የደብረ ምህረት ቅድስት ድንግል ማርያም እና አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን ሰንበት ት/ቤት
Open in Telegram
👉የቦንጋ ደ/ም/ቅ/ድ/ማርያም እና አ/ገ/መንፈስ ቅዱስ ቤ/ን ሰንበት ት/ቤት አባላት እና ምዕመናን የቴሌግራም ቻናል ነው። 👉በውስጡ የተለያዩ ስርዓተ ቤተ ክ/ን የጠበቁ ትምህርቶች፣ዝማሬዎች፣ስነፅሁፎች እና ወቅታዊ መረጃዎች ይቀርቡበታል። 👉በተጨማሪም ለተጋቢ ሙሽሮች ደረጃውን የጠበቀ ካባ በተመጣጣ ዋጋ እናከራያለን። 👉ሀሳብ ጥያቄ እና አባል መሆን ከፈለጋችሁ @debremhiret👈ያግኙን
Show more427
Subscribers
No data24 hours
+37 days
+2130 days
Posts Archive
🌿የዕለቱ ተጋባዥ🌿
መምህር ዲ/ን አቤል ካሣሁን
🥰ታህሣስ 11/2017🥰
🥰በደብረ ምህረት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን🥰
🥰ከቀኑ 9:00 እንገናኝ።🥰
አምላካችን ጠብቆን ለዕለቱ ያድርሰን፤ በቤቱ ያቁመን🙏
👇join👇
👇group👇
@bdebremhret
@bdebremhret
👇👇channel👇👇
@yedebremhret
@yedebremhret
🌿የዕለቱ ተጋባዥ🌿
ሊቀ መዘምራን ዲ/ን ይትባረክ ተገኝ
🥰ተጋበዙልን🥰
☝☝☝☝☝☝
ታህሣስ 11/2017
በቦንጋ ደብረ ምህረት ቅ/ድ/ማርያም ቤ/ን ይመጣል
🥰አምላካችን ጠብቆን ለዕለቱ ያድርሰን፤ በቤቱ ያቁመን🙏
👇join👇
@bdebremhret
@bdebremhret
@bdebremhret
@bdebremhret
🌿የዕለቱ ተጋባዥ🌿
መምህር ዲ/ን አቤል ካሣሁን
🥰ታህሣስ 11/2017🥰
🥰በደብረ ምህረት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን🥰
🥰ከቀኑ 9:00 እንገናኝ።🥰
አምላካችን ጠብቆን ለዕለቱ ያድርሰን፤ በቤቱ ያቁመን🙏
👇join👇
@bdebremhret
@bdebremhret
@bdebremhret
@bdebremhret
🥰ታህሣስ 11/2017🥰
🥰በደብረ ምህረት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን🥰
🥰ከቀኑ 9:00 እንገናኝ።🥰
አምላካችን ጠብቆን ለዕለቱ ያድርሰን፤ በቤቱ ያቁመን🙏
👇join👇
@bdebremhret
@bdebremhret
@bdebremhret
@bdebremhret
🌿የዕለቱ ተጋባዥ🌿
ሊቀ መዘምራን ዲ/ን ይትባረክ ተገኝ
🥰ተጋበዙልን🥰
☝☝☝☝☝☝
ታህሣስ 11/2017
በቦንጋ ደብረ ምህረት ቅ/ድ/ማርያም ቤ/ን ይመጣሉ
አምላካችን ጠብቆን ለዕለቱ ያድርሰን፤ በቤቱ ያቁመን🙏
👇join👇
@bdebremhret
@bdebremhret
@bdebremhret
@bdebremhret
training of winter course.pptx1.16 MB
ተናፋቂው ወርሀዊው ለኦርቶዶክሳዊያን ሁሉ የሚሰጥ ልዩ ሥልጠና እነሆ ስንዱ ሆኖ ታዳሚዎችን ብቻ ይጠብቃል።
ከመጣችሁ በእውነት አትቆጩም
አይቀርም!
#ትንሣኤ_ዘጉባኤ
⚠️የክርስቶስ መምጣት ቀርቧልና አለም ትገለበጣለች “ከበረሃ የመጣን ባሕታውያን ነን” የሚሉ ብዛታቸው... እውነተኛው በመፃሕፍት ያለው ሳይሆን ተለምዷዊው የሙታን ትንሣኤ ትምህርት “ #ሁሉም ሰው ሞቶ ይነሳል” የሚል ትምህርት በር ከፍቶላቸዋል።ስለዚህ ሲያስተምሩ “አለም ግልብጥብጥ ትልና ሁሉም ሰው ይሞታል ከዛ ክርስቶስ ይመጣል፡ክርስቶስ እንዲመጣ በአለም ያለው ሁሉም ሰው መሞት ግድ ነው ሞት መቅመስ አለበት!!” ይላሉ።
መድረክ ያገኘ እንደራሱ እሳቤ ብዙ ያልተፃፈ መናገር ልማድ ቢሆንም ቤተ ክርስቲያን ግን እንዲህ አላስተማረችም!!ታድያ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ምን ይላል የሚለውን ስናይ:-
⚠️በርግጥ ጌታችን ኢየሱስ የመሬት መንቀጥቀጥ፣ድርቅ፣ወረርሺኝና ጦርነት ለመምጣቱ #ምልክት እንደሆኑ ተናግሯል። በነዚህም ክስተቶች ሰው እንደሚሞትም የታወቀ ነው ነገር ግን ሁሉም ሰው ሞቶ ያልቃል አላለም።ይልቁን ክርስቶስ መጥቷል በዚህ አለ ቢሏችሁ እንዳታምኑ የመብረቅ ብልጭታ ለሁሉም እንደሚታይ እኔም ለሁሉ በግልጥ እየታየሁ በብዙ ክብር በደመና ነው የምመጣው ነበር ያለው። (ማቴ 24፥24-31)
ስለዚህ ጌታችን ክርስቶስ ዳግመኛ እኪመጣ ድረስ የሰው ልጅ እየተባዛና እየሞተ ኑሮው ይቀጥላል። ሲመጣም ሞት ያቆማል የሞቱም ሰዎች ይነሳሉ በሕይወት የነበሩትም የማይሞቱ በአንድነትም ዘለአለማውያን ወደመሆን ይለወጣሉ።ቅዱስ ጳውሎስም ይህንን የጌታችን ኢየሱስ መምጣትና የሙታን ትንሣኤ በሁለት መልእክታት አጠር አድርጎ በደምብ ገልፆታል።
📜1ኛ ቆሮንቶስ 15
⁵¹-⁵² እነሆ፥ አንድ ምሥጢር እነግራችኋለሁ፤ ሁላችን #አናንቀላፋም ነገር ግን የኋለኛው መለከት ሲነፋ ሁላችን በድንገት በቅጽበተ ዓይን እንለወጣለን፤ መለከት ይነፋልና ሙታንም የማይበሰብሱ ሆነው #ይነሣሉ እኛም #እንለወጣለን ።
⁵³ ይህ የሚበሰብሰው የማይበሰብሰውን ሊለብስ ይህም የሚሞተው የማይሞተውን ሊለብስ ይገባዋልና።
⁵⁴ ዳሩ ግን ይህ የሚበሰብሰው የማይበሰብሰውን ሲለብስ ይህም የሚሞተው የማይሞተውን ሲለብስ፥ በዚያን ጊዜ፦ ሞት ድል በመነሣት ተዋጠ ተብሎ የተጻፈው ቃል ይፈጸማል።
📜በተጨማሪም የተሰሎንቄ መልእክቱም ይህንን ያጠናክራል
1ኛ ተሰሎንቄ 4
¹⁶ ጌታ ራሱ በትእዛዝ በመላእክትም አለቃ ድምፅ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና፥ በክርስቶስም የሞቱ አስቀድመው ይነሣሉ፤
¹⁷ ከዚያም በኋላ እኛ ሕያዋን ሆነን የምንቀረው፥ ጌታን በአየር ለመቀበል ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን፤ እንዲሁም ሁልጊዜ ከጌታ ጋር እንሆናለን።
¹⁸ ስለዚህ እርስ በርሳችሁ በዚህ ቃል ተጽናኑ።
📖መደምደሚያ:- የቤተ ክርስቲያን ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን ትምህርት በአጭሩ ይህ ነው።ምድርና ሰማይ የሚጠፉት ከተነጠቅን በኋላ ነው።እስከዛው ፍጥረት ሁሉ እንዲህ አሁን እንዳለው ይቀጥላል።
“በክርስቶስም የሞቱ አስቀድመው ይነሣሉ ከዚያም በኋላ እኛ ሕያዋን ሆነን የምንቀረው፥ ጌታን በአየር ለመቀበል ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን፤ እንዲሁም ሁልጊዜ ከጌታ ጋር እንሆናለን።”
@bdebremhret @yedebremhret
@bdebremhret @yedebremhret
@bdebremhret @yedebremhret
በቤትህ ያለው ዳቦ ለተራበው ሰው የሚውል(ንብረቱ) ነው፥ በልብስ ማስቀመጫህ ውስጥ ያለው የማትጠቀመው ኮት የችግረኛው ገንዘቡ ነው፥ በጫማ ማስቀመጫህ ውስጥ አልፈልገውም ብለህ ሊበላሽብህ የሆነው ጫማ የደሃው ጫማ (ጫማ ለሌለው ገንዘቡ) ነው ፥ ያከማቸኸው ገንዘብ ለድሃው የሚገባው ነው....
ዛፍ በፍሬው ይታወቃል፥ ሰውም በድርጊቱ፡፡ መልካም ስራ መቼም አይጠፋም፡፡ መልካም እርዳታን የሚዘራ፥ ወዳጅነትን ያጭዳል፡፡ ደግነትን የሚተክል ፍቅርን ይሰበስባል፡፡
"ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ ብቻ የለብንም፥ ነገር ግን ካነበብነው ተምረን ማደግ አለብን፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ምንም የማይጠቅም ነገር እንዳልተጻፈ ተገንዘብ፡፡
አሁንም ለጥንካሬ፣ ለመታገስ፣ለመዳን፣ለመለወጥ ጊዜ አለህ! ተኝተሃልን? ንቃ! ኃጢአት ሰርተሃልን? እንግዲያውስ መስራቱን አቁም፡፡
ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ
@bdebremhret🙏 @yedebremhret
@bdebremhret🙏 @yedebremhret
@bdebremhret🙏 @yedebremhret
✞ እንኳን 🌼 ✞
✞ ደስ 🌼 ✞
✞ አላችሁ!! 🌼 ✞
🌻 💫 የምስራች!!💫 🌻
🌸በቦንጋ ደብረ ምህረት ቅ/ድ/ማርያምና አቡነ ገ/መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስትያን ተጀምሮ የተለያዩ #ተማሪዎችን_አስመርቆ ነገር ግን በተለያዩ ችግሮች ተቋርጦ የነበረው #የበገና_ትምህርት
🌻#በአዲስ_አደረጃጀት
🌻#በልዩ_ሁኔታ እና
🌻#ችግሮችን_ቀርፎ
እነሆ 🌼በአዲስ አመት🌼 ዋዜማ ተጀምሯል። ከእናንተ የሚጠበቀው
😍#ፍላጎት ብቻ ነው!!
✍️ለመመዝገብ:-⛪️ በአካል በቤተክርስቲያናችን ግቢ በመገኘት በሰንበት ት/ቤት ፅህፈት ቤት መመዝገብ ይችላሉ።
ወይም:- ☎️+251917617945
☎️+251904495618
📞ደውለው ያግኙን
✞"እግዚአብሔርን በመሰንቆ አመስግኑት፥አስር አውታር ባለው በበገና ዘምሩለት፤አዲስ ቅኔም ተቀኙለት፥በእልልታም መልካም ዝማሬ ዘምሩ፤"✞{መዝ 32፥2-4}
ግብዞች ምጽዋትን ሲሰጡ ለተራበ ሰው አዝነው ሳይሆን እጀ ሰፊ ናቸው ብሎ አላፊ አግዳሚው እንዲያጨበጭብላቸው ስለሚወዱ ነው፡፡ ከዚህ የበለጠ ወንድምን መጥላት ግን የለም፡፡ ምክንያቱም ወንድማቸው በረሀብ እየተሰቃየ እነርሱ ስለ ክብራቸው ይጨነቃሉና፡፡ አንተ ግን መንፈሳዊነትህ እያደገ ስትሄድ ከእንዲህ ዓይነቱ ከንቱ ነገር ሽሽ፡፡ የሰጠኸውም ሁሉ ሊቆጠር ከማይቻል ወለዱ ጋር ከላይ ይጠብቅሀል፡፡ መልሶም ላንተ ይሰጥሃል፡፡
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
@bdebremhret
@bdebremhret
@bdebremhret
"በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"።
ነገ የቀዳሜ ሰማዕት (ሊቀ ዲያቆናት) ቅዱስ እስጢፋኖስ ወርሀዊ የመታሰቢያ በዓሉ ነው።
በረከቱ ይድረሰን
✝ #ነሐሴ ፲፯ (17) ቀን።
✝ እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት አባት ለአባታች #ለካህኑ_ቅዱስ_ጸጋ_ዘአብ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን።
✝ ✝ ✝
✝ #የካህኑ_ቅዱስ_ጸጋ_ዘአብ_ዕረፍት፦ በዚያም ወራት ከሦስት መቶ ሠላሳ ሦስት ዘመን በኋላ በሐምሌ ሰባት ቀን እግዚአብሔር መንግሥትን ከዛጌ ወገን የእስራኤል ወገለሚሆን ለይኵኖ አምላክ መለሰ። በየሀገሩ ሁሉ ጸጥታ ፍቅር አንድነት ሆነ። ከጥቂት ቀን በኋላ እናቱ እግዚእ ኃረያ በነሐሴ 12 ቀን ዐረፈች እርሷም ባረፈች በአምስተኛው ቀን በነሐሴ 17 ቀን አባቱ ጸጋ ዘአብ ዐረፈ። የሁለቱ ቅዱሳን በረከት ብልህ አዋቂ የሚሆን የልጃቸውም በረከት በእኛ ላይ ትደር ለዘለዓለሙ በእውነት። ፍሰሓ ጽዮንም እናት አባቱ ስላረፉበት አዘነ ነገር ግን ፈቃደ እግዚአብሔር አጸናው። በሚናገረው ነገር በሚመራው ሥራ የሚቻለው ሆነ እግዚአብሔርንም የሚያገለግል ሆነ..."። ከአባታች ከካህኑ ቅዱስ ጸጋ ዘአብ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን!።
✍ምንጭ፦ ገድለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት 28፥1-3።
@bdebremhret
@bdebremhret
@bdebremhret
@bdebremhret
"የህይወት እናት ድንግል ማርያም ሆይ ትንሳኤሽ ሳይሆን ሞትሽ ይደንቀኛል፤ እርገትሽ ሳይሆን ወደ መቃብር መውረድሽ ይገርመኛል፤ የብርሃን እናት ድንግል ማርያም ሆይ ትወጂኛለሽን? ብየ አልጠይቅሽም ፍቅርን የወለድሽ አንቺ ለአለሙ ሁሉ ፍቅርሽ የበዛ ነውና፤ አትናፍቂኝምን? ብየም አልጠይቅሽም ዘወትር እኔን ለመጠበቅ ከጎኔ እንደማትለይ አውቃለሁኝና፤ ሆኖም እመቤቴ ሆይ፦ እንደ ቶማስ አይሽ ዘንድ በእጅጉ እጓጓለሁ የቶማስ ንፅህናና ቅድስና ግን የለኝም እንደ ዮሃንስ ከጎንሽ ልሆን እጓጓለሁ የዮሃንስ ፀጋ ግን የለኝም።
እናቴ ሆይ፦ እንደ ኤልሳዕ የልቦናዬ አይን በርቶ ሰማያዊ ክብርሽን ላይ አልተቻለኝምና አዝናለሁ ኤልሳዕ በፀሎት ሃይል የግያዝን አይን እንዳበራ አንቺም አይኔን ታበሪልኝ ዘንድ ሃይልሽን በእኔ ላይ አበርቺ፡፡
ድንግል ሆይ፦ ይህን የምል የእምነት ማረጋገጫ ፈልጌ አይደለም በልጅሽ መሰረትነት የታነፅኩኝ በልጅሽ ስምም የተጠመቅኩኝ ነኝና፤ ነገር ግን ስለምትናፍቂኝ ይህን አልኩኝ ስለዚህም ነይ ነይ እምየ ማርያም እያልኩኝ እንደ እናቶቼም እለምንሻለሁ፡፡ የብርሃን ልብስሽን ለብሰሽ ነይ የክብር አክሊልሽን ደፍተሽ ነይ አንቺ ሱላማጢስ ሆይ ነይ እናይሽ ዘንድ ነይ፡፡"
@bdebremhret
@bdebremhret
@bdebremhret
መሻገሪያ በሌለው ትልቅ ወንዝ ምክንያት ከሌሎቹ ምእመን ይልቅ ብዙ የሚደክመው ያ ሰው ከቤተክርስቲያኑ ቅጥር ወጥቶ ወደ ቤቱ ሲያቀና እንደተለመደው እዛ ድልድይ አልባ ወንዝ ላይ ደረሰ። ወንዙን ሲያየው ሰባኪው ያስተማረው የእምነት ትምህርት ድቅን አለበት። ወዲያውኑ "እኔ እኮ በእግዚአብሔር አምናለሁ እግዚአብሔርም ይህን ለእኔ ማድረግ አይሳነውም" በማለት በፍጹም እምነት ወደ ጥልቁ ወንዝ በመሄድ ረገጠው እንዳለውም ተሳካለት መራመድም ቻለ። ያን ዙሪያ ጥምጥም የሆነ የቤቱን ጎዳና በጣም አጭር በሆነ ደቂቃ አጠናቆ ቤቱ ግባ።
ሚስቱም በመደንገጥ "ቤተክርስቲያን አልሄድክም እንዴ? ምነው በጊዜ መጣህ?" ብላ ብትጠይቀው የሆነውን ሁሉ ነገራት። እሷም በጣም ተደንቃ "ባለቤቴ ይህ ተዐምር ከተደረገለት መምህሩማ ምን ያህል ኣምላክ የመረጠው ቅዱስ ነው" ብላ "በል ነገ ይዘኸው ና! ቤታችንን በበረከት ይጎብኝልን።" በማለት ባለቤቷን ተማጸነች።
በማግስቱ የዋሁ ባል ያለምንም ፍርሃት እና ጥርጣሬ በወንዙ ላይ ተረማምዶ ከተሻገረ በኋላ ትምህርቱን ተከታትሎ ጉባኤው ሲፈጸም ሰባኪውን ሄዶ፥ "ባለቤቴ እቤት እየጠበቀችን ነው እባክህን አብረን እንሂድ አለው።" ሰባኪውም ግብዣውን ተቀብሎ ጉዞ ጀመሩ። ሁለቱም እዚያ ወንዝ አጠገብ ሲደርሱ የዋሁ ሰውዬ እንደለመደው በውሃው ላይ እየተራመደ ጥቂት ከተጓዘ በኋላ ዞር ብሎ ሰባኪውን ሲመለከት ከወንዙ ዳር እንደቆመ ነው። በሰባኪው መቆም ተገርሞ "ና እንጂ መምህር ምን ሆነሃል?" ሲል ጠየቀው። ሰባኪውም "ፈራሁ" ሲል ይመልስለታል። ውሃውን እየረገጠ ወደኋላ ተመልሶ "ምነው መምህር? እኔን ለዚህ አብቅተህ እንዴት ትፈራለህ? ና ተሻገር እባክህን" ሲል ጠየቀው በሰውዬው ንግግር ጭንቅላቱ የተነካው መምህርም፡ "ወዳጄ እኛ #እናሻግራለን እንጂ #አንሻገርም!" ሲል መለሰለት።
እኛስ የምንናገረውንና የምናዳምጠውን፣ የምናስተምረውንና የምንማረውን፣ የምንሰብከውንና የምንሰበከውን እየኖርን ነውን?
@bdebremhret
@bdebremhret
@bdebremhret
"#አሻጋሪዎች"
ሰባኪው በአንድ ቤተክርስቲያን እየተገኘ ዘወትር
ያስተምራል። በየእለቱ በርካታ ምእመናን በቦታው እየተገኙ ይሰበካሉ (ይማራሉ)። ከእነዚህ በርካታ ምእመናን ውስጥ አንደኛው ራቅ ካለ ቦታ ነው ሚመጣው። ወደ ቤተክርስቲያን ሲመጣም ሆነ ሲመለስ መሻገሪያ ድልድይ የሌለውን ወንዝ እየዞረ ስለሆነ ከሌሎች ይልቅ ብዙ የሚደክመው እሱ ነው።
#አንድ_ቀን_ግን_እንዲህ_ሆነ፦
ሰባኪው የሚያስተምረው ስለ ጽኑ እምነት ነበር። " የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ፥ ይህን ተራራ፦ ከዚህ ወደዚያ እለፍ ብትሉት ያልፋል፤ የሚሳናችሁም ነገር የለም።” የሚለውን ማቴ. 17፥20 ያለውን የመጽሃፍ ቅዱስ ኃይለ ቃል ጠቅሶ ሰው በእምነቱ ጽኑ ሲሆን የሚሳነው ነገር እንደሌለ ለምእመኑ አስረዳና የዕለቱን ስብከት አጠናቀቀ።
ይቀጥላል.......👇👇
ታስታውሰኛለህ
እዘምር ነበረ
እፈራክ ነበረ
አስቀድስ ነበረ
እዎድክ ነበረ ነበረ ነበረ ነበረ
ነበረ ያልኩኝ ነውር ላይ ከርሜ፣
ያንገበግበኛልህ አንተን ያህል አባት መስቀሌ ደግሜ ።
የመመለስ መንገድ ባይሆንም ለጌታ፣
መጣል ግን አይከፋም የነበርን ቦታ።
የሰንበት ቀንና ሰንበት ትምህርት ቤት
ትዝታ የሌለው ባይኖርም አንዳች ቤት።
በልጅነት ድሮ፣
አሾረው ነበረ የደብሩን ከበሮ።
እላለው እላለው
በጊዜ በእድሜ እየደበዘዙ
ዘምሬ ነበር ማለት የሚያበዙ
ከነበር ፉከራ ጀርባ ተቀምጠን
አታውቁም ከመባል ፍረሀት ሮጠን
ሰንበት ትምህርት ቤት መልዕክት ዮሐንስ
መልከዕ እየሱስ ዘልቄ ነበረ የሚለው ሰው ቁጥር ያውም በተውሶ
ሰንበት መማር እና ሰንበት ማክበር ቀረ ነበርን ከልሶ
ነበርን በንባብ ነበርን በውርድ ነበረን በዜማ
ስናጠና ከርመን አየው ተላለፈን
ለእግዜሩም ለሰው ነበርን የተረፈን
ሙዳዬ ምፅዋት የመያዝን ትህትና
አሀን ተቀየርን በሚይዙ ሰዎች ውስጣችን ሳይቀና፣
ልክ እንደ ጅልነት ልክ እንደ ልጅነት ሰፈረነው ሲያበቃ
እኛም እንዲ ነበርን ማለት ሆነ በቃ
ትህትና ሰበርን ትህትና ቀበርን
ስናጠናው አለን መልከዓ ነበርን
ታስታውሰኛለህ
አትይብኝ ድንጉጥ ነበሴን፣
አትይብኝ ፍሬ ከርሴን።
ቁመናዬን አትታዘብ
እኔ ከንቱ መዘባዘብ
አትበርብረኝ ኩላሊቴን፣
ታውቀው ዬለህ ባዶ ቤቴን
ባዶ ሰው ነኝ አንተን ባምንም
አትመዝነኝ አልመዝንም
ስንት እመዝን እንደው
ቆዳዬን ብቀደው
ስንት ይሆን ምለካው
ጨርቁን እስክነካው
እንጃልኝ ተማፅኖዬ አንዲት
ነውሬን ተውልኝ
ሽማዬን ክላልኝ
ጨፍነህ ላሞኝህ
የውሸቴን ልሸኝህ
በልዘልቅ እንኳን ቤትህ ልርገጠው ደጅህን
በዚያው ባንተ አይንህ ጋርድልኝ አይንህን
እኔማ እኔማ ገዛው አልባስጥሮስ
ገና ነው የኔ ጦስ
እኔማ ገዛው መባ ጧፍ
ገና ነው የኔ አፍ
እኔማ ገዛው መጋረጃ
የኔን ነገር እንጃ
ታውቀኝ ዬለህ (2) ያንን መልኬን
ምን ቀየረው ያን ታሪኬን
መቼ ዎጣው ከእቅፍህ
ምን ጊዜ ነው የሸሸሁት
ምን እለት ነው ከእኛ ስር ያመለጥኩት
ምን ሰዓት ነው ምን ቅፅበት ነው ምን ደቂቃ
ትተወኛለህ ዎይ ለሞት እስክበቃ
ታስታውሰኛለህ
እዘምር ነበረ
አስቀድስ ነበረ
እፈራክ ነበረ
እዎድክ ነበረ ነበረ ነበረ ነበረ
ነበረ እያልኩኝ ነውር ላይ ከርሜ
ያንገበግበኛል አንተን ያህል አባት መስቀሌ ደግሜ
ታስታውሰኛለህ አሁንም ልጅህ ነኝ
እኔ ፈራሀለው ፍቅር እያመመኝ
ተለውጫ ቢፈርስ ፀጋና መንገዴ
መልኬን የማይረሳ እየሱስ ዘመዴ ክርስቶስ ዘመዴ አግዚአብሔር ወዳጄ
ታስታውሰኛለህ አሁንም በክብር
ቆዳዬን በለጠው ነውሬን ስደምር
ነበርኩኝ በቤትህ የምለማመንህ
ነበረኩኝ በቤትህ ያሞቀኝ እጣንህ
አይኖችህ ናፈቁኝ እጆችህ ናፈቁኝ
እቅፍህ ናፈቀኝ
ሰላም ያልኩት አለም ጭራሽ አስጨነቀኝ
ቅዳሴው እንዳለው ችለው ለታደሉ
አብ ወልድ መንፈስቅዱስ ያስጨክኑማሉ
አስጨክነኝ በአለም አስጨክነኝ በሀጥያት አስጨክነኝ በቃ
ትተወኛለህ ዎይ ለሞት እስክበቃ
አስጨክነኝና ልመለስ ከቤትህ
ተብዬ ልጠራህ እግዚአብሔር አባትህ
አስጨክነኝ
አስጨክኝኝ ማርያም
አትህጂ ትነሺኝ አኑሪኝ በግርግም
ግድ ሆኖብኝ እንጂ ከልጅሽ ቤት መራቅ እኔ አልፈልግም
ግድ ሆኖብኝ አይደል (2)የምመላለሰው
እንጂ ከአባትህ ቤት ምን ይሻለዋል ሰው
ያነጫንጨኛልህ (2)
የእናቱ መዳፍ ከእጁ እንደቀሙት
ልረፍና ጥሪኝ ከልጅሽ ስር ልሙት
ፍቅርሽ የለው ጠረፍ
መንገዴ ይቅናና ጥሪኝና ልረፍ
ደከመኝ ጌታዬ ደከመኝ ጌታዬ ደከመኝ የኔ አምላክ
ደከመኝ ማርያም ደከመኝ እመአምላክ
ወይ እንደሰው አልሆንኩ ወይ እንደመላአክ
መጀገን ከበደኝ በገዛ ስጋዬ
ልተኛበት ያልኩት አላስተኛ አለኝ የገዛ አልጋዬ
እሺ በለኝና
አስጨክነኝ እና
ልመለስ ከቤትህ በፍቅር በስምህ
ስጋዬን በስጋ ደሜንም በደምህ
አስጨክነኝ በአለም እንዳልሆን ግያስ
አስጨክነኝ እና ከቤትህ ልመለስ
ሙዳዬ ምፅዋት ልያዝ
ታስታውሰኛለህ
እዘምር ነበረ
አስቀድስ ነበረ
እፈራክ ነበረ
እዎድክ ነበረ ነበረ ነበረ ነበረ
ነበረ እያልኩኝ ነውር ላይ ከርሜ
ያንገበግበኛል አንተን ያህል አባት መስቀሌ ደግሜ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ገጣሚ ኤልያስ ሽታሁን
የአመቱ የክረምት የመጨረሻ እና የመዝግያ ስለጠና እነሆ የፊታችን እሁድ 8:00
የእውነት ያለፋት ሳምንታት ግን ምንኛ ውብ እና የፍቅር ነበሩ?🥰
ቢሆንም "እኔ እኮ አምልጦኛል እንዴት ከአሁን በኃላ እሄዳለው?" እንዳይሉ።
እንደውም በመዝጊያችን እሁድ እርሶን፣አንተን፣አንቺን፣እኔን፣እኛን ቤተክርስቲያን እየጠራችን ነው። ለ2:00 ቆይታ ብቻ ፤ ውሳኔው የኛ ነው።
መጨረሻ መልዕክታችን ነው
🌿መልካም ጊዜ 🌿
👇👇join👇👇
@bdebremhret
@bdebremhret
@bdebremhret
ሰላምታችን በያላችሁበት ይድረሳችሁ ውድ ኦርቶዶክሳዊያን የዚህ መንፈሳዊ ግሩፕ ተከታዮች።
👉በዚህ ግሩፕ ስናካሂድ የነበሩትን ተወዳጅ የሆኑ ልዩ ልዩ መርሀ ግብራት አቋርጠን በመቆየታችን ከልብ ይቅርታ እንጠይቃለን።
በቅርቡ ለእናንተ ኦርቶድክሳዊያን
👌የተመረጡ እና ውብ የሆኑ መርሃ ግብራትን ይዘን እንመጣለን እስከዚያው በትዕግስት እንድትጠብቁን ይሁን።🙏
👇👇join👇👇
@bdebremhret
@bdebremhret
@bdebremhret
@bdebremhret
@bdebremhret
@bdebremhret
@bdebremhret
