776
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
+4430 days
Posts Archive
#ሞትን #አልፈራም!
ነገር ግን ቀብር ላይ የምንጠየቀውን ጥያቄ እፈራለሁ። ቀብር ውስጥ በመጀመሪያው ቀን ምን ሊከሰት እንደሚችል አናውቅም። አዲስ ቤት፣ አዲስ ስፍራ ፈጣሪን የምናገኝበት ቀዳማዊ ክፍል ነው።
አሁን ብሞት ብለን ራሳችንን እንጠይቅ፤ ፈጣሪ ፊት የምቆምበት አስተማማኝ ስራ አለኝ? ሞት ማናችንም ልናመልጠው የማንችለው በነፍስ ወከፍ የምንጋፈጠው እውነታ ነው። ሀብታችንም ሆነ እውቀታችን፤ ቤተሰባችንም ሆነ ዘራችን ከሞት ሊታደጉን አይችሉም። የዛን ቀን ጓዳችን መልካም ስራችን ብቻ ነው።
ጌታ ሆይ ማረን
@ethioterkaa
@ethioterkaa
@ethioterkaa
🙏🙏🙏🙏🙏
ሰለ መፅሀፍት እናውራ !!!
** የመጀመሪያው የአለማችን አጭር ልቦለድ ደራሲ ከ1809-1849 አካባቢ የኖረው ገጣሚ ሀያሲ እና ደራሲ 'ኤድጋር አለን ፓ' ይባላል:: ይህ ሰው 'መፅሐፍ የማያነብ ሰው ሰለመኖሩ መጠራጠር አለበት' ይላል::
** በሀገራችን የመጀመሪያው አጭር ልቦለድ ''የጉለሌው ሰካራም'' በ'ተመስገን ገብሬ' በ1941 የተፃፈ ሲሆን:
** የመጀመሪያው በኢትዮዽያ ሆነ በአፍሪቃም ጭምር ረጅም ልቦለድ ደግሞ 'ጦቢያ' ስትሆን በ1908 'በነጋድራስ አፈወርቅ ገ/ እየሱስ' በሚባል ጎጃም ዘጌ ደሴት አካባቢ የተወለደ ሰው ተበረከተ::
** በአለም ላይ በዙ ቤተመፅሐፍት በማቁዋቁዋም የታወቀች ሀገር 'አሌክስንዳሪያ' ናት::
** በሌላ በኩል በአለም ላይ በትልቅነት ተወዳዳሪ የሌለው ቤተመፅሐፍት በአሜሪካ የሚገኘው ሚያዚያ 25. 1800 አ.ም የተቁዋቁዋመው 'ዬኮንግረስ' ቤተመፅሐፍት ነው::
** ሰለ መፅሐፍት ሲነሳ የማይረሳው ፈረንሳዊው 'ዥንዊልየምን' ነው:: ይህ ነውጠኛ ደራሲ እስር ቤት ገብቶ እንዳይፅፍ ወረቀት ብቻ ያለ ብዕር ሲሰጠውና ብዕር ለማግኘት እስከመጨረሻው ጥሮ ያለማግኘቱን ሲያረጋግጥ 76 ገፅ ሙሉ በደሙ ድርሰቱን የፃፈ አስገራሚ የጥበብ አፍቃሪ ነው::
** በአለማችን ላይ በብዛት ከታተሙ መጽሐፎች ፤ ከመፅሐፍ ቅዱስ ቀጥሎ 'The power of positive thinking' የተሰኘው የ Norman Vincent Peale መፅሐፍ ነው::
ማንበብ የተሻለ ሰዉ ያደርጋል ❣️🙌
@ethioterkaa
@ethioterkaa
@ethioterkaa
"አግባ ይሉኛል እንዴ??" የምወዳትን ፍቅረኛየን ካለያዩኝ በኋላ።
እህህ "አግባ እንጅ" ሲሉኝ አያፍሩም ኮ "አስቀያሚ ነች" እያሉ በውበቷ እንድትሸማቀቅ ያደረጓትን ፍቅሬን ከሀገር ካሰደዷት በኋላ
አወ መልኳ አያምርም፥ አወ ከንፈሯ ትልቅየ ነው፣ አወ አፍንጫዋ እንደ ዝንጀሮ ነው፣ልክ ናችሁ እግሯ ሸፋፋ ነው፥ አልተሳሳታችሁም ጥፍሮቿ ያስጠላሉ፥ አወ ጸጉሯ ዞማ አደለም ከርዳዳ ነው.....
ከመልኳ ክፋት ደግሞ ድህነቷ፥ አወ ድሀ ነች
የኔ ሀብታም!!
ታዲያ ምን ይሁን ነው የምትሉት?? እኔ ካፈቀርኳትስ፥ ከሷ ውጭ ሰው ያለ ካልመሰለኝስ
ምነው ከአፏ ስለሚወጣው መልካም ቃላቶች አልመሰከራችሁም፥ ምነው ስለ ሰው አክባሪነቷና አዛኝነቷ መናገር አስፈራችሁ፥ ምነው ሃይማኖቷን አክባሪ መሆኗን ዘነጋችሁ፥ ምነው ስለ ከርዳዳ ጸጉሯ መስክራችሁ ዞማ ሀሳቦች ሉጫ ንግግሮች ስለሚያፈልቀው ብሩህ አእምሮዋ መናገር ፈራችሁ።
ወይስ ፈጣሪ የፈጠረውን መልኳን በመተቸት ተጠመዳችሁ።
ስለ መልኳ እሷን ተዋት የፈጠራትን ጠይቁ።
ስለ ድህነቷ እሷን ተዋት እኔን ጠይቁ፤የሀብቷን መጠን እኔ ብቻ ነኝና የማቀው!!
ለአፍታ ቀርባችኋት እንኳ ስለ ስብእናዋ ለመመስከር አልደፈራችሁም።ፈሪወች!!
ብትቀርቧትማ የወደፊት እቅዷን ትነግራችሁ ነበር ፥ያኔ ታድያ ሰልካካ ህልሟ ድፍጥጥ አፍንጫዋን ያስረሳችሁ ነበር።
የህጻናት ማሳደጊያ የአረጋውያን መጦሪያ መገንባት እንደምትፈልግ ስትነግራችሁ የተንሸዋረረ አይኗን ረስታችሁ ፥ በ ጠንጋራና ጨለምተኛ ሀሳብ ውስጥ እንደምትኖሩ ይገባችሁ ነበር!!
ታዲያ መቸ ቀረባችኋትና፤ ከሩቅ አይታችሁ ፈረዳችሁባት እንጅ።
"እህህህ አግባ ይሉኛል እንዴ??"
'ይሄን የመሰለ መልከመልካም የሀብታም ልጅ ይቺን ፉንጋ እንዴት ተወዳጀ' እያላችሁ የቡና መጠጫ ቁራሸ እንጀራ ካደረጋችኋት ፍቅረኛየ ከለያያችሁኝ በኋላ
በጎዳንው አቅፊያት ስሄድ በጦሩ አይናችሁ ወግታችሁ አንገቷን ስታስደፏት ያላየሁ መሰላችሁ...
"እኔ ላንተ የማልገባ ሰው ነኝ??" ትላለቸ ጣቶቿን እያንቋቋች
"እንደሱ አትበይኝ ውዴ፥ የሚሆነኝን የሚወስነው ማን ነው፥ ማህበረሰቡ ነው?? ወይስ አታፈቅሪኝም"
"ከምንም ከማንም በላይ እወዳሀለሁ" ትልና አንገቴ ስር ሽጉጥ ትላለች ፥ የእንባ ዘለላወቿ ከአንገቴ ወርደው ደረቴኝ ያቃጥሉኛል
ትኩስ እንባ፥ ከመሸማቀቅ የፈለቀ አሳዛኝ እንባ፥ ማህበረሰቡ የፈጠረው እንባ
"አግባ ሲሉኝ አያፍሩም እህህ ወገኞች፥ በመፍረድ የተጠመዳችሁ ብኩኖች"
ያለችበትን ሀገር እንኳ አላቅም ፥ የኔ ስደተኛ የት ይሆን ያለሽው??
"አግባ እንጅ"
"አግባ እንጅ"
"ወለድ እንጅ"
:
:
"ያችን አስቀያሚዋን ድሃወን ፍቅሬን ውለዷት እና አገባለሁ"
✍️ቹቹ ደሳለኝ
@ethioterkaa
@ethioterkaa
@ethioterkaa
@ethioterkaa💚💚💚💛💛💛❤️❤️❤️
አብርሽ አሌክስስስስ
# ለመፍረድ_አንቸኩል ! ዶክተሩ ስልክ ይደወልለትና እየሮጠ ወደ ሆስፒታል ይሄዳል፡፡ሆስፒታል ከደረሰ ቦሀላ ልብሱን በፍጥነት ቀያይሮ ወደ ኦፕራሲዮን ክፍል እየተጣደፈ ሲሄድ መግቢያ በሩ ላይ ቆሞ ይጠብቀው የነበረ የታማሚው ልጅ አባት "እንዴት እዚህ ለመድረስ ይህን ሁሉ ሰአት ይፈጅብሀል ዶክተር? የሰው ህይወት ግድ አይሰጥህም?በጣም ዘገየህ" ሲለው ዶክተሩም በፈገግታ " ይቅርታ ሆስፒታል ጊቢ ውስጥ አልነበርኩም፤ስልክ ከተደወለልኝ ቦሀላ ግን አቅሜ በፈቀደ መጠን በፍጥነት ለመድረስ ሞክሬያለው፤ ተረጋጋ አለው:: "ተረጋጋ ትለኛለህ? ታሞ ሊሞት እያጣጣረ ያለውኮ የኔ ልጅ ነው፤እንዴት ተረጋጋ ትለኛለህ? ያንተ ልጅ ቢሆን እንደዚህ ትላለህ? አንተ በመዘግየትህ ልጄ ሊሞትብኝ ነው ትንሽ አታስብም?'' ብሎ ሲጮህበት ዶክተሩ አሁንም ፈገግ እያለ፦ ዶክተር የሰውን ልጅ ህይወት ሊያረዝምም ሊያሳጥርም አይችልም፤አፈር ነንና ወደ አፈር መመለሳችን አይቀርም፤አሁን ተረጋጋ እኔም ስራዬን ልስራበት" ብሎ ወደ ሰርጀሪ ክፍል ገብቶ ለተወሰኑ ሰአታት የህፃኑን ቀዶ ጥገና ካከናወነ ቦሃላ ወደ ውጭ ወጥቶ በፈገግታ የልጁን አባት "እንኳን ደስ አለህ!! ልጅህ ሰርጀሪ ከተደረገለት ቦሀላ በጥሩ ጤንነት ላይ ይገኛል፤ከዚህ ቦሀላ የሚያስፈልግህ ነገር ካለ ነርሷ ትረዳሀለች " ብሎት እየሮጠ ከሆስፒታሉ ወጣ ሰውዬው በሰማው መልካም ዜና ቢደሰትም የዶ/ሩ ሁኔታ ግራ ስለገባው ነርሷን "ዶ/ሩ ምን ሆኖ ነው እንዲህ የተዋከበው?'' ብሎ ሲጠይቃት " ዶ/ሩ ትላንትና ልጁ በመኪና አደጋ ሞቶበት ቀብር ላይ ነበር፤ያንተ ልጅ ህመም አደገኛ ስለነበር እንዲያክመው ደውለን ጠርተነው ነው፤ አሁን ያንተን ልጅ ካዳነ ቦሀላ የልጁ ቀብር ላይ ለመድረስ ነው እየሮጠ ያለው!" ስትለው ሰውዬው ድርቅ ብሎ ቀረ!! * የሰው ልጅ በምን አይነት ሁኔታ ውስጥ እንደሆነ * ሳታውቅ አትፍረድ!!! መልካም የአባቶች ቀን ❤️
@ethioterkaa
@ethioterkaa
# ለመፍረድ_አንቸኩል ! ዶክተሩ ስልክ ይደወልለትና እየሮጠ ወደ ሆስፒታል ይሄዳል፡፡ሆስፒታል ከደረሰ ቦሀላ ልብሱን በፍጥነት ቀያይሮ ወደ ኦፕራሲዮን ክፍል እየተጣደፈ ሲሄድ መግቢያ በሩ ላይ ቆሞ ይጠብቀው የነበረ የታማሚው ልጅ አባት "እንዴት እዚህ ለመድረስ ይህን ሁሉ ሰአት ይፈጅብሀል ዶክተር? የሰው ህይወት ግድ አይሰጥህም?በጣም ዘገየህ" ሲለው ዶክተሩም በፈገግታ " ይቅርታ ሆስፒታል ጊቢ ውስጥ አልነበርኩም፤ስልክ ከተደወለልኝ ቦሀላ ግን አቅሜ በፈቀደ መጠን በፍጥነት ለመድረስ ሞክሬያለው፤ ተረጋጋ አለው:: "ተረጋጋ ትለኛለህ? ታሞ ሊሞት እያጣጣረ ያለውኮ የኔ ልጅ ነው፤እንዴት ተረጋጋ ትለኛለህ? ያንተ ልጅ ቢሆን እንደዚህ ትላለህ? አንተ በመዘግየትህ ልጄ ሊሞትብኝ ነው ትንሽ አታስብም?'' ብሎ ሲጮህበት ዶክተሩ አሁንም ፈገግ እያለ፦ ዶክተር የሰውን ልጅ ህይወት ሊያረዝምም ሊያሳጥርም አይችልም፤አፈር ነንና ወደ አፈር መመለሳችን አይቀርም፤አሁን ተረጋጋ እኔም ስራዬን ልስራበት" ብሎ ወደ ሰርጀሪ ክፍል ገብቶ ለተወሰኑ ሰአታት የህፃኑን ቀዶ ጥገና ካከናወነ ቦሃላ ወደ ውጭ ወጥቶ በፈገግታ የልጁን አባት "እንኳን ደስ አለህ!! ልጅህ ሰርጀሪ ከተደረገለት ቦሀላ በጥሩ ጤንነት ላይ ይገኛል፤ከዚህ ቦሀላ የሚያስፈልግህ ነገር ካለ ነርሷ ትረዳሀለች " ብሎት እየሮጠ ከሆስፒታሉ ወጣ ሰውዬው በሰማው መልካም ዜና ቢደሰትም የዶ/ሩ ሁኔታ ግራ ስለገባው ነርሷን "ዶ/ሩ ምን ሆኖ ነው እንዲህ የተዋከበው?'' ብሎ ሲጠይቃት " ዶ/ሩ ትላንትና ልጁ በመኪና አደጋ ሞቶበት ቀብር ላይ ነበር፤ያንተ ልጅ ህመም አደገኛ ስለነበር እንዲያክመው ደውለን ጠርተነው ነው፤ አሁን ያንተን ልጅ ካዳነ ቦሀላ የልጁ ቀብር ላይ ለመድረስ ነው እየሮጠ ያለው!" ስትለው ሰውዬው ድርቅ ብሎ ቀረ!! * የሰው ልጅ በምን አይነት ሁኔታ ውስጥ እንደሆነ * ሳታውቅ አትፍረድ!!! መልካም የአባቶች ቀን ❤️
@ethioterkaa
@ethioterkaa
