1 194
Subscribers
No data24 hours
+37 days
No data30 days
Posts Archive
1 194
እግዚአብሔር አብ ሆይ እናመስግንሃለን
ቅዱስ አባት ሆይ እንደ ፈቃድህ ባንኖርም ፣ ፍቅርህን አላጎደልክብንም፣ ጠላቶችህ ሆነን ወደድከን አንተው ተበድለህ በልጅህ በኩል ታረቅከን፣ ለምትወደው አንድያ ልጅህ እንኳ ሳትራራ ስለሁላችን ይሞት ዘንድ አሳልፈህ ሰጠኸው። እኛ ልጆቻችንን ማንም ቀና ብሎ እንዲያያቸው እንዲገላምጣቸው አንፈቅድም፣ አሁን እንደውም ጎረቤቶቻችን እንኳ ሲልኳቸው ቅር እንሰኛለን። አንተ ግን ለእኛ ብለህ ልጅህ እንዲሰደብ፣ እንዲገረፍ ፣ ምራቅ እንዲተፉበት፣ በዘንግ እንዲመታ፣ ሥቃይን የሚያበዛ የእሾህ አክሊል በራሱ ላይ እንዲኖር ለሞት እንዲበቃ አደረከው። ይህንን ፍቅር እንዴት መግለፅ ይቻላል?
ታላቁ የእምነት አባት አብርሃም በእርጅና ዘመኑ ያገኘውን ልጅን መስዋዕት አድርጎ ለማቅረብ ሲሄድ ምንም እንኳ እግዚአብሔር ከሞት ያስነሳልኛል ብሎ ቢያምንም፣ ልጅን ለመሰዋት ማቅረብ ግን ለአብርሃም ቀላል አልነበረም። የሰውን ሞት የማይፈቅደው እግዚአብሔር ግን በይስሐቅ ፈንታ በግ በመስጠት ይስሐቅን ከሞት፣ አብርሃም ከልቡናው ጭንቀት አዳነው። እግዚአብሔር አብም ምንም እንኳ ልጅ ከሞት የሚነሳ መሆኑን ቢያውቅም ልጅን ለመከራ አሳልፎ ሲሰጠው ፈቃድ የመስጠት ያህል ቀላል አልነበረም። በውስጣቸው ያለ የአባትና የልጅ የፍቅር ትስስር የልጅ መከራ እንዲሰማው ያደርገዋል። እናቱ ድንግል ማርያም መከራውን ባየች ጊዜ በልብሽ ሰይፍ ያልፋል እንደተባለ፣ ልቧ በመከራ ይጨነቅ እንደነበር ሰማያዊ አባቱም የልጅ ጭንቀትና ስቃይ ይሰማዋል። ነገር ግን እግዚአብሔር ለእኛ ካለው ፍቅር የተነሣ ልጅን ለመድኃኒት እንዲህን ለሞት አሳልፎ ሰጠው ሐዋርያው “ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል” ሮሜ 5:8 ሲል ፍቅሩን እንድገነዘበው ይጋብዘናል።
አባት ሆይ ልጅህ ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን። ኢሳ53:5 በልጅህ ሥቃይ ኃጢአታችንን ክብደት አየን። ያፈሰሰው ደም ኃጢአታችንን ሁሉ አጠበ፣ ከእንግዲህ ወዲያ ደሙን አልፎ ሊከሰን የሚችል ደፋር ኃጢአት የለም፣ ሥጋውና ደሙን ለዘላለም የኃጢአት ይቅርታን እናገኝበት ዘንድ በቤተክርስቲያን ተክለሃልና። በሞቱ ከሰይጣን አገዛዝ አርነት አወጣን የተመረጠ ትውልድ፥ የንጉሥ ካህናት፥ ቅዱስ ሕዝብ፥ ለርስቱ የተለየ ወገን አደረገን። 1ዼጥ 2:9 ቅዱስ አባት ሆይ ስለ ታላቅ ፍቅርህና ስለ በጎህ ሥጦታህ ሁሉ እናመሰግንሃለን። 🙏🙏🙏
“ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ድል መንሣትን ለሚሰጠን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን።” 1ቆሮ 15:57
1 194
ሕማማት
ሕማማት የክርስትና ባህርይና ብቸኛ መገለጫ ነው። ከክርስትና ውጪ አምላኬ ተይዟል በሰዎች ተገርፏል ተሰቃይቷል ሞቷል የሚል ሃይማኖት የለም። " አምላክ አሸናፊ ነው!" ከዚህ ማንነቱ የተነሳ በሰዎች ሊገደል ሊሰቃይ አይችልም የሚለው የብዙዎቹ እምነት ነው። እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን። የተሰቀለውን አምላክ ማለት የክርስትና ብቻ ጠባይ ነው።
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሕማም በሁለት ይከፈላል፦
1ኛ፦ የመጀመሪያው ሰው መሆኑ ነው። ሰው መሆኑ እንደ አጠቃላይ ለዘላለማዊ አምላክ የሚገባ አይደለም። ለባህርይው የማይስማማ ነውና። የማይወሰነው መወሰኑ ጊዜ የማይቆጠርለት በጊዜ ስፍር ውስጥ መግባቱ ለፍቅር እንጂ ተገብቶት አይደለም።
2ኛ፦ ሁለተኛው ሕማም አሁን የያዝነው ሳምንት ነው። ከሆሳዕና ፍጻሜ እስከሞቱ ድረስ ያለውን የመከራ ሰዓት ሰሞነ ሕማማት እንለዋለን።
የክርስቶስ ሕማም የክርስትና መሠረት ነው። ለሰው መዳን የተከፈለ ዋጋ ነው። ፍቅር የተገለጠበት ነው። የእግዚአብሔር ተስፋ ፍጻሜ ያገኘበት ነው። ይህም ተስፋ የዘላለም ሕይወት ነው።
የክርስቶስ ሕማም የመጽሐፍ ቅዱስ ቀኖና መሠረት ነው። መጽሐፍ ቅዱስንም ለመረዳት መፍቻ ቁልፉ ሕማሙ ነው። " እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን " እንዲል። ብሉይን የሚፈታልን የክርስቶስ የማዳን ሥራ ነው።
እግዚአብሔርን የምትወዱት በዚህ ሳምንት የልጁን ሕማም አስቡ። ለኃጢያታችሁ የተከፈለ ዋጋ እንደሆነ ተረዱ። ምላሹም ሳምንቱን በስግደት ከማሳለፍ ከፍ ይልላችሁ ዘንድ ተመኙ።
ሕማማት ሰው ዳግመኛ የተፈጠረበት ነው። ጌታችን ለሐዋርያቱ ደጋግሞ የነገራቸው ዋና ነገርና እነርሱም ሊሰሙት ያልፈለጉት መቀበልም የከበዳቸው ሕማሙ ነበረ። ዛሬም የጌታን ሕማም ለማክበር እንጂ በሕማም ጌታን ማክበር የሚፈልግ ክርስቲያን እየጠፋ ነው። ሕማማት ከበዓልነት ከመታሰብም ያለፈ ነው። እንደ ሐዋርያው " በሙቱ እንድመስለው እመኛለሁ " የሚያስብል የፍቅር ዕዳ ውስጥ የሚከት የፍቅር ሳምንት ሊሆንልን ይገባል።
በሞት የተገለጠ ሕይወት የሚሰጥ ፍቅር ያለው ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው።
የምወዳችሁ የምናፍቃችሁ በክርስቶስ እህት ወንድሞቼ የምትሆኑ ሁላችሁ በእግዚአብሔር ልብ በዘላለም ፍቅር ስለታሰባችሁ ደስ ይበላችሁ። ልዑል አምላክ ለዘላለም እርሱን ከሁሉ አብልጣችሁ የምታስቡበትን ልብ ይስጣችሁ። ሳምንቱን የበረከት ሳምንት ያድርግልን።በፍቅር መተሳሰብን የፍቅር አምላክ ያድለን። ለበረከት ሁኑ!
1 194
እግዚአብሔር አብ:- “ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል።” ሮሜ 5፣8
እግዚአብሔር ወልድ:- “በውድ ልጁም፥ እንደ ጸጋው ባለ ጠግነት መጠን፥ በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን አገኘን እርሱም የበደላችን ስርየት።” ኤፌ 1:7
እግዚቀብሔር መንፈስ ቅዱስ:- “የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን ያ መንፈስ ራሱ ከመንፈሳችን ጋር ይመሰክራል።” ሮሜ 8:16
