በቅድስና | Beqidsina
"For God hath not called us unto uncleanness, but unto holiness.” — 1 Thes 4:7 Youtube.com/@beqidsina Tiktok.com/@beqidsina Instagram.com/beqidsina Feedback: @beqidsinafeedback_bot
Show more1 861
Subscribers
+524 hours
+37 days
+7230 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
Photo unavailableShow in Telegram
“ከማመስገን ጋር በጸሎት እየነቃችሁ ለእርሱ ትጉ፤”
— ቆላስይስ 4፥2
“Continue in prayer, and watch in the same with thanksgiving;”
— Colossians 4፥2 (KJV)
| @BEQIDSINA ✨
sʜᴀʀᴇ ◈JOIN◈sʜᴀʀᴇ
🥰 7👍 2❤ 2
"ድል ነው ሞት ላመነ በክርስቶስ፣
ድል ነው ምት ለዳነ በኢየሱስ።"
©Soreti Moges
https://youtu.be/Ry5LyNgUORU?si=rHrQxWbMrgxKU5Zn
ማለፊያ Malefiya || Soreti Moges (Official Lyric Video) 2023
በዚች ሕይወት ብቻ ክርስቶስን ተስፋ ያደረግን ከሆነ፥ ከሰው ሁሉ ይልቅ ምስኪኖች ነን።1ኛ ቆሮ 15:19 ገደለው ሞትን ራሱን ሰበረው መውጊያ ቀስቱን ዐወጀ ለኛ ፍጹም ሕይወት ባስፈራራን ላይ ጀገንንበት የትንሣኤው ንጉሥ ክርስቶስ ኢየሱስ አንተን ያመንን ዕለት ሞት ማለፊያ ጥቅም ኾነን ሐዘናችን የሚያቆምበት አንተን ያመንን ዕለት ይህ ሥጋችን ዐፈር ሲለብስ ወደ መጣበት ታች ሲመለስ ሕይወት አለ ገና የምንጀምረው ከድንኳን ኑሮ የተሻለው የትንሣኤው ንጉሥ ክርስቶስ ኢየሱስ አንተን ያመንን ዕለት ሞት ማለፊያ ጥቅም ኾነን ሐዘናችን የሚያቆምበት / የሚያበቃበት አንተን ያመንን ዕለት ድል ነው ሞት ላመነ በክርስቶስ ድል ነው ሞት ለዳነ በኢየሱስ
❤ 3🥰 1💯 1
Photo unavailableShow in Telegram
ጌታ ሆይ አንተን ለማስደሰት ከመፍጨርጨራችን እና ከመሮጣችን በፊት በአንተ መደሰት ይሁንልን። መኖሪያችን የሆንከውን የዘላለም አምላክ አንተን ከፊት ይልቅ ማወቅ ይሁንልን። ከስሜታችን በፊት የአንተን ስሜት፣ ከእውቀታችን በፊት የቃልህን እውቀት፣ ከፈቃዳችንም በፊት የአንተን ፈቃድ ማስቀደም ይሁንልን።
ከቃልህ ርቀን በብዙ እራሳችንን ወጋን፤ ፈቃድህን ላለመስማት ጆሮአችንን ዘግተን ግራ ቀኝ ጠፋብን፤ ስሜታችንን አስቀድመን አንተን በሚያሳዝን ነገር እኛ ድግስ ተጠራራን፤ አንተ ይገደል ይወገድ ያልከውን ነገር እኛ መባና መስዋዕት አድርገን አቀረብንልህ፤ እኔ ደስ የሚለኝ በዚህ ነው ያልከውን ገፋን ራቅን ተጸየፍን።
ያለ እውቀት የሆነውን ለአንተ መቅናታችንን አስወግድልን፤ ኃጢአታችን ብዙ ነውና ልክ የሌለውን ምህረትህን እኛ ላይ አብዛልን፤ ዛሬም የጸጋህ ጥገኞች አድርገን፤ ዝቅ ብለን ከአንተ መማር ይሁንልን፤ ያለ ልክ የተኮፈሰው ማንነታችን ልኩን ያግኝ፤ ትሁት ልብ ስጠን፤ በሕይወት ንጽሕና ባርከን፤ በሕይወትም በሞትም አንተን ብቻ ማክበር እና ማስከበር ይሁንልን።
| @BEQIDSINA ✨
sʜᴀʀᴇ ◈JOIN◈sʜᴀʀᴇ
🙏 32❤ 6👍 2👎 2🥰 2
Repost from N/a
Photo unavailableShow in Telegram
ሰላም ቤተሰብ✌️
ለናንተ ትልቅ ስጦታ አዘጋጅተናል። ከቤላ መልከ ፊደሎች መካከል "Bela Hidase Qedmo" የተባለውን መልከ ፊደል(Font) ከዛሬ ምሽት 2:00 ጀምሮ በነፃ አውርዳቹ መጠቀም ትችላላችሁ።
እስከዚያው ቴሌግራም ቻናላችንን እየተቀላቀሉ ይጠብቁን🤗
t.me/belagraph
ሌላ መልከ ፊደል ለመግዛት ካሰቡ እዚህ ያገኛሉ
t.me/belafonts_bot
Repost from GeezFonts
Photo unavailableShow in Telegram
ሰላም ቤተሰብ✌️
ለናንተ ትልቅ ስጦታ አዘጋጅተናል። ከቤላ መልከ ፊደሎች መካከል "Bela Hidase Qedmo" የተባለውን መልከ ፊደል(Font) ከዛሬ ምሽት 2:00 ጀምሮ በነፃ አውርዳቹ መጠቀም ትችላላችሁ።
እስከዚያው ቴሌግራም ቻናላችንን እየተቀላቀሉ ይጠብቁን🤗
t.me/belagraph
ሌላ መልከ ፊደል ለመግዛት ካሰቡ እዚህ ያገኛሉ
t.me/belafonts_bot
"እዳዬን ክፍሎታል በመስቀሉ ስራ፤
ቀና ብዬ ልሂድ ከእንግዲህ በኋላ።
እርሱ ሞቷልና ነፍሴ አመለጠች፤
ከዘላለም ጥፋት እንደወጣች ቀረች።
ፍቅር ነው እግዚአብሔር የሌለበት ወረት፤
ዘውትር ግድ የሚለው የኃጢአተኛው ሞት።
ምህረቱ ብዙ ነው እኔን አድኖኛል፤
ዳግም ፊቱ እንድቆም እድልን ሰቶኛል።
አምላክ ባይደርስልኝ እኔስ የት ነበርኩኝ፤
ግን ምረቱ በዝቶ በቤቱ አለሁኝ፤
አመሰግናለሁ ስለሆነልኝ፤
እግዚአብሔር ምህረቱን አገነነልኝ።
እዳዬን ከፍሎታል በመስቀሉ ስራ፤
ቀና ብዬ ልሂድ ከንግዲ በኋላ።
እርሱ ሞቷልና ነፍሴ አመለጠች፤
ከዘላለም ጥፋት እንደወጣች ቀረች።
የአንዲቷ በግ መጥፋት እጅግ ግድ የለዋል፤
መልካሙ እረኛ ፍለጋ ይወጣል።
እንዲህ ነው ያዳናት ነፍሴን ከሞት መንደር፤
ጌታ ባይደርስልኝ ተረት ሆኜ ነበር።
አጥቦ አና አንፅቶ አዲስ ሰው አረገኝ፤
ይሄ ነው የምለው ውብ ታሪክ የታለኝ።
አውቃለሁኝና ማን እንደነበርኩኝ፤
የደስታን ዜማ ሁሌ አፈሳለሁ።
አውቃለሁኝና ማን እንደነበርኩኝ፤
የደስታን ለቅሶ ሁሌ አነባለሁኝ።
አወቃለሁኝና ማን እንደነበርኩኝ፤
የደስታን ዜማ ሁሌ አዜማለሁ"
©Dawit Getachew
| @BEQIDSINA ✨
sʜᴀʀᴇ ◈JOIN◈sʜᴀʀᴇ
❤ 11👍 3
Photo unavailableShow in Telegram
"ዕዳዬን ከፍሎታል በመስቀሉ ሥራ፣
ቀና ብዬ ልሂድ ከእንግዲህ በኋላ፤
እርሱ ሞቷልና ነፍሴ አመለጠች፣
ከዘላለም ጥፋት እንደወጣች ቀረች።"
| @BEQIDSINA ✨
sʜᴀʀᴇ ◈JOIN◈sʜᴀʀᴇ
❤ 14👍 3
Photo unavailableShow in Telegram
የክርስቶስ ምትካዊ ሞት የክርስትናም የክርስቲያን መሰረታዊ ጉዳይ ነው። የእግዚአብሔር ፍጹም ቍጣ ፍጹም እና እንከን አልባው በግ ላይ አረፈ፤ ዘላለማዊው ሊቀ ካህናት ወደ ቅድስተ ቅዱሳን ይዞ የገባው የራሱ ፍጹሙ የስርየት ደም ለአንደና ለዘላለም ተቀባይነትን አገኘ፤ መንፈስ ቅዱስንም በመላክ ይህን አረጋገጠልን። እዚህ ነው የተመሠረተው ክርስትና፤ ቤተክርስቲያን ጥንት መሠረቷ ይሄ ነው። ከዚህ ውጪ ወንጌል የላትም፤ ክብሯ የክርስቶስ ሞትና ትንሳኤ ነው፤ ተስፋዋም የሙሽራዋ መምጣት ብቻ ነው።
| @BEQIDSINA ✨
sʜᴀʀᴇ ◈JOIN◈sʜᴀʀᴇ
👍 12🥰 8❤ 1