en
Feedback
Mayor Office of Addis Ababa

Mayor Office of Addis Ababa

Open in Telegram

ይህ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ፅ/ቤት የቴሌግራም ገፅ ነው፡፡ ከተማችን አዲስ አበባ እንደ ስሟ አዲስ፣ ውብና ለነዋሪዎቿ የተመቸች እንድትሆን እንሰራለን፡፡

Show more
Ethiopia3 873The category is not specified
6 890
Subscribers
-824 hours
-187 days
-6430 days
Posts Archive
Twitter❗ጥቆማ እንስጣችሁ 👇👇👇 https://twitter.com/MayorAddis ይህ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ፅ/ቤት የቲውተር ገፅ ነው! Follow በማድረግ ታማኝ እና ፈጣን መረጃዎች
Twitter❗ጥቆማ እንስጣችሁ 👇👇👇 https://twitter.com/MayorAddis ይህ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ፅ/ቤት የቲውተር ገፅ ነው! Follow በማድረግ ታማኝ እና ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ! https://twitter.com/MayorAddis

Twitter❗ጥቆማ❗ የአዲስ አበባ ከተሚ ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ የቲውተር ገፅ! www.twitter.com/AddisAbabaCity1 ይህ የአዲስ አበባ ከተማ ኮሚዩኑኬሽን ቢሮ የቲውተር ገፅ ነው! የገፁ ተከ
Twitter❗ጥቆማ❗ የአዲስ አበባ ከተሚ ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ የቲውተር ገፅ! www.twitter.com/AddisAbabaCity1 ይህ የአዲስ አበባ ከተማ ኮሚዩኑኬሽን ቢሮ የቲውተር ገፅ ነው! የገፁ ተከታይ በመሆን Follow በማድረግ ታማኝ እና ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ! www.twitter.com/AddisAbabaCity1

Twitter❗Twitter❗ ይህ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ፅ/ቤት የቲውተር ገፅ ነው! Follow በማድረግ ታማኝ እና ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ! https://twitter.com/MayorAddis?t=3sqb_BsTQYh6ZiNIQlkwBA&s=09

Twitter❗Twitter❗ ይህ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ፅ/ቤት የቲውተር ገፅ ነው! Follow በማድረግ ታማኝ እና ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ! https://twitter.com/MayorAddis?t=
Twitter❗Twitter❗ ይህ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ፅ/ቤት የቲውተር ገፅ ነው! Follow በማድረግ ታማኝ እና ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ! https://twitter.com/MayorAddis?t=3sqb_BsTQYh6ZiNIQlkwBA&s=09

ዛሬ ምሽት ከ3:00 ሰዓት ጀምሮ በቅርቡ በይፋዊ መንገድ በተላለፈው የጋራ መኖርያ ቤት እጣ አወጣጥና አጠቃላይ ሂደት ዙርያ የተዘጋጀ ዘጋቢ ፊልም በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ይከታተሉ!
ዛሬ ምሽት ከ3:00 ሰዓት ጀምሮ በቅርቡ በይፋዊ መንገድ በተላለፈው የጋራ መኖርያ ቤት እጣ አወጣጥና አጠቃላይ ሂደት ዙርያ የተዘጋጀ ዘጋቢ ፊልም በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ይከታተሉ!

ሙስና❗በአዲስ አበባ❗ ክብርት ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በአዲስ አበባ የአገልግሎት አሰጣጡ ዘርፍ የገጠመውን ብልሹ አሰራርን በተመለከተ ከተናገሩት የተወሰደ!

የቂርቆስ ክ/ከተማ አስተዳደር በ90 ቀናት በልዩ ሁኔታ የሚተገበሩ እቅዶችን ከባለሃብቶች ፤መንግስታዊ ተቋማትና፤ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጋር በዛሬው እለት ውይይት አደረገ፡፡ የቂርቆስ ክ/ከተማ
+4
የቂርቆስ ክ/ከተማ አስተዳደር በ90 ቀናት በልዩ ሁኔታ የሚተገበሩ እቅዶችን ከባለሃብቶች ፤መንግስታዊ ተቋማትና፤ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጋር በዛሬው እለት ውይይት አደረገ፡፡ የቂርቆስ ክ/ከተማ በሚቀጥሉት 90 ቀናት በልዩ ሁኔታ የሚተገበር እቅድ ይፋ አድርጓል፡፡ የዝቅተኛ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ የሚሆኑባቸው መኖርያ ቤት ፕሮጀክቶች ፤የቤት እድሳት ፤ለወጣቶችና ለሴቶች የስራ እድል የሚፈጥሩ የመስርያ ቦታዎች ፤የዳቦ ፋብሪካ ፤ፓርኮች፤የከተማ ግብርና የመሳሰሉት የእቅዱ አካላት ናቸው፡፡ በስነስርዓቱ ላይ የተገኙት ባለሃብቶችና ተቋማት በተለያየ መንገድ የክ/ከተማውን የልማት እቅድ እንደሚደግፉም ቃል ገብተዋል፡፡ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት ቂርቆስ በጉስቁልና እየተጠራች መቀጠል የለባትም፡፡ ትንሻ አዲስ አበባ ናት በማለት ገልፀዋል፡፡ እዚህ የተገኛችሁት ለበጎ እና ለተቀደሰ ተግባር ሌሎችን ለማገልገል ነው ብለው ገልፀዋል፡፡ እንደ ክብርት ከንቲባ አገላለፅ ባለፉት የ60/90 ቀናት የሰው ተኮር ተግባራት በእርግጥም ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን አንስተው ለምሳሌ በአንድ አካባቢ በተሰራ ቤት ግንባታ 6 ሰዎችን ከአካባቢው በማንሳት ለ55 ሰዎች ሚበቃ መኖያ ቤት መሰራት መቻሉን አብራርተዋል፡፡

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ በበጎ ፍቃደኞች የሚገነቡ የጋራ መኖሪያ ቤት ግንባታ መርሀ ግብር በይፋ አስጀምረዋል። በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ያ
+4
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ በበጎ ፍቃደኞች የሚገነቡ የጋራ መኖሪያ ቤት ግንባታ መርሀ ግብር በይፋ አስጀምረዋል። በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ያሉና ድጋፍ የሚሹ የማህበረሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የጋራ መኖሪያ ቤት ግንባታ የመሠረተ ድንጋይ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በዛሬው እለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የማስጀመሪያ መርሀ ግብር ተከናውኗል። በዚህም መሠረት በክ/ከተማው አራት እያንዳንዳቸው ባለ አራት ወለል ህንፃዎችን በጠቅላላ 160ቤቶችን የሚይዝ የቤት ግንባታ የመሰረት ድንጋይ በከንቲባ አዳነች አቤቤ ተቀምጧል። ሙሉ የቤቶቹ የግንባታ ወጪም የሚሸፈነው በበጎ ፍቃደኛ ኢትዮጵያውያን የጋራ ትብብር ሲሆን እነዚህም አያት ሪል ስቴት፤ ጊፍት ሪልስቴት ፤አልሳም ሪልስቴትና አምደሁን ጠቅላላ ንግድ ፤ MSW ሆራ ትሬዲንግ ይገኙበታል፡፡ መርሀ ግብሩን በይፋ ያስጀመሩት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ "ቤት ያረጃል ፤ይፈርሳል አስተሳሰቡ ግን ከትውልድ ትውልድ ይተላለፋል" ብለዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ ጨምረውም በዚህ የበጎ ፍቃድ ተግባር ላይ ተሳታፊ የሆኑ ባለሀብቶች መበልፀግ የምንችለው ህዝባችንን ይዘን ነው የሚል እሳቤን በመያዝ እያደረጉ ላለው የድጋፍ ተግባርም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ህዝቡም በዚህ አጋጣሚ አላግባብ ለመጠቀም በደላላ በተለያየ መንገድ የሚጥረውንም ሃይል ሃይ ሊል ይገባል በጋራ በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

"ሙስና ላይ ለምናደርገው ትግል ትልቅ ጉልበት የሚሆን የምስራች ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ብሄራዊ ኮሚቴ በማቋቋም አሰምተውናል ፤ ይህንን እድል እንጠቀምበት!! አዎ ! ሙስና ሀገርና ትውልድ የሚገድል
"ሙስና ላይ ለምናደርገው ትግል ትልቅ ጉልበት የሚሆን የምስራች ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ብሄራዊ ኮሚቴ በማቋቋም አሰምተውናል ፤ ይህንን እድል እንጠቀምበት!! አዎ ! ሙስና ሀገርና ትውልድ የሚገድል ነቀርሳ ነው፡፡ የሀገርንና የህዝብን ሀብት ከሌቦች ለመታደግ በምናደርገው ትግል ሌቦች አንገታቸውን ቀና አድርገው የሚሄዱበት ንፁሃንና እውነትን የተከተሉ የሚሸማቀቁበት ሃገር ልትኖረን አይገባም፡፡ ትግሉን ማቀጣጠል ይገባናል፡፡ በየመድረኩ ሙስና እንቅፋት ሆነብን ብሎ ለሚወቅሰው አመራርም ይሁን ህዝብ ይህ ትልቅ እድል ነው፡፡ እድሉን ሲገኝ ደግሞ ያለ አንዳች ፍርሀት እና ይሉኝታ በሚገባ መጠቀም ይኖብናል። ይህ ካልሆነ ነቀርሳው ካንዱ ወደ ሌላው እየተላለፈ ትውልድ እና ሀገር ይገድላል። ስለዚህ መረጃ እና ማስረጃ ያለው ፤ በተለይም የአዲስ አበባ ነዋሪና ሙስናን ለመታገል ጥረት የምታደርጉ አመራሮች ፤ ሰራተኞች ሁሉ ተገቢውን መረጃና ማስረጃ ዛሬ ለተዋቀረው ለብሄራዊ ኮሚቴ በማቅረብ ሃገራዊ ሃላፊነታችንን እንድወጣ ጥሪዬን አቀርባለሁ!!" ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በዛሬው እለት በሃገሪቱ ካሉ የተለያዩ ባንኮች ጋር በቤት ልማት ፕሮግራም በ70/30 ሞዳሊቲ አብሮ ለመስራት የሚያስችል ፍሬያማ ውይይት አካሂደዋል፡፡
+3
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በዛሬው እለት በሃገሪቱ ካሉ የተለያዩ ባንኮች ጋር በቤት ልማት ፕሮግራም በ70/30 ሞዳሊቲ አብሮ ለመስራት የሚያስችል ፍሬያማ ውይይት አካሂደዋል፡፡

የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 200 የውሃ ፖምፖችን አበረከተ!! በዛሬው እለት ለከተማ አስተዳደሩ የተበረከቱትን ለጓሮ አትክልትና የከተማ ግብርና ስራ የሚውሉ 200
+5
የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 200 የውሃ ፖምፖችን አበረከተ!! በዛሬው እለት ለከተማ አስተዳደሩ የተበረከቱትን ለጓሮ አትክልትና የከተማ ግብርና ስራ የሚውሉ 200 የውሃ ፓምፖችን የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ እጅ ተረክበዋል። በርክክብ ስነስርዓቱ ወቅት ንግግር ያደረጉት ከንቲባ አዳነች አቤቤ አዲስ አበባ ውስጥ ብዙ ወንዞችን በማከምና ፓምፖችን በመጠቀም ብዙ ምርት ማምረት እንደምንችል አጥንተናል ያሉ ሲሆን ዛሬ የተደረገልን ድጋፍ ለዚህ አቅም የሚሆን ነው ብለዋል። ከንቲባዋ የከተማ አስተዳደሩ ለከተማው እና በዙሪያዋ ላለው ገበሬ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑንም ጠቅሰው የሌማት ትሩፋት ብለን እንደ ሀገር ይፋ አድርገን እንደከተማችንም ወደስራ ገብተናል ብለዋል። መመገብ መቻል ከመስራት ይገኛል፤ መራብ የለብንም፤ የምግብ ዋስትናችንን ማረጋገጥ አለብን ከዛም ተርፈን ወደ ውጪ የምንልክ ዜጎች መሆን አለብንም ሲሉ ገልፀዋል፡፡ ኢንጂነር አይሻ አህመድ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር በበኩላቸው በከተማ ውስጥ የመስኖ ስራ እየተስፋፋ ስለሚገኝ ይህንን ስራ እንደ ሚኒስቴር መስርያ ቤት ልንደግፍ ይገባል ብለዋል፡፡ ይህንን የማስፋፋት የከተማ አስተዳደሩ ስራ ብቻ አይደለም፡፡ በከተማ ውስጥ የሚገኙ ተቋማትና ድርጅቶችም ይህንን ተግባር ማገዝ እንዳባቸው አሳስበዋል፡፡ ከንቲባ አዳነች በርክክቡ የከተማውን ሕዝብ ኑሮ ለመቀየር የሚኒስቴ መስሪያ ቤቱ ላደረገው ድጋፍ አመስግነው " ይሕንን የሰጣችሁንን ድጋፍ በትክክል ለሚገባው አካል አድርሰን ውጤቱን አብረን የምንጎበኘውና የምናየው ምርቱንም በጋራ የምንጠቀምበት እንደሚሆን ቃል ልገባ እወዳለሁ"ብለዋል።

አጠቃላይ_20_80_ነባር_ቤት_ፕሮግራም_አሸናፊዎች_ዝርዝር_xls_min_1.pdf4.80 MB

አጠቃላይ_40_60_ቤት_ፕሮግራም_አሸናፊዎች_ዝርዝር_xls_min_1.pdf1.25 MB

አጠቃላይ_20_80_አዲስ_የቤት_ፕሮግራም_አሸናፊዎች_ዝርዝር_xls_1.pdf9.88 KB

photo content
+4

በፈተና ውስጥ ሆነንም በርካታ አንፀባራቂ ድሎችን እያስመዘገብን ተጉዘናል! ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በዛሬው እለት እየተከናወነ ባለው የጋራ መኖርያ ቤቶች እጣ አወጣጥ ስነስርዓት ላይ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች 👉 ባለፉት ጊዜያት ከውስጥም ከውጪም የነበሩብን ችግሮች ገሚሱም አድምቶን፤ ገሚሱም አበርትቶንና አስተምሮን አልፏል። 👉 ሆኖም በፈተና ውስጥ ሆነንም በርካታ አንፀባራቂ ድሎችን እያስመዘገብን ተጉዘናል፤ 👉 እነኚህ ዛሬ እጣ የምናወጣባቸው ቤቶች በበርካታ ችግሮች ማለትም የፋይናንስ እጥረት ፤ የመሰረተ ልማት አቅርቦት ፤ የግንባታ እቃዎች ዋጋ መናርና እጥረቶች ፤የተቋራጭ መጥፋትና ሌሎችም ችግሮች የተወሳሰበ ቸግሮችን አልፏል፡፡ 👉 ይህንን ችግር ለመፍታት የከተማ አስተዳደሩ ከ21 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ከንግድ ባንክ በብድር በመውሰድ ለእጣ ብቁ እንዲሆኑ የተደረገበት ነው፡፡ 👉 በሌላ በኩል ደግሞ በእነኚሁ ቤቶች የእጣ አወጣጥ ስነስርዓት ሂደት ባጋጠመን የሌብነትና የማጭበርበር ድርጊት ምክንያት እጣው እንዲሰረዝና እንዲጓተት መደረጉ ነው፡፡ 👉 በተለይ ለረጅም ዘመናት በትዕግስት ሲቆጥብና ሲጠባበቅ ለነበረው ህዝባችን አሳዛኝ ዜና ነበር፡፡ በሂደቱም መንግስትና ህዝብን በማቃቃርና አለመተማመን የሚፈጥርና ፖለቲካዊ አንድምታ የነበረው ድርጊት ነበር፡፡ 👉 የከተማ አስተዳደሩ ችግሩን ለመፍታት በታማኝነት በግልፀኝነትን ተጠያቂነት ለማስፈንም ተገደናል፡፡ በዚህ ድርጊ የተሳተፉ በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ በማድረግ የህዝብ ሃብት ከዝርፊያ ማዳን ተችሏል፡፡ 👉 ከሁሉም በላይ ግን ትልቁ ስራ የነበረው ህዝባችን ውስጥ የተፈጠረውን አለመተማመንና ጥርጣሬ ለመቅረፍ እና የማያዳግም ስራ በመስራት የህዝባችንን እምነት ለመመለስ የሄድንበት መንገድ ነው፡፡ 👉 ይህንን ኢ-ፍትሃዊነት ድርጊት ለመከላከል የቤት ዕጣ ማውጫ ሲስተሙን በአዲስ መልክ ከፍተኛ ልምድ ባለዉና ሪፎርም ባደረገው በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢንሳ) እንዲለማና የሴኪዩሪቲ ደህንነቱ እንዲረጋገጥ ተደርጓል፡፡ 👉 አዲስ የበለፀገውንም የዕጣ ማውጫ ሲስተም ፍተሻ ለማድረግ (አርተፊሻል ኢንተለጀንስ፣ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩንቨርሲቲ፣ ከከተማና መሰረተ ልማት ሚንስቴር) የተውጣጡ አምስት ሙያቸው የተመሰከረላቸው ባለሙያዎች ቴክኒካል ኮሚቴ በማቋቋም የለማውን ሶፍትዌር የማረጋገጥና ተችሏል፡፡ 👉 ለእጣ ከመቅረቡ በፊት የቅድመ ኦዲት ስራ በመስራት የከተማ አስተዳደራችን አስፈላጊውን ሁሉ ጥንቃቄ በማድረግ በፍትሃዊነት ለህዝባችን እጣ መውጣት እንዲችልና ለዛሬ ቀን እንዲበቃ ማድረግ ችለናል፡፡ 👉 ይህ አይነት የዝርፊያና የህዝብን ሃብት ለግል ጥቅም የማዋል ዝንባሌና ተግባር በቤቶች ስራ ብቻ ሳይሆን በሌሎችም መስኮች ዋነኛ ፈተና ሆኖ ቀጥሏል፡፡ 👉 ሌብነትና ብልሹ አሰራር የብልፅግና ጉዟችን ዋነኛ ፀርና የምንመኘውን የህዝብ ፍትሃዊ ተጠቃሚነት እንዳናረጋግጥ ትልቁ ጋሬጣ ነው፡፡ 👉 የከተማችንም አስተዳደር ይህንን ከግምት በማስገባት የፀረ ሌብነት ትግሉ የቀጣይ ዋነኛ የርብርብ ማእከል በማድረግ እየተንቀሳቀሰ ነው፡፡ 👉 ህዝቡን እያሳተፍን ለሌብነት የማይመች ነባራዊ ሁኔታን በመፍጠር አስተማሪ እርምጃን እየወሰድንና ህዝባችንን በስፋት እያሳተፍን መሄዳችንን እንቀጥላለን፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ አወጣጥ ሥነ-ሥርዓት ተጀምሯል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለባለ ዕድሎች መልካም እድል ይመኛል
+4
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ አወጣጥ ሥነ-ሥርዓት ተጀምሯል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለባለ ዕድሎች መልካም እድል ይመኛል

ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ እየተገነባ ያለውን የተገጣጣሚ ቤቶች ግንባታ ያለበትን ደረጃ ጎብኝተዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የነዋሪዎችን የመኖርያ ቤት ችግር ለመፍታ
+6
ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ እየተገነባ ያለውን የተገጣጣሚ ቤቶች ግንባታ ያለበትን ደረጃ ጎብኝተዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የነዋሪዎችን የመኖርያ ቤት ችግር ለመፍታት የተለያዩ አማራጭ እቅዶችን በመንደፍ ወደ ስራ መግባቱ ይታወቃል፡፡ ከነዚህም መሃከል በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ እየተገነባ የሚገኘው የ10ሺህ ተገጣጣሚ ቤቶች ግንባታ ሞዳሊቲ አንዱ ሲሆን ይህ ፕሮጀክት በቦታው ላይ አጋጥሞ በነበረ የፍርድ ቤት እግድ ምክንያት ተቋርጦ የነበረና አሁን ግን በከፍተኛ ፍጥነት ግንባታው እየቀጠለ ያለ ፕሮጀክት ነው፡፡ ከንቲባዋም በቦታው ተገኝተው ግንባታው ስላለበት ሁኔታ የመስክ ምልከታ በማድረግ ግንባታው ስለሚፋጠንበት ሁኔታ የስራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡ ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘውም የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ዮናስ አያሌውም በበኩላቸው የተጀመሩትን ግንባታዎች ድርጅታቸው በአጭር ጊዜ ውስጥ እንደሚያጠናቅቅ ገልፀው አዳዲስ ብሎኮችንም በቅርቡ ውስጥ እንደሚጀምር ተናግረዋል፡፡ ከንቲባ አዳነች በዚሁ ወቅት የቤት ልማት ስራ መንግስት የተለያዩ አማራጮችን ማስቀመጡን አውስተው የቤት ፈላጊዎችና የግል ባለሃብቶች በነዚህ አማራጮች በመጠቀም በቤት ልማት ላይ ተሳትፎ ያደርጉ ዘንድ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ20/80 14ኛ ዙር እና የ40/60 3ኛ ዙር የጋራ መኖርያ ቤት እጣ በነገው እለት ህዳር 6/2015 ዓ/ም በይፋ ስነስርዓት ያወጣል፡፡ በዛሬው እለት በተሰጠው ጋዜጣ
+3
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ20/80 14ኛ ዙር እና የ40/60 3ኛ ዙር የጋራ መኖርያ ቤት እጣ በነገው እለት ህዳር 6/2015 ዓ/ም በይፋ ስነስርዓት ያወጣል፡፡ በዛሬው እለት በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የከተማ አስተዳደሩ የ20/80 14ኛ ዙር እና የ40/60 3ኛ ዙር የጋራ መኖርያ ቤት እጣ የማውጣት ስነስርዓት በነገው እለት ከሰዓት በኋላ ከ8 ሰዓት ጀምሮ እንደሚያካሂድ ተገልጿል፡፡ በመግለጫው ወ/ት ያስሚን ዋሃቢረቢ በምክትል ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ እንደገለፁት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሐምሌ 1/2014 ዓ.ም. የ20/80 14ኛ ዙር እና የ40/60 3ኛ ዙር የእጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓት በይፋ ማካሔዱ አስታውሰዋል ሆኖም ባጋጠመ የወንጀል ጥቆማ መሰረት በተደረገ ኦዲት እጣው ሙሉ ለሙሉ እንዲሰረዝ ተደርጎ በጉዳዩ የተጠረጠሩ አካላትም በህግ አግባብ እንዲጠየቁ መደረጉን አንስተዋል፡፡ በዚህም መሰረት በሁለቱም የጋራ መኖሪያ ቤት ፕሮግራም ማለትም በ20/80 18,930 ቤት እና በ40/60 6,843 ቤቶች በድምሩ 25,791 ቤቶች እጣ የሚወጣባቸው ሲሆን ቀደም ብሎ ከፍተኛ ጥያቄ ሲቀርብበት የነበረውን የባለ 3 ሶስት መኝታ ቤት ተመዝጋቢዎችን ጉዳይ ምላሽ ለመስጠት ተጨማሪ 300 መቶ ቤቶችን ቀሪ ስራ በማከናወን ለነባርና አዲሰ ተመዝጋበዎች በእጣ ለማስተላለፍ ዝግጁ መደረጉን ወ/ት ያስሚን ገልፀዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ከተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት አካሄዱ። የመወያያ ሰነዱም በዋናነት በሰላም የተገኘውን ድል በላብ ማፅናት ፣በ
+4
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ከተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት አካሄዱ። የመወያያ ሰነዱም በዋናነት በሰላም የተገኘውን ድል በላብ ማፅናት ፣በምግብ ዋስትና ራስን ለመቻል የከተማ ግብርናን ከሌማት ትሩፋት ተልዕኮ ጋር በማስተሳሰር ለስኬት መረባረብ በሚያችሉ አጀንዳዎች ሲሆኑ ፣ የሀገራችን ፈተና የሆነውን የዋጋ ግሽበትን መከላከል ፣ ለሠላም ስምምነቱ ተፈፃሚነት መረባረብ በሚያስችሉ አጀንዳዎች ዙሪያ ከነዋሪው ጋር ውይይት ተደርጓል። ውይይቱን የመሩት የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማጠቃለያው እንደተናገሩት ሠላም ሲኖር ነው ያሰብነውን የምናሳካው፣ሠላም ሲኖር ነው ሀገራችንን የምናበለፅገው በሠላም ያስመዘገብነውን ድል በኢኮኖሚው ዘርፍ በማፅናት ሀገር መገንባት ያስፈልጋል ሲሉ በኩታ ገጠም የተዘሩ አዝዕርቶችን ይበልጥ በማስቀጠል በምግብ ራስ የመቻል ስነልቦናን ማዳበር፣ከምንግዜውም በላይ ደግሞ ከሌማት ቱርፋት ስራዎች አንጻር ልዩ ትኩረት ሠጥቶ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጥላሁን አክለውም በክፍለ ከተማው እየተከናወኑ ያሉ የሌማት ትሩፋት የሆነው የሠብል ምርቶችን ለማስፋት አርሶአደሩን ማገዝ እንዲሁም በ90 ቀን የሚተገበሩ ተግባራትን ልዩ ክትትል በማድረግ የህብረተሰቡን ተሳትፎ ማሳደግ አስፈላጊ ነው ብለዋል።