Assosa online
እውነተኛ ታማኝ እና ወቅታዊ መረጃዎችን እናደርሳለን፡፡ ቻናሉን ሼር ኢንቫይት እና ጆይን በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ::
Show moreThe country is not specifiedAmharic6 280The category is not specified
760
Subscribers
No data24 hours
-87 days
-2230 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
You can convert any book or magazine photo into editable text. Join TexifyBot and try it for free! 👇👇👇
http://telegram.me/TexifyBot?start=404471182l
#የሞሰብ ምስሎች የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮችን ይቀላቀሉ
Capture your moment, on the links
https://t.me/moseb16
https://www.facebook.com/moseb21
https://www.youtube.com/mosebtube
https://www.tiktok.com/@moseb16
Moseb Pictures
Capture your moment, on the links
https://www.facebook.com/moseb21https://www.youtube.com/mosebtube
https://www.tiktok.com/@moseb16
ዛሬ ማርች 8 ነው።
ዛሬ ማርች 8 የሴቶች ቀን ነው።ለመሆኑ ዕለቱ ለምን ይከበራል?
✔• ከ3 ሴቶች አንዷ በህይወት ዘመኗ ተደፍራለች (UN)
✔• በአለማችን ዕድሜቸው ከ15 እስከ 44 የሆኑ ሴቶች ከካንሰር፣ ከጦርነት፣ ከመኪና አደጋና የወባ በሽታ ይልቅ አስገድዶ የመደፈር ስጋት ያሳስባቸዋል (UN)
✔• 603 ሚሊዮን ሴቶች ጾታዊ ጥቃት ወንጀል ባልሆነባቸው አገራት ውስጥ ይኖራሉ (UN)
✔• በአሁኑ ወቅት በአለማችን 700 ሚሊዮን ያህል ሴቶች ዕድሜያቸው 18 ዓመት በታች ሆነው ያገቡ ሲሆን 250 ሚሊዮን ሴቶች ደግሞ ዕድሜያቸው 15 ዓመት በታች ሆነው ያገቡ ናቸው (UNICEF)
✔• በየአመቱ በአለም ላይ ከ600-800 ሺህ ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውሮች ይካሄዳሉ፡፡ ከሚካሄደው የህገ ወጥ ሰዎች ዝውውር ከአምስት አራቱ ሴቶች ነው፡፡ (Trafficking.org)
✔• በየአመቱ 62 ሚሊዮን ሴቶች የትምህርት ዕድል አያገኙም (Makers)
✔• የአለማችን116 ሚሊዮን ሴት ተማሪዎች (25 በመቶ ያህሉን የሴት ተማሪዎችን ቁጥር ይዛል) አንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አያጠናቅቁም፡፡
✔• በአለማች ለሴቶች የሚከፈለው ክፍያ ከወንዶች አንጻር ከ60-75 በመቶ ያነሰ ነው (PBS)
✔• 155 አገራት ሴቶችን ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የሚገድብ ህጎች ሲኖራቸው 100 አገራት ደግሞ ሴቶች የሚሰሩትን የስራ አይነት ገድበዋል (The Guardian)
✔• በየደቂቃው አንድ እናት በወሊድ ምክንያት ትሞታለች (UN)
✔• በአለማች 200 ሚሊዮን ሴቶች በግዳጅ ይገረዛሉ (World Health Organization)
@asosaonline
የአቅም ማሻሻያ (Remedial Program) በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች እና በተለያዩ አማራጮች ለመከታተል የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆኗል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር በ2014 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ያመጡትን ከግምት ውስጥ በማስገባት እና በተመሳሳይ ሁኔታ ፈተናው የተሰጠበትን አግባብ እና ሌሎች ጉዳዮችን ከግምት በመውሰድ ለአንድ ጊዜ ብቻ የሚያገለግል የአቅም ማሻሻያ (Remedial Program) እንዲተገበር መወሰኑ ይታወቃል።
በዚሁ መሰረት በ2015 የትምህርት ዘመን ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ገብተው በ Remedial ፕሮግራም የሚከታተሉ ተማሪዎችን አነስተኛ የመግቢያ ውጤት መወሰን አስፈላጊ በመሆኑ 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ያላስመዘገቡ ነገር ግን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የሚያሟሉ ተማሪዎች የ Remedial ፕሮግራም ተጠቃሚዎች ይሆናሉ ተብሏል።
1. በሁሉም አማራጮች (በግል እና በመንግስት ተቋማት) የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል ተማሪዎች እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 30% ከመቶ እና ከዚያ በላይ ማለትም (210 ከ 700፣ 180 ከ 600 እና 150 ከ 500) የተቆረጠ መሆኑን።
2. ከላይ በተራ ቁጥር 1 የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ በመንግስት ተቋማት(ወጪያቸው በመንግስት ተሸፍኖ) የ Remedial ፕሮግራም የሚከታተሉት የሚከተሉትን መቁረጫ ነጥብ ያሟሉ ብቻ ይሆናል ተብሏል።
Lists of free VPN services available on play store
1. PSIPHON
2. Atlas vpn
3. 1.1.1.1 + WARP vpn
4. VPN master Pro
5. surfshark
6. Proto VPN
7. Turbo Vpn
8. TunnelBear Free VPN
9. Opera Free VPN
10. HideMan Free VPN
11. Betternet Free VPN
12. Hotspot Shield Free VPN
13. Hide.me Free VPN
@asosaonline
ጥቆማ !
የ12ኛ ክፍል የብሔራዊ ፈተና ውጤት ከትናንት ሌሊት ጀምሮ ይፋ ተደርጎ ተማሪዎች እና የተማሪዎች ወላጆች ውጤት እየተመለከቱ ይገኛል።
ይህን ተከትሎ የማለፊያ ነጥብ እንደተቆረጠ ተደርጎ በማህበራዊ ትስስር ገጾች እየተለቀቁ ያሉ መረጃዎች ሀሰተኛ መሆናቸውም ተነግሯል፤ ከአሳሳች መረጃዎች ተጠንቀቁ ተብሏል።
ተማሪዎችም ውጤታቸውን ከታች ባሉት አማራጮች ማየት እንደሚችሉ ተገልጿል ።
• በዌብ ሳይት https://eaes.edu.et/ ወይም
• በ6284 አጭር የጽሑፍ መልዕክት መላኪያ ላይ የምዝግባ ቁጥራቸውን (Registration Number) ብቻ በመላክ ወይም
• በቴሌግራም ላይ https://t.me/eaesbot
EAES 🇪🇹 Result bot
EAES: Educational Assessment and Examination Service Official Bot. Use this bot to check your Result.
#Update
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤትን ተማሪዎች ከዛሬ ለሊት ጀምሮ ማየት እንደሚችሉ ተገልጿል።
ተፈታኞች ከዛሬ ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም #ከሌሊቱ 5፡30 ጀምሮ ፡-
• በዌብ ሳይት https://eaes.edu.et/ ወይም
• በ6284 አጭር የጽሑፍ መልዕክት መላኪያ ላይ የምዝግባ ቁጥራቸውን (Registration Number) ብቻ በመላክ ወይም
• በቴሌግራም ላይ https://t.me/eaesbot
ማየት የሚችሉ መሆኑን ተገልጿል።
ማሳሰቢያ፡-
• ማንኛውም ቅሬታ ያላቸው ተፈታኞች በአካል መምጣት ሳያስፈልግ እስከ ጥር 26/2015 ዓ.ም ድረስ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዌብ ሳይት https://eaes.edu.et/ ላይ Compliant የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ማቅረብ ይችላሉ ተብሏል።
• ተማሪዎች ፤ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አድራሻ ላይ ብቻ እንዲጠቀሙ #ከተመሳሳይ እና #የተዛባ_መረጃ ለማሰራጫት ከሚሞክሩ አካላት እራሳቸውን እንዲጠብቁ መልዕክት ተላልፏል።
ምንጭ ፦ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
EAES 🇪🇹 Result bot
EAES: Educational Assessment and Examination Service Official Bot. Use this bot to check your Result.
የ12ኛ ክፍል ፈተናን ውጤት አልተለቀቀም!!
የ12ኛ ክፍል ፈተናን ውጤት አስመልክቶ ብዙ የቻናላችን ቤተሰቦች ጥያቄ አንስታችሁልናል። እስካሁን ባለን መረጃ መሰረት የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት አልተለቀቀም።
በአንዳንድ ገፆች እና የቴሌግራም ቻናሎች የፈተናው ውጤት እንደተለቀቀ ተደርጎ የሚወራው ሀሰት መሆኑን ልንገልፅላችሁ እንወዳለን። ትምህርት ሚኒስቴር የፈተናው ውጤት ስለሚለቀቅበት ቀን እስካሁን በይፋ ምንም አይነት የተጣራ መረጃ አልሰጠም።
ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች የፈተናው ውጤት በይፋ ሲለቀቅ በፍጥነት የምናሳውቃችሁ ይሆናል።
@asosaonline
#MoE
የትምህርት ሚኒስቴር ፤ የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና " ላልተገደበ ጊዜ " እንደሚሰጥ አሳውቋል።
የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን የሚያገኙት ፈተናውን ወስደው ብቁ መሆናቸው ሲረጋገጥ ብቻ ነው ተብሏል።
ተማሪዎች ፈተናውን ደጋግመው መውሰድ የሚችሉበት ዕድል መመቻቸቱን በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ጥራትና ብቃት ማሻሻያ ዴስክ ኃላፊ ሰይድ መሀመድ ለኢፕድ ተናግረዋል።
የዩኒቨርሲቲ ቆይታቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎች በየስድስት ወሩ ፈተናውን የሚወስዱበት ዕድል እንዳለ ኃላፊው ጠቁመዋል።
የመንግስት ዩኒቨርሲቲ ተመራቂዎች ለአንድ ጊዜ ብቻ የፈተና ወጪያቸው እንደሚሸፈንላቸው ገልጸዋል።
በመንግሥትና በግል ተቋማት ላይ የሚሰጡ ከ300 በላይ የመጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት ፕሮግራሞች እንዳሉ ያነሱት ኃላፊው፤ በየትምህርት መስኩ እየተደረገ በአስር ዙር ፈተናው ለመስጠት ታቅዷል።
#ኢፕድ
More : @asosaonline