en
Feedback
ኢትዮ መፅሀፍት እና ትረካ

ኢትዮ መፅሀፍት እና ትረካ

Open in Telegram
776
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
+4430 days
Posts Archive
ጠያቂ፦ ስለ ውሻ ስትፅፍ ውሻ ሆነህ የምታውቅ ይመስላል። ውሻን እንዴት ይህን ያህል ልትረዳው ቻልክ? አዳም ረታ፦ "ውሻ ሆኜ አውቃለሁ። እግር አንስቶ መሽናቱ ሲደክመኝ ተመለስኩ" ... ጠያቂ፦ መፅሐፍህ የአጫጭር ታሪክ ስብስብ ለምን ሆነ? ያላለቀ ይመስላል አለማየሁ ገላጋይ፦ ሰው አጭር ስለሆነ አላለቀም ይባላል ወይ? @ethioterkaa @ethioterkaa

ይኸ ምስል በ 1945 የጃፖኗ ናጋሳኪ ከተማ፣ በ2ኛው የዓለም ጦርነት በኒውክለር ቦንብ ከተመታች ጥቂት ወራቶች በኋላ በወርሃ መስከርም የተነሳ ነው። ፎቶው 'የቆመው የናጋሳኪ ልጅ 'በመባል ይታወቃል።
ይኸ ምስል በ 1945 የጃፖኗ ናጋሳኪ ከተማ፣  በ2ኛው የዓለም ጦርነት በኒውክለር ቦንብ ከተመታች ጥቂት ወራቶች በኋላ  በወርሃ መስከርም የተነሳ ነው። ፎቶው 'የቆመው  የናጋሳኪ ልጅ 'በመባል ይታወቃል።  ይኸ ፎቶ በጃፓን በጦርነቱ የሞቱት ከሚታወሱበት በዓል ላይ በግምት 10 ዓመት የሚሆነው ልጅ ሟች ወንድሙን በጀርባው አዝሎ  የሚያሳይ ነው። ስለሁኔታው ይኸን ፎቶ ያነሳው  የአሜሪካ የባህር ሃይል ወታደር  ጆ ኦ ዶኔል ሲናገር እንዲህ ይላል። "በግምት 10 ዓመት የሚሆን ልጅ ልጅ አዝሎ አየሁ። በዚያን ጊዜ ልጅ አዝሎ የሚሄዱ ልጆችን ማየት አዲስ አልነበረም፤ ነገር ግን የዚህ ልጅ ከሁሉ ይለያል። ልጁ ምንም ጫማ አላረገም፤ ፊቱም ገርጥቷል። የታዘለውም ልጅ ከጭንቅላት በከባድ እንቅልፍ ውስጥ እንዳለ ሰው አዝንብሏል። "ልጁ ባለበት ከ5 እስከ 10 ደቂቃ ቆመ። አንድ ነጭ ጭንብል ያደረገ ሰው ወደ እሱ በመጠጋት ገመዶቹን ሲፈታት የማየውን ማመን ነው ያቃተኝ። የታዘለው ልጅ ለካ በሃይወት አልነበረም፤ አስከሬን ነበር የተሸከመው። ሰውዬው አስከሬኑን ተቀብሎ  እሳት* ላይ አኖረ.. "አስከሬኑ በእሳት ሲቀጣጠል   ልጅ በጥርሱ ከንፈሩን ደም እስኪወጣው ድረስ ይነክስ ነበር። በአይኑ እንባ እንደ ዶፍ ይጎርፍም ነበር። እሳት እንደሚጠልቅ ፀሐይ እየጨለመ ሲሄድ በጥልቅ ሃዘን ይመለከት ነበር። በስተመጨረሻም በሃዘን ውስጥ ሁኖ የሄደው አካሄድ ዐይኔ ላይ ቀረ" ብሏል። ይኸ ፎቶ ተደብቆ ቆይቶ በ 1989 ነው ይፋ የሆነው።  ይኸ የወንድም ፅኑ ፍቅር ያሳየ ፎቶ አለምን አስደምሟል። @ethioterkaa @ethioterkaa @ethioterkaa

ሲም ካርድ ( በዲያቆን ዳንኤል ክብረት) አንድ ጓደኛዬ ቢሮ መጣ፡፡ በመንገዱ መጨናነቅ ምክንያት አርፍዷል፡፡ ስልክ ስላልነበረው መንገድ ላይ ለመደወል አልቻለም፡፡ የተቀጣጠርነው በወንድሙ ስልክ ነው፡፡ ቢሮ ሲደርስ ደግሞ አሣንሰሩ አይሠራም፡፡ በእግሩ ነው አምስት ፎቅ የወጣው፡፡ ቢሮ ደረሰና ‹እፎይ› ብሎ ወንበሩ ላይ ተዘረጋ፡፡ ስልኩ ከኪሱ ወደቀ፡፡ ‹ይህን የመሰለ ስልክ እያለህ ነው የማትደውለው?› አልኩት፡፡ ‹ምን ዋጋ አለው፡፡ ሲም ካርድ ከሌለው› አለኝ፡፡ የያዘው ስልክ በኢትዮጵያ ብር ከ30 ሺ ብር በላይ ያወጣል፡፡ የ15 ብር ሲም ካርድ አጥቶ ነው መከራ የሚያየው፡፡ ‹ሲም ካርድ ለምን አላወጣህም?› አልኩት፡፡ ‹ሁለት ቦታ ሄጄ የለንም አሉኝ፡፡ ቴሌ ስሄድ ደግሞ የፓስፖርት ፎቶ ኮፒ ጠየቁኝ፤ መብራት ስለሌለ ፎቶ ኮፒ አይሠራም› አለኝ፡፡ የ30 ሺ ብር ስልክ የ15 ብር ሲም ካርድ አጥታ በድን ሆነች፡፡ ስልክ ምን ውድ ዋጋ ቢያወጣ ሲም ካርድ ከሌለው ለካስ ሕይወት አይኖረውም፡፡ ሲም ካርድ (subscriber identification module) ዋጋዋ በጣም ትንሽ ነው፡፡ ለትልቁ ስልክ ሕይወት የምትሰጠው ግን እርሷ ናት፡፡ ሲም ካርድ የሌለው ስልክ ካሜራ ይሆናል እንጂ ስልክ አይሆንም፡፡ በሕይወታችንም ውስጥ እንዲሁ ነው፡፡ ለሕይወት ጣዕም የሚሰጧት ነገሮች በጣም ርካሾች ናቸው፡፡ ውዱን ሕይወት ጣዕም የሚሰጡት እንደ ሲም ካርድ ጠቃሚ ግን ርካሽ የሆኑ ነገሮች ናቸው፡፡ ለአምስት ደቂቃ መጸለይ አምስት ደቂቃ በስልክ ከማውራት ይልቅ በጣም ርካሽ ነው፡፡ ግን ውሏችንን ጣዕም እንዲኖረው ያደርገዋል፡፡ አምስት ሰዓት ከጓደኞቻችን ጋር አምሽተን ብንመጣ ከምናወጣው ወጭ አንጻር አንድ ሰዓት ከትዳር አጋራችንና ከልጆቻችን ጋር ማሳለፍ እጅግ ርካሽ ነው፡፡ ቢበዛ ቡናና ፈንድሻ ቢጠይቀን ነው፡፡ ነገር ግን ትዳራችን ጣዕም እንዲኖረው ያደርገዋል፡፡ በሥራችን መካከል ለአምስት ደቂቃ ያህል ተነሥተን ብንንቀሳቀስ በሰውነታችን የደም ዝውውርና በአካላችን መፍታታት ላይ የሚያመጣው ውጤት ተአምራዊ ነው፡፡ በታክሲ ወይም በአውቶቡስ ስንጓዝ ፌስቡክ ከምንጎረጉር ይልቅ መጽሐፍ ብናነብ በጣም ርካሽ ነው፡፡ በገንዘብ የማይገዛውን አእምሯችንን ሕይወት እንዲኖረው እናደርግበታለን፡፡  ለደቂቃ ረጋ ብሎ መመሪያዎችን ማንበብ በጣም ቀላል ነገር ነው፤ ነገር ግን ውድ የሆነውን ሕይወት ለአደጋ ከመጣል ይታደገናል፡፡ ጾም ርካሽ ነው፡፡ ምን ወጭ የሌለው፡፡ ምግብ ከጾም ይልቅ ውድ ነው፡፡ ኪስ ይነካል፤ ጤናንም ያናጋል፡፡ ርካሽ የሆነውን ጾም በመጾም ውድ ለሆነው ጤናም ሆነ ክቡር ለሆነው የዘላለም ሕይወት መብቃት ግን ይቻላል፡፡  ብዙ ጊዜ ሕይወታችን ሙት የሚሆነው በነገሮች ውድ መሆን አይደለም፡፡ ርካሽ ነገሮችን በሚገባ ለመጠቀም ባለመቻላችን እንጂ፡፡ . . ........💐💐መልካም ምሽት 💐💐........ ቻናሉን ከወደዳችሁት like እና share በማድረግ ለጓደኞቻችሁ እንድታጋሩ በአክብሮት እንጠይቃለን🙏🙏🙏🙏🙏 @ethioterkaa @ethioterkaa @ethioterkaa

የሰው ልጅ ሶሻል ሚዲያን ፈጠረ፥ በሰው የተፈጠረው ሶሻል ሚዲያም ሰውን አፍርሶ እንደ አዲስ መስራት ጀመረ ! ፌስቡክ በአንድ ወቅት ስሜት የሚሰጥ ጥናት አደረገ። በጥናቱ መሰረት በፌስቡክ አጠቃቀም የሰዎችን ስነልቦና መረዳት ይቻላል። ያውም ሪአክት ብቻ በማጥናት ከቅርቦቻችን ሰዎች በላይ ፌስቡክ ያውቀናል! እንዲህ ነው፤ አስር ፖስት ላይ ያለንን ሪአክሽን በመተንተን ከስራ ባልደረባ በላይ ስለእኛ ፌስቡክ ይናገራል። በ150 ፖስቶች ላይ የሰጠናቸው ላይኮችን በማየት ደግሞ የቅርብ የሚባሉ ጓደኞቻችን ስለኛ ከሚያውቁት በላይ ፌስቡክ ስለኛ ያውቃል። እጅግ የጠበቀ ግኑኝነት ያላቸው ባለትዳሮች ስለ ትዳር አጣማሪያቸው መናገር ከሚችሉት በላይ ፌስቡክ ስለ እነሱ ይናገራል። ይህን ለማድረግ 350 ፖስቶች ላይ የተሰጡ ላይኮች ብቻ ለፌስቡክ በቂ ነው። እጅግ ጥቂት በሚባሉ ላይኮች ብቻ ከቅርብ ጓደኛ እና ቤተሰብ በላይ ፌስቡክ  ግለሰቦችን የሚረዳበት ደረጃ ላይ ደርሷል። ተወዳጁ ፀሐፊ ዮቭል ኖሃ ሃራሬ 'Homo deus' በሚል መፅሐፉ አይን ገላጭ ሃሳቦችን አስፍሯል። የአሜሪካ ምርጫ ከመደረጉ በፊት ፌስቡክ ማን እንደሚመርጥ፥ እያንዳንዱ ሰው ማን ፕሬዝዳንት እንዲሆን እንደሚፈልግ በዝርዝር ያውቅ ነበር። ይህን ያወቀው የሰዎችን ሚስጥራዊ መረጃ በመበርበር አይደለም። ይልቅ ሰዎች ለፖስቶች የሚሰጡትን ላይክ በማየት እንጂ! ሰዎች ላይክ የሚያደርጉትን በማወቅ የፖለቲካ ዝንባሌያቸው፥ ርዕዮተ አለማዊ ምርጫቸው ወዘተ ታውቋል። ይህ ብቻ ሳይሆን ምን አይነት አካሄድ ምርጫቸውን እንደሚያስለውጣቸው ጭምር! ጎግል በ2012 ላይ በእንግሊዝ ምድር የተፈጠረውን እንፍልዌንዛ ከ እንግሊዝ ጤና ሚኒስቴር ቀድሞ አውቋል። ዛሬ ላይ አብዮት ከመፈንዳቱ በፊት በማህበራዊ ትስስር ገፆች ይታወቃል። 'እንዴት?' ከተባለ ደግሞ ሰዎች የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀማቸው  ስነልቦናቸውን ፥ ፖለቲካዊ አስተሳሰባቸው ፥ ህልማቸውን እና ስጋታቸውን የመግለፅ አቅም አለው። እኔ እንዲህ አምናለሁ። ዝርዝር ድርጊቶቻችን ከዋናው ስነልቦናዊ ስሪታችን ይቀዳል። እያንዳንዷ ነጠላ ድርጊታቸን ማንነታችንን የመግለፅ ጉልህ አቅም አላት። እለታዊ ውሳኔያችን የህይወት ፍልስፍናችንን ያሳያል። የፌስቡክ አጠቃቀማችን ማንነታችንን ይገልፃል። አየሩን የሞላው ወሬ አስተሳሰባችንን ያሰጠዋል። የታሪክ ተመራማሪ ፀሐፊ እና ፈላስፋው ሃራሬ ማህበራዊ ትስስር ገፆች የሰዎችን ማንነት ከመግለፅ አልፎ ሰዎችን ወደ መግራት እና ወደ አንድ አቅጣጫ ወደ መምራት አድገዋል ይላል። ቲክቶክ ላይ በሚጫን የድመት ቪዲዮ ፥ ፌስቡክ ላይ በሚፖሰት አጭር ፅሁፍ፥ በዩትዩብ በሚጫን አዝናኝ ምስል ፥ ማንነታችን ገሃድ ይወጣል። ፈገግ እያልን ሚስጥራችንን እንገብራለን። ይህ ብቻ አይደምለም! ቴክኖሎጂ ሁለት አስፈላጊ ነገሮችን እየነጠቀን ነው። "አሁን" እና "እዚህ" በቴክኖሎጂ ተፅዕኖ የተነጠቅናቸው ናቸው። የፌስቡክ ማህበረሰብ የተገነባው ከፌስቡክ ውጭ ያለውን ህይወት ዋጋ በማስከፈል ነው! ሰዎች አካል አለን። ባለፈው ክፍለዘመን ግን ቴክኖሎጂ ከገዛ አካላችን እያፋታን ነው። ለምንቀምሰው እና ለምናሸተው ነገር ትኩረት መስጠት ካቆምን ቆይተናል። ይልቅ በስማርት ስልኮች እና በኮምፒውተር ተውጠናል። ጎረቤታችን ከሚደረገው ነገር ይልቅ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ስለሚሆነው እንጨነቃለን።... #ግራ_አጋቢው_ዘመን @ethioterkaa @ethioterkaa @ethioterkaa

ከመፅሐፍ ገፅ ........ ━━━━✦✗✦━━━━ ⇲⇲⇲⇲ ሼር ያድርጉ!! ⇲⇲⇲⇲ አዘጋጅ፦⇨ @ethioterkaa           ⇨ @ethioterkaa ━━━━✦✗✦━━━━

   ❤️❤ለኔ ፍቅር ማለት ❤❤ ━━━━✦✗✦━━━━ ⇲⇲⇲⇲ ሼር ያድርጉ!! ⇲⇲⇲⇲ አዘጋጅ፦⇨ @ethioterkaa           ⇨ @ethioterkaa ━━━━✦✗✦━━━━

  #🌹 ደሞ አየሁሽ በህልሜ 🌹 ━━━━✦✗✦━━━━ ⇲⇲⇲⇲ ሼር ያድርጉ!! ⇲⇲⇲⇲ አዘጋጅ፦⇨ @ethioterkaa           ⇨ @ethioterkaa ━━━━✦✗✦━━━━

ሳይኮሎጂ ፕሮፌሰሩ ወደ ክፍል ገብቶ የእለቱን ወሳኝ ትምርት ለመጀመር ወደ ቦርድ እንደዞረ ፉጨት ሰማ። ወደ ተማሪዎቹ ዞሮ ማን እንዳፏጨ ጠየቀቃቸው ፣ሁሉም ዝም አሉ። ፕሮፊሰሩ ተረጋግቶ ፣እስክሪቢቶው
ሳይኮሎጂ ፕሮፌሰሩ ወደ ክፍል ገብቶ የእለቱን ወሳኝ ትምርት ለመጀመር ወደ ቦርድ እንደዞረ ፉጨት ሰማ። ወደ ተማሪዎቹ ዞሮ ማን እንዳፏጨ ጠየቀቃቸው ፣ሁሉም ዝም አሉ። ፕሮፊሰሩ ተረጋግቶ ፣እስክሪቢቶውን ወደ ኪሱ እየከተተ ፣የዛሬው ሌክቸር እዚ ላይ ያበቃል፣ፈገግ ብሎ ነገር ግን መጀመሪያ አንድ ታሪክ እነግራችዋለው አላቸው።ሁሉም በጉጉት መጠበቅ ጀመረ " ትላንት ቤቴ እንቅልፍ ስላስቸገረኝ ፣ዝም ብዬ ተነስቼ ነዳጅ ልሞላም በዛውም ልናፈስ ለዛሬም ጊዜ ለመቆጠብ ከመሽ ወጣሁ🚗🚗🚗,ነዳጅ ከሞላሁ በኋላ ከትራፌክ ነጻ የሆነው መንገድ ላይ እየተንሸራሸርኩ ከሆነ ፖርቲ ነገር የወጣች የምትመል ቆንጂዬ ወጣት አየሁ። መኪናዬን አዙሬ እርዳታ እንደምትፈልግ ጠየኳት "ታክሲ እንዳጣች እና ቤቷ እንዳደርሳት ነገረችኝ" ጋቢና ገባች....ማውራት ጀመርን....ውበት ብቻ ሳይሆን ባወራነው ርእስ ሁሉ  በጣም ስማርት ጭንቅላት እንዳላት ከምታወራው መገመት ቻልኩ። ቤቷ እንደደረስን ፣በጣም ጥሩ ሰው እንደሆንኩ ነገረችኝ፣እኔም ጥሩ አስተሳሰብ እንዳላት ነግሬአት እንደወደድኳት ነገርኳት፣ዩኒቨርስቲ ፕሮፌሰር እንደሆንኩ አውርተን ፣ስልክ ተለዋወጥን። አንድ ነገር ላስቸግርህ ስትለኝ ፣ምንም ችግር የለውም አልኳት ።"ወንድሜ አንተ የምታስተምርበት ዩኒቨርስቲ ተማሪ ነው፣በኛ ግንኙነት እንዳይጎዳ ቃል ግባልኝ" አለችኝ ....ችግር የለም ብዬ ስሙን ጠየኳት።አንድ መለያ ባህሪ አለው በሱ ታውቀዋለህ፣ፉጨት ማፏጨት ያዘወትራል። አለችኝ ከዛ ሁሉም ተማሪ ወደ አፏጨው ልጅ ዞሮ ማየት ጀመረ ፕሮፌሰሩ "የሳይኮሎጂ PHD ዬን አልገዛውትም፣ሰርቼ ነው ያገኘውት ና ውጣ "🙆‍♂😂😂 . .💐💐መልካም ቀን💐💐. ቻናሉን ከወደዳችሁት like እና share በማድረግ ለጓደኞቻችሁ እንድታጋሩ በአክብሮት እንጠይቃለን @ethioterkaa @ethioterkaa

🕯🕯🕯መልካም ምሽት    ❤❤❤🕯🕯🕯       🔉@ethioterkaa    🔉@ethioterkaa    🔉@ethioterkaa

ዮዲት ጉዲት ማን ናት ከክርስቶስ ልደት በኋላ ፡ በአንደኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ በንግሥት ህንደኬ ዘመን ወደ ኢትዮጵያ የገባው የጥምቀት ዜና በአራት ኛው ክፍለ ዘመን በኦብርሃና አጽብሐ ዘመነ መንግሥት በአባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ስብከት ተስፋፍቶ አብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ ስብከተ ወንጌልን አምኖ ጥምቀትንና ክርስትናን ተቀበለ፡፡ እጅግ በጣም ጥቂት የሆኑ የአይሁድ (ጁዳይዝም) ሃይማኖት አማኞች በወንጌል አናምንም ክርስቲያን አንሆንም ፣ ሕገ ኦሪትን አንለቅም በማለት በ፱፻፹፪ (982) ዓ. ዓለም ግደማ በቀዳማዊ ምኒልክ ዘመን የመጣውን እምነተ እሥራኤል መከተልን ቀጠሉ፡፡ የክርስትና ሃይማኖት አንቀበልም ብለው በአይሁድ (የኦሪት) እምነታቸው የፀኑት ሕዝቦች በነገሥታቱ ትእዛዝ የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ከሆነችው ከአክሱምና ከዙሪያዋ አየለቀቁ በመውጣት በወልቃይት፣ በሰሜንና ፥ በወገራ ፣ በደምቢያ ፥ ዛአገው ፥ በላስታ ፥ በሰቆጣና በመሳሰሉት ሊኖሩ እንደሚችሉ ስለ ተገለጸላቸው አክሱምንና አካባቢዋን እየለቀቁ በመሔድ ተበታትነው ይኖሩ ጀመረ ። በዚህ ምክንያት ፈላሻ ተባሉ ፡፡ ፈላሻዎች እምነታቸው ሕገ ኦሪት ቢሆንም ኢትዮጵያዊነታቸው የተረጋገጠ ስለሆነ ፥ በመንግሥት ትእዛዝ በተፈቀደላቸውና በሚኖሩባቸው በሰሜንና በላስታ እንዲሁም በተለያዩ ሥፍራዎች ለረዥም ጊዜ በመኖር ቁጥራቸው እየበዛ ሔደ ፡፡ የሕዝቡ ቁጥር አየበዛ ሲሄድም ለአክሱም መንግሥት ግብር እየክፈለ በሰላም ይኖር ጀመር፡፡ ዮዲት ጉዲት በዘጠነኛው ምዕተ ዓመት ፰፻፶፪ (852) ዓ.ም ገደማ ዮዲት የተባለችው የጌዴዎን ልጅ ንግሥት ዘሯ ከፈላሻ ውስጥ በመሆኑ ፈላሾችን ይዛ ተነሣች። በላስታ የሚኖር የክርስትያን ሃይማኖት ተከታይና የቡግና ባላባት በዮዲት ውበትና ኃይለኛነት ስለተማረከ ሃያማኖቱን ለውጦ አገባት። በዚህም ምክንያት ተጨማሪ ኃይል ለማግኘት ቻለች ፡፡ በዚህ ዘመን በአክሱም ዙፋን ላይ የተቀመጠው የንጉሥ ድግናዣን ልጅ አንበሳ ውድም ነበር ። አንበሳ ውድም አባቱ ሲሞት ገና የዐሥራ ሁለት ዓመት ልጅ ቢሆንም የንግሥና ሥልጣኑን ያዘ፡፡ ዮዲትም ንጉሡ ገና ሕፃን ስለሆነ የሧን ጥቃት የሚቋቋም ኃይል ሊያሰባስብ እንደማይችል በመገመት አጋጣሚውን ተጠቅማ ልትወጋው አሰበች ፡፡ በዚያን ጊዜ አክሱም የእስልምናን ሃይማኖት ለማስፋፋት በሚደረገው ጥረት የተነሣ ጠረፎቿ በመወረራቸው በቀይ ባሕር የነበራትን የበላይነት ያጣችበት ወቅት ነበር ፡፡ ይህች የክርስቲያን ባላጋራ የሆነች ንግሥት ፈላሾች የሆኑትን ሁሉ በአንድነት አስባስባና አሥተባብራ የአክሱም ንጉሥ አንበሳ ውድምን ለመውጋት ተነሣች ፡፡ ከላስታ ፣ ስሜንና ወልቃይት የተሰበሰቡትን ፈላሾችና ሌሎችም ቀሥቅሣና አስፈራርታ በማሥነሣት ብዙ ሠራዊት እየመራች ወደ አክሱም ዘመተች ፡፡ ወደ አክሱም በምትጓዝበት ጊዜ ያለፈችበትን ሥፍራ ሁሉ ሠራዊቷ ይመዘብርና ያጠፋ ነበር ። አብዛኛዎቹ አብያተ ክርስቲያናትና ሌሎችም ውድ የሆኑ የባህል ቅርሶች የተቃጠሉትና የወደሙት በዮዲት ጭካኔ የተሞላበት ወረራ ነበር ፡፡ ብዙ ጊዜ አምረውና ደምቀው ግርማ ሞገስ የነበራቸው አብያተ ክርስትያናትና ሐውልቶች፡ ጭራሽ ከወደሙት ሌላ ለታሪክ ምሥክርነት በእሳት ጋይተው ፍርስራሻቸው ብቻ የሚታየው ብዙ ናቸው፡፡ ብዙ ክርስትያኖች ሲጨፈጨፉና የቀሩትንም በታላቅ አደጋና ሥጋት ተውጠው የመከራ ዘመናት አሳልፈዋል፡፡ የዮዲት ፍላጉት የክርስትና ሃያማኖትንን አጥፍታ የአይሁድን እምነት ለማስፈን ነበር፡፡ ይህን በስፋት ይካሄድ የነበረውን ጭፍጨፋ ለመቋቋም የተሳናቸውና በሥጋት ላያ ወድቀው የነበሩት የአክሱም መሳፍንትና መኳንንት ፋታና ጊዜ አግኝተው መልሰው ለማጥቃት እስኪችሉ ድረስ ሕፃኑን ንጉስ ይዘው ሸዋ ውስጥ ወደሚገኘው ወደ መንዝ ሸሹ ፡፡ መንዝ የተመረጠበትም ዋናው ምክንያት የመልክዓ ምድሩ አቀማመጥ ገደላማና ዋሻ በመሆኑ ጠላት ስለማይደፍረው ፥ ገፍቶም ቢመጣ ለመከላከል አመቺ በመመሆኑ ነበር ፡፡ ዮዲት የክርስትናን ሃይማኖት አጥፍታ የፈላሻን ሃይማኖት በሰፊው እንዲሰበክና እንዲስፋፋ ስለፈለገች በአክሱም ሕዝቦች የተገነባውንና ሁለት ሺህ ዓመታት ያህል አብቦ የቆየውን ሥልጣኔና የሥልጣኔ ውጤት የሆኑትን ታሪካውያን ሥራዎች ማፈራረሷን ተያያዘችው ፡፡ አብያተ ክርስቲያናትን ማቃጠልና ካህናትን መግደል የዕለት ሥራዋ ሆነ፡፡ በተለያዩ አጋጣሚዎች ከተረፉትና እስካሁን ድረስ ካሉት ጥቂቶች በስተቀር ሐውልቶችን ውብ የሆኑ የሥነ ጥበብ ቅርሶችንሞ አፈራርሳለች፤ አብያተ ክርስትያናትን አቃጥላለች ። የክርስትና ሃይማኖት ተከታይ ተራው ሕዝብና ቄሶች ተሰየፉ ። የመንግሥት ዘርነት የነበራቸው የመሳፍንት ልጆችም መንግሥቱን አንዳይቀናቀኑና አንዳይሸፍቱ ሕዝቡንም እንዳያነሣሡ ተብሎ ወደ ደብረ ዳሞ ተራራ አየተወሰዱ በእስር እንዲቀመጡ ይደረግ ነበር ። በቆየው ሥርዓት በዚህ ገዳም ውስጥ የመሳፍንት ልጆች በቁም አስረኛነት አየተጠበቁ ይቆዩና ንጉሡ ሲሞት ከመሳፍንቱ ውስጥ ሕዝቡ የመረጠው ይነግሥ ነበር ፡፡ በዚሁ ምክንያት የተሰበሰቡበትን ፬፻ (400) የሚሆኑ የመሳፍንት ልጆች በጅምላ አሳረደቻቸው። ዮዲት በፈጸመችው ጭካኔ ሥራና ከፍተኛ ጥረት የተነሣ ተግባሯንና ክፋትዋን የሚገልጹ የተለያዩ ቅጥያ ስሞች ተስጥቷታል። በትግራይ ሕዝብ ጉዲት (ጉደኛ) በአፋር ሕዝብ ጋፅዋ (አስፈሪ አውሬ) በመባል ስትታወቅ በአማራ ሕዝብም እሳቶ (የምታቃጥል) ብለዋታል፡፡ ጉዲት ሕፃኑን ንጉሥ አንበሳ ውድምን በመንዝ የመደበቁን ዜና በሰማች ጊዜ ኃይሉን ሰብሮ እሱን ማርኮ እንዲያመጣ ጦር ልካ ነበር ነገር ግን የላከችው ሠራዊት በመሸነፉ ሐሳቧ ሳይሰምር ቀረ ፡፡ ስለዚህ አንበሳ ውድምንና ተከታዮቹን አጥፍታ እርካታ ለማግኘት በማሰብ ራሷ ሠራዊቷን እየመራች ወደ መንዝ ዘመተች። አንበሳ ውድምና ተከታዮቹ ግን ለማጥቃት ይበልጥ አስቸጋሪ ወደ ሆነውና እዚያው ሸዋ ውስጥ ወደሚገኘው ወደ መርሐቤቴ ሸሹ። ዮዲትም በዚሁ ሳትገታ ልትከታተለው ሞክራ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ከመሬቱ አቀማመጥ አስቸጋሪነት ሌላ የንጉሡ ወታደሮች የመንዝና የመርሐቤቴ ሕዝብ በየጊዜው ያደርሱባት የነበረው ጥቃት አንድ ላይ ተዳምረው ስሳደክሚት ዓላማዋ ሳይሳካላት ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ እንደገና እንድትመለስ ተገደደች ፡፡ ከዚህ በሇላ ለ፲፫ (13) ዓመታት ስትገዛ ቆየች ፡፡ ይህች ጨካኝ ንግሥት አብዛኛዎቹ የኢትዮጵያ ቅርሶች ያጠፋችበትን የ፵ (40) ዓመታት ዕድሜ ገዝታ ማክተሚያ ላይ የእብርሃ ወአጽብሐን ቤተክርስቲያን አቃጥላ በምትመለስበት ጊዜ እግዚአብሔር መንገዷን አሳስቶ አዲንፋስ ከሚባለው ቦታ ከፍተኛና አስፈሪ አውሎ ነፋስ አስነሥቶ ወርውሮ አደካውህ ከሚባለው ቦታ ላይ አንደ ጣላትና በዚሁ ምክንያት አንደ ሞተች ብዙ ሊቃውንት ይናገራሉ። መቃብሯም ከውቅሮ ከተማ በታች በሚገኘው አደካውህ አጠገብ የድንጋይ ምልክት ተቀምጦበት ይገኛል ፡፡ ምንጭ:- "የኢትዮጵያ ሥልጣኔ" ፣ በላይ ግደይ፣ መጋቢት ፲፱፻፹፫"ቅዱሳን መካናት በኢትዮጵያ"፣ ዘመድኩን በቀለ፣ የካቲት ፩፱፱፪ "የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ታሪክ"፣ አቡነ ጎርጎርዮስ፣ ሴኔ ፲፱፻፸፬ 💚💛❤️ @ethioterkaa @ethioterkaa @ethioterkaa

ለገና ስጦታ ምን ሊሰጡ አስበዋል !!!! ሰላም ሰላም ውድ የቻናላችን ተከታታዮች ምስሉ ላይ እንደምትመለከቱት ስዕል ማሳል የምትፈልጉ @Abrishjano @janoooooom አናግሩን በስልክ ቀጥር 09
+7
ለገና ስጦታ ምን ሊሰጡ አስበዋል !!!! ሰላም ሰላም ውድ የቻናላችን ተከታታዮች ምስሉ ላይ እንደምትመለከቱት ስዕል ማሳል የምትፈልጉ @Abrishjano @janoooooom አናግሩን በስልክ ቀጥር 0989511531 በተመጣጣኝ ዋጋ

      " አይተሽ ታውቂያለሽ " መልካም ሰንበት ━━━━✦✗✦━━━━ ⇲⇲⇲⇲ ሼር ያድርጉ!! ⇲⇲⇲⇲ አዘጋጅ፦⇨ @ethioterkaa           ⇨ @ethioterkaa ━━━━✦✗✦━━━━

🕯🕯🕯መልካም ምሽት    ❤❤❤🕯🕯🕯       🔉@ethioterkaa    🔉@ethioterkaa    🔉@ethioterkaa

Watch ""ፀሀይ" የፍቅርን ❤ ጥግ እሚያሳይ 😘በአይነቱ ልዪ 🕯🕯እንዳያመልጦጦ✒️" on YouTube https://youtu.be/zN5_1vMmGdo

ሀገር ወይስ አንቺን ❤️❤️❤️ ━━━━✦✗✦━━━━ ⇲⇲⇲⇲ ሼር ያድርጉ!! ⇲⇲⇲⇲ አዘጋጅ፦⇨ @ethioterkaa           ⇨ @ethioterkaa ━━━━✦✗✦━━━━

"ጩኸት መሰል ስብከት" 🔉አብርሽ 🙏 ሀሳብ  አስተያየታቸውን በ- @Abrishjano እንድታደርሱን በትህትና እንጠይቃለን         ቻናላችን እንዲያድግ ሼር እንዲያረጉ ለ ወዳጆ      ያካፍሉ        🕯@ethioterkaa      🕯@ethioterkaa     🕯@ethioterkaa

🕯🕯🕯መልካም ምሽት    ❤❤❤🕯🕯🕯       🔉@ethioterkaa    🔉@ethioterkaa    🔉@ethioterkaa

🕯🕯🕯መልካም ምሽት    ❤❤❤🕯🕯🕯 "ብርሀን"🕯🕯🕯🕯       🔉@ethioterkaa    🔉@ethioterkaa    🔉@ethioterkaa

🕯🕯🕯መልካም ምሽት    ❤❤❤🕯🕯🕯 "አየኋት"       🔉@ethioterkaa    🔉@ethioterkaa    🔉@ethioterkaa