cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

የወንጌሉ እውነት

@Alexsandro1020 Inbox

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
191
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ሰለሞን 700 ሚስቶች እና 300 እቁባቶች ነበሩት። [1ኛ ነገ 11፥3] @goodnewisGospel @goodnewisGospel
Show all...
በ ሰማይ መካከል የምትበሩ ወፎች ተሰብሰቡ ከ እግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከ እየሱስ ክርስቶስ ፀጋና ሰላም ለ እናንተ ይሁን። ወንድሞቼ ሆይ በህብረት ተሰብስቦ ስለመብላት ምን ታስባላቹ?እኔ በ አንድ ትሪ ብዙ ሰው ተሰብስቦ አንድ ማእድ መቋደስ በጣም ደስ ይለኛል ይህ የግል አስተያየቴ ነው።ምክንያቱም በ አንድ ማእድ መብላት ልባዊ ትስስርን ይፈጥራል ብዬ ስለማምን ነው።ከዚህ ባለፈ ደግሞ መፅሀፍ ቅዱሳዊም እውነት ነው ደቀ መዛሙርቱ በ አንድ ልብ ሆነው አንድ ማእድ ይቋደሱ እንደነበር መፅሀፍ ቅዱስ ያስተምረናል።ብዙ ግዜ አብረው ማእድ የሚቋደሱ ሰዎች እርስ በርሳቸው ይዋደዳሉ ምክንያቱም አንድ ሀሳብ ያወራሉ ይጫወታሉ ይስቃሉ መስማማት በመካከላቸው አለ ይህ ጥናታዊ መረጃ ነው።አሁን አሁንማ ቁርጥ የሚባል ዘመናዊነት ልበለው ወይስ በሽታ በእየቤቱ ገብቷል ሁሉም የእየራሱን ይይዛል የራሱን ይበላል ከእራሱ ጋር ያወራል በልቶ ይጨርሳል ወቶ ይሄዳል እኔ በበኩሌ ይሄ ግለብተኝነትን የሚያመጣ ህብረትን የሚያጠፋ ንፉግነትን እና እራስ ወዳድነትን የሚያሰፋ ነው ብዬ አምናለሁ ይህ ግለሰባዊ አስተያየቴ ነው።ይሄ ቁርጥ ከመጣ የብዙ ትውልድ ልብ ተቆራርጦ ለየ ቅሉ ሆኗል በዘመናችንም የምናስተውለው ይህን ነው ብዙዎች በዘር ተከፋፍለው በ ድንበር ተወስነው ይሄ የኔ ለኔ በማለት ገንዘብን በመውደድ በቅናት,በአድመኝነት,ለጥቅማቸው ሲሉ ወንድሞቻቸውን በመጨቆን እና ደምን በማፍሰስ ደም ጠጥተው በደም ሰክረው ዓለምን የእርኩሰት አደባባይ እድርገዋታል በዚህ አመፅ ውስጥም ብዙ የምድር ነገሥታቶችም ተሳትፈዋል የአውሬውም መጠቀሚያ ሆነዋል።“አሕዛብ ሁሉ ከዝሙትዋ ቍጣ ወይን ጠጅ የተነሳ ወድቀዋልና፥ የምድርም ነገሥታት ከእርስዋ ጋር ሴሰኑ የምድርም ነጋዴዎች ከቅምጥልነትዋ ኃይል የተነሳ ባለ ጠጋዎች ሆኑ ብሎ ጮኸ።(ራዕይ 18፥3)ከምንም በላይ ደግሞ እጅግ የሚያሳዝነው ደግሞ ይሄ ባቢሎናዊነት ወደ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሾልኮ መግባቱ ነው ብዙ ክርስቲያኖችም የዚህ አመፅ ተካፋይ ሆነዋል ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይናገራል:-“ከሰማይም ሌላ ድምፅ ሰማሁ እንዲህ ሲል፦ ሕዝቤ ሆይ፥ በኃጢአትዋ እንዳትተባበሩ ከመቅሠፍትዋም እንዳትቀበሉ ከእርስዋ ዘንድ ውጡ።(ራእይ 18፥4) እንግዲህ ከእርሷ ዘንድ ወጥታችሁ ከስጋና ከደም ተለይታቹ አመፅን ጠልታቹ ከፅድቅ ጋር የተባበራቹ የእግዚአብሔር ወገኖች በሰማይ ወደተፃፈ ወደ በጉ በኩራት ማህበር ለደረሳቹ ለእናንተ እግዚአብሔር በመልእክተኛው በኩል እንዲህ ይናገራል:-“አንድም መልአክ በፀሐይ ውስጥ ቆሞ አየሁ፥ በሰማይም መካከል ለሚበሩ ወፎች ሁሉ፦ መጥታችሁ የነገሥታትን ሥጋና የሻለቃዎችን ሥጋ የብርቱዎችንም ሥጋ የፈረሶችንም በእነርሱም የተቀመጡትን ሥጋ የጌታዎችንና የባሪያዎችንም የታናናሾችንና የታላላቆችንም ሁሉ ሥጋ እንድትበሉ ወደ ታላቁ ወደ እግዚአብሔር እራት ተከማቹ ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ(ራእይ 19፥17-18) በሰማይ መካከል የምትበሩ ወፎች ሲል ምድር ያልሳበቻቸው ከአመፃ ጋር ህብረት የሌላቸው ነውር የሌለባቸው በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመሩ በህልውናው የሚራመዱ ድል የነሱ ቅዱሳኖች ለማለት ነው።የታላላቆችን እና የነገስታትን ስጋ ትበሉ ዘንድ ሲል ደግሞ ትፈርዱባቸው ዘንድ ለማለት ፈልጎ ነው።ወደ ታላቁ ወደ እግዚአብሔር እራት ተከማቹ በአንድ አላማና በአንድ ሀሳብ በአንድ መንፈስ አውሬውን እና ወኪሎቹን ትወጉ ዘንድ ተሰለፉ።የጦር አዝማቹ የጭፍሮች አለቃ የሆነው ጌታ እየሱስ ከእናንተ ጋር ነውና ድሉ የእናንተው ነው።ነገር ግን ለዶሮዎች እና ለሰጎኖች ምድር ሲጭሩ ለሚውሉ በሀጢያት ለሚመላለሱ እርኩሱን ነገር ለሚነኩ ወየውላቸው!። ማራናታ ✍ beku @goodnewisGospel @goodnewisGospel
Show all...