en
Feedback
🇪🇹ኢትዮ-News መረጃ

🇪🇹ኢትዮ-News መረጃ

Open in Telegram

Broadcast & media production company ⌛️ አለም አቀፋዊነት 🌐 🌐 🌐 ⌛️ ወቅታዊነት ⌚️🕰🎙 ⌛️ ተደራሽነት 📲💻📡📺 ⌛️ ሚዛናዊነት ⚖ ⚖ ⚖ ከኛ ጋር ይሁኑ | ያጋሩ https://t.me/ethiomereja0 https://t.me/ethiomereja0

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
7 778
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ለስራ ፈላጊዎች በሙሉ __________________ ❖ ሳፋሪ ኮም ኢትዮጲያ አዲስ የስራ ማስታወቂያ በ0 አመት በተለያዩ ፊልዶች _____________________ ♦ Deadline: 28-Oct-2021  Safaricom Telecom Ethiopia Vacancy Fresh Graduates. Sign up today and get the chance to work with Ethiopia’s newest telecommunications network. ✔ Position 1: Finance Degree: Finance, Logistics & Supply Chain ✔ Position 2: External Affairs Degree: Business Administration, Public Policy, Economics, Law, Engineering, Public Relations ✔ Position 3: Enterprise Business Unit Degree: Business Administration, Technology, Engineering, Legal, Marketing ✔ Position 4: Consumer Business Unit Degree: Marketing, Data Analytics, HR, Psychology, Economics, Business Administration, Corporate Communication ✔ Position 5: Sales and Distribution Degree: Business Administration & Data Analytics ✔ Position 6: HR(Human Resource) Degree: Business Administration, Economics, Finance, HR, Civil Engineering ✔ Position 7: Legal & Risk Degree: Corporate Law, BBIT (SQL Knowledge; scripts) ✔ Position 8: Technology Degree:Computer Science, Electrical Engineering, Mechanical Engineering, Mechatronics, Data Science, Data Analytics, Sofware Engineering, Geospatial Engineering, Civil Engineering, Structual Engineering, Architecture, Information Technology, Land Economics, Quantity Survey. How to Apply?? 👇👇👇👇👇👇 https://bit.ly/SafaricomVacancy2021 https://effoysira.com/2021/10/16/safaricom-telecom-ethiopia-vacancy-fresh-graduates/ Broadcast & media production company ⌛️ አለም አቀፋዊነት 🌐 🌐 🌐 ⌛️ ወቅታዊነት ⌚️🕰🎙 ⌛️ ተደራሽነት 📲💻📡📺 ⌛️ ሚዛናዊነት ⚖ ⚖ ⚖ ከኛ ጋር ይሁኑ | ያጋሩ https://t.me/ethiomereja0 https://t.me/ethiomereja0

አዲስ መረጃ በመተከል ____________________ በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል በመተከል ዞን በድባጤ ወረዳ በጋሌሳ ቀበሌ የጁንታው ተላላኪዎች :– ወሮ በላው ኦነግና ጉህዴን ፀረ ሰላም የሽብር ጥምር ሀይሎች በመንግስት ሰላም አስከባሪዎችና ሰላማዊ ህዝቦች ላይ ፅረ ሰብዓዊ የጦር ዘመቻ ተከፍቶል። ወረራው የጀመረው ከጦቱ 11:30 ጀምሮ ሲሆን እስከ ቀኑ 6: 00 ገደማ ቀጥሎ ውሎል። ሆኖም ግን በሀገር ወዳድ የቁርጥ ቀን የኢትዬጲያ ብርቅዬ ልጆች የጥምር ሀይል የሽብር ሀይሉ አላማ መክሸፉን የአይን እማኞች ተናግረዋል። የጥፋት ሀይሉ በንፁሀን ህይዎት ላይና በሀገር ንብረት ላይ ጥፋት ያደረሰ መሆኑ ተሰምቶል። ሰለሆነም በነዚህ ፀረ ሀገር ፣ፀረ ሰው አሸባሪ ሀይሎች ላይ መንግስት የማያዳግም ፈጣን እርምጃ በመውሰድ የሰላማዊ ሰዎችን ሂዎት መታደግና ሀገርን ማረጋጋት ይጠበቅበታል። ይሄንን መረጃ ለሌሎች ቸር በማድረግ ለተጉዱ ወገኖቻችን ድምፅ እንሁን። Broadcast & media production company ⌛️ አለም አቀፋዊነት 🌐 🌐 🌐 ⌛️ ወቅታዊነት ⌚️🕰🎙 ⌛️ ተደራሽነት 📲💻📡📺 ⌛️ ሚዛናዊነት ⚖ ⚖ ⚖ ከኛ ጋር ይሁኑ | ያጋሩ https://t.me/ethiomereja0 https://t.me/ethiomereja0

የአድስ ተመራቂዎች የስራ ማስታወቂያ / job vacancy/ -የግብርና ሚኒስቴር 🔔 👩‍👩‍👦‍👦ተፈላጊ ብዛት: 32 በዜሮ አመት የስራ ልምድ 📚የትምህርት ዓይነት እና ደረጃ: BSc Degree in Plant Science, Computer Science, IT, Animal Science, Accounting, Auditing, Business administration Agribusiness management, Agricultural mechanization, Agricultural science, Agriculture engineering, management, marketing, Rural development, Urban land management, NARM and related. 🇪🇹የስራ ቦታ: አድስ አበባ 🧭የምዝገባ ጊዜ: እስከ ነሃሴ 14 ቀን 2013 ዓ.ም; 🔔ሰለ ሰራው ሙሉ መረጃ ለማየት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ https://jobs.amazonethiopia.com/ministry-of-agriculture-job-vacancy/ --------------------- 🔰ወደፊት የምናወጣቸው የስራ ቅጥር ማስታወቂያዎች በፍትነት እንዲደርስዎ የቴሌግራም ገጻችን እና የፌስቡክ ገጻችን ይወዳጁ! ቴሌግራም: Broadcast & media production company ⌛️ አለም አቀፋዊነት 🌐 🌐 🌐 ⌛️ ወቅታዊነት ⌚️🕰🎙 ⌛️ ተደራሽነት 📲💻📡📺 ⌛️ ሚዛናዊነት ⚖ ⚖ ⚖ ከኛ ጋር ይሁኑ | ያጋሩ https://t.me/ethiomereja0 https://t.me/ethiomereja0

DV 2023 እንዴት ራሳችን መሙላት እንችላለን? ዲቪ 2023 ለመሙላት መከተል ያለብንን መንገዶች እነሆ ›በመጀምሪያ ዲቪ መሙላት የምንችለዉ ከ መስከረም 27,2014 በኢትዮጵያ ወይም በፈረንጆች ኦክቶበር ሀሙስ 07/2021 ጀምሮ ህዳር 09/2021 ለሊት 6፡00 ድረስ ብቻ ነው። DV-2023 Program: Online Registration DV-2023 Program: The online registration period for the DV-2023 Program begins on Wednesday, October 7, 2021 at 12:00 noon, Eastern Daylight Time (EDT) (GMT-4), and concludes on Tuesday, November 09, 2021 at 12:00 noon, Eastern Standard Time (EST) (GMT-5). Individuals who submit more than one entry during the registration period will be disqualified. DV-2023 Program Instructions ›የዲቪ ፎርሙን ከመሙላታችን በፊት ማሟላት ያሉብን ነገሮች፦ እያንዳንዱ የ DV አመልካች የትምህርት / የሥራ ልምድ ማሟላት አለበት ማለትም በ ፕሮግራሙ መሰረትም- • ቢያንስ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ወይም ተመጣጣኝ, የ 12 ዓመት ትምህርት በሚገባ ያጠናቀቀ / ያጠናቀቀች። ወይም • ባለፉት አምስት ዓመታት ውስጥ የሁለት አመት የሥራ ልምድ ያለው። •ጉርድ ፎቶ ግራፍ በመቀጠልም www.dvlottery.state.gov በሚለው ዌብ ሳይት መግባት ›ዌብ ሳይቱ ዉስጥ ገብተን Entry ሚለውን በመጫን መቀጠል በፎቶ መልክ የተቀመጠልንን Authentication code በድጋሚ በመጻፍ ወደ ፎርም መሙያዉ መግባት። ፎርም አሞላል 1. Name - ስም - Last/Family Name (የመጨረሻ/የቤተሰብ ስም ወይም የአያት ስም) ፣ Middle Name- (የመካከለኛ ስም ወይም የአባት ስም) ፣ First Name (የመጀመሪያ ስም ወይም የእርሶን ስም) በፓስፖርትዎ ላይ ያለውን ስም ሳያሳስቱ በእንግሊዝኛ መጻፍ። 2. Gender - ፆታ - ወንድ (Male) ወይም ሴት(Female) መምረጥ። 3. Birth date - የልደት ቀን - መጀመሪያ Month (ወር) ፣ Day (ቀን) ፣ Year ( ዓመት) በፈረንጆች አቆጣጠር በተሰጠው ቦታ መጻፍ።. 4. City Where You Where Born - የተወለዱበትን ከተማ. 5. Country Where You Were Born - የተወለዱበትን ሀገር 6. Country of Eligibility for the DV Program - ለ DV መርኃ-ግብር ብቁ የሆነ ሀገር ማለትም yes ሚለዉ ላይ በመተው ማለፍ 7. Entrant Photograph - የመግቢያ ፎቶግራፍ ማስገባት - የቅርብ ጊዜ ጉርድ ፎቶግራፍ -ፎቶ ግራፉ በደንብ የሚታይ ልኬቱ 600ፒክስል * በ600 ፒክስል የሆነ መጠኑ ከ 240 ኪሎባይት የማይበልጥ ከለር ፎቶ ግራፍ ፣JPEG Format መሆን አለበት። 8. Mailing Address - የፖስታ መላኪያ አድራሻ መሙላት 9. Country Where You Live Today - አሁን የምንኖርበትን ሀገር መምረጥ 10. Phone Number - ስልክ ቁጥር ማስገባት ለኢትዮጲያ +251 ብለን በመጀመር ስልካችንን ማስገባት / አለማስገባትም ይቻላል 11. E-mail Address - የ ኢሜል አድራሻንን ማስገባት 12. What is the highest level of education you have achieved, as of today? የትምህርት ደረጃችንን መምረጥ 13. What is your current marital status?- በአሁን ሰአት ያለን የትዳር ሁኔታ መምረጥ 14 . Number of Children - የልጅ ብዛት በቁጥር መጻፍ እያንዳንዱ የተወለዱ ሕጻናት እንዲሁም የማደጎ ልጆች፣ የእንጀራ ልጆች በእርስዎ ፎርም ውስጥ እያንዳንዱ ያላገቡ ህጻናት, ምንም እንኳን ልጅዎ ከእርስዎ ጋር አብረው ባይኖሩም መሞላት አለባቸዉ። »በመጨረሻም continue በማለት Confirmation Number ያለበትን ወረቀት ፕሪንት በማድረግ ማስቀመጥ እና በ Confirmation Number ን DV-2023 ሲወጣ ማየት እንችላለን። DV-2023 Submission Confirmation : Entry success በዚ መሰረት ፎርሙን በመሙላት እድላችሁን መሞከር ትችላላችሁ ፔጃችንም መልካም እድል ይመኝላቹሀል ይሄን መረጃ ለወዳጆ ሼር ያርጉ Broadcast & media production company ⌛️ አለም አቀፋዊነት 🌐 🌐 🌐 ⌛️ ወቅታዊነት ⌚️🕰🎙 ⌛️ ተደራሽነት 📲💻📡📺 ⌛️ ሚዛናዊነት ⚖ ⚖ ⚖ ከኛ ጋር ይሁኑ | ያጋሩ https://t.me/ethiomereja0 https://t.me/ethiomereja0

የቀረቡት የሚኒስትሮቹ ዝርዝሩ ፦ 1. ግብርና ሚኒስቴር - ዑመር ሁሴን 2. የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር - መላኩ አለበል 3. የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር - ገ/መስቀል ጫላ 4. የማዕድን ሚኒስቴር - ታከለ ዑማ 5. የቱሪዝም ሚኒስቴር - ናሲሴ ጫሊ 6. የስራና ክህሎት ሚኒስቴር - ሙፈሪያት ካሚል 7. የገንዘብ ሚኒስቴር - አህመድ ሽዴ 8. የገቢዎች ሚኒስቴር - ላቀ አያሌው 9. የፕላንና ልማት ሚኒስቴር - ፍፁም አሰፋ 10. የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር - በለጠ ሞላ 11. የትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር - ዳግማዊት ሞገስ 12. የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር - ጫልቱ ሳኒ 13. የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር - ሀብታሙ ኢተፋ 14. የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር - አይሻ መሐመድ 15. የትምህርት ሚኒስቴር - ብርሀኑ ነጋ 16. የጤና ሚኒስቴር - ሊያ ታደሰ 17. የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር - ኤርጎጌ ተስፋዬ 18. የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር - ቀጄላ መርዳሳ 19. መከላከያ ሚኒስቴር - አብረሀም በላይ 20. የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር - ደመቀ መኮንን 21. የፍትህ ሚኒስቴር - ጊዲዮን ጢሞቲዎስ 22. የሰላም ሚኒስቴር - ብናልፍ አንዳለም

#SaudiArabia በጄዳ የሹሜሲ ዲፖርቴሽን ማዕከል ከገቡ በኃላ ባደረባቸው ህመም ምክንያት በተለያዩ ሆስፒታሎች ውስጥ ህይወታቸው ያለፈ የኢትዮጵያ ዜጎችን የሚያውቃቸው ቤተሰብ ፣ ዘመድ እና ጎደኞች ሪፖርት እንዲያደርጉ ተጠየቀ። ከዚህ በታች የሟቾች ስም አስክሬናቸው የሚገኝበት ሆስፒታል የተገለፀ ሲሆን የምታውቋቸው ሰዎች በቢሮ ቁጥር 13 ቀርባችሁ ሪፖርት እንዲያደርጉ በጄዳ የሚገኘው የኢትዮጵያ ቆንስላ ፅ/ቤት አሳውቋል። - ሂክመት መሀመድ (የአስክሬን መገኛ👉 ሸርቅ ጂዳ ሆስፒታል) - ከዲጃ ማህመድ (የአስክሬን መገኛ👉ሸርቅ ጂዳ ሆስፒታል) - ሮዳስ ሙሉ (የአስክሬን መገኛ 👉 ሸርቅ ጂዳ ሆስፒታል) - ጀማል ከማል (የአስክሬን መገኛ 👉 ሸርቅ ጂዳ ሆስፒታል) - ቢንያም ምሩፅ ሃጎስ (የአስክሬን መገኛ 👉 ሰግር ሆስፒታል) - የኢንዲያ ተማም /ህፃን ልጅ/ (የአስክሬን መገኛ 👉 ሰግር ሆስፒታል) - መሃሪ ኃይሌ (የአስክሬን መገኛ 👉 ንጉስ አብዱላአዚዝ ሆስፒታል) - ሱልጣን ሙሀመድ (የአስክሬን መገኛ 👉 ንጉስ አብዱላአዚዝ ሆስፒታል) - በህታ ነጋሲ አፈወርቂ (የአስክሬን መገኛ 👉 ንጉስ አብዱላአዚዝ ሆስፒታል) - ሰለሞን ሀዱሽ ተካ (የአስክሬን መገኛ 👉 ንጉስ አብዱላአዚዝ ሆስፒታል) በዚሁ አጋጣሚ በሳዑዲ አረቢያ የሚገኙ ዜጎችን የመመለስ ስራ ዳግም የተጀመረ መሆኑ ቢታወቅም አሁንም ከፍተኛ ስቃይ ውስጥ ያሉ ዜጎች በርካታ በመሆናቸው ልዩ ትኩረት ሊደረግ ይገባል።

"..የኢኮኖሚ አሻጥሮችን በመፍጠር ያለአግባብ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ የማያዳግም እርምጃ እንወስዳለን" - ወ/ሮ አዳነች አቤቤ የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ፥ " የኢኮኖሚ አሻጥሮችን በመፍጠር ያለአግባብ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ፣ ሰዉ ሰራሽ የምርት አቅርቦት እጥረት በሚፈጥሩና የህዝቡን የተረጋጋ ኑሮ ለማወክ ብሎም አገር ለማፍረስ በሚሰሩና በሚተባበሩ የህዝብና የአገር ጠላቶች ላይ የማያዳግም እርምጃ እንወስዳለን" አሉ። ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች ይህንን ተግባር በበላይነት የሚመራና የሚከታተል በፌዴራል መንግስት እና በከተማ አስተዳደሩ የተዋቀረ ግብረሃይል አቋቁመናል ሲሉ ገልፀዋል። መላው የከተማው ነዋሪ በዚህ ህገወጥ ተግባር ላይ እየተሳተፉ ያሉ ተቋማትና ግለሰቦችን በመጠቆምና በማጋለጥ እንደከዚህ ቀደሙ አብሮን እንዲሰራ ጥሪ አቅርበዋል።

የአድስ ተመራቂዎች የስራ ማስታወቂያ / job vacancy/ -የግብርና ሚኒስቴር 🔔 👩‍👩‍👦‍👦ተፈላጊ ብዛት: 32 በዜሮ አመት የስራ ልምድ 📚የትምህርት ዓይነት እና ደረጃ: BSc Degree in Plant Science, Computer Science, IT, Animal Science, Accounting, Auditing, Business administration Agribusiness management, Agricultural mechanization, Agricultural science, Agriculture engineering, management, marketing, Rural development, Urban land management, NARM and related. 🇪🇹የስራ ቦታ: አድስ አበባ 🧭የምዝገባ ጊዜ: እስከ ነሃሴ 14 ቀን 2013 ዓ.ም; 🔔ሰለ ሰራው ሙሉ መረጃ ለማየት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ https://jobs.amazonethiopia.com/ministry-of-agriculture-job-vacancy/ --------------------- 🔰ወደፊት የምናወጣቸው የስራ ቅጥር ማስታወቂያዎች በፍትነት እንዲደርስዎ የቴሌግራም ገጻችን እና የፌስቡክ ገጻችን ይወዳጁ! Broadcast & media production company ⌛️ አለም አቀፋዊነት 🌐 🌐 🌐 ⌛️ ወቅታዊነት ⌚️🕰🎙 ⌛️ ተደራሽነት 📲💻📡📺 ⌛️ ሚዛናዊነት ⚖ ⚖ ⚖ ከኛ ጋር ይሁኑ | ያጋሩ https://t.me/ethiomereja0 https://t.me/ethiomereja0

የ2013 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ የ2013 የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ይፋ መደረጉን አሳውቋል። ፈተናው ካለፉት አመታት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ውጤት የተመዘገበበት ሆናል ተብሏል። ከነገ ነሃሴ 11 ቀን 2013 ዓ/ም ጀምሮ ተማሪዎች ውጤታቸውን በየትምህርት ቤቶቻቸው መመልከት እንደሚችሉ ተገልጿል።

የታሊባን ኃይሎች ዛሬ ምሽት ወደአፍጋኒስታን የፕሬዜዳንቱ ቤተ መንግስት ገብተዋል። የታሊባን ኃይሎች ወደ ቤተመንግስቱ ዘልቀው የገቡት የሀገሪቱ ፕሬዜዳንት ሀገራቸውን ጥለው ከወጡ ከሰዓታት በኃላ ነው። ታሊባኖች ካቡል መግቢያና መውጫ ላይ የነበሩ ሲሆን ወደካቡል መግባት ጀምረዋል። የአፍጋኒስታን ፕሬዝዳንት አሽራፍ ጋኒ ሀገራቸውን ጥለው ወደታጃኪስታን ሄደዋል፤ ምክትል ፕሬዜዳንቱም አምሩላህ ሳሌህም ሀገሪቱን ለቀው ወጥተዋል ተብሏል። የታሊባን ኃይሎች የአሜሪካ እና ኔቶ ኃይሎች ለ20 ዓመታት የቆዩበትን የአፍጋኒስታን ምድር ለቀው ከወጡ በኃላ ከሀገሪቱ መንግስት ጋር ውጊያ አድርገው በአጭር ጊዜ ውስጥ ዋና ከተማይቱን ካቡልን ጨምሮ የሀገሪቱ መውጫ እና መግቢያ በሮችን በመዳፋቸው ውስጥ አስገብተዋል። ታሊባን ከ20 ዓመት በፊት በአሜሪካ መራሹ ጦር ከስልጣን የተወገደ ሲሆን ከዚህ ሁሉ ዓመታት በኃላ አፍጋኒስታንን ለማስተዳደር ቤተ መንግስት ገብቷል። Broadcast & media production company ⌛️ አለም አቀፋዊነት 🌐 🌐 🌐 ⌛️ ወቅታዊነት ⌚️🕰🎙 ⌛️ ተደራሽነት 📲💻📡📺 ⌛️ ሚዛናዊነት ⚖ ⚖ ⚖ ከኛ ጋር ይሁኑ | ያጋሩ https://t.me/ethiomereja0 https://t.me/ethiomereja0

#PMDrAbiyAhmed የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ዛሬ ባሰራጩት መልዕክት ፥ "ቃል እንደገባነው እጅን አፍ ላይ የሚያስጭን ገድል መፈፀማችንን የምናበስርበት ጊዜ ቅርብ ነው" አሉ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፥ "ጠላት ወደወጥመዳችን እየገባ ነው" ያሉ ሲሆን የማሸነፍ አቅማችም ተጠናክሮ እየወጣ ነው ሲሉ አሳውቀዋል፤ በቅርብ ጊዜ ውስጥም እጅን በአፍ የሚያስጭን ገድል መፈፀማችንን እናበስራለን ብለዋል። የያዝነው የኢትዮጵያን አምላክ ነው ያሉት ጠ/ ሚኒስትሩ የምንታገለው ለኢትዮጵያ ነው ፤ የሚዋጋው የኢትዮጵያ ጦር ነው ፤ በመጨረሻም ታሪክ እንደሚነግረን አሸናፊዋ ኢትዮጵያ ናት ሲሉ ገልፀዋል። ከዚህ በተጨማሪ ጠ/ሚኒስትሩ ሁሉም ሀገር ወዳድ ዜጋ ፦ - በኢትዮጵያ ላይ የተከፈተውን የሚዲያ ዘመቻ እና የዴፕሎማሲ ጫና ለመመከት እንዲረባረብ፤ - የውሸት ዜናዎችን እየተከታተለ እንዲያመክን፤ - ህወሓት በሚነዛው ፕሮፖጋንዳ ሳይደናበር፤ የሴራ ትንታኔ ውስጥ የገቡ ከሴራ ትንታኔ በመውጣት ህወሓት ጦርነት የከፈተበትን የዴፕሎማሲና የጦር ግንባር እንዲቀላቀሉ፤ - ሁሉም ለሀገሩ አምባሳደር ሆኖ ለሀገሩ እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል። Broadcast & media production company ⌛️ አለም አቀፋዊነት 🌐 🌐 🌐 ⌛️ ወቅታዊነት ⌚️🕰🎙 ⌛️ ተደራሽነት 📲💻📡📺 ⌛️ ሚዛናዊነት ⚖ ⚖ ⚖ ከኛ ጋር ይሁኑ | ያጋሩ https://t.me/ethiomereja0 https://t.me/ethiomereja0

#Afar "...ህወሓት የጅቡቲን መስመር ለመቁረጥ ተደጋጋሚ ማጥቃት ቢያደርግም ሰራዊታችን በጣም አስገራሚ በሆነ መንገድ ድል እያመጣ ነው" - ሜ/ጄነራል በላይ ስዩም መንግስት ከቀናት በፊት ባወጣው መግለጫ "ህወሓት" የታወጀውን የተናጠል ተኩስ አቁም አላከበረም፤ ይባስ ብሎ አጎራባች ክልሎች በመግባት ትንኮሳ እየፈፀመ በመሆኑ ሀገር መከላከያ ከሌሎች የፀጥታ ኃይሎች ጋር በመሆን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እንዲደመስሰው አቅጣጫ ሰጥቻለሁ ማለቱ ይታወሳል። ይህን ተከትሎ የምስራቅ ዕዝ የሰራዊቱ አባላት በተሰለፉበት የአፋር ግንባር አኩሪ ገድል እየፈፀሙ መሆኑን ዋና አዛዥ ሜ/ጄነራል በላይ ስዩም ተናግረዋል። ሜ/ጄነራል በላይ ይህን ያሉት የዕዙን የግዳጅ አፈፃፀም ተዘዋውረው ከተመለከቱ በኃላ ባሰሙት የመመሪያ ንግግር ላይ ነው። ሜ/ጀነራል በላይ ፥ ለሰራዊቱ አባላት ሲናገሩ 'ህወሓት' "እዛ ቦታ ተረራ ያዘ፣ ከተማ ያዘ ፤ ይያዝ ነገር ግን መቀበሪያው ነው የሚሆነው የትም ቦታ እንደማይደርስ እርግጠኛ ሁኑ" ብለዋቸዋል። ህዝቡ በቁጣ እየተነሳ መሆኑን የገለፁት አዛዡ የገባው ኃይል በሙሉ በገባበት እንደሚቀር በእርግጠኝነት መናገር እችላለሁ ሲሉ ተደምጠዋል። ሰራዊቱ ባደረገው የግዳጅ አፈፃፀም በርካቶች መደምሰሳቸውን እና ቀሪዎቹም ቁስለኛና ምርኮኛ መሆናቸውን ገልፀዋል። ህወሓት የኢትዮጵያ ማዕከል የሆነውን የጅቡቲ መስመር ለመቁረጥ ተደጋጋሚ ሙከራ ቢያደርግም ሰራዊቱ አስገራሚ በሆነ መንገድ ድል እያመጣ ነው ብለዋል። ሜ/ጄነራል በላይ ሰራዊቱ አሁን ባለው ቁመና እና ዝግጁነት የትኛውንም ግዳጅ በብቃት መፈፀም እንደሚችል ገልፀው "ህወሓት" ወደፊት መሄድ ያልቻለውና የቆመው ወዶ ሳይሆን ሰራዊቱ ስለቀጠቀጠው ነው ብለዋል። "ነገ ቢመጣም ትቀጠቅጠዋለህ፤ እውነታው ይህ ነው" ሲሉ ገልፀዋል

በተያያዢ ዜና በሱዳን በኩል ጥቃት ለመፈፀም ሲንቀሳቀሱ የነበሩት የጉህዴን ፣ የኦነግ እና የህውሀት ቡደኖች በጋራ ተደራጂተው መሆኑን በአከባቢው ያሉ ባልደረቦቻችን ገልፀዋል። Broadcast & media production company ⌛️ አለም አቀፋዊነት 🌐 🌐 🌐 ⌛️ ወቅታዊነት ⌚️🕰🎙 ⌛️ ተደራሽነት 📲💻📡📺 ⌛️ ሚዛናዊነት ⚖ ⚖ ⚖ ከኛ ጋር ይሁኑ | ያጋሩ https://t.me/ethiomereja0 https://t.me/ethiomereja0

በሱዳን በኩል በመግባት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ሽብር ለመፍጠር እና በንጹሃን ዜጎች ላይ ጥቃት ለማድረስ የተንቀሳቀሱ ከ170 በላይ ግለሰቦች መደምሰሳቸው ተገለፀ። ፀረ ሰላም ኃይሎች ናቸው የተባሉት ግለሰቦች መተከል ዞን ጉባ ወረዳ "አልመሃል" አከባቢ ሽብር ለመፍጠር እና በንጹሐን ዜጎች ላይ ጥቃት ለማድረሰ ሲንቀሳቀሱ እንደነበር የክልሉ ሠላም ግንባታ እና ጸጥታ ቢሮ አስታውቋል። ቢሮው ፥ ሽብርተኛ ተብሎ የተፈረጀው የሕወሃት ቡድን ከክልሉ እና ከክልሉ ወጪ ከሚንቀሳቀሱ ተባባሪዎቹ ጋር በመሆን በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ግጭት ለመፍጠር ሲሠራ ቆይቷል ያለ ሲሆን፣ በእነዚህ ኃይሎች ላይ ማያዳግም እርምጃ መውሰድ መጀመሩን ገልጿል። እስከ ትላንት ድረስም የመከላከያ ሠራዊት፣ የፌዴራል ፖሊስ ከክልሉ የጸጥታ አካላት እንዲሁም በክልሉ ከሚገኙት የደቡብ፣ የጋምቤላ እና የሲዳማ ክልሎች ልዩ ኃይል አባላት ጋር በመቀናጀት በተወሰደ እርምጃ ከ170 በላይ የሚሆኑ የጸረ ሰላም ኃይሎች ተደምስሰዋል፣ የቆሰሉና የተማረኩም አሉ ተብሏል። እነዚህ ኃይሎች በሱዳን ድንበር በኩል በመግባት በመተከል ዞን የሕዳሴ ግድብ መገኛ ጉባ ወረዳ አልመሃል ቀበሌን እንደ ማዕከል ተጠቅመው ወደ ግድቡ የሚደረገውን የእንቅስቃሴ መስመር በመቁረጥ ሥራውን ለማስተጓጎል አላማ እንደነበራቸውም ተነግሯል። የህዳሴ ግድብ ሥራውን ከማስጓጎል ባለፈ በክልሉ ሽብር በመፍጠር በንጹኃን ዜጎች ላይ ጥቃት የማድረስ ዓላማ እንደነበራቸውም እና አልማሃልን ማዕከል በማድረግ ወደ አማራ ክልል ለመንቀሳቀስ ዝግጅት እንደነበራቸው ቢሮው ገልጿል። በተወሰደው እርምጃ ከተደመሰሱት የጸረ-ሠላም ኃይሎች ናቸው ከተባሉት ግለሰቦች መካከል ከ16 በላይ የሚሆኑት የሕወሃት አባላት መሆናቸውን ቢሮ አሳውቋል። Broadcast & media production company ⌛️ አለም አቀፋዊነት 🌐 🌐 🌐 ⌛️ ወቅታዊነት ⌚️🕰🎙 ⌛️ ተደራሽነት 📲💻📡📺 ⌛️ ሚዛናዊነት ⚖ ⚖ ⚖ ከኛ ጋር ይሁኑ | ያጋሩ https://t.me/ethiomereja0 https://t.me/ethiomereja0

#Dessie ሀጂ ሠይድ ያሲን ከሠሜን ወሎ ተፈናቅለው ደሴ ከተማ ውስጥ ለሚገኙ ወገኖች ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የምግብ እና አልባሳት ድጋፍ አደረጉ። በደሴ ከተማ በ4 ጊዜያዊ መጠለያዎች ተፈናቃዮች የሚገኙ ሲሆን ሀጂ ሠይድ ያሲን በእነዚህ መጠለያዎች ላሉ ወገኖች ነው ድጋፍ ያደረጉት። የሀጂ ሠይድ ያሲን ድጋፍ ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ሲሆን ነጭ ዱቄት ፣ ብርድ ልብሶችና የሠሌን ምንጣፎችን ያካተተ ነው ፤ ድጋፉ በደሴ ከተማ ህዝባዊ መጅሊስ አማካይነት መደረጉን ከደሴ ኮሚኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያሳያል። Broadcast & media production company ⌛️ አለም አቀፋዊነት 🌐 🌐 🌐 ⌛️ ወቅታዊነት ⌚️🕰🎙 ⌛️ ተደራሽነት 📲💻📡📺 ⌛️ ሚዛናዊነት ⚖ ⚖ ⚖ ከኛ ጋር ይሁኑ | ያጋሩ https://t.me/ethiomereja0 https://t.me/ethiomereja0

#Ethiopia የአሜሪካው ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን ፤ ጄፍሪ ፌልትማንን በድጋሚ ወደኢትዮጵያ ሊልኳቸው ነው። የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጄፍሪ ፌልትማን ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡ ትላንት ለሊት አሳውቋል። ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩት የአሜሪካው የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ጄፍሪ ፌልትማን በድጋሚ ወደ ኢትዮጵያ ይመጣሉ። ፌልትማን ከነሃሴ 9 ቀን 2013 ዓ/ም እስከ ነሃሴ 18 ቀን 2013 ዓ/ም ባሉት ቀናት ወደጅቡቲ ፣ ኢትዮጵየ እና UAE እንደሚጓዙ ከአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመላክታል። ልዩ መልዕክተኛው በጅቡቲ፣ ኢትዮጵያ እና UAE በሚኖራቸው ቆይታ ከ3ቱ ሀገራት ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ይነጋገራሉ ተብሏል። የፌልትማን ውይይት ዋነኛ አላማው አሜሪካ በአፍሪካ ቀንድ "ሰላምን የምታበረታታባቸው" እና የቀጠናውን "መረጋጋት እና ብልጽግና የምትደግፈባቸውን" ዕድሎች የተመለከተ ነው። Broadcast & media production company ⌛️ አለም አቀፋዊነት 🌐 🌐 🌐 ⌛️ ወቅታዊነት ⌚️🕰🎙 ⌛️ ተደራሽነት 📲💻📡📺 ⌛️ ሚዛናዊነት ⚖ ⚖ ⚖ ከኛ ጋር ይሁኑ | ያጋሩ https://t.me/ethiomereja0 https://t.me/ethiomereja0

በአፋር ክልል ለ3 ቀናት የሀዘን ቀን ታወጀ። የአፋር ክልል መንግስት ሽብረተኛ ተብሎ የተፈረጀው "ህወሓት" በፈንቲ ረሱ በጋሊኮማ ጊዚያዊ መጠለያ ተጠልለው የነበሩ በንፁሀን አርብቶ አደሮች ላይ የፈፀመውን አሰቃቂ ያለውን ጭፍጨፋ አስመልክቶ ከዛሬ ጀምሮ ለ3 ተከታታይ ቀናት የሀዘን ቀን እንዲሆን መታወጁን ገልጿል። የአፋር ክልል ባንዲራ ለሶስት ቀናት ዝቅ ብሎ እንዲውለበለብ የክልሉ መንግስት ወስኗል። የአፋር ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ አሚና ሴኮ ይህን ጉዳይ አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል። ህወሓት በጋሊኮማ በንፁሀን ላይ ያደረሰው ጭፍጨፋ እጅግ ዘግናኝ ነበር ያሉ ሲሆን የክልሉ መንግስት ይህን ጥልቅ ሀዘን አስመልክቶ የሶስት ቀናት ሀዘን ማወጁን ገልፀዋል። ጥቃቱን ታሪክ የማይረሳው ነው ያሉት አፈ ጉባኤዋ "ህወሓት" ድንገት በከፈተው የከባድ መሳሪያ ጥቃት 107 ህፃናትን፣ 89 ሴቶችን እና 44 አዛውንቶችን ህይወት ተቀጥፏል፤ በርካቶች ተጎድተዋል፤ በመጋዝን የነበረ የአስቸኳይ እርዳታም ሙሉ በሙሉ ወድሟል ሲሉ አስታውሰዋል። የተፈፀመውን ኢ ሰብአዊ ድርጊት ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች በያሉበት ሆነው እንዲቃወሙና እንዲያወግዙ የክልሉ መንግስት ጥሪ አቅርቧል። Broadcast & media production company ⌛️ አለም አቀፋዊነት 🌐 🌐 🌐 ⌛️ ወቅታዊነት ⌚️🕰🎙 ⌛️ ተደራሽነት 📲💻📡📺 ⌛️ ሚዛናዊነት ⚖ ⚖ ⚖ ከኛ ጋር ይሁኑ | ያጋሩ https://t.me/ethiomereja0 https://t.me/ethiomereja0

ህገወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር ፦ #1 - የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን 19 ክላሽ እና 2 ብሬን ሕገ ወጥ የጦር መሳሪያዎች በሆለታ ከተማ በቁጥጥር ስር ውለዋሉን ሪፖርት አድርጓጋ። ሕገ ወጥ የጦር መሳሪያዎቹ በመኪና ተጭነው ከጋምቤላ ወደ ባህርዳር እየተወሰዱ እያሉ ነው በሆለታ ከተማ ከእነ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር የዋሉት። #2 - የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በቡታጅራ ከተማ 35 ክላሽንኮቭ ሕገ ወጥ የጦር መሳሪያዎች ከጥይት መያዣ ካርታዎች ጋር በቁጥጥግ ስር ማዋሉን ሪፖርት አድርጓል። ህገወጥ መሳሪያው በ2 ተሽከርካሪዎች ተጭኖ ሲጓጓዝ የነበረ ነው። መሳሪያውን ሲያዘዋውሩ የነበሩ 3 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል። ምንጭ፦ የደቡብ ክልል ፖሊስ እና የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ Broadcast & media production company ⌛️ አለም አቀፋዊነት 🌐 🌐 🌐 ⌛️ ወቅታዊነት ⌚️🕰🎙 ⌛️ ተደራሽነት 📲💻📡📺 ⌛️ ሚዛናዊነት ⚖ ⚖ ⚖ ከኛ ጋር ይሁኑ | ያጋሩ https://t.me/ethiomereja0 https://t.me/ethiomereja0

የደቡብ ክልል መንግስት ተጨማሪ የክልሉን ፀጥታ ኃይሎች ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ ክፍል ለማሰማራት ዛሬ የሽኝት መርሃ ግብር እያካሄደ ይገኛል። የሽኝት መርሐ ግብሩ በሀዋሳ ከተማ ነው እየተካሄደ የሚገኘው። የደቡብ ክልል ልዩ ሀይል ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ ክፍል የግዳጅ ቀጠና ሲሰማራ ይህ ለሁለተኛ ዙር ነው። ከጥቂት ቀናት በፊት ክልሉ የልዩ ሀይል አባላትን ወደ ግዳጅ ቀጠና ማሰማራቱ ይታወሳል። Broadcast & media production company ⌛️ አለም አቀፋዊነት 🌐 🌐 🌐 ⌛️ ወቅታዊነት ⌚️🕰🎙 ⌛️ ተደራሽነት 📲💻📡📺 ⌛️ ሚዛናዊነት ⚖ ⚖ ⚖ ከኛ ጋር ይሁኑ | ያጋሩ https://t.me/ethiomereja0 https://t.me/ethiomereja0

#Afar የአፋር ክልል የአደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጽ/ ቤት አፋር ክልል ከትግራይ እና ከአማራ ክልሎች ጋር በሚዋሰንበት አካባቢ የተከሰተውን ግጭት ተከትሎ ከ70,000 በላይ ሰዎች መፈናቀላቸውን አሳውቋል። ይህንን ይፋ ያደረጉት የፅህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ መሐመድ ሁሴን ለቢቢሲ በሰጡት ቃል ነው። ነዋሪዎቹ የተፈናቀሉት ከቅዳሜ ጀምሮ በክልሉ ዞን 4፣ ፋንቲረሱ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ግጭት በመፈጠሩ ነው ብለዋል። ይህ አካባቢ ከአማራ ክልልና ከትግራይ ክልል ጋር የሚዋሰን አካባቢ መሆኑን ያነሱት ኃላፊው የትግራይ ታጣቂ ኃይሎች ያን ጥሰው ገብተው በአካባቢው ከነበረው ማኅበረሰብ ጋር ግጭት ውስጥ ገብተዋል ብለዋል። እሰከ ትላንት ምሽት ድረስ ከጎሊና፣አውራ እንዲሁም ኡወና ቴሩ ከሚባሉ ወረዳዎች ከ70 ሺ በላይ ሰዎች መፈናቀላቸውን ሪፖርት አድርገዋል። ግጭቱ እየተስፋፋ ከሄደ የተፈናቃዮች ቁጥር ሊጨምር ይችላል የሚሉ ስጋቶች መኖራቸውን ጠቅሰው "በአጠቃላይ ግማሽ ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ ስጋት ውስጥ እንዳለ ለተመድና ለእርዳታ ድርጅቶች መልዕክት አስተላልፈናል" ብለዋል። ክልሉ እስካሁን ባለው አቅም ለ1ሺ ሰው የሚሆን ምግብ አልባሳት እና የህጻናት ምግብ አጋጉዟል ብለዋል። ለጋሽ ድርጅቶች ተፈናቃዮችን እንዲረዱ ንግግር እንደተጀመረ፤ ለፌደራል መንግሥት ጥያቄ ማቅረባቸውንና አስቸኳይ ምላሽ እንደሚጠብቁ ገልጸዋል። Broadcast & media production company ⌛️ አለም አቀፋዊነት 🌐 🌐 🌐 ⌛️ ወቅታዊነት ⌚️🕰🎙 ⌛️ ተደራሽነት 📲💻📡📺 ⌛️ ሚዛናዊነት ⚖ ⚖ ⚖ ከኛ ጋር ይሁኑ | ያጋሩ https://t.me/ethiomereja0 https://t.me/ethiomereja0