en
Feedback
ኢትዮ መፅሀፍት እና ትረካ

ኢትዮ መፅሀፍት እና ትረካ

Open in Telegram
776
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
+4430 days
Posts Archive
ይህ ቀዝቃዛ ዝናብ ገላሽን ይንካና @ethioterkaa @ethioterkaa 💚💛❤️

ድንገት መንገድ ላይ ስንገናኝ አይን ለአይን ተጋጨን።በቆምኩበት ደርቄ ቀረሁ። ምን ያክል እንደተጎዳች አፏን ተክቶ ሁኔታዋ ይናገራል።ፍጹም ተቀይራ ሌላሰው መስላለች። እብደቷ የሷነቷ ግማሽ ክፍል ነበር።ይሄ ጭምትነትና ጉስቁልና የምን ውጤት እንደሆነ ሁለታችንም እናውቃለን።አካሏን ባገኘውም የጎደለ ነገር እንዳለ ተሰማኝ። "እንዴት ነሽ!?" (በሀፍረት ተሸማቅቄ አይኔን መሬት ላይ ተክየ) ምንም መልስ የለም።መጠየቄን ከቁብ አልቆጠረችውም።አይኔን እየተከተለች ባይኖቿ አሳደደቻቸው። የበደሌን መጠን ስለማውቀው ዝም ስትል ቅጣቴን ልታከብደው እንደሆነ ተሰማኝ።ቃላቶች የበደልን መጠን ይናገራሉ። ዝምታ ግን ልክ የለውም።የሆነ ነገር ብትለኝ ተመኘሁ። ያ ውበቷ፣አፈር አይንካው የተባለለት ገላዋ፣ ህይወት ያለው ሳቋ ሁሉም እንዳልነበር ሆኖ የሀዘን ድባብ ወርሷታል። አንድ ቅጽበት እንዴት የሰውን እጣ ፈንታ በዚህ መልኩ ይቀይራል። ....... ያች ቅጽበት መደፈሯን ስሰማ በገላዋ ላይ የተመሰረተው ፍቅሬ እንደ አሸዋ ክምር ልቤ ውስጥ ሲናድ ተሰማኝ። ስለተበደለች በደልኳት፤ስለተከፋች አሳዘንኳት።ቁስሏ ላይ እንጨት ሰደድኩ። ከጉዳቷ በላይ ለኔ ለማስረዳት ስትለፋ አመናጭቄ ማባረሬ ጎዳት።የሷ ጥፋት ምኑ ላይ እንደሆነ ሳላውቅ በጭፍን ሸሸኋት።የሰገድኩለት ገላዋን ለመንካት ተጠየፍኩ።አይኗን ማየት አስጠላኝ። ቀያፋ'ው ማንነቴ ከፍቅሬ ጉባኤ አውግዞ ለያት። ከጠላቶቿ ጋር በማ'በር የመኖር ፍላጎቷን አጨለምኩት። "አምሮብሀል" (የአለት ድንጋይ አናቴ ላይ ያረፈብኝ ያህል ተሰማኝ።) 'አንችም አምሮብሻል' ብየ አጸፋውን እንደማልመልስላት እያወቀች ለምን እንደዚህ ትላለች? ማማሯን፣ውበቷ፣መልኳና ቁንጅናዋን የቀማኋት ልጅ 'አምሮብሀል' ስትል ከመስማት በላይ ምን በቀል አለ። ምን አፍ አለኝ።ምንስ መልስ አለኝ።ዝም አልኩ። ቀጠለች፦ "አገባህ አሉ።" (በድንጋጤና በሀፍረት መሬቱ ላይ ከማፍጠጤ የተነሳ መሬት በአይን የሚቆፈር ቢሆን ገብቸ ተደብቄበት ነበር) 'አገባሻለሁ' እያልኩ ሴትነቷን እንደ አገዳ የመጠጥኳት ልጅ ማግባትቴን እንዳወቀች ስትነግረኝ ከዚህ በላይ ልብ ሰባሪ ነገር ምን አለ?ላለማግባቷ ምክንያት መሆኔን መናገሯ ነው። ጥያቄውን ከነመልሱ እየነገረችኝ ምን ብየ እመልሳለሁ። የምጠይቀኝ በመልሴ ውስጥ የክህደቴን መጠን ልታሳውቀኝ ፈልጋ እንደሆነ ገባኝ። ቀጠለች በቀሏን፦ "ህይወት እንዴት እያደረገህ ነው።"(ሁኔታዋ ላይ መረጋጋት ይታያል ከተገናኘን ጀምሮ ለውጥ አላየሁባትም) ተቀበልኩ በቀሌን። የነጠኳት ህይወቷን፤የቀማኋት እሷነቷን፤ ያጨለምኩት ተስፋዋን፤የከዳሁት እምነቷን ልታስታውሰኝ ፈልጋ እንጅ ስለህይወት ያነሳችው ውጫዊ ስኬት ላይ እንዳለሁማ ሰምታለች።ውስጣዊ ሰላም እንደሌለኝ ማን በነገራት። የቀማኋትን ነገር እያነሳች እኔ እንዳለኝ ስትነግረኝ የበቀሏን ርቀት የበደሌን ጥንካሬ አሳየችኝ። ለበቀል ጦር አልተጠቀመችም፤ጥይት አላባከነችም።ሰው እንዴት በቃል ብቻ ከጦር በላይ ይዋጋል፤ከጥይት በላይ ያቆስላል። ለበቀል ቃላት መጠቀሟ ከመሳሪያ ሊያመልጥ ወይ ሊተርፍ ይችላል ብላ አስባ ይሆን? በቃላት አሳደደችኝ።ከህሊና ወዴት ይሸሻል፤ከራስስ ወዴት ማምለጥ ይቻላል።የወዳጅ በሚመስሉ ደና ቃላት ሀጢኣት ሳትገባ የራሴ እስረኛ አድርጋ አስቀመጠችኝ።ለበደሌ ቢያንስም ቅጣቴ በሌላ ቢቀየር ተመኘሁ። የ'በደለን ሰው የህሊና እረፍት አሳጥቶ እራሱን እድሜ ልክ እንዲቀጣ ከማድረግ በላይ ምን በቀል አለ። ....... 'ሄሎ ሄሎ' የሚል ሀይለኛ ድምጽ ካጠገባችን አንባረቀ።ሁለታችንም ከሀሳብ ወጥተን ወደ ሰውየው ዞርን። ስልኩ ላይ ያለው የገንዘብ መጠን አነስተኛ ሆኖ ማውራት እንደማያስችለው ስላወቀ ከሸቀጥ አዟሪወች ካርድ ገዝቶ ስልኩ ጋር ሞላ። ልክ ስልኩ ጋር በትክክል እንደተሞላ የሚያሳውቀው መልዕክት እንደደረሰው ሰውየው ካርዱን ጭብጥ አድርጎ ቆሻሻ ማጠራቀሚያ ላይ ጣለው። አይኗን ከሰውየው ላይ አንስታ ወደኔ አዞረቻቸው። "ለምን ይመስልሀል ሰውየው ካርዱን ዝም ብሎ መጣል ሲችል ጭብጥ አድርጎ ያኮማተረው?" "አርቆ ለመጣል አስቦ መሰለኝ ማለቴ ቆሻሻ መጣያው ጋር እንዲደርስለት"(ምን እንዳሰበች ግራ ስለገባኝ በፍርሀት መንፈስ መለስኩኝ) "አየህ አንተ እንደዛ ነህ።የኔና የካርዱ እጣ ፋንታ ተመሳሳይ ነው።ሁለታችንም መ'ጣል!..." (እንባዋ እየተናነቃት ቃላቶቿን ሲያግዳቸው ታወቀኝ።) ዝም ብላ ማዶ ማዶ እያየች ቆየች። አይኖቿ ወደ ውጭ ይዩ እንጅ ልቧ ግን ወደ ውስጥ ነበር የሚያየው።አዕምሮዋ ውስጥ ያስቀመጠችውን በደሌን ተመለከተቻቸው። አስፈሯት መሰል አይኖቿን ገጥማ እንባዋን ጨመቀችው።ተዘረገፉ። "...ያንተ እንድሆን በውብ ቃላቶች ገዛሀኝ።ተጠቀምክብኝ።እንደማርባ ስታውቅ እንዳልዘረጋ አድርገህ ጨበጥከኝ፤በሰው ፊት አኮማተርከኝ!..."(ትኩስ እንባ ከአይኗ እየወጣ ጉንጯ ላይ ተንከባሎ አዳፋ ጨርቋ ላይ ያርፋል።) እንባየ ሳይታወቀኝ መፍሰስ ጀምሯል። የስራየን ውጤት ምድር ላይ አየሁት። ለዚች ነፍስ ሰይጣኗ ከኔ በላይ ማን ሊሆን?ሲኦሏስ እኔ ካደረስኩባት ስቃይ በላይ ምን ሊሆን!? "...እንደማፈቅርህ ነገርኩህ፤ጉዳቴን ሳላስታምም ወደጎን ብየ ተማፀንኩህ፤ ከብዙወች አስበልጨ እንደወደድኩህ እያወክ ተውከኝ፤ባንተ ምክንያት ዋጋ እንደከፈልኩ እያወክ..." (ለመናገር እየከበዳት እያንገሸገሻት እያረፈች ነው ምታወራ።) ፍርዱን እንደሚቀበል እስረኛ ደርቄ ቆሜያለሁ። "አንተ ግን!አንተ ግን!እ!...ፍቅራችን ከምንም ሳትቆጥር...እኔንም እንደ ካርዱ አርቀህ ቆሻሻ ውስጥ ወረወርከኝ!" "አሁን የሆንኩትን ለመሆኔ ያኔ የሆንክብኝ ከበቂ በላይ ነበር!የምኖረው ከሞቴ በላይ ህይወቴ ስለሚቀጣህ ነው!" (ፊቷን በጨርቋ እየጠረገች።) ምናለ ተስፋ ብሰጣት።አብሬሽ ነኝ አታስቢ ከጎንሽ ነኝ ብላት።ልጅነቷን ማጣቷን ከጥፋት ቆጥሬ ለውድቀቷ ገደል ያበጀሁ ለምን ነው? የተጎዳችው፣የተሰቃየችው፣ የተንገላታችው...እሷ ሁና ሳለ የኔ እንደዛ መሆን ምን ይሉታል።መውደዴ ቢቀር መጥላት ለምን አስፈለገኝ፤ማቀፌ ቢቀር መግፋቴ ለምን? መሸሸጊያ ይሆነናል ያልነው ሰው ካሳደደን፤ ይጠግነናል ያልነው ሰው ከሰበረን፤ ይፈውሰናል ያልነው ሰው ካሳመመን፤የኔ ያልነው ሰው ከጠላን በህይወት ለመቆየት ምን ምክንያት ይኖረናል።የስቃይ ዳሩ ከዚህ በላይ ምን ሊሆን። በወዳጅ አለመታመን በጥላት ከመከዳት የበለጠ ያማል! በደሌን በጥፊዋና በስድቧ ተሸሽጌ እንዳላመልጠው ሳትሰድበኝ፣ሳትመታኝ ቀረች።ከተበዳይ የሚሰነዘር በትር ለበዳይ ሸክም ማቅለያ ይሆናል። እንደ ጨው ሀውልት ተገትሬ በቆምኩበት ከነ'ንጽህናዋ ለፀፀት ጥላኝ ሄደች። እንዳልከተላት በደሌ አስሮ ያዘኝ። ከሀጢአቴ ጋር ብቻየን ቀረሁ። @ethioterkaa @ethioterkaa @ethioterkaa

"...አትደንግጭ።ያኔ ገላሽ ሌላ ሲያቅፍ፤ያኔ ከኔ ውጭ አልጋ ተጋርተሽ አንሶላ ስትጋፈፊ። አወ! ያኔ ነው የፈታሁሽ።መቸም ፈጣሪ አይኮንነኝም። መጽሐፉም በዝሙት ምክንያት ካልሆነ ሚስቱን አይፍታ ስለሚል።እና መፍታት አያንሰኝም?እኔ ላይ መች ገላሽ ብቻ ማገጠብን?" "እ...እ...እና ይህን ሁሉ እያወክ ነው አብረኸኝ የኖርከው?(ተንተባተበች። አይኗን ስታርገበግበው እንባዋ ጉንጫ ላይ እየተንከባለለ ይረግፋል) "አወ!አንች ግን ከድህነቴና ከችግሬ ጋር መኖር ሰልችቶሻል።መቋቋም አልችልም ልሂድ ብለሻል!ያውልሽ በሩ፤ይሄውልሽ ቤቱ እንደፈለግሽ።መቆየትም መሄድም ትችያለሽ ምርጫው ያንች ነው።አሁንም የለመንኩሽ ሄደሽ እንዳትጎጅ፤ቤት ውስጥ ቆይ ብየ እንጅ ልቤ ውስጥ ካስወጣሁሽ ቆይቻለሁ" (አይኖቿ ቀልተው ፊቷ በእንባ እየታጠበ ቀስ ብላ እየተጠጋችኝ በእጇ ወደኔ እየጠቆመች) "ቀጣኸኝ!መጥፎ ሰው ነህ!ያኔ ያየኸኝ ጊዜ ብትነግረኝ፤ያኔ ብትወቅሰኝ፤ የፈለከውን ብታደርገኝ ምን ነበረበት።ቀን በቀን እየዋሸዉህ እንደሆነ እያወክ እንደማታውቅ ሆነህ ሌላ ውሸት እንድጨምር አደረከኝ።ክህደቴን እንዳላየህ አልፈህ እንዲያድግ አደረግከው።ልታስቆመኝ ትችል ነበር። አረመኔ ነህ!"(እጆቿን ደረቴ ላይ አፈራርቃ እያሳረፈች) (እጆቿን በእጆቸ አጣብቄ ይዠ ወደ ፊቷ እየተጠጋሁ) "አሀ!እኔ ነኝ ጥፋተኛው?እ?እንደዛ ነው?እንኳን ያኔ አሁንም እኮ ላስቆምሽ አልቻልኩም!ቀድሞውኑ ልብሽ ሄዶ ገላሽኝ ባስቀረው ምን ዋጋ አለው።የዋሸሽኝና የከዳሽኝ እኮ ስታደርጊው አይደለም። መጀመሪያውኑ ይሄንን ስታስቢ እንጅ!" (ፊቴ በእንባና በላብ ራሰ ንዴቴን መቆጣጠር አቃተኝ) "ግን እንዴት ስቃዮን ቻልከው?አትወደኝም ነበር እንዴ?"(አፍንጫና ፊቷን እየጠረገች ሶፋው ላይ ራሷን ይዛ ተቀመጠች) "ስለምወድሽማ ነው የቀለለኝ።አየሽ የምትወጅው ሰው ሊጎዳሽ የሚችለው አንዴ ነው።እሱም መጀመሪያ ላይ እምነትሽን ሲሰብር።ከዛ በኋላ በቃ ምንም አይሰማሽ። ልክ መጀመሪያ ላይ ከባድ በትር ያረፈበት ሰው ራሱን ስቶ ከዛ በኃላ የሚያርፍበትን በትር እንደማይሰማው ሁላ።" (ወደ ሶፋው ሄጀ ፊት ለፊቷ ተቀጥኩ። አንገቷን ደፍታ አይኗን መሬት ላይ ተክላ) "ያለፈውን መመለስ አልችልም። ወደፊትህን ማበላሸት አልፈልግም። ባየሁህ ቁጥር ክህደቴን እያሰብኩ እንዴት እኖራለሁ" (ግንባሬን በእጀ እያፍተለተልኩ) "የታገስነው የመሰለንን ሰው እንደታገሰን ስናውቅ፤የቻልነው የመሰለንን ሰው እንደቻለን ስንናውቅ፤የከዳን የመሰለንን ሰው እንደከዳነው ሲገባን፤የበደለን የመሰለንን ሰው እንደበደልነው ስንረዳ፤ያቆሰለን የመሰለንን ሰው እንዳቆሰልነው ስንደርስበት ምን ይሰማን ይሆን?ስሜቱን ላንች ትቸዋለሁ።ለኔ የ'መካድ፣ የ'መተው፣ የመረሳት፣ የ'መሰልቸት የእነዚህ ስሜት ይበቃኛል። ሌላ ስሜት ማወቅ አልፈልግም።" (ፊቴ በፀፀት እየገረፋት ቀና ብላ አታየኝም) "ይቅርታህን ማግኘት አልችልም።እኔም አፌን ሞልቸ አልጠይቅህም።የትኛውም ቅጣት ለኔ በቂ አይደለም።" "ጥፋትሽን ማወቅ ላንች ከቅጣት በላይ ነው።ወዳጅን ከበመደል በላይ ምን ቅጣት አለ።..." (ፊት ለፊቷ ጠጋ ብየ በርከክ አልኩ። እጇን በእጀ ያዝኩት) "...ያረግሽኝን እያነሳሁ አልወቅስሽም። እውነቱን ለመናገር መርሳት አልችልም። ልርሳ ብልም የሚሆን ነገር አይደለም። ግን አይዞሽ እተወዋለሁ።ይቅር ምን ይሆናል።ከዛ በላይ ላጣሽ አይደል። ታዲያ።ልሂድ ካልሽ ስትሄጅ እኔ ተጎድቸ ከሱ ጋር ያለውን የቆይታ ጊዜሽን ላረዝመው እችላለሁ።ደስ የሚያሰኝሽ ከሆነ።" "እባክህ ተው እንደዛ አትበል!ደግሞ እጀን ልቀቀኝ የረከስኩ ነኝ።" "እኔ አሁን በሆንሽው አለካሽም።ቀን ጥሎሽ እንጅ ይች አንች አይደለሽም። አንች እንዲህ አልነበርሽም።በአሁኗ አንች አሻግሬ ያኔ ሳውቅሽ የነበርሽውን አንችን ነው የማየው። ይህ ያንች መጥፎ ጊዜ ነው። የተጋባነው ይህን ጊዜ ለማለፍ እንደሆነ ነገሬሽ ነበር።" (በእጆቸ ሙሉ ፊቷን ጠረግኩት።ቀና ብላ አየችኝ።ሁለታችንም አለቀስን) "አንተ የተሳሳትክ በመሰለኝ ጊዜ ይህን ስትነግረኝ መች ሰማውህ!አሁን 'እውነትክን'ነው ብልህ ይባስ ራስ ወዳድነቴን አታየውም።" (እንባዋ እየተናነቃት ቃላት ማውጣት ተሳናት) "ራስን መውደድ ችግር አይደለም። ችግሩ ራስን ብቻ መውደድ ነው። አንዳንዴ ለምንወዳቸው ሰወች ስንል ራሳችንን መውደድ አለብን።" (ወደራሴ ሳብኳት ወለሉ ላይ ተቀመጥን።) "ለምን ነው እንደዚህ ጥሩ ምትሆንልኝ?" "ፍቅር መርጦ መውደድ አይደለም የሚወዱት ሰው ያለውን ነገር መውደድ እንጅ።ከነ እንከን መቀበል።ጉድለትን አለመጥላት ነው።አንችም የሆነ ጊዜ ላይ ለኔ እንደዚህ ነበርሽ" (እግሮቻችን ተገናኙ ተጠጋጋን) "ደግሞ አትርሽ አዲስ የሚባል ፀጉር የለም። አዲስ ያልሽው ወይም የመሰለሽ ከድሮው ተቆርጦ የቀረው ነው።" "ልክ ነህ!እባክህ ከበፊቱ ጋር እንዳረጅ ፍቀድልኝ" "አዲስ ለማብቀል የበፊቱን ልትላጭበት የነበረውን ምላጭ ሀሳብ አስቀምጭው።" "አርቄ እንድወረውረው አግዘኝ" "እንዳይመለስ ቆፍረን እንቅበረው።" ብዙ ጊዜ ዝም ያለ ሰው ሁሉ በዳይ፤ የሚጮህ ተበዳይ ነው የሚመስለን። ሊጎዱን ስላልፈለጉ እየተጎዱ የሚኖሩትን መበደላችን ሳያንሰን እንደጎዱን አየነገርን የነሱን ስቃይና የኛኝ በደል እናበዛለን። ስላልነገሩን ያልከፋቸው፤ስላልጮሁ ያልተበደሉ እየመሰሉ ከነሱ ይምጣ ብለው ዝም ያሉን።ነገ እስክንቀየር እየጠበቁ ህመማቸውን ታግሰው ለፍቅራቸው ለትዳራቸው ለልጆቻቸው በየዕለቱ መስዋትነት እየከፈሉ የሚኖሩ ብዙ አሉ። (ክፉን ሀሳብ ቀብረን ፍቅር ዘራን።) እቅፌ ውስጥ አስገባኃት መራራዋን የመድኋኒት ኪኒን በእምነት ውሀ አሟሙቸ ሰውነቴ ጋር አዋሀድኳት። ፈወሰችኝ።እምነቴ ፍቅሬን ከማጣት አዳነኝ።ፍቅሬ ትዳሬን ታደገልኝ። @ethioterkaa @ethioterkaa @ethioterkaa

"መፋታት አለብን"(ከስራ መጥቸ በሩን ከፍቸ ከመግባቴ ቆማ የምጠብቀኝ ሚስቴ) "እንደዛ አትበይ በዚህ ጉዳይ ስንት ጊዜ ተነጋገርን"(በትከሻየ ያንጠለጠልኩትን ቦርሳ ሶፋው ላይ ወርውሬ እያስቀመጥኩ) "ነገርኩህ" "ምክንያትሽ ምንድነው?" "ሰለቻችሁኝ" "እነማን?" "አንተና ችግርህ" "እንደዚህ የምትይው ድህነቴ የኔ ምርጫ ነው?ገንዘብ ባገኝ ጠልቸ ነው?ከሰው በታች መሆን ወድጀ ነው?ቤት መግዛት ስላልፈለኩ ነው?" "ኧረ!እንደዛ ነው?መርጠህ አይደለም¡ልክ ነህ!ካንተ በኋላ ተቀጥረው ባለብዙ ንብረት ባለቤት የሆኑት አንተ ድህነትን ስላልመረጥክ ነው አይደል። በመኪና እስከ ቢሮ የሚሸኙህ የበታች የስራ ባልደረቦችህ የሆኑት አንተ በእግርህ መጓዝ ስለፈለክ አይደለም። በቤቴ ስለማፍር ጓደኞቸን የማልጋብዘው አንተ ቤት መግዛት ስለማትፈልግ አይደለም። ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ ገንዘብ ብታገኝ አትጠላም።እንዴት ድንቅ ነው!"(ወገቧን ይዛ እየተናጠች ትናገራለች) "ታውቂያለሽ እኔ ስራየን እወዳለሁ። ገንዘብም አልጠላም ግን አመጣጡ ይወስነዋል።ከኛ በታች እየኖሩ ፈጣሪያቸውን የሚያመሰግኑ ሰወች ባሉበት እኛ ከነሱ በላይ ሁነን ለምን ፈጣሪን እናማርራለን።"(በድካም ስሜት) "እውነት ነው።ከኛ በታች የሚኖሩ አሉ ግን ደግሞ ከኛ በላይም የሚኖሩ አሉ።እና ለምን ከኛ በላይ እንዳሉት ኑረን ፈጣሪን ይበልጥ አናመሰግነውም?እ?ምን ታስባለህ?"(ንግግሯ ሁሉ ንግግሬ ላይ የተመሰረተ ሹፈት መሰለኝ) "እሽ ምን ጉደለብን?"(እጆቸን እያፍተለተልኩ) "ምን አለንና! ደግሞስ የተሻለ ካለ የሚጠላ ማን አለ!" "የተሻለ ለማግኘት የድሮውን መጣል አስፈላጊ ነው?" "በትክክል።ለራስ አዲስ ፀጉር የሚበቅለው ከተላጨ ብቻ ነው" "ባይላጭም እኮ በእየለቱ ስሩ ላይ አዲስ ፀጉር እየጨመረ ማደጉ አይቀርም" "ግን አዲስ አይደለም።ከድሮው ጋር የተያያዘ ነው።ከድሮ ፀጉር ካልተለየ፤አዲስ ቢቀጥል ምን ዋጋ አለው።የድሮው ፀጉር አዱሱን ፀጉር ስለሚበልጠው ማስረጀቱ አይቀርም። "ግን ማስተዋል ያለብሽ አዲስም ከጊዜ በኃላ ማርጀቱ አይቀርም።" "ከጊዜ በኃላ እስኪያረጅ ራስ በአዲሱ ፀጉር ያጌጥበታል።" "ከዛ አጣፋንታው እንዳሮየው መጣል ይሆናል።" "በሚያሳዝን ሁኔታ መጨረሻቸው አንድ ነው።" "የፀጉሮቹ ብቻ አይደለም።ይዘገያል እንጅ የራስም መጨረሻው እንደ ፀጉር አፈር ውስጥ መቀበር ነው" "ያማ ያጌጡም ያላጌጡም ራሶች እጣፋንታ ነው።ታዲያ አጊጦ ማለፍ አይሻልም ትላለህ?" "ይሁን እንግዲህ።ቀድመሽ ልትሄጅ ወስነሻል ማለት ነው"(ሻንጣዋን እያየሁ) "ምክንያቶችህ እኔን ካንተ ጋር ለማቆየት በቂ አይደሉም" "እስኪ የሚያቆይሽን ምክንያት ንገሪኝ?" "እንደ ጓደኞችህ ሆነህ እንደጓደኞቸ ብታደረገኝ እቆይ ነበር።" "እነሱን እያነሳሽ አታነጻጽሪኝ።ደጋግሜ ነገርኩሽ።የራሴ የሆነ ችግር አለብኝ ለምን ቁስሌን ትነኪያለሽ።ሌላ ሰው ለመሆን በሞከርሽ ቁጥር ራስሽን ታጫለሽ።እኔ እኔ ነኝ።አንችም ራስሽን ነሽ። ጓደኞችሽን አይደለሽም።ሌላ መሆን አንችልም። ገባሽ!"(ከመቀመጫየ እየተነሳሁ) "በቃ ሰለችቶኛል!" "እሽ ወዴት ነው ምትሄጅ?" "አዲስ ፀጉር ጋር" "ስለዚህ አዲስ እንዲበቅል የድሮውን መጣል አስፈላጊ ነው።እና ልትቆርጭኝ ነው?ለኔ ለድሮው ፀጉር ምላጭ አነሳሽ?ግን ከስር አዲስ ተስፋ እያበቀልኩ ነበር።እየለፋሁ ነው።እየጣርኩ ነው።"(የሀዘን ስሜት ወረረኝ) "ጥረትክን እያየሁ ነው።ግን ፍቅር ብቻ ምን ዋጋ አለው።በጣም እንደምወድህ ታውቃለህ።የመጀመሪያም የመጨረሻም ፍቅሬ አንተ ነህ።የትም ብሄድ አንተ የሚተካ አላገኝም።ልቤ አንተ ጋር ነው።" "አትወጅኝም!ብትወጅኝማ ፍቅርሽ ከፍላጎትሽ ሚዛን ይደፋ ነበር።" "ግን እኔ ሴት ነኝ ፈተናወችን ያንተን ያክል መቋቋም አልችልም።ከማንም ማነስ አልፈልግም።ለቤተሰቦቸ መድረስ አለብኝ።" "የተጋባነው በእንደዚህ አይነት ሰዓት ልንደጋገፍ ነበር።ውድቀቴን ተደግፌ ላልፍበሽ ደስታየን ላጋራሽ፤ጭንቀትሽን ልትነግሪኝ ሀዘንሽን ልካፈለው፤ በአብሮነታችን መዶሻ የችግርን ግንብ ልናፈርስ ፤ፍቅራችን ላይ ቆመን ነገን ልናይ ነበር።..." (ላስረዳት ወደሷ እየተጠጋሁ) "...ሳገኝ፣ሲሞላልኝ ያኔማ እንኳን አንች ሚስቴ ሌላ ሰውስ ያደርገው የለ።" "የድሮው ግትር ማንነነትህ አዲስ አንተነትህን ይሸፍነዋል።ምንም ያክል ብትሞክር አንተ አዲስ ልትሆን አትችልም።ብዙ ጠብቄህ ነበር።" "ከጉኔ ብትሆኝ አያቅተኝም ነበር።ብትረጅኝ ለምን እንደዚህ እንደሆነ ስነግርሽ ብትቀበይኝ አይከብደኝም ነበር።ከመቸውም በላይ አሁን ታስፈልጊኛለሽ።" "አንተ ጥሩ ነህ።ላንተ ከኔ የተሻለች ሴት ትገባሀለች።"(የሀዘን ፊት እያሳየችኝ) "የራስሽን ፍላጎት ለኔ አዝነሽ ያደረግሽው በማስመሰል ስህተትሽን ለመሸፈን አትሞክሪ!ፍቅሬን ነጥቀሽ ሀዘኔታሽ አትስጭኝ።የሚያስፈልገኝን ደግሞ አንች አትነግሪኝም!" "ለመሄድ ወስኛለሁ።"(ወደ ሻንጣዋ እየሄደች) "የምችለውን አድርጊያለሁ።ደከመኝ።እጅ ሰጠሁ።ከዚህ በላይ ዕድሌ ጋር የመታገል አቅም የለኝም።"(ተስፋ በቆረጠ ፊት) "እሱን ነው የምልህ።አንተ የምትችለው እስከዚህ ነው።ያ ደግሞ ያንተ ጥፋት አይደለም። ካንተ በላይ መታገል የሚችል ካለ ምን ይደረጋል።"(ሻንጣዋን እያነሳች) "የምትሄጅበት አዲስ ፀጉር ማለቴ ሰው አንድ ቀን እንደኔ ያረጅብሻል" "አንድ ቀን እስኪያረጅ እኖራለሁ" "ከዛስ እንደኔ ይተዋል።" "መጨረሻችሁ አንድ ስለሆነ ልታዝንለት ነው?" (የሶፋው ጫፍ ላይ እየተቀመጥኩ) "የማዝነው ላንች ነው።ምክንያቱም ራስ በፀጉር የሚያጌጠው በህይወት እስካለ ድረስ ነው። በህይወት የሚኖረው ደግሞ ልብ መምታቱን እስካላቆመ ድረስ ነው።ልብሽ ደግሞ እኔ ጋር ነው።" (ሻንጣዋን አስቀምጣ እየተጠጋችኝ) "ምን ለማለት ፈልገህ ነው" "የምትሄጅበት ሰው የወደደሽ ከኔ ጋር ስላየሽ ነው።እኔን ለመጉዳት።ስትለይኝ ካልተጎዳሁ ጥቅምሽ እዚህ ላይ ያበቃል።ጥለሽኝ ስትሄጅ ካልከፋኝ ለሱ መሳሪያነትሽ ዋጋ ያጣል።እንደዛ ነው እያልኩሽ ያለሁት።" "የት እንደምሄድ እንዴት አወክ?"(ግራ በገባው አስተያየት እያየችኝ) "ልብሽ እኔ ጋር አይደል።እሱ ነግሮኝ።"(ፈገግ እያልኩ) "እየቀለድኩ አይደለም!"(በንዴት ጮኸች።ሰው ለምን ሲያጠፋ እንደሚጮህ ይገርመኛል።) (ከሶፋው ጫፍ ላይ ተስፈንጥሬ ተነስቸ እየተጠጋኋት) "እኔም የምሬን ነው።ማወቅ ትፈልጊያለሽ? እንግዲያውስ ስሚዋ። ታስታውሻለሽ የመስሪያ ቤታችን አመታዊ በዓል ላይ ወስጀሽ ሳለ፤አውቃለሁ ያኔ ነው የተዋወቃችሁ። እንዳንች እሱም 'አልበላ አላስበላ' የምለውን ግትር ማንነቴን አይወደውም ነበር። ከአንድ ወንዝ የተቀዳችሁት ከሱ ጋር ይመስለኛል።እኔና አንች የተለያየ ቦታ ነው የተቀዳን።..." (አይኖቿ ከተደበቁበት ወጥተው ፈጠጡ) "...መስሪያ ቤት ውስጥ ግንኙነታችን ጥሩ አልነበረም።ሊጎዳኝ እንደሚችል ሲነግረኝ እኔም እንደማይችል ስነግረው እርግጠኛ ሆኘ ነበር። በሌላ እንደማይችል ሲያውቅ የልብሽን ስስነት አይቶ ባንች መጣ።የት እና መቸ እንደምትገናኙ ሁሉንም አውቃለሁ። እንፋታ ስትይ 'ተይ' የምልሽ እንዳትጎጅ እንጅ..." (እየተረጋጋሁ...እሷ ድንጋጤ ውስጥ ናት) "...እኔ የፈታሁሽ የማላውቃት የአክስትሽ ልጅጋ ሂደሽ ያደርሽ ቀን ነው።ለኔ የሞትሽው ያኔ ነው!..." (አፏን ከፍታ አይኖቿን ፊቴ ላይ ተክላ ደንዝዛ ቀረች)

ርዕስ የተውኔት ድርሰት አፃፃፍ ዘዴ ፀሀፊ ፋንታሁን እንግዳ ገፅ ብዛት 236 ዓ.ም 2005

ትግርኛ አትችልም "አባቴ ይሙት !" አለችኝ እየሳቀች። እውይ ጥርሶቿ ታይተው አይጠገቡም። የውበት አምላክ በጥንቃቄ የደረደራቸው የቀይ ባህር ዕንቁዎች ይመስላሉ። "ይህ ጉሮሮ የሚፍቅ ቋንቋ ! መጓጉጥ
ትግርኛ አትችልም "አባቴ ይሙት !" አለችኝ እየሳቀች። እውይ ጥርሶቿ ታይተው አይጠገቡም። የውበት አምላክ በጥንቃቄ የደረደራቸው የቀይ ባህር ዕንቁዎች ይመስላሉ። "ይህ ጉሮሮ የሚፍቅ ቋንቋ ! መጓጉጥ ነው። አልኳት "እንጥላችሁ ስላልተቆረጠ ይሆናል " "እሰኪ መቶ በይ " "ሞቶ " " እስኪ አንተ በይ " "አንቴ "    " አንቺም አማርኛ አትችይም አባቴ ይሙት " አልኳትና መጠጧን ላመጣላት ሄድኩ። መጠጧን አመጣሁላትና " ሕራይ ትግርኛ ክትምህርኒ እሺ " ሺ እምበአር ? ጸጋዬ ኃይለማርያም እባላለሁ " አልኳትና መጠጧን ቀምሼ ሰጠኋት። እውነትም ጥሩ መጠጥ ነው። "በቲቪ አውቅሀለሁ አንተም አማርኛ ታስተምረኛለህ "አለች ፡ ጠጉሯን እየነሰነሰች ፈገግታዋ ይናፍቃል።       " ማን ብዬ ልጥራሽ ሰሜናዊት ጽብቅቲ ?" ብዬ ስሟን ጠየኳት ሳቀችና "ፊያሜታ ጊላይ እባላለሁ " ብላ ስሟን ነገረቺኝ። ስሟ ደንቆኝ ቅንድቤን ከፍና ዝቅ ሳደርግ አይታኝ "ምነው አለች።               " እንግዳ ስም ነው ...."              "የጣሊያን ስም ነው ...."             "ምን ማለት ነው ? "             "ትንሽ ነባልባል ...." "እውነት አንቺን ከሩቅ መሸሽ ይሻላል "አልኳት "                 "ለምን አለችኝ " " ስምን መላክ ያወጣዋል ይባላል። እንደ ስምሽ ከሆንሽ አደገኛ ነው። በትንሽ ነበልባል ተቃጥሎ ማለቅ ደግ አይደለም። እንደ ስምሽ እንዳልሆንሽ ተስፋ አደርጋለሁ አልኳት።              "ነኝ አባቴ ይሙት "አለች ስቃ" #ኦሮማይ #በዓሉ_ግርማ @ethioterkaa @ethioterkaa @ethioterkaa

ውበት ፈላጊና ተመልካች ሃሳቦች! ሴት ከመልኳ ማማር፣ ከተክለ ቁመናዋ ሳቢነት፣ ከድምፀቷ ማራኪነት፣ ከሳቋ አደንዛዥነት፤ ከፆታዊ ፍቅር አፍዛዥነቷ በላይ ሴትነቷ የተለየ ውበትና ጥበብ ነው፡፡ ወንድነት ትክክለኛ ውበቱ ያልተመረመረና ያልተዘረዘረ ይመስለኛል፡፡ ወንድንም ሆነ ሴትን ከፆታዊ መለያቸው ባሻገር አፈጣጠራቸው የተለያየ ነው፡፡ ባይበላለጡም፣ ባይተናነሱም እኩል ግን አይደሉም፡፡ ሴት የሌላት ወንድ አለው፤ ወንድ የሌለው ሴት አላት፡፡ የሴቶች እኩልነት የሚባለው ዓለማዊ መፈክር አዕምሮ አልባዎች በፈጠሩት ርዕዮት፤ በጉልበት በሚያስቡ ሰዎች በሚዘወር ስርዓት አማካኝነት የመጣ የተበዳይነት የብሶት ጥያቄ እንጂ ማስተዋል ባለው ህብረተሰብ የሚቀነቀን መፈክር አይሆንም፡፡ ምክንያቱም ላስተዋለና ለመረመረ፤ እውነቱን ለተረዳና ሚስጥሩ ለገባው ሰው ሁለቱም ተፈጥሮዎች እርስበራስ የማይበላለጡ በራሳቸው ብቁና ሙሉ መሆናቸውን ያውቃል፡፡ ይህንንም ያስተዋለ አንዱ የአንዱ የበላይ ወይም የበታች ነው ብሎ አያስብም፡፡ ሴትን በሌላት ነገር ከወንድ ጋር ማወዳደርና ማፎካከር ምክንያታዊ አይደለም፡፡ ወንድንም በሌለው ነገር ከሴት ጋር ማነፃፀር ልክ አይመጣም፡፡ ሴት የሚገባትን ቦታዋን መንጠቅ ኋላቀርነት ነው፡፡ ወንድንም በሴት እኩልነት ስም የሚገባውን ማሳጣት ፍትሐዊ አይደለም፡፡ ይሄን የሚያደርገው ያልሰለጠነ ማህበረሰብ ብቻ ነው፡፡ የሰለጠነ ማሕበረሰብ ግን ልክ ፕሌቶ እንዳረቀቀው ለሁሉም የሚስማማ፣ የበላይና የበታች የሌለበት እንከን አልባ ስርዓት (UTOPIA) ይቀርፃል፡፡ እናንተ ወንዶች ሆይ... ሴትን ቀሚሷን ገልቦ ጭኗ ውስጥ ከመመርመጥመጥ ባሻገር እውነተኛ የሰውነት ሚስጥሯን፣ ትክክለኛ ውበቷን አስተውላችሁ አግኝታችኋልን? የሴትን ስስ ገላዋን ሳይሆን የሰውነቷን ውበት ፈልጎ ያገኘ የትኛው ወንድ ይሆን? እናንተ ሴቶች ሆይ... ወንድን ደረቱ ላይ ተጋድሞ በፆታዊ የስሜት እሳት እየተለበለቡ ከማለቃቀስ ይልቅ ከጊዚያዊ ስሜት ነፃ ሆናችሁ ወንድነት ውስጥ ያለውን ውበት አይታችኋልን? ለእቅፍሽ የምትመኝውን ወንድ በሰውነቱ ተረድተሸው እውነተኛ ውበቱን አግኝተሻልን? አይመስለኝም፡፡ ከደረቱ ይልቅ ልቡን የሚመለከቱ ጥቂቶች ናቸው፤ ከኪሱ በስተጀርባ ያለውን እውነተኛ ማንነቱን ለማወቅ የምንደፍር ሴቶች እንኖር ይሆን? እርግጥ ነው ፍቅር የሚባል የተቃራኒ ፆታ አደንዛዥ እፅ እርስበራሳችን እንዳንተዋወቅ እንቅፋት የሆነ ይመሰለኛል፡፡ እውነተኛ ፍቅር ከፆታዊ ግንኙነት በላይ ነው፡፡ እርሱም ተፈጥሮውን፣ ሰውን፣ ትዕይንተ ዓለሙን፣ ሁሉንም ያለምንም መያዣ በነፃ መውደድና ውበቱን መረዳት ነው፡፡ አዎ ፆታዊ ፍቅር ያጠብበናል፡፡ የተፈጥሮ ፍቅር ግን ያሰፋናል! አለም የበላይና የበታች ስርዓት የቀረፀው ስላልሰለጠነ ነው፡፡ ለዚህ ነው አልበርት ካሙስ The Stranger በተባለ መፅሐፉ፡- ‹‹ማንም ከፊት ለፊቴ አይራመድ፤ ምክንያቱም አልከተለውም፡፡ ማንም ከኋላዬ አይከተለኝ፤ እኔ ማንንም አልመራም፡፡ ባይሆን ከአጠገቤ ሆነህ እየተራመድክ ጓደኛዬ ሁን፡፡›› የሚለው፡፡ ❤️❤️❤️❤️❤️❤️ የበላይነትና የበታችነት ይውደም!❤️ #ሞጋቿነኝ @ethioterkaa @ethioterkaa @ethioterkaa

በፍቅር ውስጥ የሚመር ነገር የለም።" * * አንድ የተከበረ ሱፊ ከአንዲት ሴት ጋር በመንገድ ላይ ተገናኘና ይኸን ጠየቃት፡- “የፍቅር መጨረሻው ምንድነው?" እሷም መለሰች፦ “ፍቅር መጨረሻ የለውም። ሱፊው ዳግመኛ ጠየቃት፡- “ለምን?” እሷም በመልሷ አስደነቀችው:- “ምክንያቱም ፈጣሪ መጨረሻ የለውምና!!” ሱልጣን መሐመድ እጅግ አድርገው የሚወዱትን አገልጋያቸውን አያዝን አንድ ቀን ወደ ገበታቸው በመጥራት ከፊታቸው ከተቀመጠው ፍሬ አንዱን አንስተው ሰጡት። አያዝም ከሚወደው ጌታው እጅ የተቀበለውን ፍሬ በልቶ እንዳጋመሰ ሱልጣኑ ሌላ ፍሬ አንስተው አንዴ ገመጡና ትንሽ አኝከው ተፉት። በመገረምም ወደ አያዝ እየተመለከቱ፡- “እንዲህ ዓይነት መራራ ፍሬ እንዴት ትበላለህ?” አሉት። “የምወድህ ሱልጣን ሆይ” አለ አያዝ “የጣፈጠኝ ፍሬው ሳይሆን የስጠኝ እጅህ ነው" በማለት መለሰ። " በፍቅር ውስጥ የሚመር ነገር የለም።" በፍቅር ከተደረገ መራሩ ጣፋጭ ይሆናል። @ethioterkaa @ethioterkaa

ፍቅር በእምነት ውስጥ፣ እምነትም በፍቅር ውስጥ ይኖራል:: ይኸ ሲሆን የትኛውም ተፈጥሯዊ እና ስነ ሕይወታዊ ነገር ሁሉ ልዩነቱን አጥብቦ በህብር አንድ ይሆናል፣ በነፍሱ ይግባባል:: ትናንት በይና ተበ
ፍቅር በእምነት ውስጥ፣ እምነትም በፍቅር ውስጥ ይኖራል:: ይኸ ሲሆን የትኛውም ተፈጥሯዊ እና ስነ ሕይወታዊ ነገር ሁሉ ልዩነቱን አጥብቦ በህብር አንድ ይሆናል፣ በነፍሱ ይግባባል:: ትናንት በይና ተበይ፣ አሳዳጅና ተሳዳጅ፣ የነበሩት ነፍሶች በፍቅር ማግኔጢሳዊ ኃይል ተቃቅፈው የውስጣቸውን የሚተነፋፈሱበት አጋጣሚና ሁኔታም እንዳለ ልብ እንበል! ተፈጥሮ የምስጢር ጎተራ ነች:: ታላቁ የብዕር ሠው ብርሃኑ ዘሪሁን " የአብዮቱ ዋዜማ፣ የአብዮቱ መባቻ፣ የአብዮቱ ማግስት" እንዲል የትንሣኤ በዓልን ዋዜማና መባቻውን በሰላም እንዳሳለፋችሁ በማመን፣ መልካም የትንሣኤ በዓል 'ማግስት' ሰኞ ብበላችሁ አይከፋችሁም መቸም 😊🙏 @ethioterkaa

በቅርብ ቀን እሚለቀቁ የትያትር ድርሰቶች የከርሞ ሰው ደራሲ ፀጋዬ ገ/መድህን ይዘት ትያትር ገፅ ብዛት 84 ማክቤዝ ደራሲ ዊልያም ሼክስፒር ትርጉም ጸጋዬ ገ/መድህን ሀምሌት ደራሲ ዊልያም ሼክስፒር ትርጉም ፀጋዬ ገ/መድህን ገፅ ብዛት 134 በልግ ደራሲ ፀጋዬ ገ/መድህን ይዘት ተውኔት ገፅ ብዛት 140 ሀሁ ወይም ፐፑ ደራሲ ፀጋዬ ገ/መድህን ገፅ ብዛት 47 @ethioterkaa @ethioterkaa @ethioterkaa

በ ቅርብ ቀን እሚለቀቁ መፅሀፍት ዝርዝሮች ✒️የተውኔት ድርሰት አፃፃፍ ዘዴ pdf ✒️ ሶስቱ ጠብደል ሰዎች pdf ✒️ አላቲኖሶ pdf ✒️ እንደ እከሌ pdf @ethioterkaa @ethioterkaa

ከጨለማ ያውጣን ከሞት ቤቱ አዳር ተነሱ ይበለን መጥቶ እንደአላአዛር ድምፆችን ይስማን እንደመቅደላዊት፣ በግንቡ ይጎብኜን መጥቶ በኛ ሌሊት፣ እንደመሼ መስሎ  የፍሲካ ማታ አጋጣሚ አይደለም ሳይፀና ወገግታ በ ዘጠኝ ሰአቱ የተነሳ ጌታ ሊያመስለን ቢሻ ነው የኛኑ ወገግ ማለት ፀሀይ ሳትወጣ ሌቱ ሳይነጋበት ክርስቶስ ሌባ ነው በሌሊት ይመጣል ክርስቶስ ሊዘርፈን በሌቱ ይገኛል ሀር ነጩን ለብሶ ሌሊት ሳይታዬን ጉዝጓዝ መከራችን ሳይታይ ሊሰርቀን ሰርቆ ጠራርጎ ፍቅር ሊያበድረን፣ ሰላም ሊተካብን በልባችን ሳንቃ በነፍሳችን ጫንቃ፣ ክርስቶስ ይሰርቃል ሊነጋጋ ሲል እንባን እና ሲቃ፣ __ # አይዞን ፍሲካችን አለ  # #  ግዕዝ  ሙላት @geez_mulat @ethioterkaa @ethioterkaa @ethioterkaa

ነገ ልደቷ ነው!(ልዑል ሀይሌ) ነገ ልደቷ ነው! ልቤ ወዴት ሄዶ ዳቦ አይቆረስም፤ አሰናዳሁላት ትቁረሰው በሷ ስም፤ . በዕድሜዋ ቁጥር ሻማም አይበራላት፤ ምን ይጎልባታል ብርሃን የሚያፈልቁ ጥርሶቿ እያሉላት፤ . ነገ ልደቷ ነው! አሰናድቻለሁ ሚቆረሰው ልቤን፤ አሰናድታዋለች ደማቅ ፈገግታዋን ልትሰርቀው ሐሳቤን፤ . መቼ ነው ሚነጋው? እሱ ነው የኔ ሐሳብ የሌሊት ጥበቃ፤ መች ነው ማገኛት ከፀሐይዋ በፊት የምትወጣው ደምቃ፤ . እንቅልፍም አልተኛም ቢያዳፋኝም ደርሶ፤ ሕልም ሆኖ እንዳይነጥቀኝ ምኞቴን አፍርሶ፤ . እጠብቃታለሁ በልደቷ ዕለት ሚቆረስ ልብ ይዤ፤ ለሷ አይደለም ወይ ግሳንግስ ኑሮዬን የመጣሁ ተጉዤ፤ @Leulha @ethioterkaa @ethioterkaa @ethioterkaa

አምስቱ ቅንዋተ መስቀል! "ተቀንዎ በቅንዋት ማለት በችንካር መቸንከር ማለት ነው። ይህስ እንዴት ነው ቢሉ ፤ ከዚያ ከቀራንዮ ቀርተው የነበሩት ጠበብቶች ስለታቸውን እንደ ወስፌ፤ እንደ መርፌ ፤ ወርዳችውን እንደ ሞረድ አራት ማዕዘን ራሳቸውን እንደ መሮ፤ ቁመታቸውን ክንድ ከስንዝር እያደረጉ ፤ 5ት ችንካር ሰርተው ጠበቋቸው። እነርሱም አካሉን አንስተው በመስቀሉ ላይ አጋድመው፤ ግራና ቀኝ እጁን በሐብል፤ ስብው #ሳዶር  በሚባል ችንካር ከግደመ መስቀሉ ጋራ ደርበው ቀኝ እጁን ቸነከሩት። #አላዶር በሚባል ችንካር ግራ እጁን ስበው ከግድመ መስቀሉ ጋራ ደርበው ቸነከሩት። #ዳናት በሚባል ችንካር ሁለቱን እግሮቹን ስበው ከጉንደ መስቀሉ ጋራ ደርበው ቸነከሩት። #አዴራ በሚባል ችንካር ራሱን ከፍ አድርገው ስበው ከጉንደ መስቀሉ ጋራ ደርበው ቸነከሩት። አንድም " አጽነነ ርእሶ መንገለ የማን" ይላልና ቀኝ ደረቱን ከጉንደ መስቀሉ ጋራ ደርበው ቸነከሩት። #ሮዳስ በሚባል ችንካር ግራ ደረቱን ከጉንደ መስቀሉ ጋራ ደርበው ቸነከሩት። ጌታ ስለኛ ብሎ በዕለተ ዓርብ የተቀበላቸው 5ቱ ቅንዋተ መስቀል እኒህ ናቸው። ይህስ ቢሆን ምነው  ሌላ አካሉን ያልተቸነከረ ደረቱን የተቸነከረ ቢሉ፤ የበሉትን ሁሉ ተቀባይ ደረት ነው። አዳም የበላትን ቆፅል በለስ ደረቱ ተቀብላ ነበረችና፤ ስለዚህ ጌታ ደረቱን ተቸነከረ። እሊህንም ሲቀበላቸው በሰውነቱ ነው እንጂ በመለኮቱ አደለም።  በመለኮቱስ ርኁቅ እምቅንዋት ወጥዑይ እምሕማማት ነው። "ሐማሚ በትስብእቱ ኢሕማሚ በመልኮቱ" እንዲሉ ፫ቱ፻ት።" "ሳዶር፤ አላዶር፤ ዳናት፤ አዴራ፤ ሮዳስ፤ ፭ቱ ቅንዋተ መስቀሉ ለእግዝእነ ኢየሱስ" እንዲል ደራሲ። "ኦ አእጋር እለ አንሶሰዋ ውስተ ገነት ተቀነዋ በቅንዋተ መስቀል ኦ አእዳው እለ ለሐኳሁ ለአዳም ተቀነዋ በቅንዋተ መስቀል ኦ አፍ ዘነፍሐ ውስተ ገጹ ለአዳም መንፈሰ ሕይወት ብሒዐ መጺጸ ዘምስለ ሐሞት ሰረበ" እንዳለ ዮሐንስ አፈወርቅ በቅዳሴው። "ለፀዋሬ ሰማያት ወምድር በኃይሉ ፆሮ ዕፅ ድኩም በዲበ ዕፀ መስቀል" እንዳለ ቅዱስ ቄርሎስ በቅዳሴው ቁጥር 24። ምነው አይሁድ ጨከኑበት፣ ጌታችንስ ስለምን እጁን፣ እግሩን ተቸነከረ ቢሉ አይሁድ ጠልተውታልና መከራውን አበዛነው፣ ሥቃዩን አጠናነው ብለው ደስታቸው ነው። ጌታ ግን "ቀነዉኒ እድውየ  ወእገርየ" ብሎ ክቡር ዳዊት በመዝ 21//16 ተናግሮ ነበርና፤ ይህን ለመፈጸም ነው። ምሥጢሩ ግን ለአርአያ ለቤዛ ነው። ሣህሉ ወምሕረቱ ለእግዝእነ ወአምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ወሞገሰ መስቀሉ ክቡር የሃሉ ምስለ ሕዝበ ክርስቲያን ለዓለም ዓለም አሜን። (ሕማማተ መስቀል፣ ምዕራፍ ፫፣  ክፍል ፲፩ ቁጥር ፶።  አሳታሚና አክፋፋይ የደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም።) አብርሃም ደመቀ @ethioterkaa @ethioterkaa @ethioterkaa

#ዕንባዋ.እና.እውነት ከሚስለመለሙ ዐይኖቿ ጠርዝ ላይ ከሚያብረቀርቀው የቆቧ ድንበር ላይ ወዟ ሲቀር አየሁ መሄዴን ተውኩና ከሷ ጋራ ቆየሁ፡፡  ካደመኝ እንባዋ…… ጠጉሮቿን ጎዝጉዞ ጢሳሲስ ትንፋሿ ወደኔ ተጉዞ፡፡ ቃላት ሳታወጣ ተለማመነችኝ ‹‹ልሂድ ወይ?›› ሳልላት ቀድማ ‹‹ቆይ!›› አለችኝ፡፡ ቃላትን ሳታወጣ ተለማመነችኝ፡፡ ሊፈስ የቀረረ ቅልስልስ እንባዋ ለኔ የታሰበ ልመና፣ መባዋ ቃላት ሳታወጣ እኔ ጋረ ደረሰ ሊሄድ የከጀለ አቋሜን መለሰ፡፡ ይልቅስ! እጣቴን ወደ ጉንጯ ግድም    ሰድጄ አበስኩት እንባዋ ሲያወዛኝ ሀዘኗን አዘንኩት፡፡ የወዛ እጣቴን የታከከች እንባ  ወደ እግሬ ብትዘም፣ ደርሳ ተንጠባጥባ  እግረ-ሙቅ ሆናብኝ አስራ አስቀረችኝ ዝም ባለ፣ ዝምታ ‹‹አትሂድ›› አለችኝ፡፡  አፏ ባይላወስ፣ ከንፈሯ ባይለቅም የግዷን ፈግጋ ከኔ እኩል ብትስቅም የገዛ እውነቷ ከዐይኗ ስር አይርቅም፡፡ (አዎ!) የይመስል ፈገግታ በእንባ ይታጠባል አፍ ያድበሰበሰው በዐይን ያመልጣል፡፡      by @Lee_wrld            @ethioterkaa @ethioterkaa

ከሶስቱ የቱ ይከብዳል ሀሳባችሁን ኮመንት ላይ ስጡን @ethioterkaa @ethioterkaa
ከሶስቱ የቱ ይከብዳል ሀሳባችሁን ኮመንት ላይ ስጡን @ethioterkaa @ethioterkaa

#እሰይ ፡ ፡ ፡ ከመሳሳት ይልቅ ትክክል መሆንን ሰርክ ስለሚመርጥ፤ ይላል ያገሬ ሰው “ አስር ግዜ ለካ አንድ ግዜ ቁረጥ”። ፡ ፡ እኔ ግን እላለው... በመሳሳትክ ውስጥ የሚገኘው እክል፤ እሱ ነው ቁምነገር እሱ ነው ትክክል። ፡ ፡ አሁንም እላለው... ከትናንቱ ዛሬ በስለ እንድትጎመራ፤ “ አንድ ግዜ ለካ አንድ ግዜ ቁረጥ ” እሰይ ስህተት ስራ። #ሄኖክ_ብርሃኑ @ethioterkaa @ethioterkaa