en
Feedback
ኢትዮ መፅሀፍት እና ትረካ

ኢትዮ መፅሀፍት እና ትረካ

Open in Telegram
776
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
+4430 days
Posts Archive
ከሶስቱ የቱ ይከብዳል ኮመንት ላይ ሀሳባችሁን አካፍሉን @ethioterkaa @ethioterkaa
ከሶስቱ የቱ ይከብዳል ኮመንት ላይ ሀሳባችሁን አካፍሉን @ethioterkaa @ethioterkaa

የሕይወት ጥሪ፦ ካድማስ ባሻገር የበአሉ ግርማ የበኩር ድርሰቱ ነው ። ይህ መፅሐፉ ፍልስፍናንና ቅኔን አዋህዶ የያዘ ነው። በዚህ መፅሐፍ በአሉ የድርሰት ችሎታውን አሳይቶናል። አንጋፋ ገፀ ባኅሪያት አበራና ኃይለ ማርያም ናቸው ። መፅሐፉ ስለ ሕይወት ጥሪ ሚስጥራትን ያዘለ ነው። ሕይወትን በአሉ ከሚሠበር ሸክላ ጎራ ያሠልፋታል፣ ጥሪዋን ያልተረዳች ሕይወትም ከንቱ እንደሆነች አበክሮ ይገልፃል በካድማስ ባሻገር መፅሐፉ። ለበአሉ በሕይወት ውስጥ ፍቅር አለ ፣ የሙያ መሥዋእትነት አለ፣ የሚያሠለችም ሆነ የሚያጓጓ ተግባር አለ ፣ መሮጥ አለ፣ መውደቅ አለ፣ መነሳት አለ ፣ የማያቋርጥ ትግል አለ ፣ የማያባራ ሮሮ አለ፣ ብቅ ጥልቅ የሚል ደስተኛነትን እንዲቀጥል የማያደርግ ደስታ አለ። ለበአሉ ሕይወት ጣፋጭ ናት፣ ሕይወትም መራራ ናት፣ በአስተውሎት ካልያዟት፣ ጥሪዋን ካልተረዱ በኦና ቤት አሥራ የምታስቀምጥ፣ በኃዘን ፣ፀፀትና ትካዜ የምታስውጥ፣ ፀጥታን የምታደፈረስ፣ አለሁ እያለች የለሁም የምትል፣ በአንድ ራስ ሁለት ምላስን ተሸካሚ ናት ። በዚህች ጨለማንና ብርሀንን እያፈራረቀች ልብን ሠርቃ በቀላሉ በማትመልስ ሕይወት ውስጥ ነው እንግዲህ ቆፍጠን ያለውና የሕይወት ጥሪዬን አገኘሁ የሚለው ኃይለ ማርያም አበራን በሕይወት ጥሪው መሥመር እንዲጓዝ ለተቀን የሚጨቀጭቀው። እንዲህ ይለዋል፦ " አበራ ስንት ግዜ ልንገርህ! አሁንም በድጋሜ እነግርሀለሁ። አንተም ብትሆን እኔ የፖለቲካ ሠዎች አይደለንም። ይህን አንተ ከእኔ የበለጠ ታውቃለህ። ግዜያችንና ሕይወታችንን ነው የምናባክነው...... በከንቱ ።" " አውቃለሁ ኃይሌ ፣ ሕይወት የተሳሳተ መንገድ ላይ አውጥታ ጥላናለች... ግን ምን ይሁን ?" " የጣለችን ሕይወት አይደለችም፣ አኛው ነን ራሳችንን የጣልነው። ፊቴን መሥተዋት ውስጥ ስመለከተው ጎልቶ የሚታየኝ ፍርሀቴና ወኔ ቢስነቴ ነው፣ ሌላ ነገር አይታየኝም። በምግባራችን የራሳችንን ደኅንነት ልንፈጥር እንችላለን። ይህን ለማድረግ አስቀድመን በትንሹ መሞት ያሻናል.....በልጅነት ወላጆች ጫንቃ ላይ ከዚያም በኋላ ለትምህርትም ሆነ ለሥራ መንግስት ትከሻ ላይ ተንጠልጥለን አሰከ መቼ ድረስ ! እስካሁን ድረስ ከመውሰድ በስተቀር መልሰን የተካነው ምን ነገር አለ ? ምንም ! ምንም !" ውይይታቸው እንዲህ እያለ ይቀጥላል ። የሕይወት ስንክሳር የሕይወት ጥሪ፣ ኃይለ ማርያም ጥሪው ደራሲ መሆን ነው፣ የአለምን ሚስጥራት መግለፅ ነው፣ አለምን ለአለም ማሳወቅ ነው፣ ውስጣዊ የሥሜት ተሠጥዖዎችን ወደ ውጭ ማውጣትና ከውጭኛው አለም ማዋሀድ ነው ፣ ማሳወቅ፣ ማስገንዘብና ማሥተማር ነው፣ ኃይለ ማርያም ጥሪውን አገኝቶ እግቡ ለማድረስ እየተፍጨረጨረና እየታገለ ነው ፣ አበራስ ? ለመቁረጥ ይታገላል፣ ጥሪውን መቀበል ቀላል ሆኖ አልታየውም፣ ጥሪውን እግብ ለማድረስ ወኔው ቢኖረውም የጥሪው ፍላጎቶች የትዬሌለ በመሆናቸው ይቃትታል፣ ይዋትታል። የሕይወት ጥሪዬን ተግባራዊ ለማድረግ ሥራዬን መልቀቅ አለብኝ፣ ሥራዬን መልቀቁ ብቻ አይደለም ፣ ጥሪዬን ለመከወን ገንዘብ ያስፈልገኛል፣ አጋር ያስፈልገኛል፣ ጥሪዬ የሥእል ሙያ ነው፣ እውስጤ ተቀርጿል፣ ስሜቴና ፍላጎቴ ባያሌው ወደዚያ አዘንብሏል። ከፍፃሜ ለመድረስ ወኔ አጣሁ፣ ፈራሁ ይላል አበራ። ታዲያ ጥሪውን ከግብ አድርሶት ይሆን ? ጀመረ ግን አልጨረሠውም፣ ፍቅር፣ ቅናት፣ ቁጣ፣ ገንፍሎ የወጣ ስሜት አሯሯጠው፣ ጥሪው በአጭሩ ተቀጨ። የሚያፈቅራትን ልጅ በቅርቡ ሚስቱ ያደረጋት ሉሊት ቆንጆዋና ቁምነገረኛዋ፣ ስሜቱን አዳመጠች ፣ አጋሩ ለመሆንና ከጎኑ ለመቆም ወሰነች የሥእል መሣሪያዎችን ለመፈለግና ለማሟላት ወጣች ። ካጠገቡ በመሠወርዋ ግራ ተጋባ፣ እርሷን የምትመሥል ሴት ከአንዱ ጋር በማርቼዲስ መኪና ሲሄዱ አዬ፣ ተከታተለ ፣ አልጋ ይዘው ነበር፣ ስሜቱን ሊቆጣጠር አልቻለም፣ ሽጉጥ ይዞ ነበር፣ ያሉበትን በር በረገደ፣ ተኮሰ፣ ገደለ ግን ሉሊት አልነበረችም፣ ሌላ ሴት ናት፣ እርስዋ ስትሞት ከርሷ ጋር የነበረው ሠው አልሞተም፣ በድንጋጤ አልጋ ሥር ተሸሽጎ ነበር ። የሕይወት ጥሪው ከሸፈ፣ ነፍሰ በላ ሆነ ወደ ወህኒ ቤት ወረደ። የሕይወት ጥሪውን ለማሥጀመር ታጥቃ ተንስታ የነበረችው አጋሩ ሁኔታውን አወቀች፣ ስሜቱን ረገመች፣ የሠው ከንቱነት ታወቃት፣ አመነችው ግን አላመናትም። የሕይወት ስንክሳር፣ የሕይወት ጥሪ በዚህ መልኩ ተጨናገፈ። ይህ የበአሉ ድርሰት አጥብቆ የሚያስገነዝበን አላማን ለማሳካት ማንገብ ያለብን ስሜትን የመቆጣጠር ብቃትን ነው" Emotional intelligence" ከብቃቶች ሁሉ ላቅ ያለ ብቃት፣ እነ ክሊንተን ሁሉ የተሸነፉበት፣ የበአሉ ገፀ ባኅሪይ አበራም ሊታጠቀው አልቻለም። ሊዮናርዶ ዳቬንቺ ሞናሊዛን አሳምሮ በመሳል እውቅናን አገኘ ፣ የኛው ሎሬትስ አፈወርቅ ግሩም ሰአሊ ነበር፣ የሕይወት ጥሪውን አግኝቶ ለበረከት የበቃ። ሠአሊነት ትልቅ ሙያ ነው። የተለጠፈው ሥእልስ አግራሞታችሁን አለጫረም ? ፊት ለፊት የሚተያዩ ሴትና ወንድ አዛውንቶች፣ አይኖቻቸው ከሚያማምሩ ወጣቶች አፍና ጉንጭ የተገነባ ፣ አፍንጫቸውም ከክንዶቻቸው ፣ አንዱን ከሌላው ጋር ማዋሀድ፣ የማይታሠብ ውብ ነገርን መፍጠር ፣ የአይን እይታን መሳብ፣ ለምርምር መጋበዝ። አወን ሰአሊነት መልካም ጥበብ፣ የሕይወት ጥሪ ለሆነው ጥሩ አእምሮን ፈታሽና አጎልባች ነው። ሮጦ ሳይቀድም ተጠልፎ የወደቀው፣ የሕይወት ጥሪው ያልተሳካለት አበራ ያሳዝናል፣ አንጀት ይበላል፣ አጋሩ ሉሊት ስኬትን ለመጋራት ያሠበችው አልተሳካላትም፣ በደራሲው ሁለቱም የሕይወት ጥሪያቸው ተጨናገፈ፣ የሀዲስ ገፀ ባኅሪያት የሠብለ ወንገልና የበዛብህ የሕይወት ጥሪ እንደተጨናገፈ ሁሉ። ደራሲያን ጨካኞች ናቸው ብል ያምርብኝ ይሆን ? ስለማያምርብኝ ተውኩት። በሰበብ አስባቡ የማከብራቸውንና የማወድሳቸውን ደራሲያን በአሉንና ሀዲስን በአእምሮዬ ቃኘኋቸው፣ ብራቦም ብዬ አንደኝነትን አጎናፀፍኳቸው። የሕይወት ጥሪ ስንክሳር፣ ደራሲና ሠአሊ፣ ኃይለ ማርያምና አበራ፣ በአሉና ሀዲስ፣ ሰብለ ወንገልና ሉሊት ተደበላለቁብኝ። ለደራሲያንም ሆነ ለፈጠሯቸው ገፀ ባኅሪያት ክብርን በመቸር ተሰናበትኳቸው፣ በቸር ያንቀላፉ። @ethioterkaa @ethioterkaa @ethioterkaa 💚💛❤️

#እሰይ ፡ ፡ ፡ ከመሳሳት ይልቅ ትክክል መሆንን ሰርክ ስለሚመርጥ፤ ይላል ያገሬ ሰው “ አስር ግዜ ለካ አንድ ግዜ ቁረጥ”። ፡ ፡ እኔ ግን እላለው... በመሳሳትክ ውስጥ የሚገኘው እክል፤ እሱ ነው ቁምነገር እሱ ነው ትክክል። ፡ ፡ አሁንም እላለው... ከትናንቱ ዛሬ በስለ እንድትጎመራ፤ “ አንድ ግዜ ለካ አንድ ግዜ ቁረጥ ” እሰይ ስህተት ስራ። #ሄኖክ_ብርሃኑ @ethioterkaa @ethioterkaa

የሰማይ ቤት ግሮሰሪ (አሱ እንደፃፈዉ) . . "ጨረቃ" ምንላት ግሮሰሪ ቤት ናት!!! "ሰማይ" ለምንለው ፣ ቀውጢ ከተማ ሥራ ምትጀምረው ፣ሲሆን ነው ጨለማ!!! .................................................. በር እንደከፈተች ፣ አብረው የሚወጡ ከዋክብት ደሞ... ሰካራሞች ናቸው ፣ እሷ ጋ ሚጠጡ!!! ***** በጣም የሰከረው... ከሰማይ ፈጥፍጦ ፣ ራሱን ሲገድል "ተወርዋሪ ኮከብ" .. ማለት ነው የኛ እድል!!! **** ተወርዋሪ ጠርሙስ ሊሆንም ይችላል! ማን ያውቃል? @ethioterkaa @ethioterkaa

በኔ ቤት…(ልዑል ሀይሌ) በኔ ቤት…… ፍየል ቅጠል አይታ ሳትበላ ታድራለች ዶሮ ጥሬ ረግጣ ልፆም ነው ትላለች ውሻ ስጋ እያየ በረሀብ ይሞታል ሰው እህል ቀርቦለት ባዶ ድስት ይከፍታል … በኔ ቤት…… አንበሣ ሚዳቋን አቅፎ ይስማታል ጅብ ስጋ ላይበላ ምሎ ይገዘታል ዕባብ ሰውን አይቶ አይተናኮልም ነብር ጎሽ አይጥልም … በኔ ቤት…… አንድ ብር ላይ ያለው ትንሹ እረኛ መሳቁን ያቆማል የሰፌዱም ስፌት ሳንቲም ላይ ይሆናል ወተት የጠጣ ህፃን ሰክሮ ተንገዳግዶ የአስር ዓመት ልጅ አስር ልጆች ወልዶ የሰፈር አዛውንት ሰፈር ይቦርቃል ሩቅ ያለው ቀርቦ ቅርብ ያለው ይርቃል … … አሁንም… ከጣልሺኝ ቦታ ላይ ብቻዬን ቁጭ ብዬ ታምራዊ ስዕል በአይምሮዬ ስዬ ሀሳቤን ጥጃለሁ ማይበስል ማይመስል ዳግም በህይወቴ አገኝሽ ይመስል @❤❤❤❤❤ @ethioterkaa @ethioterkaa @ethioterkaa 💚💛❤️

" # እጅ_ከፍንጅ "? - አንዲት ባለትዳር ፥ በጓዳዋ ሳለች ፥ ጉንዳን ቆነጠጣት ከእግር እስከ ራሷ ፥ ተርመስምሶ ገብቶ ፥ ነክሶ ፋታ አሳጣት - ይሄን ጊዜ ጮኸች፤ ልብሶቿን አራግፋ ፥ ራቁቷን ቀረች! - ጩኸቷን የሰማ ፥ ላጤ ጎረቤቷ ፥ ገባ ተንደርድሮ ያቺን ቆንጆ እንስት ፥ እርቃኗን ሲያያት ፥ ቀረ ተገትሮ! - በዚህ ሁነት መሃል ፥ ሰይጣን አይኑን ሲጥል ፥ ባል ድንገት ይደርሳል ሰበብ የጠፋ 'ለት ፥ የጉንዳን ወረራ ፥ ትዳርን ያፈርሳል ። ---------//---------- (✍ በርናባስ ከበደ ) @ethioterkaa @ethioterkaa

♡ ስሞት አትቅበረኝ ♡♡♡ በሂወት እያለሁ እንባዬን ካልጠረግህ ፣ በእኔ እንባ ማንባት ካላዘነ ልብህ ፣ ሰታመም ዝም ካልህ ፣ እራቤ ካልገባህ ፣ ጭንቀቴም ብሶቴም ከመሰለህ ተራ ፣ ድፍርሱ ሂወቴ በፍቅርህ ካልጠራ ፣ ደብዛዛዉ ሂወቴ በፍቅርህ ካልበራ ፣ ተልካሻዉ ኑሮዬን ካላሰናዳከዉ ፣ የተደላደለ ቦታ ካላሲያዝከዉ ፣ ማየት የተሳነዉ ፍቅሬን ካልመራሀዉ ፣ እዉነት እልሃለሁ ዉዴ... ስሞት አትቅበረኝ ፣ እንባም አታንባልኝ ፣ ፀፀትም አትግባ ይልቁንስ ፍቅሬ... እንደ ሻማ ቀልጦ ፍቅሬ ሳያልቅብህ ፣ እጂጉን አምሮ ልቤ ሳይቆርጥብህ ፣ ስታመም አስታመኝ ፣ ሰከፋ አፅናናኝ ፣ ስወድቅ ደግፈኝ ፣ የጭንቀቴን ብሶት የዉስጤን ተረዳኝ ፣ ድፍርሱን ሂወቴን በፍቅርህ አጥራልኝ ፣ ደብዛዛዉ ሂወቴን በፍቅርህ አብራልኝ ፣ ተልካሻዉ ኑሮዬ ፈጥነህ አሰናዳዉ ፣ የተደላደለ ቦታዉን አሲዘዉ ፣ ማየት የተሳነዉ ልቤን ይዘሀ ምራዉ ፣ ደስታና ፍቅርን ከልብ አስተምረኝ ፣ ሁል ጊዜ ሳቅልኝ ፣ ይሄ ካልሆነ ግን ስሞት አትቅበረኝ :: ምንጭ፦ ወንጌላዊት እሙ ======================= ለ "ስሞት አትቅበረኝ" ግጥም ምላሽ ከአያልቅበት ሰለሞን እሙ በህይወት እስካለሽ እንባሽን አብሼ ስታለቅሺ ሳይሽ ተንሰቅስቄ አልቅሼ ስትዝኚ ዕያየሁ እጥፍ ካላዘንኩኝ ምኑን ሰው ተባልኩኝ ሢያምሽ ካላመመኝ እራብሽ ካልራበኝ ምኑን አፈቀርኩሽ ምኑን ወዳጅ ሆንኩኝ ጭንቀትሽ ብሶትሽ ከመሰለኝ ተራ ድፍርሱ ህይወትሽ በፍቅሬ ካልጠራ ተልካሻው ኑሮሽን ካላሰናዳሁት የተደላደለ ቦታ ካላሲያዝኩት ምናል ባልተዋወቅን እላለሁኝ ዕኔ ለፍቅርሽ መከታ ስላለመሆኔ ይልቅስ አታስቢ ፍቅሬ ቃል ልግባልሽ ዛሬ ስታለቅሺ አልቅሼ ስታዝኝም አዝናለው ባስለቀሰሽ ጉዳይ ዳኛም እሆናለው እፋረደዋለው። ፍቅርሽን ቀንበቀን በፍቅሬ አድሳለው ምስቅልቅል ህይወትሽን ዘውትር አድሳለው እታመንሻለው አይንሽ አያለቅስም ልብሽ አይቆዝምም ፈገግታሽ አይፈዝም የፊትሽም ፀዳል ከቶ አይደብዝዝም ይኸውልሽ ፍቅሬ ቃል ልግባ ደግሜ ፍቅርሽ ተሰራጭቷል ባካልና ደሜ ሲያምሽ ያምመኛል ሥታዝኚም አዝናለው ስታለቅሺ አልቅሼ ስትስቂም ስቃለው በፊትሽ ብርሐን እኔም እደምቃለው ነገርግን ፍቅሬ ሆይ ስሚኝ በጽሞና ምናልባት ሚሆነውን አላውቀውምና አድምጭ እንደገና ምናልባት ይህ ቃሌን መጠበቅ ቢያቅተኝ ለፍቅርሽ መከታ መሖን ቢያታክተኝ ህይወትሽን ማቃናት ባልችል በስንፍና ይሄ ወዳጅነት ከቶ አይሆንምና አድምጭ እንደገና በፍቅሬ ፍቅርሽን መፈውስ ቢሳነኝ ሀዘንሽን ማዘን ከቶ ባይቻለኝ ዕንባሽን አብሼ ባንቺ ፈንታ አልቅሼ ሀዘንሽን አዝኜ ሥታባክኝ ባክኜ ካልተገኝኁ እኔ ስትሞች አላለቅስም ለቅሶ አልቀመጥም በሞትሽ አላዝንም ይልቅስ አድምጭ ነግርሻለው ስትሞቺ ሞታለው እከተልሻለው እዚሕ በበደልኩሽ ላይ ቤት እክስሻለው እመኝኝ ቃሌ ነው። ምንጭ፦ አያልቅበት ሰለሞን ♡ ስሞት አትቅበረኝ ♡♡♡ በሂወት እያለሁ እንባዬን ካልጠረግህ ፣ በእኔ እንባ ማንባት ካላዘነ ልብህ ፣ ሰታመም ዝም ካልህ ፣ እራቤ ካልገባህ ፣ ጭንቀቴም ብሶቴም ከመሰለህ ተራ ፣ ድፍርሱ ሂወቴ በፍቅርህ ካልጠራ ፣ ደብዛዛዉ ሂወቴ በፍቅርህ ካልበራ ፣ ተልካሻዉ ኑሮዬን ካላሰናዳከዉ ፣ የተደላደለ ቦታ ካላሲያዝከዉ ፣ ማየት የተሳነዉ ፍቅሬን ካልመራሀዉ ፣ እዉነት እልሃለሁ ዉዴ... ስሞት አትቅበረኝ ፣ እንባም አታንባልኝ ፣ ፀፀትም አትግባ ይልቁንስ ፍቅሬ... እንደ ሻማ ቀልጦ ፍቅሬ ሳያልቅብህ ፣ እጂጉን አምሮ ልቤ ሳይቆርጥብህ ፣ ስታመም አስታመኝ ፣ ሰከፋ አፅናናኝ ፣ ስወድቅ ደግፈኝ ፣ የጭንቀቴን ብሶት የዉስጤን ተረዳኝ ፣ ድፍርሱን ሂወቴን በፍቅርህ አጥራልኝ ፣ ደብዛዛዉ ሂወቴን በፍቅርህ አብራልኝ ፣ ተልካሻዉ ኑሮዬ ፈጥነህ አሰናዳዉ ፣ የተደላደለ ቦታዉን አሲዘዉ ፣ ማየት የተሳነዉ ልቤን ይዘሀ ምራዉ ፣ ደስታና ፍቅርን ከልብ አስተምረኝ ፣ ሁል ጊዜ ሳቅልኝ ፣ ይሄ ካልሆነ ግን ስሞት አትቅበረኝ :: ምንጭ፦ ወንጌላዊት እሙ ======================= ለ "ስሞት አትቅበረኝ" ግጥም ምላሽ ከአያልቅበት ሰለሞን እሙ በህይወት እስካለሽ እንባሽን አብሼ ስታለቅሺ ሳይሽ ተንሰቅስቄ አልቅሼ ስትዝኚ ዕያየሁ እጥፍ ካላዘንኩኝ ምኑን ሰው ተባልኩኝ ሢያምሽ ካላመመኝ እራብሽ ካልራበኝ ምኑን አፈቀርኩሽ ምኑን ወዳጅ ሆንኩኝ ጭንቀትሽ ብሶትሽ ከመሰለኝ ተራ ድፍርሱ ህይወትሽ በፍቅሬ ካልጠራ ተልካሻው ኑሮሽን ካላሰናዳሁት የተደላደለ ቦታ ካላሲያዝኩት ምናል ባልተዋወቅን እላለሁኝ ዕኔ ለፍቅርሽ መከታ ስላለመሆኔ ይልቅስ አታስቢ ፍቅሬ ቃል ልግባልሽ ዛሬ ስታለቅሺ አልቅሼ ስታዝኝም አዝናለው ባስለቀሰሽ ጉዳይ ዳኛም እሆናለው እፋረደዋለው። ፍቅርሽን ቀንበቀን በፍቅሬ አድሳለው ምስቅልቅል ህይወትሽን ዘውትር አድሳለው እታመንሻለው አይንሽ አያለቅስም ልብሽ አይቆዝምም ፈገግታሽ አይፈዝም የፊትሽም ፀዳል ከቶ አይደብዝዝም ይኸውልሽ ፍቅሬ ቃል ልግባ ደግሜ ፍቅርሽ ተሰራጭቷል ባካልና ደሜ ሲያምሽ ያምመኛል ሥታዝኚም አዝናለው ስታለቅሺ አልቅሼ ስትስቂም ስቃለው በፊትሽ ብርሐን እኔም እደምቃለው ነገርግን ፍቅሬ ሆይ ስሚኝ በጽሞና ምናልባት ሚሆነውን አላውቀውምና አድምጭ እንደገና ምናልባት ይህ ቃሌን መጠበቅ ቢያቅተኝ ለፍቅርሽ መከታ መሖን ቢያታክተኝ ህይወትሽን ማቃናት ባልችል በስንፍና ይሄ ወዳጅነት ከቶ አይሆንምና አድምጭ እንደገና በፍቅሬ ፍቅርሽን መፈውስ ቢሳነኝ ሀዘንሽን ማዘን ከቶ ባይቻለኝ ዕንባሽን አብሼ ባንቺ ፈንታ አልቅሼ ሀዘንሽን አዝኜ ሥታባክኝ ባክኜ ካልተገኝኁ እኔ ስትሞች አላለቅስም ለቅሶ አልቀመጥም በሞትሽ አላዝንም ይልቅስ አድምጭ ነግርሻለው ስትሞቺ ሞታለው እከተልሻለው እዚሕ በበደልኩሽ ላይ ቤት እክስሻለው እመኝኝ ቃሌ ነው። ምንጭ፦ አያልቅበት ሰለሞን @ethioterkaa @ethioterkaa

የቀበሮ ፀሎት (ታገል ሰይፉ) ------ እባክህ አምላኬ- ብትሬን ቀባና እኔም ልወዝወዘው-የሙሴን ጎዳና ያላንዳች ፍርሃት-ያለምንም ችግር ባህሩን ከፍዬ- ህዝቤን እንዳሻግር፡፡ * አቤት የኔ ጌታ ይህም አያረካም በቃልህ ታምኜ -ከሆንኩልህ መልካም ለእኔም ፍቀድልኝ-ያብራምን ምልክት ከምድር አሸዋ-ዘሬ እንዲበረክት፡፡ * አቤቱ ምን ልሁን-ይህም አልጠቀመኝ እስቲ እንደ ዮናስ-ህዝብ ፊት አቁመኝ * ትንቢቴን ሰምቶልኝ-ሀገር ይተራመስ ሰው እህል ይጡም-ከብቱም ሳር አይቅመስ፡፡ ይህም አያረካም-ይልቅ እንደዳዊት አንተን በሚፈራ-ብዙ ሺህ ሠራዊት ዙፋኔ ተከቦ-በደስታ እንዳመልክህ የዚህን ሰው ኮከብ -አውጣልኝ እባክህ * አደራህን ታዲያ- ጭንቅ አትወድም ነፍሴ ልመናዬን ሰምተህ-ካደረግከኝ ሙሴ መከራውን ማረኝ-ያርባ ዓመት ስደቱን በሲና በረሃ-መራብ መጠማቱን፡፡ * ነቢዩ ዮናስን -አርገህም ስትፈጥረኝ የባህሩን ፍዳ- ያሳውን ሆድ ማረኝ፡፡ * አብረሃምን ሆኜም-በደስታ ሳመልክህ ልጅህን እረደው-አትበለኝ እባክህ፡፡ *** የዲዊትም ኮከብ-በኔ ላይ ሲወጣ እባክህ አምላኬ -ጎልያድ አይምጣ፡፡ @ethioterkaa @ethioterkaa

ናፍቆት (በላይ በቀለ ወያ) . . እንዲህ እንደዛሬ... በመሀከላችን ንፋስ ሳይግባብን ፣ ፍጥረት ሳይፈጠር በኔና አንቺ መሀል... የነበረው ክፍተት ፣ አንድ ስንዝር ነበር። አንቺ ሰማይ ሆነሽ እኔ ደግሞ ምድር!!! ............................................ በዚህ ስንዝር መሀል.... እስትንፋስ ያላቸው ሰዎች ተፈጠሩ እነዚህ ሰዎችም.... ቅርብ ላለች ሰማይ የምድርን ሀጥያት ይነግሯት ጀመሩ። "ምድር ዘማዊ ነው ምድር ሀጣዊ ነው ብትሸሺው ይሻላል ይህ ዓለም ጠፊ ነው" እያሉ ሲነግሯት የሰው ወሬ ሰምታ ሰማይ ፊኛ ሆና... ትለጠጥ ጀመረ ከኔ ተለይትል በሰዎች እስትንፋስ... ወደ ላይ ተነፍታ ወደጎንም ሰፍታ። ....................................... እንጂማ አውቃለሁ እንጂማ ታውቂያለሽ የሰው ወሬ ሰምቶ ልብሽ ባይረበሽ እንዲህ እንደዛሬ ሳትርቂኝ በፊት ሰማይ ቅርብ ነበርሽ። ................................................ እንደውም እንደውም... በዛ ስንዝር መሀል ያኔ የተፈጠሩ እዛሬ ላይ ሆነው.. "ሰማይ ቅርብ ነበር" እያሉ ሚያወሩ እድሜ የሰጣቸው ጥቂት ሰዎች አሉ የኔና ያንቺ ፍቅር የሚመሰክሩ። ............................................. እንደውም እንደውም.... ሌላ አይነት ማስረጃ ሌላ አይነት ምስክር ሰማይ ቅርብ ሳለሽ ምጣድ ሆኜ ምድር እንዲህ እንደዛሬው... ነፋስ አቀጣጥሎት ነፋስ የሚያጠፋው እሳት ሳይፈጠር የሰው ልጆች ሁሉ በፀሐይ በርሀን ምግብ ያበስሉ ነበር። ............................................. ፀሐይ ውበትሽ ነው ጠዋት የምሞቀው ቀን ተቃጥዬበት ሌት የምናፍቀው። ለሊት ላይ ያመኛል ህመሜም አንቺው ነሽ ቀኑ ጨለማ ነው... ነግቶ እስካይሽ ድረስ ትናፍቂኛለሽ። ........................................... መቼ ነው ሚነጋው? ፀሐዩ ውበትሽ ምድርን የሚከድነው መርዙ መድሀኒትሽ... በሽታዬን ገድሎ ህመሜን ሚያድነው ካፈቀሩት ጋራ.... እንኳን ላንድ ለሊት ላፍታ ያህል እንኳን መለያየት ሞት ነው። ............................................. መቼ ነው ሚነጋው ልቤን ይበርደኛል ንጋት ላይ የሚሸሽ.. ወረተኛ ፍቅር ጤዛው በዝቶብኛል አንቺ የሌለሽበት... ራሴን ሳስበው ራሴን ያዞረኛል። ለራስ ምታት ህመም.. መድሀኒት እንዲሆን በሽታን የሚገድል መርዝ ነው ሚቀመም። ................................... እንጂማ አውቃለሁ እንጂማ ታውቂያለሽ የሰው ወሬ ሰምቶ ልብሽ ባይረበሽ እንዲህ እንደዛሬ. ሳትርቂኝ በፊት ሰማይ ቅርብ ነበርሽ። ........................ እየሔዱ መጠበቅ @ethioterkaa @ethioterkaa

♻️አንድ ሰው ማሃቪራን እንዲህ ሲል ጠየቀው፡- 🗣እውነተኛ ቅዱስ ማን ነው? እና ማን ነው ጥፋተኛ? ምናልባት ጠያቂው በሃይማኖታዊ ጽሑፎች ውስጥ የሚሰጠውን ዝግጁ የሆነ መልስ ፈልጎ ሊሆን ይችላል፣ ነገር ግን እንደ ማሃቪራ ያሉ ሰዎች ከራሳቸው ነባራዊ ግንዛቤ ነው የሚናገሩት። የተናገረው ነገር በጣም ያምራል። የሰጠው ፍቺ ልዩ ነው። በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ምንም ተመሳሳይነት የለውም። 🗣ማሃቪራ እንዲህ ብሏል፦ የነቃ ቅዱስ ነው። የሚተኛው ኃጢአተኛ ነው። ቀላል ፣ ግን በጣም አስፈላጊ… "ንቃት" ያለው ብቸኛው ቅድስና ነው።እና ፤ንቃተ-ህሊና ማጣት ብቸኛው ኃጢአት ነው. ሌሎች ኃጢአቶች የሚመነጩት ከዚህ ካለማወቅ ነው። ሥሩን ይቁረጡ፤ ሥሩን ራሱ ይምቱ! ቅጠሉን አይቁረጡ። ኦሾ @ethioterkaa @ethioterkaa

ይሄ ፎቶግራር ትግራይ ውስጥ አንድ ታዳጊ ከውሻው ጋር በግዙፍ ቦንብ ላይ ተቀምጦ የሚያሳይ ልብ ሰባሪ ፎቶ ነው። በፈረንጆቹ አቆጣጠር በ1991 በጣልያናዊው ዳሪዮ ሚቲዲሪ የተነሳና "በአፍሪካ ምርጡ ፎ
ይሄ ፎቶግራር ትግራይ ውስጥ አንድ ታዳጊ ከውሻው ጋር በግዙፍ ቦንብ ላይ ተቀምጦ የሚያሳይ ልብ ሰባሪ ፎቶ ነው። በፈረንጆቹ አቆጣጠር በ1991 በጣልያናዊው ዳሪዮ ሚቲዲሪ የተነሳና "በአፍሪካ ምርጡ ፎቶግራፍ" ተብሎ የተወደሰለት ስራው ነው። መማር ለሚፈልግ ብዙ የምንማርበት ታሪክ ሞልቶናል። "በጦርነት ውስጥ ማንም አሸናፊ የለም!!!" @ethioterkaa @ethioterkaa @ethioterkaa

አያ ሙሌ ቁጭ ካለበት ሱቅ የተጋበዛትን ኮካ ኮላ ለባለሱቁ ትቀመጥልኝ ብሎ ይሰጠዋል። ባለሱቁም ኮካኮላዋን ወደ ሳጥኑ ሳይሆን መደርደሪያ ላይ ያስቀምጣታል። አያ ሙሌ ከአንድ ወር በላይ ቆይቶ ወደዚህች
አያ ሙሌ ቁጭ ካለበት ሱቅ የተጋበዛትን ኮካ ኮላ ለባለሱቁ ትቀመጥልኝ ብሎ ይሰጠዋል። ባለሱቁም ኮካኮላዋን ወደ ሳጥኑ ሳይሆን መደርደሪያ ላይ ያስቀምጣታል። አያ ሙሌ ከአንድ ወር በላይ ቆይቶ ወደዚህች ሱቅ ሲመለስ ባለሱቁ "አያ ሙሌ አስቀምጥልኝ ያልካት ኮካ ኮላ አለች በማለት ከመደርደሪያው ላይ አንስቶ ይሰጠዋል። አያ ሙሌ ተገርሞ ብቻ ዝም አላለም። እንዲህ ሲል ነበር የልቡን ምኞት ጭምር የተናገረው:— " ለአንተ ነበር ሃገርን አደራ መስጠት " ሱራፌል አየለ እንደከተበው። @ethioterkaa @ethioterkaa @ethioterkaa

አያ ሙሌ ቁጭ ካለበት ሱቅ የተጋበዛትን ኮካ ኮላ ለባለሱቁ ትቀመጥልኝ ብሎ ይሰጠዋል። ባለሱቁም ኮካኮላዋን ወደ ሳጥኑ ሳይሆን መደርደሪያ ላይ ያስቀምጣታል። አያ ሙሌ ከአንድ ወር በላይ ቆይቶ ወደዚህች ሱቅ ሲመለስ ባለሱቁ "አያ ሙሌ አስቀምጥልኝ ያልካት ኮካ ኮላ አለች በማለት ከመደርደሪያው ላይ አንስቶ ይሰጠዋል። አያ ሙሌ ተገርሞ ብቻ ዝም አላለም። እንዲህ ሲል ነበር የልቡን ምኞት ጭምር የተናገረው:— " ለአንተ ነበር ሃገርን አደራ መስጠት " ሱራፌል አየለ እንደከተበው። @ethioterkaa @ethioterkaa @ethioterkaa

አብርሃም ሊንከን አሜሪካ አለን ከምትላቸው  አንዱ፤ ምናልባትም የመጀመሪያው ነው።  ኘሬዝዳንቱ ከአንባቢነቱ በተጨማሪ በቀልድ እና ጨዋታ አዋቂነቱ ይታወቃል። ከሰማኋቸው ጨዋታዎች ሁለቱ፦ 1- 'አንድ ቀን ለሴናተሮች ሲያወራ ይኸን ታሪክ ብሏቸዋል። አሉ' "በድሮ ጊዜ አንድ ንጉስ ነበር። አደን ለመውጣት ብሎ ሚኒስትሮችን 'ዛሬ ዝናብ ይዘንባል አይዘንብም?' ብሎ ጠየቃቸው። እነሱም 'ንጉስ ሆይ ዛሬ አይዘንብም፤ የሰማዩን ጥራት ይመልከቱ።' አሏቸው። ንጉሱም እነሱን ሰምቶ፤ ለአደን ወጣ። እየሄዱ እያለ አንደ ገበሬ አህያ ላይ አህል ጭኖ ይመጣል። ገበሬውም "ንጉስ ሆይ፤ ዛሬ አይሄዱ፤ ዝናብ ይዘንባል።" ሲል ገአላቸው። ማስጠንቀቅያውን ከቁብ ሳይቆጥሩ ቸላ ብለው አለፉ። በሚገርም ሁኔታ ሀይለኛ ዝናብ ዘንቦ ንጉሱን አበሰበሳቸው። ከዚያ ንጉሱ ቤት መጥቶ ገበሬውን ጥሩልኝ አሉ። ገበሬው ሲመጣ "እንዴት እንደሚዘንብ አወቅክ?" "እኔ አላወቅኩም ንጉስ ሆይ። አህያዬ ናት ያወቀችው።" "እንዴት ?" አሉ ንጉሱ። "አህያዬ ሁሌም ዝናብ ሲመጣ ጆሮዋን ታቆምና ወደ ቤት ትገሰግሳለች።" አሉ። ንጉሱም ሁሉን ሚኒስተሮችን አባርሮ አህያዋን ሚኒስተር አረገ" አለ ሊንከን። ከዚያ በመቀጠል፦ "የዛያኔ ነው ንጉስ ትልቅ ስህተት የተሳሳቱት" አላቸው። ሴናተሮች ግራ በመጋባት "እንዴት?" አሉ። "ከዚያ በኋላ ነዋ አህያዎቹ ሁሉ ሚኒስተር መሆን የጀመሩት።" 2- በ1858 አብርሃም ሊንከን ከስቲፈን ዳግላስ ጋር በአሜሪካ ም/ቤት የኢሊኖይስን መቀመጫ ለማግኘት ፓርቲዉን ወክሎ በተወዳደረበት ወቅት ዳግላስ ስለ ሊንከን ሲናገር ፦ "ይህን ሰው መጀመሪያ የማዉቀዉ ዉስኪ ቀጂ ሆኖ ነው"  አለው። ይኸን የሰማው ሊንከን፦ "አሁን ዳግላስ የተናገረው ሁሉ እዉነት ነው። በግሮሰሪ ዉስጥ ዉስኪ ሲጋራና የመሳሰሉትን እየሸጥኩኝ እዚህ ደርሻለሁ። ስለዚያ ጊዜ የማስታዉሰዉ ሚስተር ዳግላስ በዉስኪ ቤቱ ደንበኛዬ ከነበሩት ሰዎች ዋነኛው ነው። በተደጋጋሚ ጊዜያትም እኔ በባንኮኒዉ ውስጥ ቁሜ  ለዳግላስ ዉስኪ እቀዳለት ነበር። የአሁኑ ልዩነታችን ግን እኔ ዉስኪ የመቅዳት ስራዬን ትቼ ከባንኮኒዉ  ስወጣ ዳግላስ ግን አሁንም ዉስኪ የመጠጣቱን ነገር አጠናክሮ ከባንኮኒዉ ላይ አለመላቀቁ ነው።" ብሏል። ሊንከን ቀልዶቹ አስተማሪና ትምህርት አዘል እንደሆኑ ብዙዎች ይመሰክሩለታል። ለተቺዎቹና ለተሳዳቢዎቹ በቀልድ መልክ ሸንቆጥ ማድረግ የሚቀናው መሪ እንደነበር ይነገርለታል። የአህያዋ ታሪክ የኛ(የኢትዮጵያ) ናት የሚሉ አሉ። በርግጥ የኛ ብትሆን የበለጠ ደስ ይለኛል። ግን ጨዋታውን ብቻ አንብቡና 'ባለቤትነቷን' አጣርቼ አጋራለሁ። @ethioterkaa @ethioterkaa @ethioterkaa

አብርሃም ሊንከን አሜሪካ አለን ከምትላቸው አንዱ፤ ምናልባትም የመጀመሪያው ነው። ኘሬዝዳንቱ ከአንባቢነቱ በተጨማሪ በቀልድ እና ጨዋታ አዋቂነቱ ይታወቃል። ከሰማኋቸው ጨዋታዎች ሁለቱ፦ 1- 'አንድ ቀን ለሴናተሮች ሲያወራ ይኸን ታሪክ ብሏቸዋል። አሉ' "በድሮ ጊዜ አንድ ንጉስ ነበር። አደን ለመውጣት ብሎ ሚኒስትሮችን 'ዛሬ ዝናብ ይዘንባል አይዘንብም?' ብሎ ጠየቃቸው። እነሱም 'ንጉስ ሆይ ዛሬ አይዘንብም፤ የሰማዩን ጥራት ይመልከቱ።' አሏቸው። ንጉሱም እነሱን ሰምቶ፤ ለአደን ወጣ። እየሄዱ እያለ አንደ ገበሬ አህያ ላይ አህል ጭኖ ይመጣል። ገበሬውም "ንጉስ ሆይ፤ ዛሬ አይሄዱ፤ ዝናብ ይዘንባል።" ሲል ገአላቸው። ማስጠንቀቅያውን ከቁብ ሳይቆጥሩ ቸላ ብለው አለፉ። በሚገርም ሁኔታ ሀይለኛ ዝናብ ዘንቦ ንጉሱን አበሰበሳቸው። ከዚያ ንጉሱ ቤት መጥቶ ገበሬውን ጥሩልኝ አሉ። ገበሬው ሲመጣ "እንዴት እንደሚዘንብ አወቅክ?" "እኔ አላወቅኩም ንጉስ ሆይ። አህያዬ ናት ያወቀችው።" "እንዴት ?" አሉ ንጉሱ። "አህያዬ ሁሌም ዝናብ ሲመጣ ጆሮዋን ታቆምና ወደ ቤት ትገሰግሳለች።" አሉ። ንጉሱም ሁሉን ሚኒስተሮችን አባርሮ አህያዋን ሚኒስተር አረገ" አለ ሊንከን። ከዚያ በመቀጠል፦ "የዛያኔ ነው ንጉስ ትልቅ ስህተት የተሳሳቱት" አላቸው። ሴናተሮች ግራ በመጋባት "እንዴት?" አሉ። "ከዚያ በኋላ ነዋ አህያዎቹ ሁሉ ሚኒስተር መሆን የጀመሩት።" 2- በ1858 አብርሃም ሊንከን ከስቲፈን ዳግላስ ጋር በአሜሪካ ም/ቤት የኢሊኖይስን መቀመጫ ለማግኘት ፓርቲዉን ወክሎ በተወዳደረበት ወቅት ዳግላስ ስለ ሊንከን ሲናገር ፦ "ይህን ሰው መጀመሪያ የማዉቀዉ ዉስኪ ቀጂ ሆኖ ነው" አለው። ይኸን የሰማው ሊንከን፦ "አሁን ዳግላስ የተናገረው ሁሉ እዉነት ነው። በግሮሰሪ ዉስጥ ዉስኪ ሲጋራና የመሳሰሉትን እየሸጥኩኝ እዚህ ደርሻለሁ። ስለዚያ ጊዜ የማስታዉሰዉ ሚስተር ዳግላስ በዉስኪ ቤቱ ደንበኛዬ ከነበሩት ሰዎች ዋነኛው ነው። በተደጋጋሚ ጊዜያትም እኔ በባንኮኒዉ ውስጥ ቁሜ ለዳግላስ ዉስኪ እቀዳለት ነበር። የአሁኑ ልዩነታችን ግን እኔ ዉስኪ የመቅዳት ስራዬን ትቼ ከባንኮኒዉ ስወጣ ዳግላስ ግን አሁንም ዉስኪ የመጠጣቱን ነገር አጠናክሮ ከባንኮኒዉ ላይ አለመላቀቁ ነው።" ብሏል። ሊንከን ቀልዶቹ አስተማሪና ትምህርት አዘል እንደሆኑ ብዙዎች ይመሰክሩለታል። ለተቺዎቹና ለተሳዳቢዎቹ በቀልድ መልክ ሸንቆጥ ማድረግ የሚቀናው መሪ እንደነበር ይነገርለታል። የአህያዋ ታሪክ የኛ(የኢትዮጵያ) ናት የሚሉ አሉ። በርግጥ የኛ ብትሆን የበለጠ ደስ ይለኛል። ግን ጨዋታውን ብቻ አንብቡና 'ባለቤትነቷን' አጣርቼ አጋራለሁ። @ethioterkaa @ethioterkaa @ethioterkaa

#ከህይወቴ ተምሬያለው 💥. አንዳንድ ሰው እንዲያፈቅራችሁ ማድረግ እንደማይቻል ተምሬያለሁ ፤ ማድረግ የሚቻለው ጥሩ አፍቃሪ መሆን ብቻ ነው ። 💥.ብስለት የሚመጣው ከሚያጋጥሙን ተሞክሮዎች ዓይነትና
#ከህይወቴ ተምሬያለው 💥. አንዳንድ ሰው እንዲያፈቅራችሁ ማድረግ እንደማይቻል ተምሬያለሁ ፤ ማድረግ የሚቻለው ጥሩ አፍቃሪ መሆን ብቻ ነው ። 💥.ብስለት የሚመጣው ከሚያጋጥሙን ተሞክሮዎች ዓይነትና ከተሞክሮዎቹ ከቀሰምናቸው ትምህርቶች እንጅ ካከበርናቸው የልደት በዓሎች ብዛት እንዳልሆነ ተምሬያለሁ ። 💥.እንዳንዴ የቱንም ያህል ለሌሎች ብጨነቅ እና ግድ ብሰጥ አንዳንዴ አንዳንዶች በመልሱ ግድ ላይሰጡ እንደሚችሉ ተምሬያለሁ ። 💥.ጓደኞች ምንም ያህል ጥሩ ቢሆን አልፎ አልፎ ማስቀየማቸው እንደማይቀር ተምሬያለሁ ። ባስቀየምናቸው ሰዎች ይቅር መባል በቂ ያለመሆኑንና ራስንም ይቅር ማለትም እንደሚያስፈልግ ተምርያለሁ ። 💥.መታመንን ለመግንባት  ዘመናት እንደሚያስፈልግ ፤ ለማውደም ግን ሰከንዶች ብቻ እንደሚበቁ ተምሬያለሁ ። 💥.አንዳንድ ጊዜ ተንሸራትተህ ስትወድቅ ይረጋግጡኛል ብለህ የምትጠብቃቸውና የምትፈራቸው ሰዎች ብድግ አድርግው በማንሳት እንደሚያስገርሙህ ተምሬያለሁ ። 💥.እውነተኛ ጓደኝነት እንደዚህም እውነተኛ ፍቅር በቦታ ርቀት ሳይግደብ ማበብ መፍካቱ እንደማይቆም ተምሬያለሁ ። 💥.በአስተዋይነት "እምቢ" ማለት ሁልጊዜም የንፉግነት ምልክት ያለመሆኑን “እሺ” ማለትም ሁልጊዜ ምግባረ ሰናይነትን እንደማያሳይ ተገንዝቢያለሁ ። 💥.ራስን ከጥፋተኝነት ስሜት እንዲሁም ከጥላቻ የምንገላገልበት ብቸኛ መንገድም የአለፈውን ጊዜ ረስተን ከአሁን ጋር እርቅ ማድረግ ስንጀምር እንደሆነ ተምርያለው ። @ethioterkaa @ethioterkaa @ethioterkaa

#ከህይወቴ ተምሬያለው 💥. አንዳንድ ሰው እንዲያፈቅራችሁ ማድረግ እንደማይቻል ተምሬያለሁ ፤ ማድረግ የሚቻለው ጥሩ አፍቃሪ መሆን ብቻ ነው ። 💥.ብስለት የሚመጣው ከሚያጋጥሙን ተሞክሮዎች ዓይነትና ከተሞክሮዎቹ ከቀሰምናቸው ትምህርቶች እንጅ ካከበርናቸው የልደት በዓሎች ብዛት እንዳልሆነ ተምሬያለሁ ። 💥.እንዳንዴ የቱንም ያህል ለሌሎች ብጨነቅ እና ግድ ብሰጥ አንዳንዴ አንዳንዶች በመልሱ ግድ ላይሰጡ እንደሚችሉ ተምሬያለሁ ። 💥.ጓደኞች ምንም ያህል ጥሩ ቢሆን አልፎ አልፎ ማስቀየማቸው እንደማይቀር ተምሬያለሁ ። ባስቀየምናቸው ሰዎች ይቅር መባል በቂ ያለመሆኑንና ራስንም ይቅር ማለትም እንደሚያስፈልግ ተምርያለሁ ። 💥.መታመንን ለመግንባት  ዘመናት እንደሚያስፈልግ ፤ ለማውደም ግን ሰከንዶች ብቻ እንደሚበቁ ተምሬያለሁ ። 💥.አንዳንድ ጊዜ ተንሸራትተህ ስትወድቅ ይረጋግጡኛል ብለህ የምትጠብቃቸውና የምትፈራቸው ሰዎች ብድግ አድርግው በማንሳት እንደሚያስገርሙህ ተምሬያለሁ ። 💥.እውነተኛ ጓደኝነት እንደዚህም እውነተኛ ፍቅር በቦታ ርቀት ሳይግደብ ማበብ መፍካቱ እንደማይቆም ተምሬያለሁ ። 💥.በአስተዋይነት "እምቢ" ማለት ሁልጊዜም የንፉግነት ምልክት ያለመሆኑን “እሺ” ማለትም ሁልጊዜ ምግባረ ሰናይነትን እንደማያሳይ ተገንዝቢያለሁ ። 💥.ራስን ከጥፋተኝነት ስሜት እንዲሁም ከጥላቻ የምንገላገልበት ብቸኛ መንገድም የአለፈውን ጊዜ ረስተን ከአሁን ጋር እርቅ ማድረግ ስንጀምር እንደሆነ ተምርያለው ።

ጠያቂ፦ ስለ ውሻ ስትፅፍ ውሻ ሆነህ የምታውቅ ይመስላል። ውሻን እንዴት ይህን ያህል ልትረዳው ቻልክ? አዳም ረታ፦ "ውሻ ሆኜ አውቃለሁ። እግር አንስቶ መሽናቱ ሲደክመኝ ተመለስኩ" ... ጠያቂ፦ መፅሐ
ጠያቂ፦ ስለ ውሻ ስትፅፍ ውሻ ሆነህ የምታውቅ ይመስላል። ውሻን እንዴት ይህን ያህል ልትረዳው ቻልክ? አዳም ረታ፦ "ውሻ ሆኜ አውቃለሁ። እግር አንስቶ መሽናቱ ሲደክመኝ ተመለስኩ" ... ጠያቂ፦ መፅሐፍህ  የአጫጭር ታሪክ ስብስብ ለምን ሆነ? ያላለቀ ይመስላል አለማየሁ ገላጋይ፦ ሰው አጭር ስለሆነ አላለቀም ይባላል ወይ? @ethioterkaa @ethioterkaa