያልፈቀደለትን ፡ የፊጥኝ በካቴና ታስሮ ለነብሱ የሚማጸንን ሰው በመግደል ውስጥ ግን ያለውን የህሊና እረፍት ማጣት እራሳቸው ገዳዮቹ እድሜ ሰጥቷቸው የመሰከሩትን የህሊና ስብራት በብዛት አድምጠናል።
በዛች ቅዳሜ ምሽት የመንግስቱ ኃይለማርያም የግድያ አስፈጻሚ በሆነው በኮሎኔል ዳንኤል አስፋው ትእዛዝ ተቀባይነትና በሻለቃ
ጌታቸው ሺበሺ የቡድን መሪነት ሀምሳ ዘጠኙ ሰዎች የመትረየስ ጥይት ተርከፍክፎባቸው ቅሪተ አካላቸው እንዳይገኝ
በመቃብራቸው ላይ ኖራ ተነስንሶበታል። የግድያውን ሁኔታ ያጠናው ልዩ አቃቤ ህግ እንደመሰከረው ከሆነ በእለቱ በጠቅላላው 393 ጥይቶች መተኮሳቸው ተረጋግጧል። (በአማካይ ለአንድ ሟች 7 ጥይት እንደማለት ነው) ይህ ቁጥር በደርግ አባላቱ ብቻ የተተኮሰውን የሚያካትት እንጂ በሌሎች ወታደሮች የተተኮሰውን አይጨምርም።
ለደርጉ ሃላፊዎች አዲስ አበባ ወህኒ ቤት ግቢ (በተለምዶአዊ አጠራሩ ከርቸሌ በሚባለውና በአሁን ግዜ የአፍሪካ ህብረት ዋና
ጽህፈት ቤት በተገነባበት ግቢ) ውስጥ በአካል ተገኝተው የአፄ ኃይለስላሴን ጄኔራሎችና ሚኒስትሮች ተኩሰው የገደሉ የደርግ
አባላት ስም ዝርዝርና የተኮሱት ጥይት መጠን በሻለቃ ጌታቸው ሺበሺ ሪፖርት በተደረገው መሠረት፣
- ሻለቃ ጌታቸው ሺበሺ - 43 ጥይት
- ሻምበል ተፈራ - 32 ጥይት
- ሻምበል ኃይሌ መለስ - 25 ጥይት
- ባሻ ተፈራ ጅፋር - 60 ጥይት
- 50 አለቃ በቀለ ደጉ - 32 ጥይት
- ፒቲ ኦፊሰር ሚካኤል - 25 ጥይት
- 50 አለቃ ዳምጤ - 16 ጥይት
- ወታደር ደጀኔ አ/አገኘሁ - 40 ጥይት
- ወታደር ገብረ ጊዮርጊስ ብርሃኑ - 50 ጥይት
- ሻለቃ ባሻ ለማ ኩምሳ - 7 ጥይት
- ምክትል አስር አለቃ ግርማ አየለ-3 ጥይት ተኩሰው ርሸናውን በትዕዛዙ መሰረት መፈጸማቸውን ሪፖርቱ ያሳያል።
✍ ለግድያው የተሰጠው ደረሰኝ።
የግድያውን አፈጻጸም አስገራሚ ከሚያደርጉ ነገሮች አንዱ ለግድያው የተሰጠው ደረሰኝ ነው። በዛች እለት በትዕዛዙ መሰረት
ሰዎቹ ተገደሉ። የወህኒ ቤቱ አባል ሻምበል ነጋሽ ማሞ የ60 ሰዎችን አስክሬን ተረክቦ ደረሰኝ ሰጠ። 60ኛው በዛው ዕለት ከደርጉ ጋር ተዋግተው እራሳቸውን የገደሉት የጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግ የመጀመሪያው ሊቀመንበር የነበሩት የሌ/ጄኔራል አማን አምዴ ሚካኤል አንዶም አስክሬን ነበር።
ይህ ከሆነ እነሆ ዛሬ 48 ዓመት አስቆጥሯል !!!
ህዳር 14 ቀን 1967 ዓ.ም
👉 ጀኔራሎቹ
@Tarikawi_fotowech
ህዳር 14 ቀን 1967 ዓ.ም..... ጸለምት ቅዳሜ !!!
ለኢትዮጵያ ፖለቲካዊ አለመግባባቶች መግደል መፍትሄ እንደሆነ ሰይጣናዊ ምክር የተቀበልንበት ለሀገር ለወገን ያገለገልከው
ግልጋሎት በግልብ ፖለቲከኞች ዘንድ ሚዛን እንደማይደፋ የተረጋገጠበት በጥቂቶች እጅ በትረ ስልጣን ከወደቀ ሀገርን ሊያጠፉ እምደሚችሉ ያሳዩበት ስልሳ ሰዎችን በአንድ ሰው ፊርማ መግደል እንደሚቻል ያየንበት በአንዳንድ ጸሀፍት ዘነድ “ ጸለምት
ቀዳሚት” #ጨለማዋ_ቅዳሜ ተብላ የምትጠራዋ ህዳር 14 1967 በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ጥቁር ነጥብ አኑራ እንርሳሽ
ቢሏት የማትረሳ የጥፋቶች ሁላ መነሻ ሆና ተመዝግባለች።
ህዳር 14 ቀን 1967 ዓ.ም ምሽት ላይ ከሰአታት በፊት በመኖሪያ ቤታቸው በተኩስ ልውውጥ የተገደሉትን ሌፍተናንት ጀነራል
አማን አምዶምን ጨምሮ ስልሳ የቀድሞው መንግስት ሹማምንት ተጨፈጨፉ፡፡ የብዙ ሺህ አመታት ዘውዳዊ መንግስትም
ተገርስሶ በወታደራዊ ጁንታ ተተካ፡፡ ከዚያም ወዲያማ ህዳር 14 ያስጀመረች የክፋት ቡራኬ ለአስራ ሰባት ተጋግሞና ግድያን
የፖለቲካ ልዩነት ማሸነፊያ አድርጎ ከረመ፡፡
ሃገራችንን ለብዙ የፖለቲካና የማህበራዊ ምስቅልቅል የዳረገች ይህች ክፉ ቀን ቀደም ብላ ታስባ የታሰበባትና የተጠናች ውሳኔ
ነች? ወይስ በሂደት በደርጉ አባላትና እና መሪዎቹ በስሜታዊነት ድንገት የተፈጸመች?
እርግጥ ይህ ጉዳይ ዛሬም ቢሆን አወዛጋቢነቱ ያበቃለት አጀንዳ አልሆነም። በህይወት የተረፉም ይሁኑ አንዳንድ የታሪክ ምሁራን
በአንድ አይነት ሀሳብ ለመስማማት አልተቻላቸውም። አንዳንዶች በተለይ የወቅቱ ምክትል ሊቀመንበር ሻለቃ መንግስቱ
ኃይለማርያምን ለግድያው ዋና ተጠያቂ በማድረግ “ከመነሻው ጀምሮ ሲያውጠነጥኑት የነበረ ሴራ ውጤት ነው” ሲሉ ሌሎች
ደግሞ “እጅ በማውጣት የግድያውን ውሳኔ ሲያጸድቁ የነበሩ የደርጉ አባላት ስሜታዊ ውሳኔ ነው” ይላሉ።
ሌተና ኮሎኔል ፍስሀ ደስታ "እኛና አብዮቱ"በተሰኘው መጽሀፋቸው እንደመሰከሩት ከሆነ ግን የደርጉ ተቀዳሚ ምክትል
ሊቀመንበር ሻለቃ መንግስቱ በጻፉት የትእዛዝ ደብዳቤ የስልሳዎቹ ግድያ መፈጸሙን ይመሰክራሉ። እንደ ኮሎኔል ፍስሀ ደስታ
አባባል ግድያው ህዳር 14 ሊፈጸምና ህዳር 14 ደርጉ ተሰብስቦ ሊወስን አንድ ቀን ቀደም ብሎ ህዳር 13 ቀን እጃቸውን የሰጡ
የቀድሞ መንግስት ሹማምንት ላይ እርምጃ ይወሰድባቸው የሚል የምክትል ሊቀመንበሩ የሻለቃ መንግስቱ ኃይለማርያም ፊርማ
ያረፈበት የትእዛዝ ደብዳቤ በአንድ አጋጣሚ እጃቸው ገብቶ መመልከታቸውን መስክረዋል፡፡
ከጥቂት ግዜ በኋላም ታደሰ ቴሌ ሳልቫኖ በመጽሃፋቸው የደብዳቤውን ኮፒ ይፋ አድርገዋል።
ሻለቃ (የኋላው ፕሬዚደንት) መንግስቱ ኃይለማርያም በፊርማቸው አስደግፈው ለደርግ ጥበቃና ዘመቻ መምሪያ መኮንን( ለያኔው
ዋና የግድያ አስፈጻሚያቸው) ለኮሎኔል ዳንኤል አስፋው የይረሸኑ ደብዳቤ ቀደም ብለው ልከውለታል፡፡ (ግድያው ህዳር 14 ቀን
ሊፈጸም ህዳር 13 ቀን መላካቸው ለይሙት በቃ የሚሰበሰቡት የደርግ አባላት ውሳኔውን ከማስተላለፋቸው በፊት መሆኑን ልብ
ይሏል)፡፡ ግደል የተባለውን ያለማመንታት በመፈጸም የሚታወቀው ኮሎኔል ዳንኤልም በምላሹ የደብዳቤው ግርጌ ላይ "በትዕዛዙ
መሰረት እንተገብራለን" በማለት የአለቃውን ትእዛዝ ለመፈጸም እንደማያወላዳ አረጋግጧል።
✍ ቀዳሚው ሰለባ ኮዳ ትራሱ....
ደርጎች በህዝቡም በሰራዊቱም ዘንድ እውቅና እንደሌላቸው በሚገባ ስለተረዱ ነበር በቀዳማዊ ኃይለስላሴ መንግስት ውስጥ
ጉልህ ጀብድ በመፈጸም የሚታወቁትንና "ኮዳ ትራሱ"በሚል። ተቀጽላ የሚታወቁትን ሌፍተናንት ጀነራል አማን አምዶምን
ሊቀመንበር እንዲሆኗቸው የጠየቋቸው።ከፖለቲከኛነትና ከዲፕሎማትነት ይልቅ የቆፍጣና ወታደርነት ባህሪያቸው
እንደሚያዘነብልባቸው አብረዋቸው የሰሩ ሰዎች የሚመሰክሩላቸው ጀነራል አማን: ከደርጎች ጋር ተስማምተውና ተግባብተው የሊቀመንበርነታቸውን ወንበር ከሁለት ወር በላይ ሊቆዩበትት አልተቻላቸውም ነበር። ከሻለቆቹና ከሻምበሎቹ ጋር መግባባት የተሳናቸው ሌፍተናንት ጀነራል አማን አምዶም ነገር አለሙን ትተው ጦር ሀይሎች አካባቢ ይገኝ ከነበረው መኖሪያቸው ውስጥ መቀመጥን መረጡ።
በጦሩ ዘንድ ያላቸውን ተወዳጅነት ተጠቅመው መልሰው ሊያጠቁን ይችላሉ ብለው የሰጉት ደርጎችም ገዳይ
ቡድን ቤታቸው ድረስ ልከውባቸውና ለረዥም ሰአት ከጀነራሉ ጋር ተታኩሰው ገደሏቸው። የአማን አምዶም ግድያም ለቀሩት ሀምሳ
ዘጠኝ ሰዎች ግድያ ማስጀመሪያ ፊሽካ ሆነች።
እጃቸውን በሰላም ነበር የሰጡትእድሜ አግኝተው ታሪክን ለመመስከር የበቁ የደርግ ባለስልጣናት ስለ ሌሎች የቀይ ሽብር
ሰማዕታት ጉዳይ እምብዛም ጸጸት ሲሰማቸው ባይታይም( ኮሎኔል መንግስቱ ሀይለማርያምን ጨምሮ) በስልሳዎቹ ላይ
የተደረገው ግድያ ግን ፍጹም ስህተት እንደነበር ይመሰክራሉ። ለነገሩ ጸጸታቸው የፈሰሰ ውሀ የማያሳፍስ: የጠፋውን ጥፋት
የማይመልስ ነበር፡፡ በጥይት ተደብድበው የተገደሉት ሰዎች ሀገርና ወገንን ያገለገሉና ብዙ ሊያገለግሉ የሚችሉ ምናልባትም
መጠነኛ ጥፋታቸው ተቆጥሮ መጠነኛ ቅጣት ብቻ የሚገባቸው ሰዎች ነበሩ። (በስልጣን ዘመናቸው ያጠፉትን ጥፋት ለማጣራት
የተቋቋመው የመርማሪ ኮሚሽን ሪፖርት የሚያረጋግጠውም ይሄንኑ ነው፡፡)
የመጋቢት 1966 ህዝባዊ አመጽን ተከትሎና ከሚያዝያ አጋማሽ ወር ጀምሮ በርካታ የቀዳማዊ ኃይለስላሴ ሹማምንት ከያሉበት
እየተያዙ እስር ቤት እየታጎሩ ነበር፡፡
አመጹ እየተፋፋመ ሄዶ በመጨረሻም ደርግ መስከረም 2 ቀን 1967 በትረ ስልጣኗን ሲይዝ እጁ ላይ የወደቁትን (ንጉሰ ነገስት
ቀዳማዊ ኃይለላሴን እና አክሊሉ ሃብተወልድን ጨምሮ) በርካታ ሹማምንት ተገቢዉን ፍርድ እሰጣቸዋለሁ በማለት ለህዝብ ቃል
ገባ፡፡ ለዚህም መርማሪ ኮሚሽን በአዋጅ ተቋቁሞ ስራዉን መስራትም ጀምሮ ነበር፡፡ ሆኖም ግን የመርማሪ ኮሚሽኑ አዝማሚያ የፈለገውን አይነት ቅጣት ማድረግ እንደማያስችለው ያወቀው የደርጉ መንግስት ፍርድን እራሱ ሊሰጥ ወሰነ፡፡
በመጀመሪያ “እርምጃ እንዲወሰድባቸው” ስማቸው የቀረበው 250 ሰዎች የነበሩ ሲሆን በመጨረሻ ቁጥራቸው ወደ 141 ዝቅ
ብሎ፣ ከመካከላቸው ለግድያ የተመረጡት ባለሥልጣናት ስም ተራ በተራ እየተነበበ ድምጽ እንዲሰጥባቸው ተደረገ፡፡ በዚህም
መሰረት 59 ሰዎች በጥይት ተደብድበው እንዲገደሉ በአብላጫ ድምጽ ተወሰነ። በዚያች ክፉ ቀን ብቻ...
👉 ሁለቱ ጠቅላይ ሚኒስትሮች
👉 አንዱ ልዑል
👉 አንዱ ሪር አድሚራል
👉 አስራ ሰባቱ ሚኒስትሮች
👉 አስራ አንዱ የጠቅላይ ግዛት እንደራሴዎችና የአውራጃ ገዥዎች
👉 አንዱ ገበሬ
👉 ዘጠኙ ሌፍተናንት ጀነራሎች
👉 ሶስቱ ሜጀር ጀነራሎች
👉 ሶስቱ ብርጋዴር ጀነራሎች
👉 ሶስቱ ኮሎኔሎች
👉 ሰባቱ መስመራዊ መኮንኖችና
👉 ሁለት የበታች ሹማምንት የመትረየስ ጥይት ዘንቦባቸው ተረሽነዋል።
ከተረሸኑት ስልሳ ባለስልጣናት መካከል ሀምሳዎቹ ከኢጣልያ ወረራ ጀምሮ ሀገራቸውን በተለያየ መልኩ ሀገራቸውን ያገለገሉ
እስከ 45 አመት የሚደርስ የአገልግሎት ዘመናቸው የሚቆጠር፣ ከእነዚህም ውስጥ 17 አርበኞች ይገኙበታል። የእድሜያቸው
ነገር ሲነሳ ደግሞ በ 19 አመት የአፍላነት እድሜው ከተረሸነው አንስቶ እስከ 75 አመት የሚደርሱ አዛውንቶች የጥይት እራት
ሆነዋል። 3 ወንድማማቾችና ሎሎች 2 ወንድማማቾች የወንድማቸውን ሞት እያዩ እንዲገደሉ ተደርገዋል። የሚያሰቃያቸውን ደዌ እያስታመሙ ካሉበት ሆስፒታል አልጋ ሁለት በሽተኞች ግሉኮሳቸው ተነቅሎ ተወስደው ተገድለዋል።
✍ ስልሳዎቹ...
በናፍጣ እና በኤሌክትሪክ የሚሰሩ አዲስ ሞዴል ባቡሮች በአዋሽ ባቡር ጣቢያ። በአብዛኛው ከ1960 እስከ 1964 ዓ.ም ድረስ
ባለው ጊዜ የተነሱ ፎቶግራፎች
https://www.train-franco-ethiopien.com/photos_cfe/autorails_cfe/index.html
https://www.train-franco-ethiopien.com/autorails_en.php
@Tarikawi_fotowech
የዘጌው አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስትያን/ገዳም? ህንጻ፥ ቀሳውስትና መኖሪያቸው እንዲሁም የአቡነ ተክለሃይማኖት ቅዱስ ዛፍ በዘጌ - በ1929 ዓ.ም የተነሱ
ፎቶግራፎች።
Italian Geographical Society Photographic Archive/Grotanelli, Vinigi Lorenzo Photograph:
http://www.archiviofotografico.societageografica.it
@Tarikawi_fotowech
The streets of modern Addis Ababa back in 1955
Alfred Eisenstaedt photographs/Life Magazine Collection/Ethiopia Essay '55 hosted by Google:
Images.google.com/hosted/life
@Tarikawi_fotowech
በ 25 እና በ 50 ሳንቲም ለዘመናት በኪሳችን ይዘናቸው ስንዞሮ ኖረናል
አቶ አቶ ተሾመ ሰይፉ
ወ/ሮ ለፈኒ ወቶ
@Tarikawi_fotowech
አዲስ አበባ ከ1950 እስከ 1952 ዓ.ም ድረስ
Herbert S Lewis Photographs/National Library of Australia:
trove.nla.gov.au/picture/
@Tarikawi_fotowech
@Tarikawi_fotowech
ደብረ-ብርሀን ከ1956 እስከ 1958 ዓ.ም ድረስ
Peace Corps Ethiopia Volunteers - Ethiopia Memory Photographs: 1964-1966
Copyright: Darrel Betty Hagberg/Peace Corps Ethiopia Volunteers:
http://darrel-betty-hagberg.com/ethiopia3/Ethiopia3-photos.html
@Tarikawi_fotowech
@Tarikawi_fotowech
እምድብር/ጉራጌ በ1959/1960 ዓ.ም
Beautiful pictures you may have never seen before
How life has been treating my people in the past decades? Are you better off in the hands of
your ethnic 'lords'?
Former United States Peace Corps volunteer Charlie Ipcar photographs
@Tarikawi_fotowech
የአዲስ አበባ ከተማ እሳት አደጋ መከላከያ ሰራተኞች - 1928 ዓ.ም
About 800 Photographs taken in Ethiopia by Swiss/German documentary filmmaker Martin Rikli
in 1935 & 1936 have been preserved at the University of Florida in three albums, and can be
viewed here:
ufdc.ufl.edu/rikli
@Tarikawi_fotowech
