እውነት ለሁሉ ewnetlehulu.net
Open in Telegram
“እውነት ለሁሉ” በዓለም ዙርያ በሚገኙ በጎ ፈቃደኛ ክርስቲያኖች የተመሠረተ ድረ-ገፅ ሲሆን እስልምናንና ክርስትናን የተመለከቱ መጣጥፎችን፣ መጻሕፍትን፣ ዜናዎችንና የመሳሰሉትን ያስነብባል፡፡ የኦዲዮና የቪድዮ መረጃዎችንም ያቀርባል፡፡ የበለጠ ለማወቅ http://www.ewnetlehulu.org ይጎብኙ።
Show more9 218
Subscribers
No data24 hours
+157 days
+5630 days
Posts Archive
ከዓመታት በፊት የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ሳለሁ አሁን ርዕሱንና ጸሐፊውን የማላስታውሰውን የታሪክ መጽሐፍ አንብቤ ነበር። (አንብቦ ለመጨረስ የማይመች ግዙፍ መጽሐፍ ስለ ነበር ገጾቹን አገላብጬ ነበር ማለት ይቀላል)። ይህ መጽሐፍ የሀገራትንና ሕዝቦችን ከታሪክ ህልውና የመክሰም ትወራዎችን በሚዘረዝርበት ርዕስ ስር - በትክክል ካስታወስኩ - ወደ ሰባት የሚሆኑ መላ ምቶችን ያስቀምጣል። እነዚህን መላ ምቶች ከዘረዘረ በኋላ የአይሁድ ሕዝብ ከእነዚህ መላ ምቶች በአንዱም ሊገለጽ እንደማይችል ያሳስባል። መላ ምቶቹ ትክክል ከሆኑ የአይሁድ ሕዝብ እንደ ማንኛውም ህልውናው እንደ ከሰመ ሕዝብ መጥፋት የነበረበት ቢሆንም በልዩ ሁኔታ ተጠብቆ እስከ ዛሬ ድረስ አለ። በታሪክ ሁሉ በአይሁድ ሕዝብ ላይ የደረሰውን መከራና እንግልት ስንመለከት ህልውናው ተጠብቆ መኖሩ ተዓምር የሚያሰኝ ነው።
መጽሐፍ ቅዱስን ስንመለከት የአይሁድ ሕዝብ እንዲጠፋ ከፍተኛ ጥረት ያደረገ ሐማ ስለ ተባለ ፋርሳዊ (ኢራናዊ) ታሪክ እናነባለን። በመጽሐፈ አስቴር መሠረት ሐማ የአይሁድን ሕዝብ ክፉኛ የሚጠላ ሰው የነበረ ሲሆን የአይሁድ ሕዝብ እንዲጠፋ ለማድረግ ከፍተኛ የጥፋት ድግስ አዘጋጅቶ ነበር። ነገር ግን ሐሳቡ ከሽፎ ለአይሁዳዊው ለመርዶክዮስ ባዘጋጀው መስቀያ ላይ እርሱ ራሱ ተሰቅሏል (አስቴር 7፡10)። በሌላ ወገን ደግሞ የአይሁድ ሕዝብ በምርኮ ሲሠቃይ ከነበረበት የግፍ አገዛዝ ነጻ ወጥቶ ወደ ሀገሩ እንዲመለስና እንደ ሕዝብ ህልውናው እንዲቀጥል ስላደረግ ሌላ ኢራናዊ ንጉሥ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እናነባለን። የንጉሡ ስም ቂሮስ ሲሆን የአይሁድ ሕዝብ ህልውና እንዲቀጥል ሰበብ ከሆኑት ሰዎች መካከል ዋነኛው ነው (ዕዝራ 1፡2)።
ፖለቲከኞች እንደሚሉት በፖለቲካው ዓለም ዘላቂ ጥቅም እንጂ ዘላቂ ወዳጅም ሆነ ጠላት የለም። ዛሬ እርስ በርስ ለመጠፋፋት የሚቀጣቀጡት እስራኤልና ኢራን ከሃምሳ ዓመታት በፊት በፓህላቪ ዘመን ወዳጆች ነበሩ። በአያቶላዎች ዘመን ደግሞ ጠላቶች ሆነዋል። ነገ ደግሞ ተመልሰው ወዳጅ ሊሆኑ ይችላሉ።
እግዚአብሔር አምላክ ከአይሁድ ሕዝብ ጋር ያለውን ጉዳይ ገና እንዳልጨረሰ መጽሐፍ ቅዱስን ካነበበ ሰው የተሰወረ አይደለም። ብሔራዊ ንስሐ አድርገው ወደ መሲሁ የሚመለሱበት ዘመን ይመጣል (ዘካርያስ 12፡10፣ ሮሜ 11:25–26 ፣ ሆሴዕ 3:4–5)። ሰይጣን ይህንን ሕዝብ ማጥፋት ይፈልግ የነበረው ለመሲሁ መንገድ በመሆን የአብርሃም በረከት ተፈጻሚ እንዳይሆን ነበር። የመሲሁ በረከት በዚህ ሕዝብ አማካይነት ስለ ተፈጸመ አሁን ደግሞ በበቀል ይህንን ሕዝብ ይፈልገዋል። በነገረ ፍጻሜ ውስጥ ካለው ሚና አንጻርም ይህ ሕዝብ እንዲጠፋ የሰይጣም ምኞት ነው።
በመጨረሻው ዘመን ከሚከሰቱት አስጨናቂ ክስተቶች መካከል አንዱ የጎግ ማጎግ እስራኤልን ለማጥፋት መሰብሰብ ነው (ሕዝቅኤል 38፡8)። በእስልምና የነገረ ፍጻሜ አስተምህሮ መሠረት ደግሞ መጨረሻ ከመሆኑ በፊት ሙስሊሞች የአይሁድ ሕዝብ ላይ ጭፍጨፋ እንደሚፈጽሙ ይታመናል (Sahih Muslim Book 54, Hadith 105)። በተለይም ደግሞ የሺአ ሙስሊሞች ማሕዲ ብለው የሚጠሩት ሐሰተኛ ክርስቶስ ሲገለጥ የአይሁድን ሕዝብ እንደሚጨፈጭፍ ተስፋ ያደርጋሉ። ለዚህ ነው እስራኤልን እንደ ሀገር፣ አይሁድንም እንደ ሕዝብ የሚጠሉት። በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት ደግሞ ጌታ እስራኤልን ይታደጋታል (ራዕይ 20፡7–9)። የሚገርመው ነገር በመጨረሻው ዘመን እስራኤልን ለማጥፋት ከሚሰበሰቡት ሀገራት መካከል ሁሉም ማለት በሚቻልበት ሁኔታ አሁን የሙስሊም ሀገራት ናቸው። በዚህ ውስጥ ግን ሳኡዲ አረብያ አልተካተተችም። ምናልባት ሁኔታዎች ተለዋውጠው ሳኡዲ የክርስቲያን ሀገር ወደ መሆኑ ትለወጥ ይሆን? አናውቅም። At this point, I might sound like an apocalyptic preacher but all of this is right there in the Bible.
ሐሳቤን ሳጠቃልል፦ ለኢየሩሳሌም ሰላም እንጸልይ (መዝሙር 122፡6)። እግዚአብሔር ሕዝበ እስራኤልን እንዲታደግ፣ ከሁሉ በላይ ደግሞ መሲሁን ወደ ማወቅ እንዲመጡ እንዲረዳቸው እንጸልይ። ለእስራኤል ብቻ ሳይሆን ለሁሉም የዓለም ሕዝቦች ሰላም እንጸልይ። ክስተቶችን ደግሞ በቃሉ ውስጥ በተጻፈው መሠረት እንመዝን። ሰላም ለእስራኤል፣ ሰላም ለኢራን።
አዲስ ዜና!
ብዙ የሙት ባሕር ጥቅልሎች ዕድሜያቸው ቀደም ሲል ከተገመተው እንደሚበልጥና አንዳንዶቹ እንዲያውም ኦሪጅናል ጸሐፊያኑ በነበሩበት ዘመን የተጻፉ ሊሆኑ እንደሚችሉ ተመራማሪዎች ተናገሩ። https://www.theguardian.com/science/2025/jun/04/many-of-dead-sea-scrolls-may-be-older-that-thought-experts-say
በዚህ ርዕስ ላይ የበለጠ መረጃ ለማግኘት ተከታዮቹን ሊንኮች መጠቀም ትችላላችሁ 👇
https://ewnetlehulu.net/muhammad/mo_marriage_to_aisha/
https://ewnetlehulu.net/mo-and-aisha/
አሕመዲን ጀበል እንደ ተለመደው የሙሐመድን የጋብቻ ሕይወት ትክክል አድርጎ ለመሳል እንደ ገለባ ክምር የተኮፈሰ ነገር ግን ፍሬ የሌለው ሐተታ ለንባብ አብቅተዋል። ሙሐመድ የ6 ዓመት ህፃን አጭቶ በ9 ዓመቷ አብሯት መተኛቱ ትክክል እንደሆነ ሊያሳምኑን ይህንን ያህል መድከማቸው አሳዛኝ ነው። ጽሑፎቻቸው ብዙ ስህተቶችን የሸከፉ ቢሆኑም የተወሰኑትን ብቻ ላንሳ።
1. የጌታን እናት ቅድስት ድንግል ማርያምንና አኢሻን ለጌታ እናት አክብሮት በጎደለው መንገድ ማነጻጸራቸው እጅ በጣም ስህተት ነው። ሁለቱንም “ድንግል” በሚል ቃል የጠቀሱ ሲሆን የጌታን እናት ወደ አኢሻ ደረጃ ዝቅ ለማድረግ አልመው የተናገሩት ነው። የጌታ እናት “ድንግል” በሚል መጠርያ የምትጠራበት ምክንያት በድንግልና ጌታን ስለወለደች ነው። አንዲት ሴት በድንግልና ስላገባች “ድንግል” የሚል ማዕርግ ለሕይወት ዘመኗ ሁሉ መስጠት የተለመደ ካለመሆኑም በላይ በጋብቻ ኖራ ሕይወቷ ያለፈን ሴት በዚህ አጠራር መጥቀስ ትርጉም አይሰጥም። ይህንን ልዩ ዓላማ ያለው አጠራር ተገቢ ባልሆነ ቦታ አስገብተዋል። አቶ አሕመዲን አንዲትን በጋብቻ እየኖረች ያለችን ሴት በድንግልና ስላገባች ብቻ “ድንግል እገሊት” ብሎ መጥራት ተቀባይነት ያለው ጉዳይ እንደ ሆነ የሚያስቡ ከሆነ በአካባቢያቸው በሚኖሩት ባለ ትዳር እናቶች ላይ ይህንን አጠራር በመሞከር ግብረ መልሳቸውን ቢያዩ ጥሩ ትምህርት የሚያገኙበት ይመስለኛል። የገዛ ባለቤታቸውንም "ድንግል እገሊት" እያሉ በሰዎች ፊት መጥራትን ቢያዘወትሩና ለሌሎች ምሳሌ ቢሆኑ ምን ይላቸዋል?
2. የጌታን እናት በተመለከተ በምንጭነት የጠቀሱት “የያዕቆብ ወንጌል” በክርስቲያኑ ማሕበረሰብ ዘንድ ተቀባይነት የሌለው የፈጠራ ጽሑፍ፤ መስመ ወንጌል (Pseudo Gospel) እንጂ በያዕቆብ የተጻፈ አይደለም። ሙስሊም ሊቃውንት እስላማዊ ምንጮችን ጠንካራ፣ ደህና፣ ደካማ እና ቅጥፈት ብለው በመከፋፈል ለሚቀበሉትና ለማይቀበሉት ምንጭ ጥብቅ መስፈርት ባወጡበት ሁኔታ ምሑራን የፈጠራ ጽሑፍ መሆኑን በአንድ ድምፅ የሚስማሙበትን በያዕቆብ ስም ባልታወቀ ግለሰብ የተጻፈን ጽሑፍ ተአማኒ ማስረጃ አድርጎ ማቅረብ አስቂኝ ነው። የእርሳቸው ጊዜ ሲሆን መረጃ ከተአማኒ ምንጮች ብቻ እየጠየቁ ለክርስትና ሲሆን የፈጠራ ጽሑፍ መጥቀሳቸው ትዝብት ላይ ይጥላቸዋል።
3. የጠቀሱት የያዕቆብ ወንጌል ዮሴፍ የጌታን እናት እንዲጠብቃት እንደ ወሰዳት እንጂ ለጋብቻ እንደ ወሰዳት አይናገርም። የዮሴፍንም ዕድሜ ከፍ አድርጎ የጠቀሰበት ምክንያት የእጮኝነቱ ዓላማ ጋብቻ ሳይሆን ጥበቃ መሆኑን ለማሳየት ነው። እንዲያውም ዮሴፍ ከእርሷ ጋር ወሲብ የመፈጸም ፍላጎት እንደሌለው ምዕራፍ 15፡4 ላይ ይገልጻል። አቶ አሕመዲን የጠቀሱትን ተዓማኒነት የሌለው ምንጭ ራሱ በማጣመም የማይለውን ለማስባል ሲጣጣሩ ታይተዋል። ምን ያህል ተስፋ ቢቆርጡ ይሆን?
4. መጽሐፍ ቅዱስ ወላዲተ አምላክ ብፅእት ማርያምን ንቁ፣ በሳልና ጥበበኛ ሴት አድርጎ ቢያቀርብም ትክክለኛ ዕድሜዋን አይገልጽም። አቶ አሕመዲን በጠቀሱት በያዕቆብ ወንጌል መሠረት ግን ማርያም ለዮሴፍ የታጨችው በ12 ዓመቷ ቢሆንም ተዓምራዊ በሆነ ሁኔታ የፀነሰችው በ16 ዓመቷ ነበር። መጽሐፉ በምዕራፍ 12፡3 ላይ በግልጽ “She was sixteen years old when these mysteries happened to her” (እነዚህ ምስጢራት (ድንቃድንቆች) በእርሷ ላይ ሲከሰቱ አሥራ ስድስት ዓመቷ ነበር) ይላል። አቶ አሕመዲን ግን እንዲህ ሲሉ በገዛ ፈጠራቸው ላይ የተመሠረተ ጥያቄ ይጠይቃሉ፦
“እኛ እንደ አንዳንድ ጋጠወጦችና ተሳዳቢዎች ብንሆን ኖሮ "ማርያም በለጋ ዕድሜዋ በማርገዟ ለሥነ ልቦናና አካላዊ ጥቃት ተዳርጋለች" ወዘተ ባልን ነበር፡፡ ... እኛ በእነሱ አካሄድ ብንጓዝ ኖሮ "እንዴት የዓለሙ ፈጣሪ የሚባለው ኢየሱስ በ12 ዓመት ህፃን ማህፀን ለመረገዝ ፈቀደ?" ስንል በጠየቅን ነበር።”
ክርስቲያኖች ዕድሜው በ50ዎቹ ውስጥ የነበረው ሙሐመድ የ6 ዓመት ህፃን አጭቶ በ9 ዓመቷ አብሯት መተኛቱ ትክክል እንዳልሆነ መናገራቸው ከጨዋነት የጎደለ ነገር እንደሌለው ለመረዳት ሚዛኑን ያልሳተ ኅሊና ያለው ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው። እንደ አሕመዲን ግን ተአማኒነት ከሌለው ምንጭ ከጠቀሱ በኋላ ይህ አልበቃ ብሎ በምንጩ ውስጥ ያልተባለን ቅጥፈት ከኪስ አውጥቶ መጻፍ ኅሊና ቢስነትን ይጠይቃል። እኛ እርሳቸው የተጠቀሟቸውን “ጋጣወጦች፣ ተሳዳቢዎች” የሚሉ ቃላትን ልንጠቀም አንሻም፤ ነገር ግን እርሳቸውን ከሚያክል ሙስሊሙን ማሕበረሰብ ወክሎ ሊናገር ከሚችል ሰው እንዲህ ያለ ቅጥፈት እንደማይጠበቅ መግለጽ በቂ ነው። ሌላውን ጋጣወጥና ተሳዳቢ አድርገው የሳሉት አሕመዲን ይህንን ስህተታቸውን ለማረምና ይቅርታ ለመጠየቅ የሚበቃ ህሊና ያላቸው እንደሆን በቀጣይ የምናይ ይሆናል።
5. በመጀመርያው ጽሑፋቸው ከተዛባ ምንጭ በመጥቀስ፣ የጠቀሱትን ምንጭ ደግሞ በማስዋሸት የጀመሩት አቶ አሕመዲን በሁለተኛው ጽሑፋቸው ርዕሱን ከአኢሻ የጨቅላ ዕድሜ ጋብቻ “ዮሴፍና ማርያም ባልና ሚስት ነበሩ” ወደሚል ርዕስ በማዞር ሐሳብ ለማስቀየር ሲታገሉ ታይተዋል። ይህ ግልጽ Red Herring Fallacy ነው። የማርያምን ዕድሜ በተመለከተ መነሻ ያደረጉት የማይታመን ምንጭና የገዛ ፈጠራቸውን ሆኖ ሳለ ገና ከመሠረቱ የተበላሸውን መረጃቸውን እንደ እውነት በመቁጠር ሌላ ክርክር መጀመራቸው ለአኢሻ ጉዳይ መልስ እንዳጠራቸው ማሳያ ነው።
6. አቶ አሕመዲን ይህንን ሁሉ እያወሩ ያሉት የሙሐመድንና የአኢሻን ጋብቻ በዘመኑ በነበረው ባሕል መመዘን ተገቢ መሆኑን ለማሳመን እንደሆነ ግልጽ ነው። ለዚህ ነው የአይሁድን ባሕል እንዲሁም ቅድመ ኢንደስትሪ አብዮት የነበረውን የምዕራባውያን ባሕል በእማኝነት የጠቀሱት። ይህ ደግሞ ሙሐመድ ለሰው ልጆች ሁሉ ምሳሌ ሊሆን የሚችል የላቀ ስብዕና የነበረው ሰው ነው የሚለውን የእስልምና አእማድ ትምህርት ውድቅ የሚያደርግ ነው። እኛስ ምን አልን? ሙሐመድ በሰባተኛው ክፍለ ዘመን ኋላ ቀር ባሕል ኖሮ ያለፈ አንድ ግለሰብ ካልሆነና ለሰው ልጆች ሁሉ ምርጡ ምሳሌ እንዲሆን የተላከ ከሆነ ስነ ምግባሩ መመዘን ያለበት በሰባተኛው ክፍለ ዘመን ባሕል ሳይሆን የሰው ልጆች በደረሱበት የላቀ ስነ ምግባር ነው፡፡ ለሰው ልጆች ሁሉ ምሳሌ እንዲሆን በፈጣሪ የተላከ ሰው በእርሱ ዘመን ከነበረው ኋላ ቀር ባሕል የላቀ ስብዕና ሊኖረው ይገባል፡፡ ካልሆነ ግን ለሁሉም የሰው ልጆች የሚመጥን ምሳሌ መሆን አይችልም ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ሙስሊም ወገኖች ሙሐመድ ከነቢያት ሁሉ የላቀ ሥነ ምግባር የነበረውና የእርሱን ምሳሌነት መከተል ለጀነት እንደሚያበቃ ማመናቸው ስህተት ነው፡፡ አሕመዲን ጀበል ሙሐመድ የ6 ዓመት ህፃን አግብቶ በ9 ዓመቷ አብሯት መተኛቱ ትክክል መሆኑን ሊያሳምኑን ያደረጉት ተጋድሎ ሁሉ መቋጫው ሙሐመድ በዘመኑ ከነበረው ኋላ ቀር ማሕበረሰብ ያልተሻለ ስነ ምግባር የነበረው ለሰው ልጆች ምሳሌ ሊሆን የማይበቃ ግለሰብ ነበር የሚል ሆኗል። ስለዚህ ለሰው ልጆች ሁሉ ምርጡ ምሳሌ አድርጎ በቁርአንና በሐዲስ ራሱን ማቅረቡ ሐሰተኛ ነቢይ ያደርገዋል፤ ያልሆነውን እንደ ሆነ በማስመሰል የሚናገር ሰው ሐሰተኛ ነውና። ለሙሐመድ ሐሰተኛነት እንዲህ ያለ ጠንካራ ሙግት በማቅረባቸው አቶ አሕመዲን ሊመሰገኑ ይገባል። በዚህ ርዕስ ላይ የበለጠ መረጃ ለማግኘት ተከታዮቹን ሊንኮች መጠቀም ትችላላችሁ 👇
https://ewnetlehulu.net/muhammad/mo_marriage_to_aisha/
ባለፈው አንድ ወር 8,000 ሰዎች 27,000 ጊዜ የኛን ዌብሳይት ጎብኝተዋል። በአሁኑ ሰዓት እውነት ለሁሉ በሀገራችን ውስጥ ትልቁ ክርስቲያናዊ የምካቴ እምነት ድረ-ገጽ ነው። በርግጥ ከሥራው ስፋት አንጻር ብዙ ተደራሽነት ይቀረናል። ይህንን ታላቅ አገልግሎት በማስተዋወቅ ከጎናችን እንድትቆሙ በትህትና እንለምናችኋለን። ewnetlehulu.net
አሕመዲን ጀበል ሙሐመድ ለ25 ዓመታት ከኸዲጃ ጋር በአንድ ለአንድ ጋብቻ ተወስኖ መኖሩን ከህልፈቷ በኋላ ለኖረበት መድብለ ጋብቻ እንደ ማፅደቂያ አድርጎ አቅርቧል። ሙሐመድ የሴሰኝነት ችግር ቢኖርበት ኖሮ እስከ 25 ዓመቱ ለምን ሳያገባ ኖረ? ከ25-50 ዓመቱ እንዴት በኸዲጃ ብቻ ተወስኖ ኖረ? የሚሉትን የመሳሰሉ አስቂኝ ጥያቄዎችን ይጠይቃል። መልሱ ግልፅና ቀላል ነው።
ሙሐመድ ከኸዲጃ ጋር በጋብቻ እስከ ተጣመረበት ጊዜ ድረስ በድኽነት ይኖር የነበረ ተንከራታች ወጣት ነበር። በዚያ የችግር ዘመን ደርሳ ከድኽነት ያስጣለችው ኸዲጃ ናት። እርሷ በሕይወት በነበረችበት ዘመን በአንድ ለአንድ ጋብቻ ተወስኖ የመኖሩም ምስጢር ይኸው ነው። በእርሷ ንብረት ከድኽነት ወጥቶ በቤቷ እየኖረ በእርሷ ላይ ደርቦ ማግባት የማይታሰብ ነው። ከእርሷ ህልፈት በኋላ በአንድ ለአንድ ጋብቻ ተወስኖ ቢኖር ኖሮ ከኸዲጃ ጋር በዚያ መንገድ የኖረው በፈቃዱ እንጂ ተገድዶ እንዳልሆነ መደምደም በቻልን ነበር። ከእርሷ ህልፈት በኋላ ደስ ያሰኘችውን ሴት ሁሉ (ዘመዶቹን ጨምሮ) እንዲያገባ አላህ እንደ ፈቀደለት በመናገር የቻለውን ያህል ሴት አግብቶ ኖሯል። ለምሳሌ ተከታዩን ጥቅስ እስኪ እንመልከት:-
ሱራ 33:50 “አንተ ነቢዩ ሆይ! እኛ እነዚያን መህሮቻቸውን የሰጠሃቸውን ሚስቶችህን፣ አላህ ባንተ ላይ ከመለሰልህም እነዚያን እጅህ የጨበጠቻቸውን ምርኮኞች፣ እነዚያንም ከአንተ ጋር፣ የተሰደዱትን የአንጎትህን ሴቶች ልጆች፣ የአክስቶችህንም ልጆች፣ የየሹማህንም ሴቶች ልጆች ፣ የየሹሜዎችሕንም ሴቶች ልጆች (ማግባትን) ለአንተ ፈቅደንልሃል፤ የአመነችንም ሴት ነፍሷን (ራሷን) ለነቢዩ ብትሰጥ ነቢዩ ሊያገባት የፈለገ እንደ ሆነ፣ ከምእምናን ሌላ ላንተ ብቻ የጠራች ስትሆን፣ (ፈቀድንልህ)፤ በነርሱ (በምእምናን) ላይ በሚስቶቻቸውና እጆቻቸውም በጨበጧቸው (ባሮች ነገር) ግዴታ ያደረግንባቸው በእርግጥ አውቀናል፤ ባንተ ላይ ችግር እንዳይኖር፣ (ያለፉትን ፈቀድንልህ)፤ አላህም መሐሪ አዛኝ ነው።"
በዚህ የአላህ ፈቃድ መሠረት ሙሐመድ የአክስቱ ልጅ የነበረችውን ለማደጎ ልጁ ተድራ የነበረችውን ዘይነብን ጭምር ከባሏ ነጥቆ አግብቷል። እነ አሕመዲን መልስ የሌለውን ጉዳይ አንስተው ራሳቸውን ከሚያስጨንቁ ዝም ቢሉ ይሻላቸው ነበር። ለበለጠ መረጃ ይህንን ጽሑፍ ያንብቡ https://ewnetlehulu.net/zaynab/
የእውነት ለሁሉን የቴሌግራም ቻናል ተቀላቅለው የክርስቲያን-ሙስሊም ውይይቶች ተሳታፊ ይሁኑ! https://t.me/ewnetlehulu
[ይህንን መልእክት ቢያንስ ለ15 ወዳጆቻችን ሼር በማድረግ ይህንን ቻናል እናስተዋውቅ።]
ሙሐመድ የኢየሱስን አምላክነት በመካዱ ምክንያት ተቀስፎ እንደ ሞተ ያውቃሉን? ነገሩ እንዲህ ነው። ሙሐመድ ሃይማኖቱን ከመሠረተ በኋላ በአረብያና በዙርያው የነበሩ የተለያዩ ማሕበረሰቦች እንዲሰልሙ የቻለውን በጂሃድ የማስገደድና ያልቻለውን ደግሞ ደብዳቤዎችን በመላክ ጥሪ የማድረግ ዘዴዎችን ይጠቀም ነበር። የሙሐመድ ደብዳቤ ከደረሳቸው ማሕበረሰቦች መካከል በደቡብ አረብያ የሚኖር ነጅራን የተሰኘ ክርስቲያን ማሕበረሰብ ይገኝበታል። ከሙሐመድ የደረሳቸውን ደብዳቤ ምክንያት በማድረግ ከሙሐመድ ጋር ለመወያየት የማሕበረሰቡ ተወካዮች ወደ መዲና እንደ ተጓዙ ከእስላማዊ ምንጮች እንረዳለን። ውይይቱ የክርስቶስ አምላክነትና ሥላሴን በመሳሰሉት ርዕሰ ጉዳዮች ዙርያ ያጠነጠነ እንደ ነበረ እነዚሁ ምንጮች የሚናገሩ ሲሆን ባለመግባባት እንደተጠናቀቀ ተዘግቧል።
የውይይቱን ባለመግባባት መጠናቀቅ ተከትሎ ሙሐመድ “ሐሰትን የተናገረው ወገን እንዲቀሠፍ” በሚል እርስ በርስ የመረጋገም ስርዓት (ሙባሃላ) እንዲፈፅሙ ክርስቲያኖቹን የጋበዛቸው ሲሆን የክርስቲያኖቹ ምላሽ ግን አዎንታዊ አልነበረም። በዚህም ምክንያት ሙሐመድ ቤተሰቡን ሰብስቦ በማምጣት ብቻውን ተራገመ፤ እርግማኑም ደርሶበት በአንድ ዓመት ውስጥ በከባድ ህመም ሞተ። እነሆ ሙሉ ታሪኩ እዚህ ሊንክ ውስጥ ይገኛል
https://ewnetlehulu.net/mubahalah/
ወንድማችን Minas ይህንን ምሑራዊ ጽሑፍ አዘጋጅቶልናል። በተለይም ከሙስሊሞችና ከስህተት መምህራን ጋር በክርስቶስ አምላክነት ዙርያ የምትወያዩ ወገኖች በደንብ ብታጠኑት ይመከራል። አብሮ የተያያዘውንም መጨረሻ ላይ የሚገኘውን ጽሑፍ ያላነበባችሁ ወገኖች እንድታነቡ አበረታታለሁ። ካነበብን በኋላ ለሌሎች ማካፈል አንዘንጋ። መልካም ንባብ! https://ewnetlehulu.net/the-name-above-all-names/
የኢትዮ ፅንፈኛ ሙስሊሞች እፎይ የተሰኘው ወንድማችን ላይ ዘመቻ ከፍተዋል። ነፍሱን ለማጥፋት በየ ሚድያው ቅስቀሳ እያደረጉ ነው። ከትላንት ወዲያ ተሰብስበው ጥቃት ሊያደርሱበት ሞክረው ነበር። አንደኛ ነገር:- ኢትዮጵያ በሸሪአ ሕግ የምትተዳደር ሀገር አይደለችም። ሃይማኖት ላይ ጥያቄ አነሳ በሚል አንድን ሰው ተጠያቂ የሚያደርግ ሕግ የለንም። ሁለተኛ:- ልጁ ራሱ ጥፋተኛ ቢሆን በደቦ ፍርድ ጥቃት እንዲደርስበት መቀስቀስ በሕግ የሚያስጠይቅ ወንጀል ነው። ጥፋተኛን የሚቀጣ መንግሥት ባለበት ሀገር ከሕጋዊ ሂደት ውጪ አንድ ግለሰብ ላይ ጥቃት እንዲፈፀም መቀስቀስ ተጠያቂነትን ያስከትላል። ሦስተኛ:- ክርስትናን እንደ ልባቸው ሲሳደቡና ሲያንጓጥጡ የኖሩት የሀገራችን ሙስሊም ሰባኪያን በምን አንደበታቸው ሃይማኖታቸው እንደ ተነካ ስሞታ ሊያቀርቡ እንደሚችሉ ማሰብ ያዳግታል። የሰው ሃይማኖት መንቀፍ ጥፋት ከሆነ የመጀመሪያዎቹ ተጠያቂዎች እነርሱ ናቸው። የሆነው ሆኖ ይህ ወጣት እምነቱን ከመከላከል ውጪ ምንም ዓይነት ጥፋት አልፈፀመም። በእስላማዊ መጻሕፍት ውስጥ ያልተጻፈ ምንም ነገር ተናግሮ አያውቅም። ተናግሯል የሚል ሰው ካለ እስኪ አንዲት ነጥብቅ ይጥቀስ። ችግሩ እስላማዊ መጻሕፍት ሲገለጡ ብዙ አሸማቃቂ ጉዶችን የተሸከሙ በመሆናቸው ሳብያ ያለ ምንም ተጨማሪ ማብራርያ እንኳ የገዛ መጻሕፍታቸን ማንበብ ብቻውን በብዙ ሙስሊሞች ዘንድ እንደ ስድብ መቆጠሩ ነው። ሙስሊሞች ሃይማኖታቸው እንዲከበርላቸው ከፈለጉ አንደኛ:- የገዛ ነቢያቸውን የሚያንቋሽሹትን እነዚህን መጻሕፍት ሰብስቦ ማቃጠል፤ ሁለተኛ:- የሰው ሃይማኖት ሳይነኩ ዝም ብሎ መቀመጥ ያዋጣቸዋል። ችግሩ እዚያው እነርሱ ጋር በሆነበት ሁኔታ ሌላውን መወንጀል መፍትሄ አይደለም። ደግሞ ድሮ ድሮ ክርስቲያኖች እስልምናን ሳይጠቅሱ የራሳቸውን ሕይወት ሲኖሩ በነበሩባቸው ዘመናት ክርስትናን ሲሰድቡና ሲተቹ ኖረው መልስ ሲመለስላቸው ማለቃቀስ ምን የሚሉት ነው? ልጁ ዋሽቶ ከሆነ በአደባባይ ውይይት ገጥሞ ማሸነፍ፣ ያንን ማድረግ ከፈሩ ደግሞ በቪድዮ መልስ መስጠት። ሁለቱንም ማድረግ ካልቻሉ ሽንፈትን አምኖ መቀመጥ እንጂ የሰው ደም ለማፍሰስ መሯሯጥ የሃይማኖታቸውን ሐሰተኝነት ከመግለጥ የዘለለ ፋይዳ የለውም።
በግራኝ አሕመድ ወረራ ዘመን ለኢትዮጵያ ክርስትና መትረፍ ሰበብ የሆኑ በቀድሞ ሕይወታቸው ሙስሊም የነበሩና ክርስትናን የተቀበሉ ሁለት ሰዎች ነበሩ። አንደኛዋ የሐዲያዋ ተወላጅ ጥበበኛዋና ውቧ ንግሥት እሌኒ (በሌላ ስሟ የዘይላ ንግሥት) ስትሆን ሁለተኛው ደግሞ የመናዊው ባለ ብሩህ አእምሮ በቀድሞ ስሙ አቡ አል-ፈት በክርስትና ስሙ አባ ዕንባቆም ነበሩ። ንግሥት እሌኒ በፖለቲካና በወታደራዊው መስክ፣ አባ ዕንባቆም ደግሞ በመንፈሳዊ መስክ የሠሩት ሥራ የኢትዮጵያን ክርስትና ከጥፋት ታድጓል። በተለይም አባ ዕንባቆም የግራኝን ሠራዊት ያሸነፈውን ንጉሥ ገላውዴዎስን ከልጅነቱ ጀምሮ በማስተማር፣ ከዚያም በጦርነቱ ዘመን የእስልምናን ሐሰተኝነት የሚገልጡ ጽሑፎችን (ለግራኝ ለራሱ ደብዳቤዎችን መጻፍን ጨምሮ)፣ በኋላም በጦርነቱ የወደሙ ቅዱሳት መጻሕፍትን በመተካት እንዲሁም ከክርስትና የወጣውን ሕዝብ ወደ እምነቱ በመመለስ ረገድ ያበረከተው አስተዋፅዖ የሚረሳ አይደለም። የእነዚህ ሁለት ሰዎች በወቅቱና በቦታው መገኘት የእግዚአብሔር ተዓምራዊ ሥራ እንጂ ሌላ ሊባል አይችልም። የአባ ዕንባቆምን የሕይወት ታሪክና ጽሑፎች በተመለከተ አንድ ብዙ ዓመታትን የፈጀ ምሑራዊ ጽሑፍ በቅርቡ በሀገራችን ለሕትመት እንደሚበቃ መረጃው አለኝ።
ኢትዮጵያዊው የታሪክ ምሑር ስርግው ሀብለ ሥላሴ በጻፉት ታሪክ መሠረት በኡሑድ ጦርነት ላይ የኢትዮጵያ ወታደሮች ከመካ ተዋጊዎች ጎን ተሰልፈው ሙሐመድና ወታደሮቹን ተዋግተዋል። በዚህ ውጊያ ሙስሊሞች ክፉኛ የተሸነፉ ሲሆን ሙሐመድ ራሱ ቆስሎ ሁለት የፊት ጥርሶቹ ረግፈዋል (Sergew Hable Selassie, Ancient and Medieval Ethiopian History to 1270, p. 188.)። የእስልምና ውድቀትና የካዕባ መፍረስ በኢትዮጵያውያን እጅ እንደሚከናወን ሙሐመድ በትንቢት መልኩ ተናግሯል። ይህ በአረብ ሙስሊሞች ዘንድ ኢትዮጵያውያንን የመፍራትና በጥርጣሬ የመመልከት ስሜት መነሻው ከእስልምና ልደት እንደሚጀምር መረዳት ይቻላል። ከዚህ ጋር አያይዘን በየመን የኢትዮጵያ ጀነራል የነበረው አብርሃ ካዕባን ለማፍረስ ያደረገውን ዘመቻ ማንሳት እንችላለን። "መጥፊያችን በኢትዮጵያውያን እጅ ነው" የሚለው የአረብ ሙስሊሞች ስነ ልቦናዊ ስጋት ተጨባጭ ታሪካዊ መነሻ አለው። የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ እኛ ኢትዮጵያውያን እነርሱ እንደሚፈሩት በሰይፍ ሳይሆን በወንጌል እስልምናን ከምድረ ገጽ እናጠፋዋለን። መጥፊያው በኛ እጅ መሆኑን ራሱ አስቀድሞ አውቆታል።
የዐዲስ ኪዳን ቀኖና ተኣማኒነት በሚል ርዕስ በወንድማችን ሚናስ የተጻፈ ጽሑፍ በዌብሳይታችን ላይ ተለቋል። ያንብቡት ለሌሎችም ያጋሩ https://ewnetlehulu.net/nt-canon-p-1/
I just saw some of you asking me about the letter 360 of St. Basil, specifically on invocation of saints
That letter, including letters after that 361,362,..of Basil are spurious. They are forgeries. Even the catholics know this and admit it.
Back when I was looking at EO theology, I came across that letter and thought it is a big claim by Basil until I found out it is certainly spurious which someone forged after the 7th ecumenical council. Both internal and external evidences are against Basil's authorship.
