ከጥበብ ማህደር
በዚ ቻናል ላይ ጥበብ ነክ ነገሮች በስፋት ይቀርቡበታል በተጨማሪም ስዕል ማሳል ምትፈልጉ እና የግጥም ወይም የስዕል እንዲሁም አጠቃላይ የስነ ፆሁፍ ስራዎች ያላችሁ ሰዎች በዚ @binibanaa አናግሩን
Show moreThe country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
196
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
መልካም በዓል☪ #መውሊድ_አል_ነቢ_መሐመድ 🕌🕌🕌🕌🕌🕌🕌🕌🕌 መውሊድ አል-ነቢ ሰላም ፣ በረከት እና ደስታ ለእርስዎ እና ለቤተሰብዎ ተስፋ እንዲያመጣልዎ እንመኛለን። ☪☪☪☪☪☪☪☪☪ #መውሊድ_በዓል
የአልበርት አንስታይን እና የቻርል ቻፕሊን አስደናቂ ንግግር !!
አልበርት አንስታይን ከሀገሩ ወደ አሜሪካ ሲሄድ አሜሪካ ስትደርስ ማግኘት የምትፈልገው ማንን ነው ተብሎ ሲጠየቅ ማግኘት የሚፈልገው ሰው ቻርሊ ቻፕሊን ነው ብሎ መናገሩ ይነገራል።
እ.ኤ.አ በ1931 አልበርት "የCity Light" መሪ ተዋናዩን ቻርሊ ለማናገር እድሉን አገኘ።
እንደተገናኙም እንዲህ ተባብለው ነበር።
አንስታይን:- "ስላንተ ጥበብ በጣም ከሚያስደንቀኝ ነገር አለማቀፋዊነትህ ነው። አንድም ቃል ሳታወጣ መላው ዓለም ይረዳሃል"
ቻፕሊን:- "ትክክል ነህ! ነገር ግን ክብሩ ያንተ ይበልጣል እኮ። የምትናገረውን አንዱንም ሳይገባቸው መላው ዓለም ያደንቅሃል"
.......💐💐መልካም ቀን💐💐.......
ቻናሉን ከወደዳችሁት like እና share በማድረግ ለጓደኞቻችሁ እንድታጋሩ በአክብሮት እንጠይቃለን።ሀሳብ ጥያቄና አስተያየቶቻችሁን @binibanaa አድርሱን።
@ketebeb @ketebeb @ketebeb
ጎባጣው ትዳሬ
በየሳምንቱ ቅዳሜ አንድ መርህ አለኝ ፤ ያገርቤትም ሆነ የውጭ አገር ፖለቲካ ዜና እጦማለሁ፤ ኪነጥበብና ማህበራዊ ጉዳይ ላይ እጣድና ነፍሴን አለመልማታለሁ፤ በዚህ መሰረት ፥ ቅድም ዩቲዩብ ላይ ስርመሰመስ ቆየሁ ::
በቀደም አንድ የሞሮኮ ዜጋ የሆነ ዘፋኝ “ ሊጋባው በየነ” የሚለውን ዘፈን በራሱ ቃና ዘፍኖ አስደምሞኝ ነበር ፤ ዛሬ ደግሞ ሸገር ውስጥ በስደተኝነት የሚኖር ሶርያዊ ዘፋኝ “ ለዚህ ለዚህማ ምናለኝ አገሬ “ የሚለውን የጌቴ አንላይን ዘፈን ዘፍኖ አስለቀሰኝ ::
ወደ ፌስቡክ ተመለስኩ፤ ባለፈው አንዱ “ ላጤ” የሚለውን ግሩፕ እንድቀላቀል መጥርያ ልኮልኝ ነበር ፤ ያለሁበትን ተጨባጭ ሁኔታ ለመሰለል ፈልጎ ይመስለኛል፤ እኔም ግሩፑን ቀስ ብየ በለሆሳስ እየተራመድኩ ሰለልኩት፤ ፍቅር የተራቡ ” ሆርኒ” ወጣቶች የተደራጁበት ቡድን መሆኑን ደረስኩበት፤ ብዙም ሳይቆይ አንዲት ወይዘሮ ‘ በትዳራችን ጉዳይ እንመካከር “ የሚል ግሩፕ ላይ እንድሳተፍ መጥርያ ሰደደችልኝ ፤ ይሄ ግሩፕ የመጨረሻ ተመቸኝ፤የመጀመርያም ተመቸኝ :: አብዛኞቹ የግሩፑ አባላት ፥ የፍቅር ታሪካቸውን ተርከው ፤ በትዳራቸው ላይ የገጠማቸውን ችግር ዘርዝረው፥ ካንባቢ ምክርና መፍትሄ ያማትራሉ፤ እንሆ እኔም ተሞክሮየን ለማካፈል ወሰንኩ ፥
በውቄ እባላለሁ፤ ከባለቤቴ ጋራ የተገናኘነው ባጋጣሚ ነው፤ በጊዜው እሷ ሚስ ኢትዯጵያ ተብላ በቁንጅና ስትመረጥ እኔ አወዳደሪው ነበርኩ:: የመጀመርያዎቹ ሀያ አመታት የትዳር ቆይታችን ጎረቤት የሚያስቀና ነበር :: ከቢሮ ስመጣ በደስታ በፈገግታና በውዝዋዜ ትቀበለኛለች፤ ኮቴን አውልቃ ወደላውንደሪው አፍ እየጨመረች “ ምሳ እስኪደርስ ፤ ክትፎ በቆጮ እየቀማመስክ ቆይ “ ትለኛለች:: ከምሳ በሁዋላ ሶፋው ሳፋ እሲከመስል ድረስ ፍቅር እንሰራለን፤
በዙም ሳይቆይ ጸነሰች ፤ ከዘጠኝ ወራት ላልበለጠ ጊዜ በርግዝና ቆየች :: ያለ ብዙ ምጥ ወንድ ልጅ ተገላገለች፤ ልጃችንም ያለ ብዙ ለቅሶ ተገረዘ ! ልጃቸን በተወለደ በአንድ አመቱ ዶንኪቲዩብ ላይ እየቀረበ ለኢትዮጵያ ህዝብ ጠቃሚ ምክር መለገስ እና አቅጣጫ ማስቀመጥ ጀመረ:: ሰባት አመት ሲሞላው ካሮጌ ቅጥቅጥ ሚኒባስ ሂሊኮፍተር ሰራ :: አሁን ካዲስ አበባ ብሾፍቱ ራይድ እየሰራበት ይገኛል ::
ከጥቂት ጊዜ በሁዋላ ባለቤቱ ጸባይ መቀየር ጀመረ:: የገቢ ምንጯና ለኔ ያላት ፍቅር በፍጥነት እየጨመረ ሄደ፤ ለልደቴ ፍልውሃ ያለውን ፓርክ ገዝታ በስጦታ አበረከተችልኝ ::
በዚህ አይነት ሁሉን የሚያስቀና ትዳር ውስጥ እየኖርን እጅግ የሚያሳዝን ነገር ተከሰተ፤ ሄቲ ውስጥ የመሬት መንቀጥቀጥ ደረሰ ! ታሊባን አፍጋኒስታን መልሶ ተቆጣጠረ፤ ይህ ግን በፍቅራችን ላይ የፈጠረው አሉታዊ ተጽኖ አልነበረውም ::
አንባቢ ሆይ !! ትዳራችን ፈረሰ የሚለውን ለመስማት፥ ምክርና ከንፈር መጠጣ ለማዋጣት ሰፍ ብለህ እየጠበቅህ ነውን ? በቃ ሼም የለህም? ለምን የሟርተኞችና የክፉ ታሪክ ናፋቂዎች ግሩፕ አታቋቁምም ?
.
.
........💐💐መልካም ቀን💐💐........
ቻናሉን ከወደዳችሁት like እና share በማድረግ ለጓደኞቻችሁ እንድታጋሩ በአክብሮት እንጠይቃለን🙏🙏🙏🙏🙏
ሃሳብ፣ጥያቄና አስተያየቶቻችሁን @binibanaa አድርሱን።
@felsefena @felsefena @felsefena
አንዱ ጨዋ አንዱን ሊቅ ፦ ማይም ብሎ ይሳደባል፡፡ ሊቁም ተገርመው፦ ታድያ ሊቁ ማነው፡፡ ቢሉት፦ እኔ ነኝ አለ፡፡ ነገሩ ለፍርድ ቀረበ፡፡ ነገሩን ያዩት ዳኛ፦ የት ውለው ነበር ቢባሉ፦ ስም ቦታ ተቀያይሮ እያስመለስን ነበር አሉ ይባላል፡፡ የዘንድሮ ተራራ ቦታዉን ቀይሮ አሁን እየተመለሰ ነው፡፡
ዳንኤል ክብረት
........💐💐መልካም ቀን💐💐........
ቻናሉን ከወደዳችሁት like እና share በማድረግ ለጓደኞቻችሁ እንድታጋሩ በአክብሮት እንጠይቃለን🙏🙏🙏🙏🙏
ሃሳብ፣ጥያቄና አስተያየቶቻችሁን @binibanaa አድርሱን።
@felsefena @felsefena @felsefena
✍✍በላይ በቀለ ወያ
ይኸውልሽ
ያለፈው ቅዳሜ ፣ ሞቅ ብሎት ባልሽ
"ከሚስቴ ራስ ውረድ ፣ ብሎ ፈነከተኝ
"ወንድ አይደለህም ወይ?"
ብሎ ወንድነቴ ፣ እስከሚሞግተኝ
ታግሼ አለፍኩት ፣ በመላ በዘዴ
የፈራሁት መሥሎት
ዛሬም ሊደግመኝ ሲል ፣ ይሔ ብርቱ ክንዴ
ጉንጩ ላይ አረፈ
እንጃ ስንት ጥርሱ ፣ በአንዴ እንደረገፈ
ይኮላተፍ ጀመር ፣ ቃል ከአፉ እስኪጎድለው
በሚያገኘኝ ቁጥር
"ከሚስቴ ራስ ውረድ" ፣ እያለ የሚለው
ቆይ ያንቺን ሒዩማን ሔር ፣ ምኔ ነው ሚመስለው?
ነይ አሁን ሬሳሽን ፣ ሰብስቢ ሳልገድለው
#ሼርርርርርርርርር
........💐💐መልካም ቀን💐💐........
ቻናሉን ከወደዳችሁት like እና share በማድረግ ለጓደኞቻችሁ እንድታጋሩ በአክብሮት እንጠይቃለን🙏🙏🙏🙏🙏
ሃሳብ፣ጥያቄና አስተያየቶቻችሁን @binibanaa አድርሱን።
@ketebeb @ketebeb @ketebeb
ፀ III
ፈራን ፍቅር ፈራን
ከምንጭ አጠገብ ሆነን ተጠማን
ከሌቱ ነቅተን በቀኑ ተኛን
ሩቁን ስናይ ቅርቡን ተቀማን
እየ ፈራን
ፍቅር እየፈራን
ለሀገር ብለን የሠው ልጅ ጠላን
ከላይላይ ድነን ከውስጥ ደማን
ሀገርም እናት ወላጅም እናት
ይቅደሙ ቢባል እውነት ከማናት?
እውነቱን ከልብ ተፅፎ እያየን
ፍቅርን መፍራት እያስዘገየን
ለስርጉ ፈጥነን ለለቅሶው ቆየን
ለእንጨት አጥር ዛፍን ሰበርን
ለእናት ሀገር እናት ገደልን
እውነትን ፈራን ፍቅርን ፈራን
ብርሀን አጣን እያደር ቀላን::
ቀላነ
ቀላነ
ግዜው የመቅላት ነው አያማረብነ
ጊዜን ተማሰልነ
ከጥላ እየዋሉ
ሰዋች በጣም ቀሉ
ፀሀይ ራቃቸው
ብርሀን የላቸው
ጨለማ አቀላቸው
የጥላው ስር ሰዋች
እነ ፍጥር ስሞች
በስልካቸው መስኮት ከሩቅ የማያቸው
ዘመነኛ ውበት አቤት መቅላታቸው
ከፀሀይ ላይ ውሎ ጠበል የተጠማ
የኔ አይነቱማ
ከፀሀይ ላይ ውዬ
ሠው ይቀድማል ብዬ ሦሥት III ድንኳን ጥዬ
አለቅሳለሁ ብዬ
ከጥላው ተቀምጠው
የለቅሶውን ጠዲቅ እንደድግስ በልተው
ያዩኝና ርቀው
በስልካቸው መስኮት ሶስቴ ጊዜ ወጥተው
ሶስት ጊዜ ገብተው
ከሰውነት ተራ ወተሀል አንተዬ
ጠቁረሀል ይሉኛል ኸረ አንተሰውዬ
ከሰውማ ተራ ቀልተው መውጣታቸው
ማን በነገራቸው::
ከቀሉት አልገጥም ወጥቻለሁ ጥዬ
ከእውነት ብርሀን ተፀሀይ ላይ ውዬ
ግድ የለም ይሁና ይህ ከሆነኝ ጠበል
የእውቀት ባሪያ ሠው ጥቁርቁር ልበል
ጥቁር ነኝ አንዳለው ሰለሞን
ጥበብ የተቀባ ሰሞን
ጥበቡ አቃጥሎ በእውቀት ቢያጠቁረው
ልጄ ሠው ሁን ብሎ ዳዊትም ሲመክረው
እንደሆነው
እኔስ ልቤ እውነት አየ
ማን እንደሆንኩኝ ለየ
ሠው ነህ ይላል::
ሠው ይቀድማል::
አውቄ ፈገየሁ
ከመንጋው ተለየሁ
በእውቀት የበረየ
ካመለጠ ቆየ
ከጥላው ስር ውሎ ከቀላው ቀላቶ
ፀሀይ ላይ የዋለው ያጥቁር ቡትቶ
መልኬ ይሁነኛ
እውነት ተሻለኛ
ፍቅርን አልፈራም
ሎሬቱ በኔ ላይ ገጥሞ አያቅራራም
እኔ ፍቅር አልፈራም
ፀጋዬ ሊወሰድ እምቢን አላቅማማም
ይሁን ለፈሩቱ
ከጥላው ላሉቱ
ብርሀን ከሌለበት
ከሠው ለቀሉቱ::
.
.
.
ሮፍናን:: III
..
..
........💐💐መልካም ቀን💐💐........
ቻናሉን ከወደዳችሁት like እና share በማድረግ ለጓደኞቻችሁ እንድታጋሩ በአክብሮት እንጠይቃለን🙏🙏🙏🙏🙏
ሃሳብ፣ጥያቄና አስተያየቶቻችሁን @binibanaa አድርሱን።
@ketebeb @ketebeb @ketebeb
#አልሰማህም
አንድ ሰው መጥቶ ሶቅራጥስን:- " እገሌ ስለተባለው ወዳጅህ የሰማሁት ደስ አይልም" አለው። ሶቅራጥስ ግን ዝም አለ።
ሰውየውም እንደገና:-
" ይገርማል ከእሱ አይጠበቅም ገርሞኛል" አለው።
ሶቅራጥስም እንደማይለቀው ስለተረዳ:- "ስለወዳጄ ልትነግረኝ የፈለከውን ልሰማህ የምችለው ሦስት ጥያቄወች አሉኝ እነርሱን ስትመልስልኝ ብቻ ነው" አለው። ሰውየውም ተስማማ።
" የመጀመሪያው ጥያቄ የእውነት ጥያቄ ነው፣ስለወዳጄ የሰማኸው መቶ በመቶ እውነት ነው ወይ?" አለው። #ሰውየውም፦ " መቶ በመቶ እርግጠኛ መሆን አልችልም" አለው። #ሶቅራጥስም ፦ "ልትነግረኝ የፈለከው እርግጠኛ ያልሆነ ነገር ነው፤
ሁለተኛው ጥያቄየ የመልካምነት ነው፤ የምትነግረኝ መልካም ነገር ነው ወይ?" አለው። #ሰውየውም፦ " እርሱማ መልካም አይደለም" አለው።
#ሶቅራጥስም፦ " አንደኛ እውነተኛነቱ ያልተረጋገጠ ሁለተኛ መልካም ያልሆነ ነገር ልትነግረኝ ፈልገሃል፤ ሦስተኛ ጥያቄ አለኝ" አለው። ሰውየውም እሽ አለ።
ሶቅራጥስም፦ " ለእኔ የሚጠቅመኝ ነገር አለው ወይ?" አለው። ሰውየውም የለም ብሎ መለሰ።
ሶቅራጥስም፦ " እውነትነቱ ያልተረጋገጠ፣ መልካም ያልሆነ፣ ለእኔ የማይጠቅም ነገር አልሰማም" አለው።
እነዚህ ሦስት መስፈርቶች ተግባራዊ ቢሆኑ ጆሮ ይቀደሳል።
ለጆሮአችን ስንጠነቀቅ ሌሎች ደግሞ ለአንደበታቸው ይጠነቀቃሉ።
........💐💐መልካም ቀን💐💐........
ቻናሉን ከወደዳችሁት like እና share በማድረግ ለጓደኞቻችሁ እንድታጋሩ በአክብሮት እንጠይቃለን🙏🙏🙏🙏🙏
ሃሳብ፣ጥያቄና አስተያየቶቻችሁን @binibanaa አድርሱን።
@felsefena @felsefena @felsefena
.
.
.
........💐💐መልካም ቀን💐💐........
ቻናሉን ከወደዳችሁት like እና share በማድረግ ለጓደኞቻችሁ እንድታጋሩ በአክብሮት እንጠይቃለን🙏🙏🙏🙏🙏
ሃሳብ፣ጥያቄና አስተያየቶቻችሁን @binibanaa አድርሱን።
@ketebeb @ketebeb @ketebeb
Choose a Different Plan
Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.