የታይም አካዳሚ የቀድሞ ተማሪዎች መገናኛ ቻናል ‼️
Open in Telegram
651
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ለውድ የታይም አካዳሚ ቤተሰቦች በሙሉ :-
የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት መረጃዎች ለተጠቃሚዎች ለማድረስ ይመች ዘንድ በት/ቤታችን ስም አዲስ የቴሌግራም ቻናል ስለከፈትን አዳዲስ መረጃዎች ለማግኘት ከታች የተያያዘው ሊንክ በመጫን ቤተሰብ መሆን (join) እንደምትችሉ እየገለፅን ከዚህ በኋላ መልዕክቶቻችን የምናስተላልፈው በዚሁ ቴሌግራም ቻናል ብቻ መሆኑን በመገንዘብ ሊንኩን ተጭናችሁ ቤተሰብ ሁኑ ።
https://t.me/+7LIboVIE2hY4YjJk
ለ2016 ዓ.ም አዲስ ቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉን መረጃዎች ይህንን ሊንክ ተጭነው ያግኙ
የ2016 ዓም የትሞህርት ዘመን ምዝገባ ለነባር ተማሪዎች ከሀምሌ 07 ቀን 2015 ዓ.ም እስከ ሀምሌ 30 2015 ዓ.ም ብቻ
ለአዲስ ተመዝጋቢ ተማሪዎች ከሀምሌ 07 ቀን 2015 ዓ ም ጀምሮ ባሉን ውስን ቦታዎች ቅድሚያ የመጡትን ብቻ የሚያስተናግድ መሆኑን እንገልፃለን።
ማሳሰቢያ :- ከዚህ በፊት እንደተለመደው ቆይተው ለመመዝገብ የሚመጡት ተማሪዎች ት/ቤቱ ሀላፊነት አይወስድም
ዘንድሮ ደጋግመን ባሳወቅነው መሰረት እስከ ሀምሌ 30 ብቻ መሆኑን ተገንዝባችሁ አሁንኑ ተመዝገቡ።
ታይም አካዳሚ !!
::::::::::::::::::::::::
በተማሪዎች ባህርይ እና በተማሪዎች ውጤት ላይ በማተኮር እየሰራን እንገኛለን ነገን በማየት ዛሬ ላይ ተግተን እንሰራለን !!
ተመራጭ ት/ቤትም ነን እንሆናለንም !!
በተማሪዎቻችን ፣ በመምህራኖቻችን እና በወላጆች ኮርተናል እንኮራባችኋለን !!
ዛሬ በእጅጉ የተደሰትኩበት ቀን
የወላጆች በዓል ቀን በ6/11/2015 ዓ.ም በአንተነህ አዳራሽ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በደማቅ ኘሮግራሞች ታጅቦ ይካሄዳል። በመሆኑም ሁሉም ወላጆች /አሳዳጊዎች /ተማሪዎች እና መምህራን በዕለቱና በሰዓቱ ተገኝታችሁ ሀላፊነታችሁን በተግባር እንድታሳዩን በአክብሮት እንገልፃለን ።
ለ12ኛ ክፍል ተመራቂ ተማሪዎቻችን በሙሉ :-
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሀምሌ 6/2015 ዓ.ም በአንተነህ አዳራሽ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ የወላጆች በዓልና የተማሪዎች ምረቃ ይከናወናል በመሆኑም የ12ኛ ክፍል ተመራቂዎች ጋዋን በተመለከተ
ት/ቤቱ ሁኔታዎቹን እንዲያመቻች የተማሪዎች ፍላጎት መለየት አስፈላጊ ሆኖ ስለተገኘ እስከ ሰኞ /03/11/2015/ ባለው ጊዜ ብቻ የጋዋን ፍላጎታችሁን
ለት/ቤቱ ሪፖርት እንድታደርጉ እያሳሰብን ይህንን ማድረግ ያልቻለ ተማሪ ቢኖር ጋዋን መልበስ እንደማይፈልግ ተደርጎ ስለሚቆጠር ት/ቤቱ ፍላጎታቸው ለት/ቤቱ ላቀረቡ ተማሪዎች ብቻ የምናመቻች መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን ።
መልዕክት !!
=======
ለታይም ሁለተኛ ደረጃ የ12ኛ ክፍል ተማሪ ወላጆችና አሳዳጊዎች በሙሉ:-
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የምረቃ ኘሮግራም ሀምሌ 6 /2015 ዓ.ም ሁሉም ወላጆችና የት/ቤቱ ማህበረሰብ በተገኙበት ት/ቤቱ በደማቅ ዝግጅት ያከብራል ሆኖም ከተማሪ ወላጆች ባገኘነው መረጃ መሰረት አንዳንድ ተማሪዎች ከዚህ ውጪ ኘሮግራም ለማድረግ ለወላጆች አላስፈላጊ ወጪ (ወላጆችን በማሳመን የወጪ ብር ) እየጠየቁ መሆኑን ከተማሪ ወላጆች ስለተረዳን ከሀምሌ 6 ውጪ የሚኖር የትኛውም አይነት ኘሮግራም ከትምህርት ቤቱ እውቅና ውጪ መሆኑንና ት/ቤቱ ሀላፊነት እንደማይወስድ እያሳሰብን ወላጆችም ይህንን ተረድታችሁ ለልጆቻችሁ አስፈላጊ ግንዛቤ በመፍጠር ከት/ቤቱ ጋር መረጃዎች እንድትለዋወጡ በጥብቅ እና በአክብሮት እናሳውቃለን ።
