en
Feedback
ኑ ራሳችንን በስብዕና እናሳድግ!

ኑ ራሳችንን በስብዕና እናሳድግ!

Open in Telegram

ራስዎን የሚቀይሩበት ትምህርቶችን ከዚህ ያገኛሉ!

Show more
1 535
Subscribers
No data24 hours
-77 days
-730 days
Posts Archive
አእምሮና የተተኮሰ ጥይት ማረፊያ ካላገኙ ገዳይ ይሆናሉ ።     ፈጣሪን እያየህ ሥራህን ፈጽም እንጂ ይህን እባላለሁ ብለህ አትስጋ ። ስትሮጥ እግርህን ብታይ ትወድቃለህ ፣ ተመልካቾችን ብታይም ትወድቃለህ ፤ ግብህን ስታይ ግን ታሸንፋለህ ። የተለመዱ ነገሮችን መከወን አያጣላም ። አንዳንድ መፍትሔዎች ግን ያልተለመዱ ናቸው ። ያልተለመዱ ነገሮችን መጀመር ሁሉ ሰው ይፈራል ፤ ከተጀመረ ግን ሁሉ ይከተላል ። ሰው ምን ይላል? ሳይሆን እውነት ምን ትላለች ? ብለህ ሥራህን ቀጥል ። በኳስ ሜዳ በጣት የሚቆጠሩ ተጫዋቾች አሉ ፣ ተመልካቹ ግን በመቶ ሺህ የሚቆጠር ነው ። በሕይወትም ሃያ ሁለት ሰው ይጫወታል ፣ ሚሊየኖች ያያሉ ። ሕይወት ግን መዝናኛ አይደለችምና ሃያ ሁለት ተመልካችም ሊኖርባት አይገባም ። አገር የተሰጠን በጋራ እንድንለውጠው እንጂ አንድና ሁለት ሰው እንዲለውጠው አይደለም ። “የአንድ አሳቢ ፣ የአንድ በሬ ሳቢ” የለውም ፤ ደግሞም የትም አይደርስም ። ሥራህን ሌሎች ይናገሩት እንጂ በአንተ አፍ አይደነቅ ። የሥራህን ዋጋ የምትጥለው አንተ ስታወራው ነው ። ለእርካታ የሠራኸው ከሆነ አታወራውም ፤ ረክተሃልና ። የጠጣኸውን ውኃ እንደማታወራው መልካምነትም ለራስ የሚሠራ እንደሆነ እወቅ ። የሚናገር ሥራ ያልሠራ ሰው አፉ ይናገራል ። ሥራ ከቃል በላይ የመናገር አቅም አለው ። ሰማይ ዝምተኛ ነው ፣ ነገር ግን ስፉሕ ስለሆነው ፈጣሪ ባለ መድከም የሚናገር ነው ። ተፈጥሮ የጸጥታ ትምህርት ቤት ነው ። ድምፅ አልባ መምህራን ተፈጥሮ መሆናቸውን እወቅ ። ተፈጥሮ እንኳ ዝም ብሎ አንተ ሠራሁ ብለህ አትለፍልፍ ። ስለ ሥራህ የምታወራ ከሆነ ወደፊት የምትሠራው የለም ማለት ነው ። እግሩ የቆመ አፉ ይራመዳልና ። በመንገድህ ሁሉ ሰዎች ሳይሆኑ ፈጣሪ ካንተ ጋር መሆኑን ጠንቅቀህ መርምር ። ብቸኝነት ማለትም ከሰው ሳይሆን ከፈጣሪ መራቅ ነው ። መልካም አሳብ ለኅሊና ምቹ ዕረፍትን ይሰጣል ። ቆመው የማይጠብቁ ሁለት ነገሮች አሉ ፡- ጊዜና ዕድል ። ጊዜና ዕድል ሲገጥምህ ቶሎ ተጠቀመው ። ብዙ ሰው የሚቆጨው ጊዜና ዕድልን ሸኝቶ ነው ። በነጻ የመጣ ነገር ከሄደ በኋላ በዋጋም አይመለስም ። ከመንገድ ምልክቶች አንዱ “ቁም” የሚል ነው።መቆምም የመጓዝ አንዱ ክፍል ነው ። ቆም ብለህ ሥራህን ገምግም ። አባት ሳለ መማር ፣ እናት ሳለች መሥራት ፣ ንጉሥ ሳለ መሮጥ ተገቢ ነው ። መኪና በፍሬን ካልቆመ ነዳጅ ጨርሶ ወይም ተጋጭቶ ይቆማል ። ሁሉም መቆም ቢሆንም እንደገና የሚጓዘው በፍሬን ሲቆም ነው ። አንተም ለቃልህና ለምኞትህ ፍሬን ይኑርህ ። በመንገድ ሁሉ አይኬድም ፣ በሚያደርሰው መንገድ እንጂ ። ያየኸው ሁሉ አይመርህ ። ሁሉም ያንተ እንዲሆን አትፈልግ ። ሁሉንም ታጣለህና ። መቀበሪያ እንኳ ያጡ ነገሥታት ሁሉ የእኔ ይሁን ያሉ ናቸው ። የከበረ ቀብር የምታገኘው ያነሰ ምኞት ሲኖርህ ነው ። ስግብግብ ሰው በሥጋው ጨርሶ በነፍሱ ሲወቀስ ይኖራል ። የሹም ሌባ ያጸይፋል ። ሁሉም የእርሱ ሳለ የራሱን የሚሰርቅ ነውና ። በዝምታ የዋልህበት ቀን ኃይልህ ያልባከነበት ቀን ነው ። የፈጣሪን ቃል የተናገርህበት ቀን ደግሞ ኃይልህ የሚታደስበት ቀን ነው ። ከመከራ ይልቅ ዕድልን ታገሠው ። ከቀን በኋላ ሌሊት እንደሚመጣ ከዕድል በኋላም ችግር ይመጣል ። ዕድል ማለት ፈጣሪ የሰጠህ ጊዜ ማለት ነው ። ፈጣሪ በሚበልጠው ሊሾምህ በሚያንሰው ይፈትንሃል ። ከእጅ ሌባ የአፍ ሌባ ይከፋልና አንደበትህን ተቆጣጠር ። ሰዎች አታከቱኝ ባልህበት ቀን ምናልባት ሰዎችን አታክተህ ይሆናልና ራስህን ተመልከት ። ክፉ ስትሆን የሰዎች ክፋት ይታይሃል ፣ ወደ ጽድቅ ስትቀርብ ስለ ሰዎች ኃጢአት ማልቀስ ትጀምራለህ ። ይገባሃል ተብሎ የተሰጠህን አይገባኝም ብለህ በትሕትና ያዘው ። የመንፈሳዊነት ግለት ያለው በዝማሬና በእንባ ነውና ሁለቱን እንዲሰጥህ ለምነው ። እንባ ለሠራኸው ኃጢአትና ላልሠራኸው ጽድቅ ነው ፤ ዝማሬም መልካም ላደረገልህ ፈጣሪ ነው ።ሥራ ፈት ስትሆን ለሰይጣን ትልቁን የጊቢ በር እንደ ከፈትህለት እወቅ ። ሥራ ከምትፈታ ንጹሕ ልብስህን እንደገና እጠብ ። አእምሮና የተተኮሰ ጥይት ማረፊያ ካላገኙ ገዳይ ይሆናሉ ። ፈጣሪ የረዳውን ሰው አንተ እጥለዋለሁ ብለህ አትነሣ ። የምትታገለው ከማትችለው ጋር ነውና ። መጽናናት ቋሚ የሚሆነው በመጽናት ነው ። መጽናናትን ከመለመን ጽናትን መለመን መልካም ነው ። ያለ ምክንያት የወደደህን ፈጣሪ እያሰብህ ያለ ምክንያት የሚጠሉህን ሰዎች ልትረሳ ይገባሃል ። ምክንያት የሚጥመው ለራሱ ለምክንያት ብቻ ነው ። ውሸት ከመሆን የማያመልጡ ሁለት ነገሮች አሉ ይባላል ፡- የማይፈጽሙትን ተስፋ መስጠትና ምክንያተኝነት ናቸው ። የቆምከው በፈጣሪ ረዳትነት ነውና አመስግነው ። ስለ ነገ ከመጸለይ ስለ ትላንት አመስግን ። ዮርዳኖስ እንዳያስፈራህ ቀይ ባሕርን እንደ ተሻገርህ አስብ ። ረጃጅሞች እንዳያስደነግጡህ ፈርዖንና ሠራዊቱን እንዳለፍህ አስተውል ። በምንም መንገድ ከትላንት የባሰ ቀን አይመጣምና አትደንግጥ ። በዓለም ላይ ከሌለህ አትኖርም ፤ ከሌለህ የምትኖረው ከፈጣሪ ጋ ብቻ ነው ። ደግሞም ፈጣሪን ያተረፈ የሚያተርፈው ነገር ወደፊት የለም ። የማይካስ ድህነት በጎ ኅሊናን መክሰር ነው ። ከጠማሞች ጋር እየዋልህ በጎ ኅሊናህን እንዳትሰረቅ ተጠንቀቅ ። ኪስህን እንጂ ኅሊናህን መጠበቅ ለምን አቆምህ ? አባቶች አልቀዋል ብለህ ስትናገር አንተ ራስህ ልጅ ነኝ ወይ ? ብለህ መጠየቅ ይገባሃል ። ልጅ በሌለበት አባት ይታጣልና ። የተደበላለቁ አሳቦች ሲመጡብህ ጊዜ ሰጥተህ አስብ እንጂ አትከውናቸው ። ከቤትህ ለመውጣትህ እንጂ ለመመለስህ እርግጠኛ አይደለህምና መንገድህን ለፈጣሪ አደራ ስጥ ። ዕድልህ ያለው በፈጣሪ እጅ ነውና የሰው ድምፅ አጣሁ ብለህ አትጨነቅ ። ሰዎች እንዲወዱህ ሳይሆን እንድትወዳቸው ፈልግ ። ነገ ግን በበፈጣሪ የሥልጣን እጅ ናትና ስለ ነገ በሰው ተስፋ አታድርግ ። ነገ ያደርግልኛል የምትለው ነገ ለማኝ ሊሆን ይችላል ። ሰው ሁሉ ነገን ቢያውቀው ዛሬን አይታበይም ደግሞም አይሸማቀቅም ነበር ። የበለጠ ምሥጢር እንዲገለጥልህ የተገለጠልህን ምሥጢር አክብረው ። የሰው ምሥጢር የማይነገር ነው ፤ የፈጣሪ ምሥጢር ግን የሚነገር ነው ። የሰው ምሥጢር የሚያስጨንቅ ነው ፤ የፈጣሪ ምሥጢር ግን የሚያስደንቅ ነው ። ሰው የሚከብረው ሲሸፈን ነው ፣ ፈጣሪ የሚከብረው ሲገለጥ ነው። ከተዋረዱ ሰዎች የሚመጣ ክብር ጊዜያዊ ነው ፤ ደግሞም የውርደት ያህል ነው ። ባለጌ የሚያከብርህ ለዛሬ የሚያዋርደው ሰው ስላለው ነው ። የሚሰድበው ያጣ ቀን ይሰድብሃል ። ትሑት ሰው በደረሰበት መከራ ሳይሆን በሰዎች ላይ በደረሰ መከራ እንደ ራሱ አድርጎ ያዝናል ። በሩቅ የሚያዩት ዓለም የቅርብ ጎረቤት ይሆናልና ። የመሰለህን ነገር አትመነው ። ግምትህ ኑሮህን እንዳይፈታው ተጠንቀቅ ። ግምት ከእውነት ይልቅ ለሐሰት ቅርብ ነውና ። መሳሳትን አትፍራ ። የጠራ ሥራም የብዙ ሙከራ ውጤት ነው ። የመሞከር ዕድል የማይሰጥ ፣ ፍጹማዊ አስተሳሰብን የሚያራምድ ማኅበረሰብ የማያድግና የእውቀት ልምሾ ያለበት ነው ። ሰው ሆነው በሰው የሚደነቁ ፤ ውዳቂ ሁነው በውዳቂዎች የሚስቁ ያልተማሩ ሕዝቦች ናቸው ። ዛሬ ድል ባገኘህበት መንገድ ነገም አገኛለሁ አትበል ። ድል ስጦታ እንጂ ሁኔታ አይደለምና ።

ለአንዳንድ ሰዎች የውሃ ጠብታ ሰጥተሃቸው አብዝተው ያመሰግኑሃል።አንዳንዶች ደግሞ መላውን ውቅያኖስ ሰጥተሃቸው እንደቀላል ይወስዱታል።እናም ጨርሰው እንዳያደርቁህ ከነዚህ ሰዎች ራቅ!

ወርቅና ጨዋ አስታራቂ ነው! ድሀ ፊደሉም ሁለት ነው፣ ሀብታም ግን ፊደሉም አራት ነው። አፍ ተከፍቶ የሚነገሩ ቃላት፣ አፍ እየከደኑ የሚነገሩ ቃላት አሉ። ድሀ የሚለውን ቃል ለመናገር አፍ ይከፈታል፣ ሀብታም ብለው ሲናገሩ ከንፈር ይዘጋል። በድሀ ላይ የማይላቀቅ አፍ ፣ ለሀብታም ዝም የማይል ከንፈር የለም። ድሀ ጥበብ ቢናገርም የሚሰማው የለም። ጥበብ ከድሀ ነበርሽ ፣ ማን ቢሰማሸ! ይባላል። ባለጠጋ ወዝም ጣዕምም የሌለው ነገር ቢናገር እንደ ጥቅስ ይወራል፣ በማስታወሻ ይያዝለታል ። የሰው ልጅ ምንም ይዞ ያልመጣ ምንም ይዞ የማይሄድ ነው። ነገር ግን ይኮራል፣ ድሀ ብሎ ለመሳደብ ይቸኩላል፣ ሀብታም ብሎ እጅ ለመንሣት ይሯሯጣል። ድሀ በትክክል የሚጠላውን ያውቃል፣ ሀብታም ግን ወዳጅና ጠላቱን ማወቅ አይችልም። ባለጠጎች ቁምነገርን ከድሀ ፣ ድሆችም በረከትን ከሀብታም እንዲካፈሉ ተወስኗል። ድሀ ነገሩ መራራ ነው። ባለጠጋው ታሞ ድሀው ተመላልሶ ቢጠይቅም ማንም ልብ አይለውም። ድሀው ግን ታሞ የሚጠይቀው አጥቶ፣ የተሻለው ቀን ባለጠጋው ቤት ሄደ የጠፋኹት ታምሜ ነው ብሎ ሪፖርት ያደርጋል። ስላልጠየቁት የመቀየም መብት የለውም። ተሽሎት የጠፋበትን ምክንያት ለማሳወቅ ይተጋል። ድሀ ይሉኝታ ኣለው። ሥርዓት የሌለው ባለጠጋ እንዳለ ሁሉ የጠባይ ምስኪን የሆነ ድሀም አለ። ገንዘብ አመል ይዞ ይመጣልና የድሀ ልጅ ያገኘና የተሾመ ቀን ምድር ትጨነቃለች። ድሀ ወርቅ አይግዛ ከገዛም አያብዛ ይላሉ። የድሀ ልጅ ወርቅ አይለምድም ይባላል። የሞል በሽታ የሚይዘው የድሀ ልጅን ነው። ድህነቱ ሄዶለት እንኳ ተመልሶ ቢመጣስ እያለ የሚባንን፣ የሚያግበሰብስ ብዙ ነው። የገንዘብ እንጂ የዕድሜ ድሀ ባትሆንም ሁሉ ይልክሃል። ነገርህ መራራ ይሆናል። ስትስቅ አስመሳይ፣ ስታለቅስ ብሶተኛ ይሉሃል። ስታጣ ለምን ድሀ ሆነ ? ብለው ጥናት ያላደረጉ አሁን ስታገኝ የገንዘብ ምንጩ ይጠና ይሉሃል። ድሀ ስትሆን ሃይማኖተኞች ተጠራጣሪ ብለው ያወግዙሃል፣ ታጣቂዎች ይገርፉሃል። አንቱ ተብለህ ሳትጠራ ታረጃለህ። ያገኘህ ቀን ለሁሉ ቆንጆ ሆነህ ትታያለህ። ስህተት ብትናገር ንግግርህን በወጌሻ የሚያስተካክልልህ አፈ ቀላጤ ታገኛለህ። ታሪክ ባይኖርህም ዜና መዋዕልህን ልጻፍ የሚል ደራሲ ይንጋጋልሃል። የሚያወግዝህ የለም፣ እንዳንተ ያለ ቆንጆ እንደሌለ ምለው ይነግሩሃል። ለምን መሰለህ ? ወርቅና ጨዋ አስታራቂ ነው! አንተን ክፉ ማለት ብዙዎች ይከብዳቸዋል። ስህተትህን በአጉሊ መነጽር እንዳላዩ ዛሬ በካባ ይሸፍኑታል። ባልዋ የበደላት፣ ወደ ሌላ ሴት ሄዶ ያሳዘናት ሚስት ወርቅ ይካሳት ተብሎ ትታረቃለች። ጨዋም አስታራቂ ነው። ተው ባይ፣ ገላጋይ፣ እሳት አጥፊ ፣ ድልድይ ሠሪ ነው። አግድም አደግ ነገር ያባብሳል፣ በሌሎች ሁከት ይደሰታል። "የእብድ ገላጋይ ድንጋይ አቀባይ" እንዲሉ። ሁሉ የሚረባረብብህ ድሀ ስትሆን ነው፣ ነገሩ አይጥመኝም የሚሉህ ያለ ጉርሻ የማይስቁት ናቸው። የአሜሪካ ፕሬዝዳንትና የዩክሬን ፕሬዝዳንት በፖፕ ፍራንሲስ ቀብር ላይ አመርቂ ውይይት አደረጉ ተባለ። ወዲያው በውድ ማዕድናት ዙሪያ ዩክሬን ፈረመች። የሞቱት ፖፕ ግን በድህነት እንደኖሩ ድሆች በሚቀበሩበት ሳንታ ማሪያ ቤተ ክርስቲያን እንደ ተቀበሩ ፣ ምንም የግል ሀብት የሌላቸው መቶ ዶላር ብቻ የተገኘባቸው እንደሆኑ ተነግሯል። እግዚአብሔር ግን ያለ ወርቅ ይታረቅሃል !

ጉዳይ ኖሮህ ለማሳካት አቅሙ ከሌለህ: አቅም ኖሮት ጉዳይ የሌለው ጌታ አለህና ፊትህን ወደርሱ አዙር!

🐦 የህይወት ዘመን ምክር 🐦 #ስለ ሰዎች_👧_🧒_ክፍል #1 ✅ በህይወት ውስጥ ትልቁ ፈተና የልብህን እውነት ሰዎች እንዲረዱህ ማድረግ ነው። ቤተሰብ፣ ወዳጅ የልቤ የምትለው ጓደኛ ላይረዳህ ሁሉ ይችላል፤ የሚሻለው መተው ነው። ✅ እነሱ እንዲረዱህ የምታባክነውን ጉልበትና ልፋት ራስህን ለማሳደግ ብታውለው ብዙ ርቀት ትጓዛለህ። በህይወትህ ላይ ልዩነት የምትፈጥረው ራስህ ላይ ስትሰራ ብቻ ነው! 👨‍🦱 ሰዎች ሲጠሉህ ጠባይህ ከፍቷል ወይም ጠባያቸው ከፍቷል ማለት ነው ፡፡ ራስህን ስለማሻሻል እንጂ ሰዎችን ለመለወጥ ሥልጣን ያንተ አይደለም ፡፡ 👦 ከመጸለይ ወጥተህ በምክሬ ሰውን እለውጣለሁ ብለህ አትታገል ፡፡ እንኳን ያንተ ምክር የፈጣሪም ቃልም ያለ እርሱ ረዳትነት አይፈጸምም ፡፡ 👦 በሌሎች ላይ እጅህን አትጠቁም ፣ እኔ እያልህ ግን ንስሐ ግባ ፡፡ ቂም መሸነፍ ነው ፡፡ የተወረወረው ጦር ነፍስህን ሲያጠቁራት እርሱ ቂም ይባላል ፡፡ 👦 ዋጋህን በሰው እይታ ውስጥ ሳይሆን በህሊናህ ውስጥ ፈልገው፣ያለ ምክኒያት የሚወድህን አምላክ❤️ እያሰብክ ያለ ምክኒያት የሚጠሉህን ሰዎች እርሳቸው😍 👦 ህይወት ውስጥ "ማለፍ" የሚባል ክህሎት ያለ ይመስለኛል ። ስንኖር በማለፍ ውስጥ ካላለፍን የህይወት ቀጣይነትና ምንነት ላይገባን ይችላል ። ፍርሃትህን ማለፍ ፣ ሽንፈትህን ማለፍና አንዳንድ ሰዎችንም ማለፍ ያስፈልጋል ። በማለፍ ውስጥ እለፍና የሚታለፉ ነገሮችን እለፋቸው ። የሚያስጨንቁህ ነገሮችም ይሁን ነገሮች አላፊ ስለሆኑ ስታልፋቸው ታርፋለህ ። ✅ አወንታዊ አስተሳሰብ ያለህ ሰው ነህ ማለት አትናደድም፣ አታዝንም፣ አትቆጣም ወይም አትሰላችም ማለት አይደለም እንዲህ ብሎ ማሰብ ኃኪም አይታመምም ብሎ እንደማሰብ ነውና አትፍረዱብኝ፡፡ ✅ሰዎች ስላወቁህ እንዲፀፀቱ አታድርጋቸው ነገር ግን ሰዎች ስላጡህ እንዲፀፀቱ አድርጋቸው ✅ ሰው ላይሆኑህ ሰው ያሳጡህንም አትርሳ ፡፡ እናስታውስ አለመርሳት ማለትም ለቀጣዩ ተጠንቀቅ ማለት ነው ፡፡ ✳️ብቸኝነትህን ያመጣው ብቻህን መሆንህ አይደለም፡፡ አብሮህ ያለውን አለማወቅህ እንጂ፡፡ ✳️አካባቢህን ካላወቅህ በሰዎች መካከል ሆነህ እንኳን ብቻህን ትሆናለህ፡፡ አካባቢህን ካወቅከው ግን መቼም ብቻህን አትሆንም፡፡ ✅ሰው የተፈጥሮ ሚዛኑን የሚጠብቀው ከበታችነትም ከበላይነትም ስሜት ነፃ መሆን ሲችል ነው። ሁለቱም ስሜቶች መርዝ ናቸው። ✅ ንፁህ ልቦች በደል ሲደርስባቸው ለመበቀል ያስቡና እድሉን ሲያገኙ ግን ህሊናቸው ይቅርታን ታስቀድማለች . . .ንፁህ ልብ ይስጠን ፣ይቅር ባዮች ያድርገን!" ✅ሁሉንም ሰዉ ልታስደስት አትችልም፡፡ ይህ ትልቅ እዉነታ ነዉ፡፡ የሆኑ ሰዎች ቢጠሉህ ምንም ማለት አይደለም፡የሚወዱህ እንዳሉ ሁሉ የሚጠሉህም እንደዚያዉ፡፡ ሰዎች ስላንተ ያላቸዉ አመለካከት ያንተ ጉዳይ አይደለም፡፡ ✅ የመሰላቸዉን ያህል ሊገምቱ፣ዋጋ ሊያወጡ ሊያወርዱ፣ወይም ሊሰቅሉ ይችላሉ፡፡ ሰዎች አንተ ላይ ባላቸዉ አመለካከት ማንነትህን ሞቅና ቀዝቀዝ እያደረክ አትኑር... ✅ ራስህን ሆነህ በሕይወትህ ትልቅ ዋጋ ለምትሰጣቸዉ ሰዎች ብቻ የሚጠበቅብህን መስዋእትነት ክፈል፡፡ ቢሆንም የተቸገሩትን መርዳት አትርሳ። ✅ ብቸኝነትህን ያመጣው ብቻህን መሆንህ አይደለም፡፡ አብሮህ ያለውን አለማወቅህ እንጂ፡፡ ✅ አካባቢህን ካላወቅህ በሰዎች መካከል ሆነህ እንኳን ብቻህን ትሆናለህ፡፡ አካባቢህን ካወቅከው ግን መቼም ብቻህን አትሆንም፡፡ ➡️ ከሰው ጋር ስትኖር ሁሉም ነገር እንዳሰብከው አይጓዝም ውለታህ እንደ ጉዳት ፣ ፍቅርህ እንደ ጥላቻ ፣ ቸርነትህ እንደ ስግብግብነት ፣ አዛኝነትህ እንደ ጭካኔ ብቻ ብዙ ነገርህን ስትሰጥ ምን አድርገህ ተብለህ ባንዴ ዋጋ ታጣለህ በሌላም ትቀየራለህ ። ይባስ ብሎ ያደረከው መልካም ነገር ሁሉ መጥፎ ነው ትባላለህ ። ይሄኔ ከራስህ ውጭ ማንንም አትፈልግም !! ስለስራህም አፍህ ተናግሮ ማስረዳቱ ድካም ይሆንብህና ዝም ትላለህ !! #ደግሞ #አንድ ነገር #ልንገርህ ምንም ይሁን ምን ከሰው ጋር ስትኖር ያልተመቸህ ነገር ካለ አለመስማማትህን ግለፅ (No) ማለት መቻል ትልቅነት ነው ፡፡#No ማለት ካልቻልክ በተዘዋዋሪ የነሱ ባሪያ መሆንህን አምነህ ተቀበል ወይም ዕራቅ 😍ሰዎችን መጥቀም ስትፈልግ እውነቱን ትነግራቸዋለህ ራስህን መጥቀም ስትፈልግ ግን መስማት የሚፈልጉትን ትነግራቸዋለህ። ⏸ አንዳንድ ሰዎች ሌላ ሰው ስላላገኙ ካንተጋ ይሆናሉ፣አንዳንድ ሰዎች ደግሞ ሌላ ሰው እስኪያገኙ ድረስ ካንተጋ ይሆናሉ፣አንዳንድ ሰዎች ግን ካንተ የተሻለ ሌላ ማንንም ስለማይፈልጉ ብቻ ካንተጋ ይሆናሉ ➡️ መሳሳት የጀመርከው በሰው መደገፍህን እንደ ጥሩ ፀባይ መቁጠር የጀመርክ ጊዜ ነው።ከተደገፍክ ወይ ከተመካህ በፈጣሪህ ተመካ! በተረፈ ግን ውስጥህ ባለው ሀያል መንፈስና አቅም የዚህን አለም ውጣ ውረድ ሁሉ እንደምታልፈው እወቅ...ከዛ እመን! ⭕️ ሰው ትላንቱን ማሰቡ ዛሬ ሌሎችን እንዳይበድል ሊያደርገው ይችላል ። ደግሞም “የመጣህበትን አትርሳ ፣ የምትሄድበት እንዳይጠፋህ” ይባላል ። 🔒 ደግሞም “ያለህበትን ለማወቅ የመጣህበትን አትርሳ” ይላሉ በሌላ አገላለጽም፡- “ዓይንህ የፊቱን ቢያይ ልብህ የኋላውን ያስብ” ይባላል

💥የትምህርቱ ርዕስ | ይሉኝታ💥 የሰው ልጅ በኑሮው ውስጥ ሦስት ተመልካቾች አሉት ። የመጀመሪያ እግዚአብሔር ፣ ሁለተኛ የገዛ ሕሊናው ፣ ሦስተኛ ሰዎች ናቸው ። ይሉኝታ ሰዎች ምን ይሉኝ ( የሚል ፍርሃት ፣ ራስ ጠይቆ ራስ የግምት መልስ መስጠት ፣ ሰዎችን ከልክ በላይ ማክበር ፣ የሚመሩበት መርሕ አለመኖር ፣ ኗሪ ሳይሆን አኗኗሪ መሆን ነው ። ለእግዚአብሔርና ለሕሊናቸው የማይጨነቁ ወገኖች ፣ ለሰዎች ያውም ለሐሜታቸው ይጨነቃሉ ። በደለ ይለኛል ብለው ሲፈሩ እነዚያ ሰዎች በሐሜታቸው እየበደሉ መሆናቸውን ይረሳሉ ። አንዳንዴ ኀጥእና ኀጥእ ሲገፋፉ ይሉኝታ ይፈጠራል ። “ቀጥ ቀጥ ያለ ሲታጣ ይመለመላል ጎባጣ” እንዲሉ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው ሲታጣ ይሉኝታ ያለውም ሰው ያምረናል ። ይሉኝታ ውስጣዊ ስሜት ሲሆን ሰውን በማይታይ ገመድ ይዞ የሚኖር ነው ። ለይሉኝታ ብለው ክፋትን የማያደርጉ ሰዎች ልባቸውም ንጹሕ ነው ማለት አይደለም ። አገር ለቀው ፣ በማያውቁአቸው ሕዝብ መካከል ኃጢአት ሠርተው የሚመጡ ሰዎች እግዚአብሔርን ሳይሆን ሰዎችን የሚፈሩ ናቸው ። ይሉኝታ እንድንሰደድ ፣ ብዙ ገንዘብ እንድናወጣ የሚያደርግ ይልቁንም የእኛን ሰው ያደከመ ትልቅ ሸክም ነው ። እውነተኛ ቅድስና በሕሊና ስምምነት ፣ በፈሪሀ እግዚአብሔር የሚፈጸም ነው ። በኦሪት ሁለት መርሖችን እናገኛለን ። የመጀመሪያው የሊቀ ካህኑ አዋጅ ነው ። በሊቀ ካህኑ ግንባር ላይ ሁሉም ሰው የሚያነበው ጽሑፍ ይታያል ። “ከጥሩ ወርቅም ቅጠል የሚመስል ምልክት ሥራ ፥ በእርሱም እንደ ማኅተም ቅርጽ አድርገህ፡- ቅድስና ለእግዚአብሔር የሚል ትቀርጽበታለህ” ይላል (ዘጸ. 28 ፡ 36)። ቅድስና ለእግዚአብሔር ነው ። ቅድስና የሰዎችን ከበሬታና ማስተዛዘኛ ማግኛ ወይም መነገጃ አይደለም ። ቅድስና ለእግዚአብሔር ነው ። እግዚአብሔርን እያዩ መራመድ ፣ የእግዚአብሔርን ዋጋ ከፋይነት ብቻ ማሰብ ፣ ለሕሊና የሚስማማ ግብር ነው ብሎ መቀበል እርሱ ቅድስና ይባላል ። እገሌ ተሐራሚ ነው ፣ ጸሎተኛ ነው ፣ በጥሬ ነው የሚጾመው ለመባል ሳይሆን እግዚአብሔር ብቻ የሚያየውን ሕይወት መኖር እርሱ እውነተኛ ቅድስና ነው ። ይሉኝታ ቅዱስ እንዲሉን ተውኔታዊ ጨዋነት ማሳየት ነው ። ክፉ መሆንን ሳይጠሉ ፣ ክፉ መባልን መጥላት እርሱ ይሉኝታ ይባላል ። ሁለተኛው የኦሪት ምክር፡- “ሰውን መፍራት ወጥመድ ያመጣል በእግዚአብሔር የሚታመን ግን እርሱ ይጠበቃል” የሚል ነው ። (ምሳ. 29 ፡ 25) ። የድብብቆሽ ሕይወት የሚኖር ሰው የይሉኝታ እስረኛ ነው ። እንደውም ድብብቆሹ የበለጠ እንዲበድል ፣ ኃጢአት እንዲጥመው ፣ አላገኘውም ብሎ እንዲጨማለቅበት ፣ የዕለት ሥራው እንዲሆን ሊያደርገው ይችላል ። ወጥመድ አያራምድም ፣ ሰውን መፍራትም ነጻነት ያሳጣል ፣ ከኃጢአት ግን አይጠብቅም ። በእግዚአብሔር መታመን ግን ነፍስን ከግድፈት ፣ ሰውነት ከዝገት ይጋርዳል ። ቅድስና ለእግዚአብሔር ነው የሚለው አዋጅ ፣ ሰውን መፍራት ወጥመድ ነው የሚለው ምክር ከይሉኝታ ሰንሰለት የሚፈታ ነው ። ሰዎች በሁለት ነገር ከክፉ ሊርቁ ይችላሉ ። እግዚአብሔርን በመፍራትና ሰዎችን በማፈር ። ወይም የሰማይን ዋጋ በማሰብና ታሪኬ እንዳይበላሽ በማለት ክፉውን ለመራቅ ይሞክራሉ ። ይሉኝታ በይሻላል መስፈርት ያለ ፣ ዓይን ካፈጠጠ ስህተት የሚጋርድ ፣ ትንሽ ሰውነት ያለበት ፣ ልክ አይደለሁም የሚል ወቀሳም ያልተለየው ሊሆን ይችላል ። እግዚአብሔር ግን የልብ አምላክ ነውና በልብ መቀደስን ይፈልጋል ። በዚህ ዓለም ላይ ሁሉም ሰው የራሱ ችግር እንዳለው ሁሉ የራሱ ግድፈትም አለው ። ንጹሕ ነኝ ብሎ የመጀመሪያውን ድንጋይ ማንሣት የሚችል ብቁ ማንም የለም ። የመውገር ፍላጎት አብዛኛው ሰው አለው ፣ ኃጢአት የሌለበት እርሱ ይውገር ቢባል ግን ሁሉም ውልቅ ብሎ የሚወጣ ፣ ጸንቶ መቆም የማይችል ነው ። ይሉኝታ ሰዎች ስለ እኔ ይህን ሊያስቡ ፣ ይህን ሊናገሩ ይችላሉ የሚል ያልተጨበጠ ፍርሃት ነው ። ከይሉኝታ የሚፈታን አንዳንድ ጊዜ ሰዎቹ ከማሰብ ወጥተው መሳደብ ሲጀምሩ ነጻነት እናገኛለን ። ሰዎች ስህተታቸው እስኪነገር ድረስ እያበረዱ የሚጓዙ ናቸው ፣ ስህተታቸው አደባባይ ከወጣ በኋላ ግን ፍሬን እንደ ተበጠሰበት መኪና ሕግን አያከብሩም ። የሰዎች ምሥጢር ጠባቂ የምንሆነው ጨርሰው የኃጢአት ሎሌ እንዳይሆኑ ነው ። ይሉኝታ እውነተኛነት የሌለው ኑሮ ነው ። ማድረግ እየፈለግን የማናደርገው ማኅበረሰቡን በመንገዳችን እንደ ቆመ ትራፊክ ስለምንፈራ ነው ። ትክክለኛውን ነገር ከማኅበረሰቡ ባሕል ጋር አስታርቆ ማድረግ የምንኖርበት ዓላማ ነው ። ይሉኝታ ማድረግ የማንፈልገውንም ማድረግ ነው ። መጠጣት የማይፈልገው ሰው ይጠጣል ፣ በውስጡ ኀዘን ሳይሰማው ልቅሶ ቤት ሄዶ ያለቅሳል ፣ ደስ ሳይለው በሰው ሰርግ ላይ ይዘላል ። የአንድ ሰው ኑሮና ሕይወት በማኅበረሰብ ደረጃ በሚወሰንበት አገር ላይ ሰው የሚፈልገውን ትቶ የማይፈልገውን ለማድረግ ይዳረጋል ። ፍጹም ይሉኝታ ቢስ የሆነው የሰለጠነው አገርና የይሉኝታ ወጥመድ ያለበት ሌላኛው ምድር መታረቅ አለባቸው ። ይሉኝታ ራስን መክሰር ሊያመጣ ይችላል ። በሰዎች ምርጫ መኖርን ፣ ሁልጊዜ የሌሎችን ውሳኔ መቀበልን ፣ እየተረገጡ አላመመኝም ማለትን ፣ መብትን አሳልፎ መስጠትን ፣ ያላመኑበትን ነገር አዎ አዎ ማለትን ፣ ሳይረዱ ገብቶኛል ማለትን ያመጣል ። ይሉኝታ ከሕሊና ነጻነት ፣ ከእውቀት ፣ ከፍልስፍና ፣ ከሃይማኖት ፣ ከመንፈሳዊነት ያግዳል ። የሕፃን ልጅን ቆሻሻ ስንጠርግ “የእገሌ ልጅ ንፍጣም ነው” ይሉሃል ብለን እንጂ ንፍጥ አስቀያሚ ነው ብለን አይደለም ። ስለዚህ ያ ልጅ ሲያድግ የሚጸዳው ለራሱ ሳይሆን ለሰው ብሎ ነው ። ምንም ነገር ለማድረግ ስንነሣ “ሰው ምን ይልሃል (” የሚል ድምፅ ከጎናችን ካሉ ሰዎች ይሰማል ። ሰው እኮ የሚኖረው ለማለት ነው ። ሰው የፈለገውን ማለት ይችላል ፣ ሕይወቱ ግን የእኔው ነው ብሎ ጥሶ የሚወጣው እንደ እብድ ይታያል ። ይሉኝታ ያረገዘችው ተደብቃ እንድትሰነብት ፣ የበላው ሰውዬ እንዳልበላ እንዲያስመስል ፣ የማያውቀውን አውቃለሁ እንዲል ያደርጋል ። በማያሳፍረው ማፈር ከይሉኝታ ይወለዳል ። መንገድ ጠፍቶን የእኛን ሰው ብንጠይቅ አላውቅም የሚል የለም ፣ ሁሉም ሰው በዚህ በኩል ነው እያለ ስድስት አቅጣጫ ይነግረናል ። አታውቅም ይሉኛል የሚል ፍርሃት አለበት ። ለዚህ ነው ያልተማረው ሰው የተማረውን የሚያርመው ። አንድ አሳብ ሲሰጥ ሁሉም ሰው አስተያየት መስጠት ግዴታው ይመስለዋል ። ለሁሉም ነገር አስተያየት አይሰጥም ። ብዙ አስተያየቶቻችን እንከን ፈላጊነት አለባቸው ። ይህ ሁሉ ይሉኝታ ድሩን ስላደራብን ያተረፍነው ጠባይ ነው ። ሊቃውንት ዝምታን ፣ ያልተማሩ መለፍለፍን የመረጡት በይሉኝታ ሥርወ መንግሥት ውስጥ ስላለን ነው ። ስንቱ ሊቅ ፣ ስንት ስህተት እያየ የቡና መጠጫ ፣ የጠላ ዋንጫ ከሚያደርጉኝ ብሎ ዝም ብሏል ። ይሉኝታ ሊቅ ገዳይ ነው ። ስሜታችንንም ሆዳችንንም እየሸሸግን የምንኖር ነን ። ሆድ አይሸሸግም ፣ እኛ ግን እየራበን በልቼ ነው እንላለን ። ስሜትም ከተሸሸገ ውስጣዊ እሳተ ጎሞራ የሚፈጥር ፣ ራስን ጠርጎ የሚወስድ ነው ። የይሉኝታ ባሕላችን ግን ሆዳችንም ሕሊናችንም በረሀብ ጠኔ እንዲኖር ያደርገዋል ። መጠየቅ መማር ባለመፈለጋችንም አላዋቂነት እንዲሰፍን አድርጎናል ። ትልቁ እስረኛ በይሉኝታ አጭር ዘመኑን ያመረረ ሰው ነው ። አዎ “እግዚአብሔር የታሰሩትን ይፈታል ።” (መዝ. 145 ፡ 7) ።

💥የትምህርቱ ርዕስ | ይሉኝታ የእግር ብረት ሲሆን የምንበላው የምንጠጣው ለራሳችን ነው ፣ የምንኖረው ግን ለሰው ነው ። ደስ ያለንን አንናገርም ፣ ደስ ያለንን ልብስ አንለብስም ፣ ሰዎች ደስ የሚላቸውን እንደ አዝማሪ እናዜማለን ፣ ሰዎች ደስ የሚላቸውን እንለብሳለን ። “ሰው አፍ እንዳትገባ” ፣ “ሰው እንዳያይህ” በሚል ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ውስጥ ወድቀናል ። ጸጋ የሚቀበረው ፣ ተሰጥኦ ፈንቅሎ የማይወጣው ፣ አገር የማያድገው እርስ በርስ በመጠባበቅ ስንኖር ነው ። የሰው ምላስ ሰባሪ ነው ፣ በእነ እገሌ አፍ አትግባ እየተባለ ስለሚነገረን ለአገር የሚበቃ ስጦታ ይዘን እቤት ተቀብረን እንቀራለን ። ፍርሃቱ እያየለ ሲመጣም የገዛ ቤተሰባችንን እንኳ ማነጋገር ፣ በጸጋችን መጥቀም አንችልም ። በርግጥም ቀና ያለውን ሰው በብረት ዘነዘና መትተው የሚፈጠፍጡ ሁልጊዜ በንቃት ላይ ናቸው ። ቀና ያለ ፣ ለዛው ያማረ ፣ እውቀቱ እያሸተ ያለ ሰው ስናይ ከመደሰት እንፈራለታለን ። በአገሩ ላይ ጥቂት ሰዎች ብቻ ሲናገሩ አፈ ማር ፣ ሲሠሩ መልአክ ተብለው ለመወደስ ተደራጅተዋል ። ቅስም ለመስበር ፣ ከመስመር ለማስወጣት ፣ ብለን ነበር የሚለው ትንቢታቸው እንዲሰምር አፋፍ ላይ ያለውን ገፍተው መጣል የሚያስደስታቸው ሰዎች ሊኖሩ ይችላሉ ። ነገር ግን ተሰብረን ካልጠበቅነው ማንም ሊሰብረን አይችልም ። ሰዎች መስበር ሥራቸው ሊሆን ይችላል ፣ አለመሰበር ደግሞ የእኛ ድርሻ ነው ። ሞተን ካልጠበቅነው ማንም አይገድለንም ። የአገራችን ሰው ላለመለወጥ ተጠንቅቆ የሚጓዝ ነው ። በዚህ ውስጥ አሸንፎ መውጣት ፣ በሚያልፍ ዕድሜ የማያልፍ ታሪክ መጻፍ ፣ እግዚአብሔር የመከረው ሰው ጠባይ ነው ። ንጽሕናችንን እንኳ የምንጠብቀው ከሰዎች ጋር ቀጠሮ ካለን ነው ። ደኅና ልብስ የምንለብሰው ሰርግ ሲገጥመን ነው ። ቤታችንን የምናጸዳው እንግዳ የሚመጣ ከሆነ ነው ። የገዛ ጥርሳችንን የምንቦርሸው ደጅ የምንወጣ ከሆነ ብቻ ነው ። ለራሳችን ክብር ፣ ለሕይወታችን ንጽሕና ያስፈልገናል ። በደጅ ስልክክ ብሎ የሚታየው ጉብል ቤቱ የተዝረከረከ ነው ። መሬት ለመርገጥ የሚጸየፈው ጎበዝ እቤቱ መሬት ላይ የሚተኛ ነው ። ይሉኝታ ጉረኛ ፣ የዛሬ መመኪያ ብናጣ በአያት በቅድመ አያት የምንመካ እያደረገን ነው ፤ ግጥም እየተወራወርን በአፍ ጦር መወጋጋት ፣ ሰውን ሰብሮ መግባት እንደ ድል መቍጠር ጠባያችን ከሆነ ሰንብቷል ። የምንማረውም እውቀት አስፈላጊ ስለሆነ ሳይሆን መሃይም ብለን ሌላውን ለመሳደብ ነው ። ያለ አቅማችን ሰዎችን መጋበዝ ፣ ተበድረን ሰርግ መደገስ ፣ በር አዘግተን የሁሉንም ሒሳብ መክፈል እንፈልጋለን ። ብዙ ትዳር የድግስ ዕቃው ሳይመለስ ጠብ የሚጀምረው ለይሉኝታ ብለው በገቡበት ዕዳ ነው ። በአቅማችን መኖር አልቻልንም ፣ እውነተኛውን ነገር ከማድረግ ለሰው አፍ ብለን የምንከፍለው ይበዛል ። ባለ ትዳሮቹን ከማቋቋም ፣ ለአሞራ አብልተን ፣ አሞራ በሰማይ ሲያይሽ ዋለ ብለን ዘፍነን እንሸኛለን ። በሚሊየን የተደገሰላቸው አዲስ ሙሽሮች የሚገቡት ኪራይ ቤት ውስጥ ነው ። ለቀጣዩ ወር የኑሮ ጭንቅ ውስጥ ይገባሉ ። ከሚለብሰው ተርፎት የሚከናነበው አለው ለመባል ቀሚስ ሳይኖረን ካባ እንደርባለን ። አስበን የምናደርገው ነገር የለም ፣ ሁሉንም ነገር ትእዛዝ እስኪመጣ እንጠብቃለን ። ሠራተኛው አለቃው እስኪመጣ የወሬ ስፌት ይሰፋል ፣ አለቃውን ሲያይ ይሯሯጣል ። የገዛ ሕሊናው የማያዝዘው ሰው ከቆሙት በታች ፣ ከሞቱት በላይ ነው ። ሽማግሌው ቆሻሻ ሲጠርግ ምነው እኛ እያለን የሚለው ብዙ ነው ፣ እኒያን ሽማግሌ የሚያዳክም እንጂ አስቦ የሚያጸዳ የለም ። እግዚአብሔር ለሠራው ምድር ፣ ለፈጠረውም ወንዝ ያስባል ፤ ስናጎሳቁለው ይቀጣናል ። የምንበክለው ተፈጥሮ ዋጋ ያስከፍለናል ። ከውጭ አገር በሚላክ ገንዘብ ሰው ሲጋብዙ የሚውሉ ፣ “እርስዋን ያቆይልን” እያሉ የሚያስመርቁ ፣ ለዚያች ልፋተኛ ግን መሬት እንግዛላት የማይሉ ብዙ ጨካኞች አሉ ። ልጆቹን እያስራበ ሲገባበዝ የሚውል ፣ አባ መስጠት ተብሎ ለመጠራት የማይጠቅም መጠጥ የሚራጭ ብዙ ነው ። ይሉኝታ ውዳሴ ከንቱ ምግቡ ነው ። በእውነቱ ስናየው ሥራ ማጣት እንዳለ ሆኖ ሥራ ቢገኝስ የሚሠራ አለ ወይ ( ብለን መጠየቅ ያስፈልጋል ። ቧንቧ ሠራተኛው ቀጥራችሁት የሚመጣው በወሩ ነው ። ሥራ ጠፍቷል ወይስ ሥራን ገፍተናል ( ብለንም መጠየቅ ያሻናል ። የምሠራውንም በመሰልቸት ስለምንሠራው የተሠራለት ሰው ሲረግመን ይኖራል ። ከሰው ጉቦ ተቀብሎ ወይም ቀምቶ ማታ ላይ ሰው ሲጋብዝ የሚውል አለ ። እንዴት ሰው ፣ ሰውን አስለቅሶ ሰውን ለማስደሰት ይሞክራል ( ይሉኝታ ፣ የይሉኝታ ኑሮ የማትሞት የማትድን አገር ይፈጥራል ። አምነንበት የምናደርገው በጎነት ፣ አምነንበት የምንተወዉ ክፋት ከሌለ እውነተኛ ሰዎች አይደለንም ። ለሚለምነው መስጠት መልካም ነው ። ለሚሠራው ማበረታታት ተገቢ መሆኑን ማመን አልቻልንም ። ለጉራ ወፍራም ቲፕ ስንሰጥ የታክሲ ረዳትን ተከራክረን ድቃቂ ሳንቲም መቀበል ግን እንደ ድል እንቆጥረዋለን ። የሚለምነው እንደሚያሳዝነን የሚሠራው ሰው ሊያስደስተን ፣ በርታ ልንለው ይገባል ። ይሉኝታ እውነታ አይደለም ። በይሉኝታ የጋበዘ ሰው ሲጸጸት ይውላል ። ይሉኝታ ሰውን ለማትረፍ እግዚአብሔርንና ራስን ማጣት ነው ። ሰዎችን የምንረዳቸው ስለራራን ነው ወይስ ለይሉኝታ ብለን ነው ( ብለን ራሳችንን መጠየቅ አለብን ። ሰዎች መልካም እንዲሉን የምናደርገው ደግነት በእግዚአብሔር ዘንድ የመጠሪያ ስሙ “ግብዝ” የሚል ነው ። ለወንበራችን ፣ ለስማችን ፣ ለታሪካችን የምንኖር ነገር ግን ለዛሬው ሰው የማንጠቅም መሆን አለመታደል ነው ። ዛሬ ላለው ሰው ምን ይጠቅመዋል ( ለትውልድስ ምን ይተርፋል ( ብሎ ሥራን መሥራት ተገቢ ነው ። የጠገቡትን ከማጥገብ የተራቡትን ማጥገብ ትርጉም ያለው ፣ ሕሊናንም እግዚአብሔርንም ማትረፊያ ነው ። ይቀጥላል...

ለክረምት ነባር ተማሪዎች በሙሉ:-
ለክረምት ነባር ተማሪዎች በሙሉ:-

👉#ይህ_የመቅደላ_አምባ_ዩኒቨርስቲ_ሬጅስትራር_ኦፊሻል_ቻናል_ነው! 👉 ትክክለኛ መረጃ ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉ! 👉 ሌሎች ተማሪዎችን እዚህ ቻናል ላይ Add አድርጉ (የአባላት ቁጥር ቢያንስ 2.5K መድረስ አለበት በዚህ ሳምንት)! 👉ሪመድያልን በተመለከተ አዲስ ነገር ሲኖር በዚህ ቻናል ብቻ እናሳውቃለን! 👉https://t.me/MAUREG1

ማህበራዊ ሚዲያዎች ያለ VPN መስራት ጀመሩ። ለወራት ያህል በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ተጥሎ የነበረው ገደብ መነሳቱን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከቤተሰቦቹ ለማረጋገጥ ችሏል። #ቴሌግራም ፣ ዩትዩብ ፣ ፌስቡክ ፣ ቲክቶክ መሰል የማህበራዊ ሚዲያዎች ከወራት በፊት (የካቲት ወር 2015 ዓ/ም) በተጣለባቸው ገደብ ያለ VPN መስራት እንዳቆሙ ይታወቃል። ዛሬ ሰኞ ከሰዓታት በፊት ግን እነዚህ የማህበራዊ ሚዲያዎች #ያለ_VPN_እየሰሩ እንደሚገኙ እና ገደቡም መነሳቱን #ማረጋገጥ ችለናል

👉#ይህ_የመቅደላ_አምባ_ዩኒቨርስቲ_ሬጅስትራር_ኦፊሻል_ቻናል_ነው! 👉  ትክክለኛ መረጃ ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉ! 👉 ሌሎች ተማሪዎችን እዚህ ቻናል ላይ Add አድርጉ (የአባላት ቁጥር ቢያንስ 2.5K መድረስ አለበት በዚህ ሳምንት)! 👉ሪመድያልን በተመለከተ አዲስ ነገር ሲኖር በዚህ ቻናል ብቻ እናሳውቃለን! 👉https://t.me/MAUREG1

ውጤት የሚታይበት website ይሰራ እየገባችሁ ማየት ትችላላችሁ!
ውጤት የሚታይበት website ይሰራ እየገባችሁ ማየት ትችላላችሁ!

ለዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ከተቀመጡት ተማሪዎች ውስጥ 40.65 በመቶዎቹ የማለፊያ ነጥብ አስመዘገቡ! ለዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ከተቀመጡት ተማሪዎች ውስጥ 40 ነጥብ 65 በመቶዎቹ የማለፊያ ነጥብ ማስመዝገባቸውን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ ከሰኔ 30 ቀን ጀምሮ ለስድስት ቀናት ሲሰጥ የቆየው የዩኒቨርሲቲ ትምህርት መውጫ ፈተና በስኬት መጠናቀቁን ገልፀዋል። ለመውጫ ፈተና ሊቀመጡ ይችላሉ ተብሎ ተገምቶ ከነበረው 240 ሺህ ተማሪዎች የመውጫ ፈተናውን 194 ሺህ 239 ተማሪዎች ብቁ ሆነው ለፈተና መመዝገባቸውንም ነው የተናገሩት። ከዚህ ውስጥ ከ48 የመንግስት ተቋማት 84 ሺህ 627 ተማሪዎች እና ከ171 የግል ተቋማት 109 ሺህ 612 ተማሪዎች የመውጫ ፈተናውን ለመውሰድ መመዝገባቸውም ነው የገለጹት። የመውጫ ፈተናውን ለመውሰድ ከተመዘገቡት ውስጥ ከመንግስት ተቋማት 77 ሺህ 981 ተማሪዎች እንዲሁም ከግል ተቋማት 72 ሺህ 203 ተማሪዎች በድምሩ 150 ሺህ 184 ተማሪዎች ፈተናውን ወስደዋል ብለዋል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ 61 ሺህ 54 ተማሪዎች ወይም 40 ነጥብ 65 በመቶ የማለፊያውን ነጥብ አስመዝገበዋል ነው የተባለው፡፡ ለተቋማትም የተማሪዎቻቸውን ውጤት የመላክ ሥራ መጀመሩንም ጠቁመዋል።

#Update ዩኒቨርሲቲዎች ላለፉት አምስት ቀናት ሲሰጡት የቆየው ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና መጠናቀቁን አሳውቀዋል። ከ44 የመንግሥት እና ከ161 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተውጣጡ ዕጩ ተመራቂዎች ከሐምሌ 03/2015 ዓ.ም ጀምሮ ሲሰጥ የቆየውን ፈተና መውሰዳቸው ተገልጿል። ከ168 ሺህ በላይ ዕጩ ተመራቂዎች ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተናውን ይወስዳሉ መባሉ ይታወሳል። ምን ያህል ተማሪዎች በኦንላይን የተሰጠውን ፈተና እንደወሰዱ መንግሥት በቀጣይ ይፋ እንደሚያደርግ ይጠበቃል። ከሐምሌ 08/2015 ዓ.ም ጀምሮ ውጤት ይገለጻል መባሉ አይዘነጋም። በሌላ በኩል ፥ የመውጫ ፈተና ከሰጡ ተቋማት አንዱ ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የፈተናው ውጤት ዛሬ ይፋ መሆኑን ገልጿል። ተቋሙ በ41 ፕሮግራሞች ካስፈተናቸው 1604 ተፈታኞች  ፡- - በ13 ፕሮግራሞች 100% - በ7 ፕሮግራሞች ከ90-99% - በ11 ፕሮግራሞች ከ80-89% በአጠቃላይ በ31 ፕሮግራሞች 80% እንዲሁም እንደ ዩኒቨርሲቲ 81% ተማሪዎቹ ማለፋቸውን በይፋ አሳውቋል። ዩኒቨርሲቲው ካስፈተናቸው 1604 ተማሪዎች 1289 ተማሪዎች ከ50% በላይ ውጤት ማስመዝገባቸውንም ገልጿል። በተጨማሪ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን  የመውጫ ፈተና (EXIT EXAM) ካስፈተናቸው 1450 ተማሪዎች መካከል 78.5% ተማሪዎችን በብቃት ማሳለፍ ማቻሉን ገልጿል። ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ካስፈተነባቸው 43 ፕሮግራሞች መካከል፡- 👉 100% ያሳለፉት 11 የትምህርት ክፍሎች/ፕሮግራሞች 👉 ከ90% በላይ ያሳለፉ 21 የትምህርት ክፍሎች/ፕሮግራሞች 👉 ከ80% በላይ ያሳለፉ 27የትምህርት ክፍሎች/ፕሮግራሞች 👉 ከ70% በላይ ያሳለፉ 32  የትምህርት ክፍሎች/ፕሮግራሞች መሆናቸውን ገልጿል።

#Update ሁሉም ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች በተቋማቸው የምርቃት መርሃ ግብር ላይ እንደሚሳተፉ ተገለጸ። መንግሥት ከዚህ ቀደም ወስዶት በነበረው ውሳኔ ላይ ማሻሻያ በማድረግ፤ “የመውጫ ፈተናን #ያላለፉ ተማሪዎችም በተቋማቸው የምርቃት ፕሮግራም ላይ እንደሚሳተፉ” የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት አሳውቋል። ከዚህ ቀደም ከግማሽ በላይ ጠቅላላ ድምር ውጤት (CGPA 2.00>) ያላቸው ተማሪዎች የምርቃት መርሃ ግብር ላይ ይሳተፉ የነበረ መሆኑን የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት አስታውሷል። አሁንም በተመሳሳይ የመውጫ ፈተናውን የማያልፉ ተማሪዎች የምርቃት መርሃ ግብር ላይ የሚሳተፉ ሲሆን ዲግሪ ለመውሰድ መሟላት የሚገባቸውን እንዲያሟሉ ይጠበቃል ብሏል። የመውጫ ፈተናውን ያላለፉ ተማሪዎች ለምዘና ብቁ ሲሆኑ በየሦስት ወሩ መፈተን እንደሚችሉም ህብረቱ ገልጿል። ያለገደብ ድጋሚ የመፈተን ፍላጎት የሌላቸው ዕጩ ምሩቃን በደረጃ ዝቅ ያለ የትምህርት ማስረጃ መውሰድ እንደሚችሉ በመመሪያ መቀመጡን ህብረቱ የላከልን መግለጫ ያሳያል። የመውጫ ፈተናውን ያለፉ ተማሪዎች በትምህርት ማስረጃቸው ላይ ከ100 ያመጡት ውጤት የሚገለፀው በጊዜያዊው ማስረጃቸው ላይ ሳይሆን በትራንስክሪፕት ላይ እንደሆነም ህብረቱ ጠቁሟል።

#Update ሁሉም ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች በተቋማቸው የምርቃት መርሃ ግብር ላይ እንደሚሳተፉ ተገለጸ። መንግሥት ከዚህ ቀደም ወስዶት በነበረው ውሳኔ ላይ ማሻሻያ በማድረግ፤ “የመውጫ ፈተናን #ያላለፉ ተማሪዎችም በተቋማቸው የምርቃት ፕሮግራም ላይ እንደሚሳተፉ” የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት አሳውቋል። ከዚህ ቀደም ከግማሽ በላይ ጠቅላላ ድምር ውጤት (CGPA 2.00>) ያላቸው ተማሪዎች የምርቃት መርሃ ግብር ላይ ይሳተፉ የነበረ መሆኑን የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት አስታውሷል። አሁንም በተመሳሳይ የመውጫ ፈተናውን የማያልፉ ተማሪዎች የምርቃት መርሃ ግብር ላይ የሚሳተፉ ሲሆን ዲግሪ ለመውሰድ መሟላት የሚገባቸውን እንዲያሟሉ ይጠበቃል ብሏል። የመውጫ ፈተናውን ያላለፉ ተማሪዎች ለምዘና ብቁ ሲሆኑ በየሦስት ወሩ መፈተን እንደሚችሉም ህብረቱ ገልጿል። ያለገደብ ድጋሚ የመፈተን ፍላጎት የሌላቸው ዕጩ ምሩቃን በደረጃ ዝቅ ያለ የትምህርት ማስረጃ መውሰድ እንደሚችሉ በመመሪያ መቀመጡን ህብረቱ የላከልን መግለጫ ያሳያል። የመውጫ ፈተናውን ያለፉ ተማሪዎች በትምህርት ማስረጃቸው ላይ ከ100 ያመጡት ውጤት የሚገለፀው በጊዜያዊው ማስረጃቸው ላይ ሳይሆን በትራንስክሪፕት ላይ እንደሆነም ህብረቱ ጠቁሟል።

#Update ሁሉም ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች በተቋማቸው የምርቃት መርሃ ግብር ላይ እንደሚሳተፉ ተገለጸ። መንግሥት ከዚህ ቀደም ወስዶት በነበረው ውሳኔ ላይ ማሻሻያ በማድረግ፤ “የመውጫ ፈተናን #ያላለፉ ተማሪዎችም በተቋማቸው የምርቃት ፕሮግራም ላይ እንደሚሳተፉ” የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት አሳውቋል። ከዚህ ቀደም ከግማሽ በላይ ጠቅላላ ድምር ውጤት (CGPA 2.00>) ያላቸው ተማሪዎች የምርቃት መርሃ ግብር ላይ ይሳተፉ የነበረ መሆኑን የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት አስታውሷል። አሁንም በተመሳሳይ የመውጫ ፈተናውን የማያልፉ ተማሪዎች የምርቃት መርሃ ግብር ላይ የሚሳተፉ ሲሆን ዲግሪ ለመውሰድ መሟላት የሚገባቸውን እንዲያሟሉ ይጠበቃል ብሏል። የመውጫ ፈተናውን ያላለፉ ተማሪዎች ለምዘና ብቁ ሲሆኑ በየሦስት ወሩ መፈተን እንደሚችሉም ህብረቱ ገልጿል። ያለገደብ ድጋሚ የመፈተን ፍላጎት የሌላቸው ዕጩ ምሩቃን በደረጃ ዝቅ ያለ የትምህርት ማስረጃ መውሰድ እንደሚችሉ በመመሪያ መቀመጡን ህብረቱ የላከልን መግለጫ ያሳያል። የመውጫ ፈተናውን ያለፉ ተማሪዎች በትምህርት ማስረጃቸው ላይ ከ100 ያመጡት ውጤት የሚገለፀው በጊዜያዊው ማስረጃቸው ላይ ሳይሆን በትራንስክሪፕት ላይ እንደሆነም ህብረቱ ጠቁሟል።

#ይነበብ2 የመውጫ ፈተና በሚሰጥባቸው ቀናት ከሚኖሩ ዲስፕሊንና እና ፕሮቶኮል መካከል ፦ - ከተፈቀደላቸው የዩኒቨርስቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ ለእለቱና ለዛ ፈተና ከተመደቡ አስተባባሪዎች፣ ለፈተናው ከተመደቡ ፈታኞች ውጭ የትኛውም አካል ወደ መፈተኛ ክፍል መግባት በጥብቅ የተከለከለ ነው። - ፈተናው በኦንላይን ስለሚሰጥ የአይሲቲ ሙያተኞች በመፈተኛ ክፍሎች አቅራቢያ በመሆን ድጋፍ ይሰጣሉ፡፡ - የፀጥታ ሃይል ወደ መፈተኛ ክፍል እንዲገባ አስገዳጅ ሁኔታ ከተፈጠረ በማንኛውም ጊዜ ሊገባ ይችላል፡፡ - የዩኒቨርስቲ የበላይ ኃላፊዎችን ጨምሮ የትኛውም አካል በምንም ሁኔታ ስልክ፣ ስማርት ዋች፣ ታብሌት እና ተመሳሳይ ቁሶችን ይዞ ወደ መፈተኛ ክፍል መግባት አይችልም፡፡ - የአይሲቲ ሙያተኞች በመፈተኛ ክፍሎች የሚስጡት ድጋፍ ከትምህርት ሚኒስቴር ባልደረቦች ወይም ከዩኒቨርስቲው አመራር ድጋፍና አመራር ማግኘትን ስለሚያካትት በልዩ ሁኔታ በዩኒቨርስቲው ተመዝግቦ የሚያዝና የሚታወቅ ቁጥር ያለው ስልክ ይዘው ወደ መፈተኛ አዳራሽ እንዲገቡ ሊፈቀድ ይችላል፡፡ - በአንዳንድ ፕሮግራሞች #ካልኩሌተር ማምጣት ይፈቀዳል፡፡ በተጨማሪም በአንዳንድ ፕሮግራሞች ለማስልያ የሚረዳ ንፁህ ወረቀት በዩኒቨርሰቲዎች በኩል ሊፈቀድ ይችላል፡፡ ይህም ሆኖ ስልክ፣ ስማርት ዋች፤ ታብሌት እና ተመሳሳይ ቁሶችን እንደ ካልኩሌተር መጠቀም ፈፅሞ አይፈቀደም፡፡ ሥራ ላይ የሚውሉ ካልኩሌተሮች የተራቀቁና ፕሮግራ መብል እንዳይሆነ ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል፡፡ - በማንኛውም ወቅት ከተፈቀደላቸውና ለድጋፍ ከተመደቡ የአይ.ሲ.ቲ ባለሙያዎች በስተቀር የተፈታኙን መፈተኛ ኮምፒውተር መንካት በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡ በድጋሚ መልካም ፈተና !