en
Feedback
🇪🇹ኢትዮ-News መረጃ

🇪🇹ኢትዮ-News መረጃ

Open in Telegram

Broadcast & media production company ⌛️ አለም አቀፋዊነት 🌐 🌐 🌐 ⌛️ ወቅታዊነት ⌚️🕰🎙 ⌛️ ተደራሽነት 📲💻📡📺 ⌛️ ሚዛናዊነት ⚖ ⚖ ⚖ ከኛ ጋር ይሁኑ | ያጋሩ https://t.me/ethiomereja0 https://t.me/ethiomereja0

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
7 778
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
#AU የኢትዮጵያ መንግስት እና የህወሓትን የሰላም ንግግር በተመለከተ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ሙሳ ፋኪ ማህማት መግለጫ አውጥተዋል። በመግለጫው ምን አሉ ? - የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት #ለመጀመሪያ ጊዜ ፊት ለፊት የተገናኙበት የሰላም ንግግር ዛሬ በደቡብ አፍሪካ ተጀምሯል። - በሰላም ንግግሩ ላይ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ድርጅት (IGAD) የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ፣ የአሜሪካ መንግስት ተወካዮች በታዛቢነት እየተሳተፉ ነው። - ደቡብ አፍሪካ የሰላም ንግግሩን ለማስተናገድ ፍቃደኛ ስለሆነች ለሀገሪቱ መንግስት እና ለፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፖሳ ምስጋና አቅርበዋል። - ሙሳ ፋኪ ማሀመት የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት የኢትዮጵያን ጥቅም ባስጠበቀ ሁኔታ ሰላምን ለማስፈን እና ለግጭቱ ዘላቂ ፖለቲካዊ መፍትሄ እንዲገኝ ለማስረግ ባሳዩት ቁርጠኝነት ይበልጥ እንደተበረታቱ ገልፀዋል። - የአፍሪካ ህብረት " የሰላም ንግግር " ተሳታፊ ወገኖች ኢትዮጵያ፤ በኢትዮጵያውያን ባለቤትነት እና በአፍሪካ ህብረት መሪነት ሰላም እንዲሰፍን ፣ የተረጋጋችና አንድነቷ የተጠበቀ እንድትሆን ህብረቱ ድጋፉን እንደሚቀጥል ቁርጠኛ መሆኑን ገልፀዋል። https://t.me/ethiomereja0

«የብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶ/ር ይናገር ደሴ ፦ - ኢትዮጵያዊያን በግለሰብ ደረጃ ከ100 ሺህ ብር በላይ ለድርጅቶች ደግሞ ከ200 ሺህ ብር በላይ ቤት ውስጥ ማስቀመጥ የተከለከለ መሆኑን መገንዘብ ይኖርባቸወል። - ገንዘብ በባንክ መቀመጥ አለበት ፤ የግብይት ስርዓትም በባንክ ማካሄድ ይቻላል። - መመሪያው ከሚፈቅደው የገንዘብ መጠን በላይ አስቀምጦ የተገኘን አካል #የጠቆመ ግለሰብ 15 በመቶ የወረታ ክፍያ ይከፈለዋል። - በውጭ አገራት ገንዘብ ግብይት መፈጸምም ሆነ በህገወጥ መንገድ ይዞ መገኘት አይቻልም። - ወርቅን በህገወጥ መልኩ ቤት ውስጥ ማከማቸት የማይቻል ሲሆን በህገወጥ መልኩ ወርቅን ያከማቸ ግለሰብ ለጠቆመ ግለሰብ ባንኩ በወቅቱ ባለው ግብይት የ15 በመቶ ወረታ ይከፈለዋል። - በህገወጥ የሃዋላ የውጭ አገራት የተሰማሩ አካላትን ለጠቆመም እስከ 25 ሺህ ብር ወረታ ይከፈለዋል። - በህገወጥ ገንዘብ ህትመት የተሰማሩ አካላትን ያጋለጠም ከ20 ሺህ እስከ 200 ሺህ ብር ወረታ ይከፈለዋል። - ጠቋሚዎች ወረታውና ሽልማቱ የሚበረከትላቸው #ደህንነታቸው እና #ሚስጥራዊነታቸው በተጠበቀ መልኩ ነው። Credit : ENA» https://t.me/ethiomereja0

አሜሪካ ሱዳንን አስጠነቀቀች። በሱዳን የአሜሪካ አምባሳደር ጆን ጎድፍሬይ ፤ ካርቱም ሩሲያ በቀይ ባህር ዳርቻ የጦር ሰፈር እንድትመሰርት ከፈቀደች ከባድ መዘዝ እንደሚኖረው አስጠንቅቀዋል። ከ25 ዓመታት በኋላ በሱዳን የመጀመርያው የአሜሪካ አምባሳደር የሆኑት ጎድፍሬይ እንዲህ ዓይነት ውሳኔ ሱዳንን ከዓለም አቀፉ ማህበረሰብ መነጠል ብቻ ሳይሆን ጥቅሟን የሚጎዳ ነው ሲሉ አስገንዝበዋል። አምባሳደር ጎድፍሬይ ከሱዳን አል ታይያር ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ፤ "ሩሲያ በቀይ ባህር ላይ የጦር ሰፈር ለመመስረት እ.ኤ.አ. በ2017 ከስልጣን ከተወገዱት ፕሬዝዳንት ኦማር አልበሽር ጋር የተፈራረመችውን ስምምነት ተግባራዊ ለማድረግ እየሞከረች ነው የሚሉ አንዳንድ ሪፖርቶች አሉ"  ብለዋል። አልበሽር ለወራት የዘለቀን ተቃውሞ ተከትሎ ከስልጣን የተወገዱት በሚያዝያ 2019 እንደነበር ይታወቃል። የአሜሪካው ዲፕሎማት " የሱዳን መንግስት የጦር ሰፈሩ (የሩስያ) እንዲቋቋም እንዲቀጥል ከወሰነ ወይም እንደገና ለመደራደር ከወሰነ ለሱዳን ጥቅም ጎጂ ነው " ሲሉ አስጠንቅቀዋል። " ሁሉም አገሮች ከየትኞቹ አገሮች ጋር አጋር እንደሚሆኑ የመወሰን ሉዓላዊ መብት አላቸው " ያሉት አምባሳደሩ " ነገር ግን እነዚህ ምርጫዎች በእርግጥም መዘዝ አላቸው " ሲሉ አፅንዖት ሰጥተዋል። እንደ ዲፕሎማቱ ገለጻ አሜሪካ በሱዳን አዲስ በሲቪል የሚመራ መንግስት እና ሀገሪቱን ወደ ዲሞክራሲያዊ ጎዳና የሚመልስ የሽግግር ማእቀፍ ለማየት ትፈልጋለች። እ.ኤ.አ ህዳር 2017 ሱዳን እና ሩሲያ በወታደራዊ ስልጠና፣ የልምድ ልውውጥ እና የጦር መርከቦችን ወደ ሁለቱ ሀገራት ወደቦች ለማስገባት የትብብር ስምምነቶችን ተፈራርመዋል። ያንብቡ : telegra.ph/Sudan-Tribune-09-29 ምንጭ፦ ሱዳን ትሪቢዩን https://t.me/ethiomereja0

#ጋምቤላ የጋምቤላ ክልል መንግስት የኢሰመኮን ሪፖርት "ለጠላት የወገነ ነው " ሲል ገልጾ ሪፖርቱን እንደማይቀበለውና እንደሚያወግዘው ገለፀ። የጋምቤላ ክልል፤ "ኢሰመኮ ሰኔ 7/2014 ዓ.ም በጋምቤላ ክልል ጋምቤላ ከተማ ላይ ተፈጥሮ በነበረው ውጊያ ተከትሎ በክልሉ ልዩ ኃይሎች፣ ሚሊሽያ እና ተባባሪ ወጣቶችን ሲመሩ የነበሩ አመራሮች አማካይነት ደረሰ ባላቸው የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ላይ ያወጣውን ሚዛናዊነት የጎደለውና የአንድ ክልል የፀጥታ ተቋምን ከተራ የአሸባሪ ቡድን ተላላኪ ጋር በአንድነት ያየ" ነው ሲል ገልጿል። ሪፖርቱ "ከሁሉ በላይ በክልልና በአገር ላይ ይደርስ የነበረ ከፍተኛ ጥቃት በመቀልበስ ሂደት የህይወት መስዋዕትነት የከፈለውን የፀጥታ ተቋማችንን በጅምላ የፈረጀና የተገኘውንም ድል በዜሮ ያባዛ ሆኖ አግኝቶታል" ብሏል። በዚህም የጋምቤላ ክልል መንግሥት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የምርመራ ሪፖርት እንደማይቀበለውና አጥብቆ እንደሚያወግዘው ገልጿል። አክሎም "የክልሉ መንግሥት ምንም እንኳን አንድም የዜጋ ህይወት እንዲጠፋ የሚፈቅድ ባይሆንም በጥፋት ቡድኖቹ በተከፈተብን ጥቃት ከንፁሃን ዜጎች እንዲሁም የፀጥታ አካላት ህይወት መጥፋት ጋር ተያይዞ ኮምሽኑ ያወጣው የምርመራ ሪፖርት ግኝት እጅግ የተጋነነ እና በወቅቱ መሬት የነበረውን ጥሬ ሀቅ ያላገናዘበ" ነው ብሏል። "የኢትዮጵያ ህዝቦች በጋምቤላ ከተማ ውስጥና ኦነግ ሸኔና ጋነግ የፈፀሙት ወረራና ጥቃት ብዥታ ተፈጥሮ የክልሉን መንግሥት እና ህዝብ በወቅቱ የተደረገውን ተጋድሎና ለዚህም የተከፈለውን መስዋዕትነት በዜሮ ያባዛ፤ ከሁሉ በላይ የክልሉን የፀጥታ ኃይል ሞራል የሚያዳክም፤ ፀረ-ሠላም ኃይሉንና መንግሥትን በአንድ ሚዛን ላይ አድርጎ ያየ በአጠቃላይ ለጠላት የወገነ ሪፖርት ሆኖ አግኝተነዋል" ሲል አሳውቋል። https://t.me/ethiomereja0

#EHRC የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጳጉሜ 1 ቀን 2014 ዓ.ም. በኦሮሚያ ክልል፣ ሆሮጉዱሩ ወለጋ ዞን አሙሩ ወረዳ በሲቪል ሰዎች ላይ የደረሰን ግድያ አስመልከቶ ባወጣው መግለጫ በዞኑ የተለያዩ ወረዳዎች ተጨማሪ የጸጥታ ሥጋቶች በመኖራቸው በታጠቁ ቡድኖች በሲቪል ሰዎች ላይ ብሔርን መሰረት ያደረጉ ተጨማሪ ጥቃቶች እንዳይፈጸሙ ለመከላከል በትኩረት እንዲሠራ ማሳሰቡን ይታወሳል። ኢሰመኮ በአካባቢው ሲቪል ሰዎችን ኢላማ ያደረጉ ጥቃቶች አሁንም ተሰፋፍተው መቀጠላቸው ገልጾ እጅግ አሳሳቢ መሆኑን አስገንዝቧል። በዞኑ በአሙሩ፣ በሆሮ ቡልቅ እና በጃርደጋ ጃርቴ ወረዳዎች ከነሐሴ 25 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ ባሉት ሦስት ሳምንታት ውስጥ ብቻ በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (በተለምዶ ኦነግ ሽኔ)፣ በአማራ ኢመደበኛ ታጣቂ ኃይሎች እና ግለሰቦች በተከታታይ በተፈጸሙ ጥቃቶች ከ100 በላይ ሲቪል ሰዎች የተገደሉ መሆኑ ታወቋል ሲል ኢስመኮ ገልጿል። እንዲሁም የግል ንበረት እና የቁም ከብቶች መዘረፋቸውን ፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎችም ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው ያለበቂ የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦት በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይ የሚገኙ መሆኑን ኮሚሽኑ ከተጎጂ ቤተሰቦች፣ ከአካባቢው የፍትሕና የአስተዳደር አካላት እንዲሁም በአካባቢው ከሚንቀሳቀሱ የእርዳታ ድርጅቶች ያሰባሰብኳቸው መረጃዎች እና ማስረጃዎች ያሳያሉ ብሏል። የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ " የክልሉ አና የፌዴራል መንግሥታት በአካባቢው ብሔርን መሰረት አድርገው የሚፈጸመው ጥቃቶችን ለመከላከል በመወሰድ ላይ የሚገኙትን እርምጃ ችግሩን በሚመጥን ደረጃ በማሳደግ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ሊወጡ ይገባል" ሲሉ በድጋሚ አሳስበዋል። https://t.me/ethiomereja0

#EthioTelecom ኢትዮ ቴሌኮም የ " ኢ-ሲም " አገልግሎት መጀመሩን ገልጿል። " ኢ-ሲም " በቀላሉ ከስልክ ቀፎ ጋር በማናበብ ብቻ የሞባይል ስልክ አገልግሎት ማግኘት የሚያስችል አዲስ ቴክኖሎጂ ሲሆን ኢትዮ ቴሌኮም በአዲስ አበባ ፤ " ቸርችል ጎዳና " በሚገኘው የፕሪሚየም አገልግሎት ማዕከሉ ማግኘት እንደሚቻል አሳውቋል። በቅርቡ ፤ በሁሉም የአገልግሎት መስጫ ማዕከሎቹ አገልግሎቱን መስጠት እንደሚጀምር ገልጿል። የኢ-ሲም አገልግሎት የሚሰጣቸው ጥቅሞች ምንድናቸው ? - ቀላል እና ብቁ የኔትወርክ ግንኙነት፤ - በአንድ ስልክ ከአንድ በላይ የአገልግሎት ቁጥር መጠቀም የሚያስችል፤ - ሲም ካርድ እየቀያየሩ መጠቀምን ያስቀራል፤ - ላፕቶፕ ፣ ስማርት ሰዓት ፣ ታብሌት የመሳሰሉትን በቀላሉ ለማገናኘት ፣ ለአምራቾች፣ አከፋፋዮች እና አገልግሎት ሰጪዎች፣ ለትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች እንዲሁም የተለያዩ ዲጂታል ዲቫይሶችን በቀላሉ በማገናኘት ቀልጣፋ አገልግሎት የማግኘት ፍላጎት ላላቸው ሁሉ የቀረበ መሆኑን ኢትዮ ቴላኮም ገልጿል። በኢ-ሲም የሚሰሩ ስልኮች የትኞቹ ናቸው ? #Samsung 📱Samsung Galaxy S20 📱Samsung Galaxy S20+ 📱Samsung Galaxy S20 Ultra 📱Samsung Galaxy S21 📱Samsung Galaxy S21+ 5G 📱Samsung Galaxy S21+ Ultra 5G 📱Samsung Galaxy S22 📱Samsung Galaxy S22+ 📱Samsung Galaxy Note 20 📱Samsung Galaxy Note 20 Ultra 5G  📱Samsung Galaxy Fold 📱Samsung Galaxy Z Fold2 5G 📱Samsung Galaxy Z Fold3 5G 📱Samsung Galaxy Z Flip #iPhone 📱iPhone XR 📱iPhone XS 📱iPhone XS Max 📱iPhone 11 📱iPhone 11 Pro 📱iPhone SE 2 (2020) 📱iPhone 12 📱iPhone 12 Mini 📱iPhone 12 Pro 📱iPhone 12 Pro Max 📱iPhone 13 📱iPhone 13 Mini 📱iPhone 13 Pro 📱iPhone 13 Pro Max 📱iPhone SE 3 (2022) #Google 📱Google Pixel 3a XL 📱Google Pixel 4 📱Google Pixel 4a 📱Google Pixel 4 XL 📱Google Pixel 5 📱Google Pixel 5a 📱Google Pixel 6 📱Google Pixel 6 Pro. 📱Google Pixel 3 XL 📱Google Pixel 2 XL #Huawei 📱Huawei P40 📱Huawei P40 Pro 📱Huawei Mate 40 Pro #Motorola 📱Motorola Razr 2019 📱Nuu Mobile X5 📱Gemini PDA 📱Rakuten Mini #Oppo 📱Oppo Find X3 Pro 📱Oppo Reno 5A 📱Oppo Reno6 Pro 5G #eSIM #DigitalSIM #EthioTelecom https://t.me/ethiomereja0

"ህይዎት በፈረቃ ናትና ታገስ‼" ምድራዊ ህይዎት ተፈጥሮዋ ፈረቃ ነው።ፍፁም ተድላና ፍፁም ችጋር የሚባል ነገር የለም። ደስታና ሀዘን፣ረሃብና ጥጋብ፣ህይዎትና ሞት፣ብርሃንና ፅልመት፣ትዳርና ፍቺ፣ጤና እና ህመም፣ልፋትና እረፍት፣ጦርነትና ሰላም፣ትርፍና ኪሳራ፣ክረምትና በጋ፣መውደቅና መነሳት፣ዕውቀትና ድድብና፣ሁከትና ፀጥታ፣ችኮላና እርጋታ፣..........የዚች አለም የፈረቃ ገፆች ናቸው። ትናንት ድሃ የነበሩ አገሮች ዛሬ በሃብታቸው አለምን እየገዙት ነው።ተሰብረው የነበሩት ተጠግነው መራመድ ችለዋል።የተጣሉት ታርቀው ወዳጅ ሆነዋል።የተናቁ የነበሩት ዛሬ አለም እየሰገደላቸው ነው።መካኖች ልጅ ወልደው ስመዋል፣ሃያላን ተሰባብረው ጎዳና ላይ ወድቀዋል፣............. ዋናው ነገር ሁለቱንም ፈረቃዎች በትዕግስትና በጥበብ ማስተናገድ ነው።የክረምቱ ወጀብ ተገልጦ የበጋው ፀሃይ እንደሚበሰረው ሁሉ ዛሬ ያለንበት የችግር ዶፍ አባርቶ የብልፅግናችንን ፀደይ የምናይበት ጊዜ ሩቅ አይደለም። ዛሬ ላይ ጠላት ቢበዛም ነገ መበተኑ አይቀሬ ነው።የዛሬው መጥፎ ገጠመኝ ለነገው ብሩህ ተስፉ ቦታውን ለቆ መሄዱ የጊዜ ጉዳይ እንጂ ግደታ ነው።ዛሬ በጥጋብ የፈነጩብን ነገ እንደማያፍሩ ዋስትና የላቸውም። የዛሬ መከረኛ ሌሊቶች በነገ የማለዳ ጮራዎች ተገፈው ያነቡ አይኖች ይታበሳሉ።ያስቸገሩን ኮረብታዎች ሁሉ በተባበረ ክንዳችን ይደረመሳሉ።የወጋን ቡዳ ማርከሻውን ሲያገኝ ይረክሳል።ሊፈጀን ያሰፈሰፈው ባቀጣጠለው እሳቱ ተቃጥሎ አመድ ሆኖ ይበናል። ወሎዬውና ትዕግስት አብሮ አደግ ናቸው።ከስልጣን ያወረዱትን፣ከማህበራዊ መስተጋብሩ ያገቱትን፣በኢኮኖሚ ማዕቀብ አሳምመው የቀጡትን፣በቀዬው ባይታወር ያደረጉትን ሁሉ በትዕግስት ትቷቸው እያለፈ ዛሬ ላይ ደርሷል። ዛሬና ትናንት ፍፁም አንድ አይደሉም።ፀንፈኝነት፣አግላይነት፣ደሴትነቴ፣ከፋፋይነት፣ስግብግብነት፣በኪነት መግዘፍ፣ቤት ዘግቶ መብላት፣ወዘተ የፍፃሜ ጊዚያቸውን ሊያገኙ የመጨረሻው ትራክ ላይ ደርሰናል።የሚጠበቅብን ሁነቶችን በትዕግስት፣በጥበብና በስራ አጅቦ ማስተናገድ ብቻ ነው።"ቀን አለና ቀና ብለህ ተራመድ "እንዲሉ በዛሬው የችግር ናዳ አንገትህን ደፍተህ ከመራመድ ይልቅ የነገውን የተስፋ ጮራ እያማተርክ ቀና ብለህ ተራመድ። እናም አብሽሩ!ሁሉም ለበጎ ነው!እርጎ ካልተገፋ ቂቤ አይወጣውም።እንጨት ካልጨሰ አይነዲም።ሻይ ካልተማሰለ ጣዕሙ አይታወቅም።በእርግጥም ከችግር በኋላ ድሎት አለና አይዞን!ነገ የእኛ አንገት ቀጥ ብሎ የግፈኞች አንገት መሰበሩ አይቀሬ ነው። https://t.me/ethiomereja0

መረጃዎች በፍጥነት ለሁሉም እንዲደርሱ ሊንኩ ሼር ማድረግን አይርሱ! https://t.me/ethiomereja0

ሰበር ዜና አሸባሪው ህውኀት ቆቦ ከተማን ተቆጣጠረ!

የሰው ልጅ ይህን ያክል ጭካኔ ጫፍ ላይ የደረሰበት አሳዛኝ ቪድዮ ነው! ይህ የምታዩት ወንድም ወንድሙን የሚደግልበት ቪድዮ ያሳዝናል! እንደዚህ አይነት ስራ እየተሰራ እንዴት ነው ታዲያ አምላክ ሊያዝንልን የሚችል!

ቻናሉን ጆይን ብላቹህ ብትገቡ ብዙ ጥቅም ታገኙበታላቹህ!

Repost from N/a
#ሼር አደርጉት! ከመጠን በላይ ማሰብ እራስን እና ልብን ያደክማል። ሁሉም ነገር ደግሞ ከራስህ አይበልጥም! ለራስህ ለነፍስህ መጀመሪያ ኑር! https://t.me/mameman520 የዩቱብ ቻናል! ht
#ሼር አደርጉት! ከመጠን በላይ ማሰብ እራስን እና ልብን ያደክማል። ሁሉም ነገር ደግሞ ከራስህ አይበልጥም! ለራስህ ለነፍስህ መጀመሪያ ኑር! https://t.me/mameman520 የዩቱብ ቻናል! https://youtu.be/pEPhCB6pyHU

ወለጋ ላይ ለሚገኙት አማራ ተወላጆች እና ሰኡዲ አረቢያ ለሚገኙ ንፁሀን ዜጎች ሁላችንም ድምፅ ልንሆን ይገባል የሁላችንም ወገን ናቸው! ስለዚህ መንግስት የወለጋን አምሀራዎችና የሳኡዲ ታሳሪ ኢትዮጵያዊያኖች ዝምታን እያበዛ ህዝባችን እየተጎዳ ነው። በሁሉም ሀገር ሰላማዊ ሰልፍ በመውጣት ማውገዝ አለብን! ሰብዓዊነት ለሚስኪኑ ህዝብ ሊኖረን ይገባል! https://t.me/ethiomereja0

#ሼር #ሼር ዛሬም ሰኡዲ አረቢያ እስርቤት ላይ አንድ ሞቷል! አሰላሙአለይኩም ወረህመቱሏሂ ወበረካቱህ እንዲሁም ክርስቲያን ወገኖቻችን ሰላም ለሁላቹህም! በሳኡዲ አረቢያ የሚገኙ ኢትዮጵያዊ ዜጎች ላይ
+3
#ሼር #ሼር ዛሬም ሰኡዲ አረቢያ እስርቤት ላይ አንድ ሞቷል! አሰላሙአለይኩም ወረህመቱሏሂ ወበረካቱህ እንዲሁም ክርስቲያን ወገኖቻችን ሰላም ለሁላቹህም! በሳኡዲ አረቢያ የሚገኙ ኢትዮጵያዊ ዜጎች ላይ የሚደርሰውን ግፍ መንግስት በእንዝላልነት እያየ ዝም ብሏል እና በሁሉም ኢትዮጵያ ክልሎች ሞቅ ሰላማዊ ሰልፍ ጉዳዩን በቃ በሎ የሚያሳውቅ ያስፈልገናል! እንነሳ! በመቀጠል በወለጋ አፋር ክልል ላይ የሚደረጉ እልቂቶችንም ትኩረት በማጣት ማህበረሰባችን እያለቀ ነው። ከዚህ በላይ መታገስ የሚኖርብን አይመስለኝም ሞቅ ያለ ውግዘት በሁሉም ቦታ ያስፈልገናል! እንነሳ! መብታችንን ተነስተን እንጂ አልቅሰን ማንም መቼም አይታዘንልም አይደርስልንም!

ጆይን ብላቹህ ተቀላቀሉት!

የሰው ልጅ ሲፈልግ #ተአምረኛ ነው ካልፈለገ ደግሞ ስበበኛ ነው! ስለዚህ አንተ ታአምር የመስራት እድል እያለህ ለምን አትሰራም? እንዳንተ አይነቱ ምንም የሌለው አለምን ጉድ ያስባለ ታዋቂ ሁኖ አይደል! ስለዚህ አንተ አሁን ባለህበት ጊዜ ተአምር የምትሰራበት ነውና ተነስ ወኔህን አንቀሳቅስ እና ወደ ስራ ግባ ፅናት ይኑርህ በርግጠኝነት ተአምር ትሰራለህ! https://t.me/mameman520

ይሄ ሊንክ ይጠቅማቹሀል!

ጠቃሚ ቪድዮወችን ይለቃል እየገባቹህ ብትመለከቱት ትጠቀሙበታላቹህ!

🔥ለህይወት መንገዳችን ምን ያስፈልገናል? በተማሪዎች የተዘጋጀ አነቃቂ ፅሁፎች ና ጥቅሶች.... በዚህ ቻናል #ለፕሮፋይል የሚሆኑ አዳዲስ ጥቅሶችን ይገኛሉ።