የታይም አካዳሚ የቀድሞ ተማሪዎች መገናኛ ቻናል ‼️
Open in Telegram
651
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ለመላው የት/ቤታችን ተማሪዎች ፣ መምህራን ፣ ወላጆች እና ማህበረሰብ በሙሉ ‼️
የ2016 ዓ.ም የመጀመሪያው መንፈቅ አመት የጥያቄና መልስ ውድድር በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 ካሉ የግልና የመንግስት ት/ቤቶች የዕርስ በርስ የጥያቄና መልስ ውድድር ከ9 ት/ቤቶች ከ6ኛ ክፍል አንደኛ በመውጣት እንዲሁም
ከ8ኛ ክፍል 1ኛ በመውጣት በግል በተማሪዎች 1ኛ እና በት/ቤትም 1ኛ በመውጣት በሁለቱም ክፍሎች ሁለት ዋንጫ በማግኘት የአሸናፊነት ደረጃን ይዘን ወረዳ ወክለን ለክፍለ ከተማ በመቅረባችን የተሰማንን ደስታ እየገለፅን በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ / ደስ አለን ‼️
የቴክኒክና ሙያ መግቢያ ነጥብ
ተቆረጠ ‼️
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
✅መግለጫውን የሰጡት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ፤ የተፈጥሮ ሳይንስ ደረጃ 5 የመቁረጫ ነጥብ ወንድ ከ218፣ ሴት 199 በላይ፣ የታዳጊ ክልል (የአርብቶ አደር አካባቢዎች) ወንድ ከ192፣ ሴት 187 በላይ፣ በተፈጥሮ ሳይንስ አካል ጉዳተኞች 147ና ከዚያ በላይ (ሁሉንም ክልሎች ታሳቢ ያደረገ ነው) ብለዋል።
✅ደረጃ 3 እና 4 ወንድ ከ173፣ ሴት 163 በላይ፣ ታዳጊ ክልሎች ወንድ ከ157፣ ሴት 156 በላይ፣ አካል ጉዳተኞች 130ና ከዚያ በላይ ነው ተብሏል።
✅ተፈጥሮ ሳይንስ ደረጃ 1 እና 2 ወንድ 172፣ ሴት 162ና ከዚያ በላይ፣ ታዳጊ ክልሎች ወንድ 156፣ ሴት 155ና ከዚያ በላይ ነው።
✅ማኅበራዊ ሳይንስ ደረጃ 5 ወንድ 179፣ ሴት 170ና ከዚያ በላይ፣ ታዳጊ ክልሎች ወንድ 166፣ ሴት 162፣ አካል ጉዳተኞች 147ና ከዚያ በላይ ነው።
✅ደረጃ 3 እና 4 በማኅበራዊ ሳንይንስ ወንድ 149፣ ሴት 147፣ ታዳጊ ክልል ወንድ 138፣ ሴት 137ና ከዚያ በላይ፣ አካል ጉዳተኞች 130ና ከዚያ በላይ ሆኗል።
✅ደረጃ 1 እና 2 በማኅበራዊ ሳይንስ ወንድ 148፣ 146፣ ታዳጊ ክልል ወንድ 137፣ ሴት 136፣ አካል ጉዳተኞች 129ና ከዚያ በላይ መሆኑን አስረድተዋል።
✅በ2016 ዓ.ም 844 ሺሕ 384 የሚሆኑ ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ወስደዋል። ከእነዚህ ውስጥ በእኛ ምልከታ 632 ሺሕ 587 የሚሆኑት ወደ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ይመጣሉ የሚል ግምት አለን" ነው ያሉት።
✅የሰው ሃይል ለመቀበል የተሻለ ዝግጁነት አላቸው ያልናቸውኝ የመንግሥትና የግል የቴኪኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማትን ፈትሸናል ያሉት ሚኒስትሯ፣ እስካሁን ባለው ከ28 ሺህ በላይ የሚሆኑ አሰልጣኞች፣ ወደ 1ሺሕ 400 ገደማ የተሻለ ብቃት ያላቸው ማሰልጠኛ ኮሌጆች አሉ ብለዋል።
ለታይም ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች/ወላጆቻችንና መምህራን በሙሉ:-
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በነገው ዕለተ ሰኞ ( 07/01/2015) መደበኛ ትምህርት በተሟላ መልኩ ስለሚጀመር እንዲሁም ከጠዋቱ 1:45 ጀምሮ እስከ 2:05 ድረስ የት/ት አጀማመር ኘሮግራምና የእንኳን አደረሳችሁ ችቦ ስለምናበራ በሰዓቱ ተገኝታችሁ እንድትሳተፉ እየገለፅን ከ2:15 እስከ 6:45 ድረስ መደበኛ ትምህርት ስለሚሰጥ አስፈላጊ የት/ት ቁሳቁሶች አሟልታችሁ እና የት/ቤቱ ዩኒፎርሞ ለብሳችሁ እንድትገኙ በአክብሮት እንገልፃለን ።
➡️ ለተከበራችሁ የት/ቤታችን ተማሪዎች/ ወላጆች /አሳዳጊዎችና
መምህራኖቻችን በሙሉ : -
መስከረም 07/2016 ዓ.ም መደበኛ ት/ት ስለሚጀመር በእለቱ እና በተለመደው ሰዓት ት/ቤት እንድትገኙ በጥብቅ እናሳስባለን ‼️
በድጋሚ የወጣ ማስታወቂያ !!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ለት/ቤታችን ወላጆች / አሳዳጊዎች በሙሉ :-
➡️🔜 ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት
---------------------------------
የ2016 ዓ.ም የተማሪዎች ምዝገባ ከሀምሌ 10 እስከ ነሀሴ 02 ብቻ መሆኑን በተደጋጋሚ ገልፀን እንደነበር ይታወሳል ሆኖም በአንዳንድ ወላጆች ጥያቄ መሰረት እስከ ነሀሴ 10/2015 ዓ.ም የተራዘመ ቢሆንም ጥቂት ነባር ተማሪዎች ጊዜው ገና ነው በማለት ያልተመዘገቡ መሆኑ መረጃዎች ጠቁመውናል ።
በዚህም መሰረት ከነሀሴ 10/2015 ዓም ባለን ቦታ አዲስ ተማሪዎች የምንመዘግብ በመሆኑ ነባር ተማሪዎች ከወዲሁ በአስቸኳይ እንድትመዘገቡ እያሳሰብን ቦታው በአዲስ ተማሪዎች ቢያዝ
ት/ቤቱ ሀላፊነቱ የተወጣ ስለሆነ ወላጆች ሀላፊነቱን የምትወስዱ መሆኑን
በድጋሚ በአክብሮት እንገልፃለን ።
፡፡።፡።።።።።።።።።።።፡ ።።።።።።።።።።።።።።
አርፍዶ የመመዝገብ ባህል አስቀርተን
ት/ቤቱ ባወጣው የምዝገባ ጊዜ ብቻ መመዝገብን ባህል እናድርግ !!
በድጋሚ የወጣ ማስታወቂያ !!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ለት/ቤታችን ወላጆች / አሳዳጊዎች በሙሉ :-
---------------------------------
የ2016 ዓ.ም የተማሪዎች ምዝገባ ከሀምሌ 10 እስከ ሀምሌ 30 ብቻ መሆኖን እንደገለፅን ይታወቃል ሆኖም አንዳንድ ወላጆች ለት/ቤቱ ባቀረቡት ጥያቄ መሰረት ያለ ቅጣት እስከ ነሀሴ 10/2015 ዓ. ም ብቻ ያራዘምነው መሆኑን ተገንዝባችሁ በቀሩት ጥቂት ቀናት እንድትመዘገቡ እያሳሰብን ከነሀሴ 03/2015 ዓ.ም በኋላ ያለን ክፍት ቦታ ታይቶ በቅጣት የምንመዘግብ መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን ።
አርፍዶ የመመዝገብ ባህል አስቀርተን ት/ቤቱ ባወጣው የምዝገባ ጊዜ ብቻ መመዝገብን ባህል እናድርግ !!
ለ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎቻችን ወላጆች/አሳዳጊዎች :-
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች በሰላም ፈተናውን አጠናቀው ወደ ት/ቤታቸው በመመለስ ላይ ይገኛሉ ወላጆች ተረጋግታችሁ ቤት እንድትጠብቋቸው እየገለፅን ለተማሪዎቻችን አቀባበል አድርገን ወደየ ቤታቸው እንሸኛለን ።
አስደሳች ዜና
***
➡️❤‼️_➡️
ለሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ለትምህርት ቤታችን እና በአከባቢው ለሚገኙ ለሌላ ለማንኛውም ት/ቤት ተማሪዎች እና ወላጆች፤
****
እንደሚታወቀው አንጋፋው ታይም አካዳሚ ላለፉት በርካታ ዓመታት በእውቀት የበለፀጉ በመልካም ሥነ ምግባር የታነጹ ዜጎችን ሲያፈራ ቆይቷል አሁንም እያፈራ ይገኛል። በተጨማሪም መልካም ሥነ ምግባር እና አማካይ ዉጤታቸዉ ከ 95% በላይ የሆኑ በርካታ ተማሪዎችን ሙሉ ነፃ በማስተማር ለአከባቢው ማህበረሰብ የራሱን በጎ አስተዋፅኦ ሲያደርግ መቆየቱ ይታወቃል።
በመሆኑም ለ2016 ዓ.ም ከእኛ ት/ቤት ሆነ ከማንኛውም ሌላ ት/ቤት አማካይ ዉጤታቸዉ ከ 95% በላይ የሆኑ እና መልካም ሥነምግባር ያላቸውን ተማሪዎች አወዳድሮ እንደተለመደው በነፃ ለማስተማር ይፈልጋል።
በመሆኑም ከላይ የተጠቀሰውን መስፈርት የምታሟሉ ተማሪዎች ከእኛም ሆነ ከየትም ት/ቤት ያላችሁ ነገ ሀሙስ 27/11/2015 እና አርብ 28/11/2015 ት/ቤት በመምጣት እንድታናግሩ እናሳውቃለን።
ይህ ዕድል እንዳያመልጥ ፍጠኑ....
የእኛ ተማሪ የሆናችሁ ሌላ የግልም ሆነ የመንግስት ት/ቤት ጓደኛ ያላችሁ ጓደኞቻችሁ የዚህ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ እንድታሳውቁ በደስታ እንገልፃለን።
ጥብቅ ማስታወቅያ !!
::::::::::::::::::::::::::::::
የ2016 ዓ.ም የአዳዲስ እና ነባሪ ተማሪዎች ምዝገባ ከሀምሌ 10 ጀምሮ መመዝገብ እንደጀመርን ይታወቃል ሆኖም የት/ቤታችን ማህበረሰብ እንደቀድሞው የተራዘመ የምዝገባ ጊዜ ያለ መስሏችሁ እንዳትዘናጉ በተደጋጋሚ በቴሌግራም ገፃችን ገልፀንላችኋል !!
በገለፅንላችሁ መሰረት ምዝገባው የሚቆየው እስከ ሀምሌ 30 ብቻ መሆኑን በድጋሚ እየገለፅን ከሀምሌ 30 በኋላ የሚመጡ ተማሪዎች በየቀኑ በሚጨምር ቅጣት የሚመዘገቡ መሆኑና እየገለፅን ላላስፈላጊ ቅጣት እንዳትዳረጉ ከወዲሁ ልጆቻችሁን አስመዝግቡ ።
አርፍዶ የመመዝገብ ባህል አስቀርተን
ት/ቤቱ ባወጣው የምዝገባ ወቅት ብቻ ማስመዝገብ እንለማመድ !!
Repost from Time Secondary school official channel
ለሁሉም የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎቻችን ወላጆች/አሳዳጊዎች :-
//::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::://
የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በሙሉ ዛሬ ወደ መፈተኛ ጣቢያቸው /ኮተቤ ዮኒቨርስቲ/ በሰላም ገብተዋል ።
መልካም ፈተና !!
Repost from የታይም አካዳሚ የቀድሞ ተማሪዎች መገናኛ ቻናል ‼️
https://t.me/+7LIboVIE2hY4YjJk
ለ2016 ዓ.ም አዲስ ቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉን መረጃዎች ይህንን ሊንክ ተጭነው ያግኙ
