en
Feedback
ቅዱሳት ሥዕላት ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

ቅዱሳት ሥዕላት ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

Open in Telegram

በዚህ ቻናል ነባር እና አዳዲስ የጥበብ ሥራዎቼን የማቀርብበት ሲሆን እናንተም ሥራዎቼን በመመልከት ውስጣችሁን ታረኩበት ዘንድ እንሆ እላለሁ ። አስተያየትዎን ገንቢ ሃሳብዎን እንዲሁም ማሣል ሲፈልጉ ከታች ባለው መረጃ ይጠቀሙ። @zersh8 0929018509

Show more
922
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
+2230 days
Posts Archive
ልዩ የበዓል መርሐ ግብር eotc Tv

።።።።።።።።።።።።+++።።።።።።።።።።።።

አኒሜሽን በደ/ን ሚልኪያስ የተዘጋጀ ሥዕለ ቅዱስ በሠዓሊ ዘሪሁን ገብረወልድ

እንኳን አደረሰን ለ ሕፅበተ እግር እና ጸሎተ ሐሙስ

።። አባ ጊዮርጊስ ዘ ጋስጫ / ኢትዮጵያዊው ቄርሎስ ።። ።።።።።። አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ።።።።።። መጋቢት 7 ከዕለታት አንድ ቀን እመቤታችን ተገልፃ ‹‹አይዞህ አታልቅስ፤ ትምህርት ተከልክሎብህ ሳይሆን የምትጠቀምበት ጊዜው እስኪ ደርስ ነው፤ አሁን ጊዜዉ ደርሷል›› አለችው፤ ‹‹እስከ ፯ ቀን በዚሁ እንዳለህ ጠብቀኝ›› ብለውም ተሠወረች። እርሳቸውም ተስፋውን ተቀብለው በሱባዔ እንዳሉ እንደተለመደው በስዕለ ማርያም ሥር ተደፍተው ሲያለቅሱ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የመልአክት አለቃ ቅዱስ ዑራኤልን አስከትላ ጽዋ እሳት (ጽዋ ልቦና እንዳጠጠው ዕዝራ ሱቱኤልን) የሕይወት ጽዋ አጠጣችው። አባ ጊዮርጊስ የሕይወት ጽዋ ከተጎነጩ በኋላ የሰማይና የምድር ምሥጢር ተገለጸላቸው። አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የደረሱት መጽሐፍት ከሃምሳ በላይ ይሆናሉ፡፡ በስም የሚታወቁት ግን ሰዓታት ዘመዓልት ወዘሌሊት፣ ኖኅተ ብርሃን ከመጽሐፈ አርጋኖን ጋር አብሮ ታትሟል፣ ውዳሴ መስቀል፣ ቅዳሴ፣ ውዳሴ ሐዋርያት፣ አርጋኖነ ውዳሴ፣ ፍካሬ ሃይማኖት፣ መጽሐፈ ምሥጢር፣ ውዳሴ ስብሐት፣ እንዚራ ስብሐት፣ ሕይወተ ማርያም፣ ተአምኖ ቅዱሳን፣ መጽሐፈ ብርሃን እንዲሁም ጸሎት ዘቤት ናቸው፡፡ አባ ጊዮርጊስ እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ሀብተ መንፈስ ቅዱስ የተሞሉ አባት ናቸው፡፡ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ‹‹ኮከበ ክብር ጽዱል ፀሐዬ አግዓዚ ብሩህ አቡነ ጊዮርጊስ ጥዑመ ስመ ወሠናየ ግዕዝ መጋቤ ሃይማኖት ወመሠረተ ቤተ ክርስቲያን፤ አባታችን ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የሚያበራ የክብር ኮከብ፣ የኢትዮጵያ ብሩህ ፀሐይ፣ ስሙ የሚጣፍጥ፣ ምግባሩ የቀና ነው።›› (ገድለ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ) (ከአቤል ተፈራ )

።።።።።። +++ ።።።።።።

።።።።።።።።።።። መጋቢት 5 ።።።።።።።። እንኳን አደረሳችሁ ለአባታችን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ የእረፍት በዓል ። ጻዲቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅድስ ዓመታዊ ዕረፍት በዓላቸው ነው። ጻድቁ አባታችን በ ግብፅ ንኂሳ እንደተወለዱ ገድላቸው ይናገራል።አባታቸው ስምዖን እናታቸው ቅድስት አቅሌስያ ይባላሉ። እሊህ ደገኛ ቤተሰብ ልጅ አጥተው ለ 30 ዘመን ተጨነቁ ታዲያ አቅሌስያ እለት እለት ወደ እግዚአብሔር ቤት በመሄድ ስዕለ ሥላሴ ስር ተደፍታ ትለምን ነበር ። ፀሎቷ በቅድመ እግዚአብሔር ፊት ደርሶ በሰማይም በምድር ክብሩ ከፍ ያለ ልጅ ጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ታህሳስ 29 ቀን ተፀንሰው መጋቢት 29 ተወለዱ። በተወለዱ ቅጽበት ከ እናታቸው እቅፍ ወርደው ስብሐት ለአብ ስብሐት ለወልድ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ ለ ዘ አውጻከኒ እም ጽልመት ውስተ ብርሃን ከጨለማ ወደ ብርሃን ላወጣኸኝ አምላክ አመሰግንሃለሁ ብለው ሰግደዋል። አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ማለት የገብረ መንፈስ ቅዱስ ስራ ማለት ነው።ጻድቁ አባታችን በፀሎት በስግደት የበረቱ ታላቅ ከባት ነበሩ ለ ኢትዮጵያ ምሕረት ከ አምላካቸው ሽተው 100 አመት በባህር ላይ ተዘቅዝቀው ፀልየዋል። በደመና ላይ ተጭነው ከ ግብፅ ወደ ኢትዮጵያ መጡ በታላቁ ምድረ ከብድ ገዳም ቦታ ማረፊያቸው አርገው ገዳሙን መስርተዋል ። ጻድቁ አባታችን ብዙ ገድላትን ከፈፀሙ በኋላ በ 562 ዓመታቸው መጋቢት 5 ቀን አርፈው ተሰውረዋል። የጻዱቁ አባታችን በረከት ይደርብን አሜን ቅዱስ ሥዕል በሠዓሊ ዘሪሁን ገብረወለድ የተሣለ ገጹን #share እና #like ያድርጉ