ናፍቆት
Open in Telegram
ሀያሉ ፍቅር ሳይሆን ናፍቆት ነው መናፈቅ ከባዱ ስቃይ ነው በርግጥ ፍቅርም ሀያል ነው ግን ደሞ ናፍቆት ከፍቅር ይበረታል ፍቅርን ፍቅር ያስባለው በመናፈቅ ውስጥ ያለው ደስታና ሀዘን የስሜት መዘበራረቅ ነው ።
Show more1 296
Subscribers
No data24 hours
+117 days
+5430 days
Posts Archive
1 296
የጻፍኩትን ቃል ብዙ ሰዎች ሲያነቡ፣ ሲያስቡበት፣ ሲሰማቸው… ዝም ብዬ ፈገግ እላለሁ። 😊
ምክንያቱም ከቃላት በላይ የሆነ ነገር እየተፈጠረ ነው፤
ልቤ የጻፈው ነገር ወደ ሌሎች ልቦች እየደረሰ ነው። ❤️🔥
ሰዎች በጽሁፌ ላይ ትኩረት ሲያደርጉ፣ የሚያስደስተኝ የታየሁ መሆኔ አይደለም…
የተሰማሁ መሆኔ ነው። 🥹
አንድ ቃል ከኔ ወጥቶ በአንድ ሰው ልብ ውስጥ ቦታ ሲያገኝ—
ያኔ ጽሁፌ ሕይወት አግኝቷል። ✍️
እናንተ ስታነቡልኝ…
እኔ ደግሞ ከልቤ እጽፋለሁ። 🌹
# እናት
1 296
በህይወቴ ውስጥ የጎዱኝ ሰዎች ቢኖሩም አልጠላቸውም በርግጥ አጥፍተዋል፥ምናልባትም የመጡበት መንገድ አጥፍቶአቸዋል።እነሱን ሳይሆን ያመጣቸውን መንገድ እጠላለሁ! በዛም መንገድ ደግሜ ላልሄድ ለራሴ እምላለሁ።
የሰው ልጅ ክፋ እና ደጉን መለየት ከጀመረ ጀምሮ ሁለት ሐሳብ ወደ ጭንቅላቱ ይመላለሳል ክፉ እና ደግ ፥የሰው ልጅ ክፉ ሐሳብ ስላሰበ ወቀሳ የለበትም።ክፉን ሐሳብ ተቀብሎ ሲተገብረው እንጂ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
አንዳንዴ ሳስበው ከሚያውቀኝ ሰው የማያውቀኝ ሰው ይሻላል ተዋውቆ ከሚፈርድብኝ ብዬ እኮ ነው
አንዳንድ ሰው ይገርኛል ሳልጠራቸው ይመጡና ነይ ተነሽ የሆነ ቦታ እንሂድ ይሉኛል እርቀን ከተጓዝን በኋላ፥የት ነበር የምትሄጅው? ይሉኛል።
ግራ ይገባኛል የት ነበር የምሄደው?
ያመኛል እንዴ?
ደህና እደሩልኝ
# እናት
1 296
Kindly Reminder, in this life Today’s pain ህመም ለዘላለም አይቆይም, Believe me 🤍
ሕይወት እንደ መጽሐፍ ናት። እያንዳንዱ ምዕራፍ የራሱ ታሪክ አለው። አንዳንዶቹ በእንባ ይሞላሉ፣ ሌሎቹ በሳቅና በደስታ። ነገር ግን ታሪኩ አይቆምም ወደ ፊት ይቀጥላል።
ዛሬ የሚሰማህ ህመም ለዘላለም አይቆይም። አንድ ቀን ወደ ኋላ ተመልሰህ ያለፍከውን ሁሉ በፈገግታ ታስታውሰዋለህ 😉፤ ምክንያቱም ከከባዱ ምዕራፍ አልፈህ ወደ መልካሙ ክፍል ትደርሳለህ።
“የሕይወት በጣም ውብ ገጾች ብዙ ጊዜ ከአስቸጋሪዎቹ ምዕራፎች በኋላ ይመጣሉ። ስለዚህ መጽሐፉን አትዝጋ ታሪክህ ገና እየተጻፈ ነው።”
ቀጥል። ተስፋ አትቁረጥ። በጣም ውብ ቀናትህ ገና ከፊትህ ናቸው።
# እናት
1 296
የኔ ሰዎች
ውድ ዋጋ ስለከፈልንበት ብቻ የሚያቆስለንን ጫማ አውልቀን ከመጣል ወደኋላ አንልም! 👟💔
በህይወታችንም ውስጥ ልክ እንደዚህ ጫማ ብዙ ጊዜ፣ ጉልበት ወይንም ስሜት አፍስሰንባቸው ነገር ግን የውስጥ ሰላማችንን የሚነሱ ነገሮች ያጋጥሙናል። "እስካሁን ብዙ ለፍቼበታለሁ" ወይንም "ብዙ ዋጋ ከፍዬበታለሁ" በሚል ሰበብ ብቻ ህመሙን ችለን መቀጠል የለብንም።
የቱንም ያህል ዋጋ ቢከፈልበት፤ ሰላማችሁን የሚነሳና ወደ ኋላ የሚጎትታችሁን ግንኙነት፣ ስራ ወይም ልማድ አውልቃችሁ ለመጣል አትፍሩ።
ከምንም ነገር በላይ የራሳችሁን ደህንነት እና የውስጥ ሰላም አስቀድሙ! ✨
ደህና እደሩልኝ✨👐
# እናት
1 296
የሆነ ቦታ ላይ በጣም በፍጥነት የሚፈስ ግዙፍ ወንዝ አለ ብዬ አስባለሁ። በዚያ ወንዝ ውስጥ ሁለት ሰዎች አሉ። እርስ በእርሳቸው እንዳይወሰዱ አጥብቀው ተቃቅፈዋል፣ ነገር ግን የወንዙ ጉልበት በጣም ጠንካራ ስለሆነ መለያየታቸው ግድ ነው፡፡ በመጨረሻም እጃቸውን ለቅቀው በየራሳቸው አቅጣጫ በውሃው ይወሰዳሉ። የኛም ህይወት እንደዚሁ ነው፡፡ እስከመጨረሻው አብረን ለመቆየት ብንመኝም፣ ጊዜና እጣ ፈንታ እንደዚያ ወንዝ ነጥቀው ይወስዱናል። ማንም ሰውን ለዘላለም ይዞ ማቆየት አይችልም፡፡"
📚ርዕስ፦የተሰበሩ ክንፎች
✍️ደራሲ፦ካህሊል ጂብራን
# እናት
1 296
የኔ ሴት ✨
ነገሮችን ባላየ ማለፍን ልመጂ...... የማይጠቅሙሽን ነገሮች!
ህይወትሽ ላይ ምንም የማይጨምርና ...የማይቀንሱን ነገሮች በመዝለል ላይ በርቺ .....ትተሽ ያለፍሻቸውን ነገሮች ዞረሽ ባለማየት ላይ ጀግኚ ......ላልሆንሻቸው ስያሜዎችሽ መልስ በመስጠት ላይ አትገኚ .......በቀኖችሽ ውስጥ የሚጠቅምሽን ብቻ ዝገኚ!
# እናት
1 296
መንገድ ላልጨለመው፣ ብርሃንም ሆኖ መሄድ ለደከመው
አንድ ጊዜ ቆመን፣ አይዞህ እንበለው
ያለውን ላላጣ፣ የሰውን ቁስል አብሮ ለታመመ
እጅ እንንሳ እስኪ፣ ራሱን አድምቶ ሌላውን ላከመ
አቅሙ ለተበላ፣ መንገዱን ላራቀ
ተስፋው ተንጠፍጥፎ፣ ተሟጦ ላለቀ
እስኪ አንድ ቆመን፣ አይዞህ እንበለው
ያልገደለን ነገር፣ ብርቱ ነው 'ሚያረገው!!!
👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏
# እናት
1 296
ሰው ሲደክም መከራከር ያቆማል።
ራሱን ለማስረዳት አይሮጥም።
ዝም ብሎ ይሄዳል።
እኔም አሁን የደረስኩበት ቦታ ያ ነው።
ሁሉም ሰው እንዲረዳኝ አልፈልግም።
ምክንያቱም አንዳንዶች ለመረዳት አይሰሙንም፤ ለመፍረድ ነው የሚሰሙን።
እና እውነት ልንገራችሁ…
ሰው በጣም ሲጎዳ ብዙ ማውራት ያቆማል።
ውስጡን እንደ ተቆለፈ ቤት ይዘጋዋል።
ምክንያቱም ያለውን ሁሉ ለማንም ማሳየት አይፈልግም።
አንዳንዴ ዝምታዬ እብሪት አይደለም…
ራሴን እየጠበቅኩ ነው።
ስለዚህ ይቅርታ…
የማብራራላቹ ማንነት የለኝም።
የቀረኝ ጉልበት ራሴን ለማረጋጋት ብቻ ነው።
# እናት
1 296
እነዛ የጫማችን ውበት ከውጭ አይተው ያደነቁልን ሰዎች...
የጫማችን ሶል ውስጡ ቀዳዳ ስለመሆኑ፣
በእያንዳንዱ እርምዳችን ውስጥ ስለወጋን እሾህና ጋሬጣ፣
ውስጥ እግራችን ላይ ስላለው ቁስል የት ያውቃሉ?
ተራምደን መድረሳችን እንጂ ህመማችን በምን ይረዳሉ?
አብረናቸው መንገድ መጀመራችን እንጂ አረማመዳችን መች ያስተውላሉ።
ካሰብነው ለመድረስ ሁሉን ችለነው እንጂ ቁጭ አድርጎ የሚያስተክዝ ብዙ ምክንያት ነበረን።
በአንድ ጫማ ውስጥ ያለውን ምቾት ወይም ስቃይ የምናውቀው ተጫምተነው ስንራመድ ብቻ ነው።
መሆን የመፍረድን ያክል ቀላል አይደለምና ፣ ሆነን ባልተገኘንበት አንፍረድ!
# እናት
1 296
የኔ ሰዎች እንዴት አደራችሁልኝ አንድ ሀሳብ ነበረኝ ብትቀበሉኝ ይሄንን ቻናላችንን ወደ ቲክቶክ ማሳደግ ብንችል እና ተጨማሪ ቤተሰብ ብናፈራ ምን ይመስላችኋል
ይኸው @hilina2313
እወዳችኋለሁ ዋሉልኝ
# እናት
1 296
"የኔ ልባም ሴት፣ 👸🏼❤️
ልባም መሆን ማለት ዝምተኛ መሆን ማለት አይደለም፤ ልባምነት ማለት መቼ መናገርና መቼ ዝም ማለት እንዳለብሽ ማወቅ ነው።
የኔ ልባም ሴት፣ አንቺ በዙሪያሽ ላሉት ሰዎች ብርሃን፣ ለቤተሰብሽ መከታ፣ ለራስሽ ደግሞ ኩራት ነሽ።
ብዙ ፈተናዎች ሊገጥሙሽ ይችላሉ፣ አለም ተስፋ እንድትቆርጪ ሊገፋፋሽ ይችላል። ነገር ግን አንቺ ውስጥ ያለው ያ የማይበገር የልባምነት መንፈስ "ገና ነኝ!" ይልሻል። እራስሽን ውደጂ፣ እውቀትሽን አሳድጊ፣ እናም በምትሄጂበት መንገድ ሁሉ በልበ ሙሉነት ተራመጂ።
አንቺ የጥበብ ምንጭ፣ የጽናት ተምሳሌት ነሽ።
ዛሬ የምታደርጊው ጥቃቅን በጎ ነገር ነገ ትልቅ ታሪክ ሆኖ ይነበባል። በርቺ፣ የኔ ልባም ሴት!
# እናት
1 296
እናም ልጅቷን ወደቤቴ ይዣት ሄድኩ ምግብ አልበላ ብሎኛል ለሷ ሰጠዃትና ግር ያሉኝን ነገሮች ጠየኳት የልጅቷ አወራር ጉድ ነው የሚያስብለው ቁመቷ አጭር የሆነች አሮጊት እንጂ 8 አመት ህጻን አትመስልም እናም ከእናቷ ጋር እንደማይስማሙ እሷን ማየት እንደማትፈልግ ነገራኝ እኔም መክሬ አባብዬ ተኛች ከአነጋገሩዋ በተኛሁበት ምታመልጠኝ ስለመሰለኝ ቁጭ ብዬ እየጠበኳት ነጋ
በጠዋቱ ቁርሷን ሰጥቼ እቃ ገዝቼ ልምጣ ብዬ አታልያት ወጣሁ ቤት እንዲጠብቋት አስጠንቅቄ ወደ እናቷ ቤት አመራሁ እንደደረስኩ ሴትየዋ ላይ የጮኩት ጩኸት የቻልኩትን የታገስኩትን ሁሉ ነበር እናም ከእሷ ጋር ወደኔ ቤት መጣን ውጪ እንዳለሁ ጥሯት ብዬ ስትታይ የለችም አበድኩ መጨረሻዬን እያሰብኩ ጮኩ እነሱም ሽንት ቤት ብላ አታላቸው ነው ለካ ያልገባንበት የለም ተፈለገች የለችም ጭራሽ ስላደረኩላት መልካም ነገር የምስጋና ደብዳቤ ጽፋ ጠፍታለች አግኝታት ለነበረችው ሴት ደውለን ስንነግራት ስልክ ሰጥታን ዘጋችው
ለካ ወንድሜ ስትል የነበረው ታውቁት ከሆነ ( ባዩሽ ኮልፌ) ሄኖክን ነው ከዛ እናቷ እኔ ጋ ተገናኝተን ነው ከኔ ነው የጠፋችው ብላ ነገሩን ለማብረድ ሞከረች እሱም ፈልጌ ፎቶ አንስቼ እንድልክለት ነግሮ ተዘጋ እንዲሁ እንዳበድኩ ሰአቱ ሂዶ ምሳ ሰአት ደረሰ ከዛ በመሀል የእናቷ ስልክ ጠራ አነሳችው የሌላ አካባቢ ፖሊሶች ነበሩ ሶሻል ሚድያ ላይ አይተዋት እንደነበር በማስታወስ ይዘዋት ነው ስልኳን የተቀበሉት እናትም ሄዳ ተቀበለቻት መጡ ደግማ ሳትጠፋ ብዬ አንድ ላይ ፎቶ አነሳዃቸው ማድረግ ያሉብኝን ነገሮች አድርጌ ለሚመለከተው አካል ላኩና ከዚ ችግር ወጣሁ ከዛ የተኛሁትን እንቅልፍ አጠይቁኝ
ይሄ በህይወቴ በጣም ከባድ የምለው አጋጣሚዬ ነው ከዛ ወዲ ርንደዚ አይነት ነገር እፈራለሁ
የኔ አጋጣሚ ይህን ይመስል ነበር🙌🤭🤭
# እናት
1 296
እኔ ልወስዳት እንደመጣሁ ማንም አልጠረጠረም ነበር ልጅቷን ሳያት አጠገቧ ያለችውን ለማናገር ተጠጋሁ እናም ማውራት ስጀምር ሰው ሁሉ ከበበን ከዛ ያለውን ሁሉ አስረድቼ ልጅቷን እንዲሰጡኝ ስጠይቅ ለእናቷ ደውይና መጀመርያ እናረጋግጥ አሉኝ እሺ ብዬ ስደውል ስልኳ ዝግ ነው እናም ሰዎቹ ልጅቷን ልሰርቅ የመጣሁ እንደሆነ ደመደሙ ካለሁበት ድካምና ርሀብ አንጻር ንዴቴን መቆጣጠር አቅቶኝ በቃ ውሰዷት ለእናቷ ነግራታለሁ ራሷ ትውሰዳት ብዬ ልሄድ ስል ሰው እውነትም ሌባ ነሽ ስለዚህ ፖሊስ ጣቢያ ነው የምንሄደው አሉኝ ያልመቱኝም ሴት ሆኜባቸው ነው
ልጅቷን ይዛ የመጣችው ሴት ትነጫነጫለች ወቅቱ የኢስላም ጾም ነበር ሰአት እየደረሰባት መሆኑንና የልጅቷ ነገር ግራ አጋብቷታል
እኔም አልፈራሁም እሺ እንሂድ አልኳቸው
ከዛ ሰዎቹ ግራ ገባቸው ከመሄዳችን በፊት ብለው ልጅቷን ሌላ ስልክ ስጭን አሏት አላውቅም ብላ ግግም አለች
ሲሰለቸኝ በቃ ፖሊስ ጣቢያ እንሂድ እነሱ ይረከቡ እኔም ወደቤቴ ነው መግባት ምፈልገው ብዬ አምባረኩ
በዛ መሀል ልጅቷ ደነገጠች ፖሊስ ጋር አትውሰዱኝ በቃ እናገራለሁ ብላ ተናገረች ስልኩ ጠራ ነገር ግን አይነሳም አሁን አማራጭ የለም ሰዎቹም ሊያምኑኝ አልፈለጉም ስለዚህ ፖሊስ ጋር መሄድ የመጨረሻው አማራጭ ሆኖ መሄድ ስንጀምር ልጅቷ አክስቷ የምትሰራበትን ሬስቶራንት አሳየችን ገባን አክስትየው ገና ስታያት አያገባኝም አላውቃትም ብላ ግግም አለች
ሴትየዋም ትነጫነጫለች በዚ መሀል ኬት መጣ ሳይባል ዝናብ ረገጠን የአፍጥር ሰአት እያለፈ ነው ለጾመኛዋ አሳስቦኛል ነገር ግን እኔም ከሷ ብሼ ነበረ በስተመጨረሻ ያለን አማራጭ ፖሊስ ሆነና ፖሊስ ጣቢያ ገባን እዛም ያሉን ነገር ቢኖር እንደዚህ አይነት ኬዝ ቢሮው ላይ እንደማይቀበሉና ነገር ግን ወደዋናው ቢሮአቸው እንድንሄድ ነገሩን
መብራት ጠፍቷል እየዘነበ ነው ጾመኛ ናት
የጠቆሙን ቢሮ ሩቅ ነው
ሴትየዋም ተመልሳ ልጅቷን ይዛ መግባት አልፈለገችም ብቻ በመሀል በመሐሀል ወንድሜን ላማክር ቆይ እያለች ስልክ ታወራለች በስተመጨረሻም በቃ ይዘሻት ሂጂ ነገር ግን ፎቶ ላንሳሽ የሆነ ነገር እንኳን ቢፈጠር ለፖሊስ ፎቶሽን እበትናለሁ ብላ ፎከረች እኔም ቶሎ መግባት ስለፈለኩ ተስማምቼ እንደወንጀለኛ ተነሳሁ
እንግዲህ ስቃዬ የጀመረው ከዚ ሰአት ጀምሮ ነው
አልጨረስኩም ይቀጥላል .....
# እናት
1 296
እነሆ የማይረሳ ገጠመኜ
አንድ ቅዳሜ ለት በማለዳ ተነሳሁ ቁርስም ሳልበላ ስራዎቼን በግዜ ለመጨራረስ አስቤ ቤት ውስጥ ሚሰራውን ሰራርቼ እንደጨረስኩ በዛ ብሎ የተጠራቀመብኝን ልብስ ማጠብ ጀመርኩ ያው ቤት ስትውሉ እና ስራ ስትሰሩ ቀለል ያለ ልብስ አደል የምትለብሱት እኔም ስስ ቲሸርት እና ስስ ሱሪ ለብሼ ልብሱን ጀመርኩ ሚገርማችሁ ቁርስ እንኳን አልበላሁም ነበር ልብሱንም የጨረስኩት ወደ 10 ሰአት አካባቢ ነው እና እንደጨረስኩ ምግብ ለመብላት ከመቸኮሌ የተነሳ ልብሴን ራሱ አልቀየርኩም እና ስልኬን እንደያዝኩ ቁጭ አልኩ ከዛ ወደ ቴሌግራም ስገባ ከጓደኛዬ መልእክት አገኘው ስገባ የአንዲት ትንሽ ልጅ የአፋልጉኝ ማስታወቅያ ነው ልጅቷን አንዲት ደግ ሴት አግኝታ ቤተሰቦቿን እንድታገኝ የተለቀቀ ነው ሳያት አዲስ አልሆነችብኝም የተጻፈውንም ሳይ እኔ ያለሁበት አካባቢ ተጠቅሷል ለጓደኛዬ ደወልኩ አስረዳችኝ ከዛ በአእምሮዬ እናቷ ምን ያህል ጭንቅ ውስጥ እንደሆነች ተሰማኝና ልበላ ያዘጋጀውትን በቅጡ ሳልበላ ስልኬን እንደያዝኩ ወጣሁ ፎቶውን ማሳያቸው ሰዎች እንደማያቋት በንቀት ነበር ሚመልሱት በስተመጨረሻ ከድካም በኋላ የሆነች ሴትዮ ለምን እንደሆነ ጠይቃኝ ስነግራት ይቺ የተረገመች ልጅ መጥፋት አዲሷ አደለም ትመጣ የለ ምን አስለጠፋችሁ ብላ ተመነቃቅራ ሄደች ነገሩን የሰሙ ሌሎችም እያጉረመረሙ ቤቷን ጠቆሙኝ ከረጅም ማንኳኳት በኋላ እናቷ ከፈተች ነገር ግን የማዘንም የመደሰትም ነገር ስሜት አላየሁባትም እናም ያለችበትን ስነግራት እኔን እሺ አትለኝም እባክሽ ተባበሪኝ ስትለኝ እናት ናት ብዬ አዝኜ በተቀመጠው ስልክ ደወልኩ ያሉበትን ነግረውኝ ልብሴን እንኳን ሳልቀይር እብድ እንደመሰልኩ ወደ ቦታው አመራሁ
ሰዎቹ የጠበቁኝ ቦታ ላይ ሰዎች የበዙበትና ነገሩን መጨረሻ ለማወቅ ጓጉቶ እየጠበቀ ያለ ህዝብ የበዛበት ቦታ ነው
እቀጥለዋለሁ
# እናት
1 296
እንዴት ቆያችሁ ቤተሰቦቼ
እስቲ በህይወታችሁ የማትረሱት ገጠመኞቻችሁን አጋሩን የኔን ነገ አጋራለሁ በገጠመኞቻችን ብዙ ትምህርቶችና አለፍ ብሎም ጨዋታ መዝናናት እናገኝበት ይሆናል
ደና ደሩልኝ
# እናት
1 296
በቻናላችን #Psychology ላይ ትኩረት ያደረጉ፦
➾ ህይወትን የሚያንፁ ምክሮች
➾ ጥልቅ ማህበራዊ እና ፍልስፍናዊ እይታዎች
➾ መጣጥፎች
➾ አባባሎች
➾ አስተማሪ አጫጭር ልቦለዶች እና ታሪኮች
➾ አነቃቂ ፅሁፎች
የሚነሱበት ተመራጭ ቻናል ነው! ይቀላቀሉን፤ ይወዱታል!
👇
https://t.me/InsightQuotes
https://t.me/InsightQuotes
