cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ክርስቲያናዊ ሕይወት

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። በዚህ ቻናል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶችን መዝሙሮችን እንዲሁም ምክሮችን ያገኙበታል። ክርስቲያናዊ ሕይወትዎን ያዩበታል.......

Show more
Advertising posts
645
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-730 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

[ ስንክሳር ሐምሌ - ፮ - ] .mp32.66 MB
🕊 [ † እንኳን ለሐዋርያው ቅዱስ መርቄሎስ እና ለነቢዩ ቅዱስ ዕዝራ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ] 🕊  †  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!  †  🕊 🕊  † ቅዱስ መርቄሎስ ሐዋርያ †  🕊 † ቅዱሱ በነገድ እሥራኤላዊ የሆነ የመጀመሪያው መቶ ክ/ዘመን ሰው ነው:: ጌታችን በመዋዕለ ስብከቱ ሲያስተምር በምሥጢሩና በተአምራቱ ተማርኮ ተከትሎታል:: ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስም ከሰባ ሁለቱ አርድእት አንዱ ይሆን ዘንድ አድሎታል:: ከጌታችን ሕማማትና ስቅለት በፊትም ድውያንን መፈወስና አጋንንትን ማስወጣት ከቻሉ አርድእትም አንዱ ነው:: ቅዱስ መርቄሎስ በበዓለ ሃምሳ ጸጋ መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ ለወንጌል አገልግሎት ተሰማርቷል:: በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ለሰላሳ አራት ዓመታት በማገልገሉ ሐዋርያት ስሙን "ጳውሎስ" ብለውታል:: ጳውሎስ ማለት ብርሃን ማለት ነውና:: ልክ ሳውል "ጳውሎስ" እንደተባለው ማለት ነው:: ስሙ የግብር [በሥራ የሚገኝ] ስም ነው:: በዚህም ምክንያት ዛሬም ድረስ ቤተ ክርስቲያን የምትጠራው "ጳውሎስ የተባለው መርቄሎስ" እያለች ነው:: ቅዱስ መርቄሎስ በ፷ [60] ዎቹ ዓ/ም አካባቢ ከቅዱስ ጴጥሮስ ጋር በሮም ይሰብክ ነበር:: ኔሮን ቄሳር ሊቀ ሐዋርያትን ዘቅዝቆ ሲሰቅለው የተመለከተና ይህንኑ የጻፈ እርሱ ነበር:: ወታደሮቹ ቅዱስ ጴጥሮስን ገድለውት ሲሔዱ ቅዱስ መርቄሎስ እያነባ ቀርቦ: ችንካሮችንም ነቅሎ: ሊቀ ሐዋርያትን ከተሰቀለበት አወረደው:: በፍጥነት ዋጋው ውድ የሆነ ሽቱ አምጥቶ በቅዱስ ጴጥሮስ ሥጋ ላይ አፈሰሰና በፍቅርና በክብር ሊገንዘው ጀመረ:: በዚህ ጊዜ ሊቀ ሐዋርያት አይኑን ግልጥ አድርጎ መርቄሎስን ተመለከተውና አለው:- "ልጄ! ምነው ለእኔ ይህንን ያሕል ሽቱ አባከንክ?" አለውና ተምልሶ ዐረፈ:: ቅዱስ መርቄሎስም እግዚአብሔርን እያመሰገነ በንጹሕ በፍታ ገንዞ እርሱ በሚያውቀው ቦታ ሠወረው:: ሊቀ ሐዋርያትን በመገነዙ የክብር ክብር ተሰጥቶታል:: ቅዱሱ አሁንም ስብከተ ወንጌልን ቀጠለ:: ከጥቂት ጊዜ በኋላ ግን እርሱም ተይዞ በኔሮን ፊት ቀረበ:: ኔሮን ቄሳር ቅዱስ መርቄሎስን ጠየቀው:: "እንዴት ባለ አሟሟት ልግደልህ? እንደ መምህርሕ ጴጥሮስ ወይስ ሌላ የምትፈልገው ዓይነት አሟሟት አለህ?" ቅዱስ መርቄሎስ መለሰለት:- "የትኛውም ዓይነት ሞት እኔን አያስፈራኝም:: የምፈልገው ወደ ጌታዬ ቶሎ መሔድ ብቻ ነው::" አለው:: ንጉሡ ኔሮንም ዘቅዝቃችሁ ስቀሉት አላቸው:: ወታደሮቹም በዚህች ዕለት እንደ ቅዱስ ጴጥሮስ ዘቅዝቀው ሰቅለው ገድለውታል:: 🕊  †   ቅዱስ ዕዝራ ነቢይ  †   🕊 ከክርስቶስ ልደት በፊት በ፭መቶ [500] ዓመት አካባቢ የነበረ ¤ እሥራኤል ከምርኮ ከተመለሱ በኋላ መጻሕፍት ተቃጥለው ጠፍተው ነበርና ስለ እነሱ አብዝቶ የለመነ ¤ ጥበብን ሽቷልና እግዚአብሔር ቅዱስ ዑራኤልን የላከለት ¤ በሊቀ መላእክት እጅም ጽዋዐ ልቡናን የጠጣ ¤ ብዙ ምሥጢራት የተገለጡለት ¤ ለአርባ ቀናት ምግብ ሳይበላ አገልጋዮቹ የጠፉ መጻሕፍትን እየነገራቸው የጻፉለት ¤ መጽሐፈ ዕዝራ የተሰኘ መጽሐፍን ያዘጋጀና ¤ በብሉይ ኪዳን ከነበሩ ዐበይት ነቢያተ ጽድቅ አንዱ የሆነ ታላቅ የእግዚአብሔር ሰው ነው:: † ስለ ቅድስናውም ሞትን አልቀመሰም:: በዚህች ዕለት ቅዱሳን መላእክት ብሔረ ሕያዋን ውስጥ አስገብተውታል:: † እግዚአብሔር ከሐዋርያውና ከነቢዩ በረከትን አይንሳን:: [  † ሐምሌ ፮ [ 6 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት  ] ፩. ቅዱስ መርቄሎስ ሐዋርያ [ከሰባ ሁለቱ አርድእት] ፪. ቅዱስ ዕዝራ ነቢይ ፫. ቅዱስ በርተሎሜዎስ ሐዋርያ ፬. ቅድስት ቴዎዳስያ ሰማዕት ፭. ቅድስት ንስተሮኒን ዘኢየሩሳሌም [  †  ወርኀዊ በዓላት  ] ፩. ቅድስት ደብረ ቁስቋም ፪. አባታችን አዳምና እናታችን ሔዋን ፫. አባታችን ኖኅና እናታችን ሐይከል ፬. ቅዱስ ኤልያስ ነቢይ ፭. ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ ፮. ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ ፯. ቅድስት ሰሎሜ ፰. አባ አርከ ሥሉስ ፱. አባ ጽጌ ድንግል ፲. ቅድስት አርሴማ ድንግል † " እግዚአብሔርም በቤተ ክርስቲያን አንዳንዶቹን አስቀድሞ ሐዋርያትን: ሁለተኛም ነቢያትን: ሦስተኛም አስተማሪዎችን: ቀጥሎም ተአምራት ማድረግን: ቀጥሎም የመፈወስን ስጦታ: እርዳታንም: አገዛዝንም: የልዩ ልዩ ዓይነት ልሳኖችንም አድርጓል:: ሁሉ ሐዋርያት ናቸውን? ሁሉስ ነቢያት ናቸውን? ሁሉስ አስተማሪዎች ናቸውን? . . . ነገር ግን የሚበልጠውን የጸጋ ስጦታ በብርቱ ፈልጉ:: " † [፩ቆሮ. ፲፪፥፳፰] † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖
Show all...
[ ራስን የመመርመር ሕይወት ] .mp36.50 MB
Photo unavailableShow in Telegram
💛 ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬ 🕊     ም ክ ረ     ቅ ዱ ሳ ን     🕊 ▷  " የጸጸትና ራስን የመመርመር ሕይወት ! " [    " ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ "    ] [                        🕊                        ] ----------------------------------------------- ❝ ኃጢአቴን ለአንተ አስታወቅሁ ፥ በደሌንም አልሸፈንሁም ፤ ለእግዚአብሔር መተላለፌን እነግራለሁ አልሁ ፤ አንተም የልቤን ኃጢአት ተውህልኝ። .... አንተ ለእኔ መሸሸጊያዬ ነህ ፥ ከጣርም ትጠብቀኛለህ ፤ ከከበቡኝ ታድነኝ ዘንድ ደስታዬ ነህ። ❞ [  መዝ . ፴፪ ፥ ፭  ] 🕊                        💖                     🕊                              👇
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
                         †                           [      🕊  ፍኖተ ቅዱሳን   🕊      ] [ የቅዱሳን አባቶቻችን የቅድስናና የተጋድሎ ሕይወት ] ▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬ [  ተርእዮን [ መታየትን ] አለመውደድና ለታይታ ብሎ ምንም ነገር አለማድረግ !  ] 🕊 "  ከዚያ አታላይ ምን ትፈልጊያለሽ ? .... !  " ........ በጡቷ ካንሰር የነበረባት አንዲት ሴት ስለ አባ ሎንጊኖስ ሰማችና ልታገኘው ሄደች፡፡ የሚኖረው ከእስክንድርያ ወጣ ብሎ ነበርና ሴትዮዋ ስለ እርሱ እየጠየቀች ወደ እርሱ ስትሄድ በባሕሩ ዳርቻ እንጨት እየለቃቀመ አገኘችውና እርሱ መሆኑን ስላላወቀች ፦ "አባ፣ የእግዚአብሔር አገልጋይ ሎንጊኖስ የሚኖረው የት ነው?" አለችው:: እርሱም ፦ "ከዚያ አታላይ ምን ትፈልጊያለሽ? ወደ እርሱ አትሂጂ ፣ እርሱ አታላይ ነውና። ግን ጉዳይሽ ምንድን ነው?" አላት፡፡ ሴትዮዋም ስለ ሕመሟ ነገረችው:: እርሱም በታመመው ሰውነቷ ላይ የመስቀል ምልክት አደረገና ፦ "ሂጂ፣ የሚፈውስሽ እግዚአብሔር ነው፣ ሎንጊኖስ ምንም የሚጠቅምሽ ነገር የለምና" አላት፡፡ እርሷም አምና ተመለሰች፣ በአንዴ ወዲያውኑ ከሕመሟ ተፈወሰች፡፡ ከዚያ በኋላ ይህን ነገር ለሰዎች አወራች፡፡ የሰውዬውን ሁኔታ ገለጸችላቸው፣ እነርሱም እርሱ ራሱ አባ ሎንጊኖስ እንደ ሆነ ነገሯት፡፡" የአባቶቻችን ጸሎትና በረከት ይደርብን፡፡ †                       †                         † 💖                    🕊                     💖
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
                         †                          [  የክብር ኮከብ ፤ የገዳም መብራት  ] 🕊 የማይሰለች ተጋዳይ ፤ የክብር ኮከብ ፤ የገዳም መብራት ስም አጠራሩ እርግናው የተመሰገነ ፤ ብፁዕ ቅዱስ ደግ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ወርሐዊ በዓላቸው ነው። †     🕊   እንኳን  አደረሰን    🕊    † እግዚአብሔር አምላክ ስለ እውነተኛ ወዳጁ ስለ አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስ ብሎ ይማረን፡፡ 🕊                        💖                       🕊
Show all...
Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.