6 971
Subscribers
No data24 hours
-367 days
-20230 days
Posts Archive
6 971
ዳኛው
ለዳኝነት የተቀመጡ ዳኞች ከፊታቸው ስለቆመው ተከሳሽ፣ ዓቃቤ ህጉ ከሚዘረዝረው የጥፋት ዝርዝር ወይም 'አላጠፋም' ብሎ ከሚሟገተው ጠበቃ ውጪ የሚያውቁት ምንም ነገር የለም። በመጨረሻም ዳኞቹ የሁለቱንም ሙግትና ያቀረቡትን ማስረጃ መርምረው ሲያበቁ (ግራና ቀኝ ይባላል) የመሰላቸውን ውሳኔ ይሰጣሉ።
መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር ዳኛ እንደሆነ ይናገራል። ያውም እውነተኛ ዳኛ። አንድ ቀን የሰው ፍጥረት የሆንን ሁሉ እርሱ በዳኝነት በተሰየመበት ዙፋን ፊት እንደምንቆም ይናገራል። ነገር ግን እግዚአብሔር ፍርድ ለመስጠት ግራና ቀኙን መስማት ወይም ምስክር መጥራት አያስፈልገውም። ምክንያቱም ያደረግነውን ሁሉ ያደረግነው በግላጭ ዓይኑ እያየ ስለሆነ በእውነት ይፈርዳል። ደግሞም ማድረጋችንን ብቻ ሳይሆን ለምንና እንዴት እንዳደረግነው የውስጥ ሀሳባችንን እንኳን ያውቃል።
አሁን ጥያቄው እግዚአብሄር ዳኛ ነው ወይ የሚለው ሳይሆን ሁሉ በፊቱ በተገለጠ ዳኛ ፊት ከፍርድ የምናመልጥበት መንገድ አለ ወይ የሚለው ነው፤ ሁላችንም በድልናልና።
ሮሜ 8፡1 "እንግዲህ በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን ኵነኔ የለባቸውም" ይላል። እንዲሁም
ዮሐንስ 3:18 በእርሱ (በክርስቶስ ኢየሱስ) በሚያምን አይፈረድበትም፤ በማያምን ግን በአንዱ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ስላላመነ አሁን ተፈርዶበታል' ይላል።
ስለዚህ ምንም እንኳ በደለኛ ብንሆንም ከፍርድ/ከኩነኔ መዳኛና ምህረትን ማግኛው ዳኛው የሰጠው ብቸኛው መንገድ በእኛ ምትክ በሞተልን በልጁ በጌታ ኢየሱስ ማመን ነው ብሎናል።
ተከሳሽ ነህ። እናስ ንጹህ ነኝ ብለህ በዚህ ዳኛ ፊት ትሟገታለህ ወይንስ ኃጢያተኝነትህን አውቀህ በተሰጠህ የምህረት ማግኛ መንገድ ለመጠቀም ዛሬ በልጁ ታምናለህ?
ምን ትላለህ? ምርጫው የአንተ ነው።
6 971
ውረድ ከመስኮቱ
መስኮቱ ላይ ተለጥፋ
ጥቂት ቀናቶቿን ስታድፋፋ
ወይ ወጥታ አትወጣ
ወይ ዞር ዞር ብላ
አትፈላልግ የሚበላ
መስኮቱ ላይ ተንጠልጥላ
ጥዝ! ጥዝ! ትላለች
ሰው ያሳመረውን የሰው ጓሮ እያየች።
ዓይኑ መች አነሳት ያያል አሳምሮ
አንገት አጣች እንጂ የሚያይላት ዞሮ።
አለሁ አለሁ ስትል
አለች ብለው ሲሏት
ጥዝ! ጥዝ! እያለች
እዛው መስኮቱ ላይ ደርቃ ትገኛለች።
መስኮቱ ላይ ተለጥፎ
ዛሬን ገድሎ ሲጥል ነገን ተደግፎ
ውጪ ውጩን እያየ በሃሳብ ይዞራል
ጥዝ! ጥዝ! እያለ
Share Like እያረገ ዕድሜውን ይፈጃል።
ወይ የራሱ የለው ተነስቶ አይሰራ
እንጨት አያቀብል ሌላው ሰው ሲሰራ
ወይ ቃሉን አያነብብ
ወይ አይንበረከክ
መስኮት ላይ ተሰቅሎ ጣቶቹን አሹሎ
የቦዙ ዓይኖቹን ከስልኩ ላይ ተክሎ
ሰው የለጠፈውን ሲሰጥ ተቀብሎ
ማን ሰው በነገረው ስለእነ አቶ ከንቱ
አለሁ አለሁ ሲሉ ያሉ እየመሰሉ
ፖስት እየፖሰቱ ጥዝ! ጥዝ! እያሉ
ጊዜአቸውን ገድለው ስንቶች በቁም ሞቱ
በል አንተም ይቅርብህ ውረድ ከመስኮቱ::
ጊዜወርቅ 10/2022
6 971
የገና በአል የማይከበርባቸው ሃገሮች
ቻይና የገና በዓልን ከማያከብሩ የዓለማችን ሀገራት መካከል ዋነኛዋ ስትሆን ዕለቱም እንደሌሎች የስራ ቀን ተብሎ ያልፋል።
ቻይና በይፋ ሀይማኖት የሌላት ሀገር ስትሆን የገናን በዓል ማክበርም ህገወጥነት ነው ተብሏል።
አፍጋኒስታን ሌላኛዋ የገናን በዓል የማታከብር ሀገር ስትሆን አብዛኛው የሀገሪቱ ዜጎች ሙስሊሞች መሆናቸው ለበዓሉ አለመከበር ዋነኛው ምክንያት እንደሆነ ተገልጿል።
ሰሜን አፍሪካዊቷ አልጀሪያ ሌላኛዋ የገና በዓል የማይከበርባት ሀገር ስትሆን በተለይም ከቅኝ ግዛት ነጻ ከወጣችበት ከፈረንጆቹ 1962 ጀምሮ የገናን በዓል አክብራ አታውቅም።
98 በመቶ የእስልምና እምነት ተከታዮች ህዝብ ያላት ኮሞሮስ የገናን በዓል የማታከብር ሌላኛዋ የዓለማችን ሀገር ናት።
ሊቢያ እና ሞሪታንያ የገና በዓል የማይከበርባቸው ተጨማሪ የአፍሪካ ሀገራት ሲሆኑ የክርስትና ዕምነት ተከታዮች አለመኖር ደግሞ ለበዓሉ አለመከበር ዋነኛው ምክንያት ነው ተብሏል።
እስያዊቷ ሞንጎሊያ የገና በዓል የማይከበርባት ስትሆን የሀገሪቱ ዜጎች የቡድሂስት እምነት ተከታዮች ናቸው ተብሏል።
ሌላኛዋ የኢየሱስ ክርስቶች ልደት ወይም ገና የማይከበርባት ሀገር አመጸኛዋ ሰሜን ኮሪያ ናት። በዚህ ሀገር የገናን በዓል ማክበር ለእስር እና ተጨማሪ ቅጣት መደንገግ የሚያስችል ህግ ማውጣቷ ተገልጿል።
ፓኪስታን ሌላኛዋ ገናን የማታከብር የዓለማችን ሀገር ስትሆን ዓለም በታህሳስ 25 በየዓመቱ የገናን በዓል ሲያከብር እሷ ግን የፓኪስታን መስራች የሚባሉትን መሀመድ አሊ ጅናህን አስባ ትውላለች።
በነዳጅ ሀብቷ የምትታወቀው ሳውዲ አረቢያ የገናን በዓል ማክበር የከለከለች ሀገር ስትሆን በዓሉን የሚያመለክት የገና ዛፍ እና ሌሎች መሰል ድርጊቶችን ማከናወን እና በንግድ ቦታዎችም ይዞ መገኘት እንዲሁም መሸጥ ለቅጣት ይዳርጋል ተብሏል።
ከሰሞኑ ከወደብ ስምምነት ጋር በተያያዘ ከኢትዮጵያ ጋር ግጭት ውስጥ መግባቷን የገለጸችው ጎረቤት ሀገር ሶማሊያም የገና በዓል ከማይከበርባቸው ሀገራት መካከል ዋነኛዋ ተብላለች፡፡
ይህች የምስራቅ አፍሪካ ሀገር ከፈረንጆቹ 2009 ጀምሮ የገና በዓል በሀገሯ እንዳይከበር በይፋ በህግ ያገደች አፍሪካዊት ሀገር እንደሆነች ተገልጿል።
ከሶማሊያ በተጨማሪም ታጃኪስታን፣ ቱኒዝያ፣ኡዝበኪስታን እና የመን የገና በዓል በሀገራቸው እንዳይከበር ህግ የደነገጉ እና ሲያከብሩ የተገኙ ዜጎችን ከሚቀጡ ሀገራት መካከል ዋነኞቹ ናቸው።
ምንጭ:አልአይን
6 971
ቀና ያድርግህ
ክፉ መንፈስ አድሮባት ለ18 ዓመታት የጎበጠች ሴት ነበረች። ገብቶ ማደሩ ሳያንሰው የክፋቱ ክፋት ማጉበጡ።
የጎበጠ ሰው የፊቱን እያየ በትክክል መጓዝ አይችልም። ደግሞም አካላችን እንደ እንስሳት አጎንብሰን እንድንሄድ አልተፈጠረምና ስንጐብጥ የሰውነት ሚዛናችንን መጠበቅ አይሆንልንም። ከዚህም በላይ ይህች ሴት ቀና ባሉ ሰዎች መካከል ስትቆም የሚሰማትንም የበታችነትን ስሜት አስቡት። አካላዊ ብቻ ሳይሆን የውስጥ ስብራትን የሚያመጣ መንፈሳዊም ነበር።
ኢየሱስም ባያትጊዜ "አንቺ ሴት ከድካምሽ ተፈትተሻል" አላትና እጁን ጫንባት፤ ያን ጊዜም ቀጥ አለች፣ እግዚአብሔርንም አመሰገነች።
የድሮ ሰይጣን የለምና ይህ የድሮ ታሪክ ብቻ አይደለም። ዛሬም ያለ ፍጥረታችን በሰዎች ፊት በበታችነት ስሜት እንድንሆን፣ በድካም ተተብትበን ነገአችንን ቀና ብለን ማየት እንዳንችል፣ ከሞቱት በላይና በሕይወት ካሉት በታች እያለን እንደሌለን የሚያደርግ የክፉ አሰራር አለ።
ኢየሱስ ያቺን ሴት ባያት ጊዜ ከድካሟ ፈትቶ ቀና እንድትል እጁን እንደጫነባት ይኼ ጌታ ዛሬም ያው ብርቱ ነውና ከድካማችሁ ፈትቶ ነገን በእርግጠኝነት እያያችሁ ቀና ብላችሁ እንድትጓዙ ቀና ያደርጋችሁ።
ለዕለተ እሁድና ለብርሃነ ልደቱ በዓል መልካም ምኞቴ ነው። ሉቃስ ምዕ13 ከ10-13
ጊዜወርቅ 2024
@Bruh_Tesfa
6 971
ቃለ መጠይቅ ከኖህ ጋር
ጥ. የሰው ሁሉ ክፋት በምድር ላይ በበዛበት ዘመን ብቻህን በእግዚአብሔር ፊት በጽድቅ ስለመገኘትህ ምን ትላለህ?
መ. የሚገርመኝ የእኔ ሳይሆን እርሱ እኔን ብቸኛውን ማየቱ ይደንቀኛል።
ጥ. መርከብን የሚያክል ፕሮጀክት እንድትሰራ አንድ አንተን ስለመምረጡስ?
መ. በጽድቅ መመላለስ ለራስ ነው። ፈልግ ቢያጣ እኔን ለአደራው አሰበኝ።
ጥ. ለመሆኑ ስላንተ የተፃፈውን አስደናቂ ታሪክህን አንብበኸዋል?
መ. አላነበብኩትም ግን ኖሬዋለሁ።
ጥ. በደረቅ ምድር መርከብ የሚሠራ የዘመኑ ምርጥ ሞኝ ብለው ሲሉህ ምላሽህ ምን ነበር? መ. የሰደቡኝ የሰማሁትን ስላልሰሙ ነው።
ጥ. እግዚአብሔር ግን የፈጠረውን ሰው ሁሉ በውሃ ሲያጠፋ ልክ ነው ትላለህ?
መ. እርሱ መቼ አጠፋቸው? ከጥፋት ሊያድናቸው መርከብ ቢያዘጋጀላቸውም በምርጫቸው አንገባም ብለው ጠፉ እንጂ።
ጥ. የመጨረሻ ጥያቄ። ለእኛስ ትውልድ ምን ትመክረናለህ?
መ. 2 ነገሮች። 1ኛ ብቻህንም ቢሆን በጽድቅ መንገድ ሂድ፣ የሚያይህ አለና። 2ተኛ ዛሬም ሊመጣ ካለው የዘላለም ጥፋት ሰውን ሊያድን እግዚአብሔር ያዘጋጀው መርከብ አለ። በልጁ አምኖ መዳን። አላምን ካሉ ግን ዛሬም በምርጫቸው በሲኦል የዘላለም ጥፋት ይሆንባቸዋል።
ጊዜወርቅ 2024
@Bruh_Tesfa
6 971
ለሂደቱ ኑሩ!
"በምትጎነጯት አንድ ሲኒ ቡና ውስጥ ድስታን ማግኘት ካልቻላችሁ፣ በእርግጥም አቅዳችሁ በምትወጡት ሽርሽር ውስጥም ልታገኙት አትችሉም።" ከዚህም አንፃር ትልቁ ወሳኝ ነገር የሚገኘው በጥቃቅኖቹ ክስተቶች ውስጥ እንደሆነ እንረዳለን። ዋነኛው የደስታችሁ ምንጮ ምንም ቢሆን ዘላቂና ትርጉም ሰጪ ካልሆነ ደስታችሁ እንደ ሰማይ ጉም ወዲያው ተኖ የሚጠፋ ነው። አስር መዳረሻ ቢኖራችሁ አስሩም ስፍራ መድረስ ብትችሉ እንኳን ውስጣችሁን ልታረኩት አትችሉም። የሰው ልጅ ተፈጥሮው በጉዞው እንዲደሰት እንጂ በመዳረሻው ተደስቶ እንዲቆም የሚያደርገው አይደለም። የፍቅር ህይወታችሁን ተመልከቱ ፍቅር የጀመራችሁ ሰሞን ብቻ በመደሰት የሚቆም ጉዞ አይደለም፣ እያንዳንዱን ነገር ከፍቅር አጋራችሁ ጋር በምታሳልፉት ጊዜ ደስተኛ በመሆንና በበጎ መንገድ በመረዳት የማሳለፍ ሃላፊነት ትወስዳላችሁ።
አዎ! ለሂደቱ ኑሩ! ለሂደቱ እራሳችሁን ስጡ። የጀመራችሁትን ለመጨረስ አትቸኩሉ ይልቅ ከጅማሯችሁ ቦሃላ ያለውን እንያዳንዱን እንቅስቃሴ በፍቅር የማጣጣም ልማድን ፍጠሩ። በየቀኑ ለምታወጡት ወጪ፣ በየቀኑ ጊዜያችሁን ለምትሰጡት፣ ትኩረት ለምታደርጉበት ነገር ዋጋ ስጡ። ህይወት የቅፅበታት ጥርቅም እንጂ የአንድ ጉዞ መጨረሻ አይደለችም። የትኛውም መዳረሻችሁ የየእራሱ ቀዳሚ እርምጃ አለው፣ ከየትኛውም ፍፃሜ በፊት ጅሜሬ አለ ቀጥሎም ሂደት አለ። በህይወት ዘመናችሁ ሙሉ አንድን ነገር እየጠበቃችሁ በእርሱ ለማረፍ፣ በእርሱ ለመደሰት፣ በእርሱም ሰላማችሁን ለማግኘት የምትጠባበቁ ከሆነ ጥበቃችሁ ከንቱ እንደሆነ ተረዱ። በሂደቱ ዋጋችሁን ጨምሩ፣ በምትወጡት ደረጃ እራሳችሁን አጠንክሩ።
ህይወትህን በመዳረሻህ ውስጥ አትፈልገው፤ እውነተኛውን ደስታህን የሆነ ጊዜ በምታገኘው ገንዘብ፣ የሆነ ጊዜ በምታፈራው ንብረት ውስጥ እንደምታገኘው እርግጠኛ አትሁን። የሁሉም ሰው የህይወት ዘመን ትልቁ ስኬት ደስተኛ ህይወት መኖር መቻል ነው። ያሰብክበት ለመድረስ በምታደርገው ጥረት ምንያክል ደስተኛ እንደሆንክ መርምር፣ አንዱን በመተው ሌላውን በማጥበቅ የምርም ህይወትህ ስለመቀየሩ አጥና። ሂደቱን ስትወደው ውድቀትህ አይሰብርህም፣ በጉዞህ ስትማረክ በማጣትህ አትጨነቅም፣ በሚገጥምህ ችግርም ተስፋህን አታጣም። ዋናው ጉዳይህ መዳረሻህ ሳይሆን ከመዳረሻህ የሚቀድመው ጉዞህ እንደሆነ በጉልህ ተረዳ።
ከምርጥ ጽሁፍ
6 971
የሽልማት ጥያቄ
በዋናው በር ለመግባት የመግቢያውን ቁልፍ ይወቁ። ቁልፉ 4 የእንግሊዘኛ ፊደሎችንና 3 ቁጥሮችን ይዟል። የሚስጥር ቁልፉንና ቁልፉ የሚያመለክተውን መልዕክት ያገኙ የመጀመሪያዎቹ 10ሩ ተሳታፊዎች እያንዳንዳቸው የ1,000 ብር ሽልማት አሸናፊ ይሆናሉ። መልሱንና አሸናፊዎችን በ7/4/2016 እናሳውቃለን።
ማስታወሻ፡- ከA - D ላሉት የሚያገኙት መልስ ከA-Z የእንግሊዘኛ ፊደሎችን ቆጥረው ቁልፍ ፊደሉን እንዲያገኙ የሚጠቁሙ ናቸው። ከ1 - 3 ላሉት ደግሞ የሚያገኙትን መልስ እንዳለ ይጠቀሙበት። በአንድ ቁልፍ 1 ፊደል ወይም 1 አሃዝ (digit) ብቻ።
መፍቻ
ቁልፍ A=ሁለት ወላጆችን ጨምሮ በአንድ ቤተሰብ ውስጥ 6 ወንድ ልጆችና እያንዳንዱ ወንድ ልጅ ደግሞ ሁለት ሁለት እህቶች አሏቸው። የቤተሰቡ ብዛት ስንት ነው።
ቁልፍB=[1,5,7] [6,8,20] [8,11,27] [X,12,42] በዚህ pattern መሠረት X ስንት ነው?
ቁልፍC=ሲያጋድሙኝ እትዬለሌ ነኝ፣ ለሁለት ሲቆርጡኝ ደግሞ ምንም ነኝ።
ቁልፍD=አባት፣ እናት፣ ወንድና ሴት ልጅ ወንዙን በጀልባ መሻገር አለባቸው። ለ1 የጀልባ ጉዞ አባት 1፣ እናት 2፣ ወንዱ 6 እና ሴቷ 7ብር ይከፍላሉ። ጀልባው 2 ሰው ይይዛል፤ ለሁለት ሲጓዙ ክፍያው ከሁለቱ በሚበልጠው ሂሳብ ነው። ሁሉንም ለማሻገር ቢያንስ ስንት ብር ያስፈልጋቸዋል?
ቁልፍ1= 3 ብርቱካን ልገዛ 30 ብር ስከፍል 7.5 መልስ ሰጡኝ። የ1 ብርቱካን፣ 2 ሙዝ እና 3 ሎሚ ዋጋ ድምር 40.5 ነው። 1 ሙዝ በምገዛበት ዋጋ 4 ሎሚ ገዛለሁ። የ1 ሎሚ ዋጋ ስንት ነው?
ቁልፍ2=1
ቁልፍ3=የሂሳብ መምህር ሲወጣ የtime management አስተማሪ ገብቶ ‘8+10 ስንት ነው?’ አለን። ስንት ነው?
6 971
“ጌታን ተቀበል” የሚሉ ጥሪዎችን እዚህም እዚያም እንሰማለን። ለጥሪውም ብዙ ዓይነት ምላሾች ይሰጣሉ። ጌታን ማን ለማን ያቀብላል? ጌታን መቀበል ምን ማለት ነው? ደግሞስ ሰው ጌታን/አምላክን ሊቀበል ይችላል? ጉዳዩ ጌታን የመቀበል ጥሪ ወይንስ ሃይማኖቴን ተቀበል የሚል ጥሪ? አሁን የያዝኩት ሃይማኖቴስ? ወዘተ
ከዚህ ቁልፍ ጥቅስ በመነሣት የማውቀውን ላካፍላችሁ፦
“ለተቀበሉት ሁሉ ግን፣ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው” ዮሐንስ ወንጌል ምዕ1 ቁ.12
‘ጌታን ተቀበል’ ጥሪ የሰው እጅ የሌለበትና አምላክ ራሱ ለሰው ልጆች ያቀረበው ጥሪ ነው። የሰዎች ድርሻ የጥሪ ወረቀትን የማደል ያህል ብቻ ነው።
ጌታን መቀበልና ማመን ማለት “አዎን አንተ የዓለም ሁሉ ፈጣሪና ጌታ ነህ፣ አሁን ግን ጌታዬ ሁን” ብለን ፈቃዳችንን የምንሰጥበት ነው። ልዩነት አለው።
ስንቀበል ለእኛ እንጂ ለጌታ የሚጨመርለት ነገር የለም፣ እርሱ ሙሉ ነውና። ለእኛ ግን የእግዚአብሔር ልጅነትን ማግኘት ይሆንልናል። አስቡት በመቀበል የእግዚአብሔር ልጅ መሆን። ስትቀበል ‘ልጅ ትሆናለህ ካለ ካልተቀበልክ ‘ፍጥረቱ እንጂ ‘ልጅ’ አይደለህም ማለት ነው።
ጌታ፣ ልጁ በመሆን ወደሚገኝ የዘላለም ሕይወት እንጂ ወደ አንድ ሃይማኖት ፈጽሞ አልጠራንም።
ልጅነት ጌታን በመቀበልና በማመን እንጂ በአባልነት የሚገኝ አይደለም።
“በእርሱ በሚያምን አይፈረድበትም፤ በማያምን ግን በአንዱ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ስላላመነ አሁን ተፈርዶበታል።” ዮሐንስ ወንጌል ምዕ3 ቁ.18
እሺም ይሁን እንቢ፣ ምላሻችንን የምንሰጠው የጥሪውን ወረቀት ላቀበለን ሰው ሳይሆን በልጁ ልጅ እንድንሆን ጥሪ ለላከልን ለሰማይና ምድር ጌታ ነው።
6 971
“ጌታን ተቀበል” የሚሉ ጥሪዎችን እንሰማለን። ለጥሪውም ብዙ ዓይነት ምላሾች ይሰጣሉ። ጌታን ማን ለማን ያቀብላል? ጌታን መቀበል ምን ማለት ነው? ደግሞስ ሰው ጌታን/አምላክን ሊቀበል ይችላል? ጉዳዩ ጌታን የመቀበል ጥሪ ወይንስ ሃይማኖቴን ተቀበል የሚል ጥሪ? አሁን የያዝኩት ሃይማኖቴስ? ወዘተ
ከዚህ ቁልፍ ጥቅስ በመነሣት የማውቀውን ላካፍላችሁ፦
“ለተቀበሉት ሁሉ ግን፣ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው” ዮሐንስ ወንጌል ምዕ1 ቁ.12
ይህ ጥሪ የሰው እጅ የሌለበትና አምላክ ራሱ ለሰው ልጆች ያቀረበው ጥሪ ነው። የሰዎች ድርሻ የጥሪ ወረቀትን የማደል ያህል ብቻ ነው።
ጌታን መቀበል ማለት “አዎን አንተ የዓለም ሁሉ ፈጣሪና ጌታ ነህ፣ አሁን ግን ጌታዬ ሁን” ብለን ፈቃዳችንን የምንሰጥበት ነው። ልዩነት አለው።
ስንቀበል ለእኛ እንጂ ለጌታ የሚጨመርለት ነገር የለም፣ እርሱ ሙሉ ነውና። ለእኛ ግን የእግዚአብሔር ልጅነትን ማግኘት ይሆንልናል። አስቡት በመቀበል የእግዚአብሔር ልጅ መሆን። ስትቀበል 'ልጅ' ትሆናለህ ካለ ካልተቀበልክ 'ፍጥረቱ' እንጂ ልጅ አይደለህም ማለት ነው።
ጌታ፣ ልጁ በመሆን ወደሚገኝ የዘላለም ሕይወት እንጂ ወደ አንድ ሃይማኖት ፈጽሞ አልጠራንም።
ልጅነት በመቀበልና በማመን እንጂ በአባልነት የሚገኝ አይደለም።
“በእርሱ በሚያምን አይፈረድበትም፤ በማያምን ግን በአንዱ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ስላላመነ አሁን ተፈርዶበታል።” ዮሐንስ ወንጌል ምዕ3 ቁ.18
እሺም ይሁን እንቢ፣ ምላሻችንን የምንሰጠው የጥሪውን ወረቀት ላቀበለን ሰው ሳይሆን ልጁ እንድንሆን ጥሪ ለላከልን ጌታ ነው።
6 971
አፍ
ራስን መግዛት ሲያቅት
ሲፈላ ደም ፍላት
መናገሪያነቱ ሥራው ሲያንስበት
ፍጥረቱን ቀይሮ አፍ ጆሮን ይሆናል
መናገር መስማትን በአንድ ይጠቀልላል።
ማቆሚያ ካልሰጡት
ገደብ ካላስያዙት
ከአንደበት ጋራ ክፉ ይወዳጅና
ሊራገጥ ይነሳል እግር ይሆንና።
ጊዜወርቅ 2004
@Bruh_Tesfa
6 971
የሽልማት ጥያቄ
ዋናውን በር ከፍቶ ለመግባት ትክክለኛውን የመግቢያ ቁልፍ ማወቅ ይጠይቃል። ቁልፉ 4 የእንግሊዘኛ ፊደሎችንና 3 ቁጥሮችን የያዘ ሲሆን በትክክለኛው ቅደም ተከተል መቀመጥም አለባቸው። የሚስጥር ኮዱን በመፍታት ቁልፉን ሲያገኙ ያገኙትን ቁልፍና ቁልፉ የሚያመለክተውን መልዕክት ይፃፉ። ቁልፉን ከነመልዕክቱ መጀመሪያ ላገኙ 10ሩ እያንዳንዳቸው የ1,000 ብር ሽልማት አሸናፊ ይሆናሉ።
ማስታወሻ፡ ከA እስከ D ላሉት የሚያገኙት መልስ ከA እስከ Z ካሉት የእንግሊዘኛ ፊደሎች ቆጥረው እንዲያገኙ የሚጠቁሙ ናቸው። ከ1 እስከ 3 ላሉት ደግሞ የሚያገኙትን መልስ እንዳለ ይጠቀሙበት። በአንድ ቁልፍ አንድ ፊደል ወይም አንድ አሃዝ (digit) ብቻ።
የሚስጥር ኮዱን መፍቻቁልፍ A= ሁለት ወላጆችን ጨምሮ በአንድ ቤተሰብ ውስጥ 6 ወንድ ልጆችና እያንዳንዱ ወንድ ልጅ ደግሞ ሁለት ሁለት እህቶች አሏቸው። የቤተሰቡ ብዛት ስንት ነው።
B= የጎደለው ቁጥር (X) ምንድነው? 1,5,7 | 6,8,20 | 8,11,27 | X,12,42
C= ሲያጋድሙኝ እትዬለሌ ነኝ፣ ለሁለት ሲቆርጡኝ ደግሞ ምንም ነኝ።
D=አባት፣ እናት፣ ወንድና ሴት ልጅ 4ቱም ወንዙን በፍጥነት በጀልባ መሻገር አለባቸው። አባት 1 ደቂቃ፣ እናት 2፣ ወንዱ 6 እና ሴቷ 7 ደቂቃ ይፈጅባቸዋል። ጀልባው 2 ሰው መያዝ ስለሚችል ሁሉም ሊሻገሩ የሚችሉበት ፈጣን ደቂቃ ስንት ነው?
1= 3 ብርቱካን ልገዛ 30 ብር ስከፍል 7.5 መልስ ሰጡኝ። የ1 ብርቱካን፣ 2 ሙዝ እና 3 ሎሚ ዋጋ ድምር 40.5 ነው። 1 ሙዝ በምገዛበት ዋጋ 4 ሎሚ ገዛለሁ። የ1 ሎሚ ዋጋ ስንት ነው?
2=1
3= የሂሳብ አስተማሪያችን እንደወጣ የbusiness management አስተማሪ ገብቶ ‘8+10 ስንት ነው?’ አለን። ስንት ነው?
6 971
ልደት ቀን ሲከበር ሁለም እንደሚያውቀው
ቀኑ ስለሆነ ልጁ ደስ እንዲለው
ይህ ቀረ ሳይባል አቅም በፈቀደ ሁለም ይደረጋል
ስሙ እየተጠራ ይዘመርለታል
ባለልደቱ ልጅ ከመሀል ላይ ቆሞ
እንደ ንጉስ ሆኖ አምሮና ተውቦ
መልካም ልደት ሲባል ዙሪያውን ተከብቦ
በልጆች ጨዋታ በወላጆች ደስታ
ተከብሮ ይውላል ደምቆ በስጦታ
ልጁም ደስ ይለዋል፣ ክብር ይሰማዋል
ምነው በዓመት ሶስቴ በተወለድኩ ይላል።
እናም ብርሃነ ልደቱ 'ገና' መጣ ሲባል
ታላቅ ዓውደ ዓመት ትልቅ ክብረ በዓል
በኢትዮጵያ አሜሪካ በምድር ዙሪያ ጭምር
የሚወደድ ዕለት፣ በድምቀት ሚከበር
ቤቱ ሞቆ… ውጩ ደምቆ
ከተማው መንገዱ ሲብለጨለጭ መብራት
ሻጭና ሸማቹ የሚናጠቁበት
ሽር ጉድ ይባላል ሁሉም ደስ ብሎታል
የኢየሱስ ልደት ሚከበር ይመስላል
ሳንታ እንደሆን እንጂ ልጁ ግን ተረስቷል::
ባለልደቱ ልጅ መሃል ባልቆመበት
ባዕድ ባዕድ መዝሙር 'ኢየሱስ' የሌለበት
ሲበላ ሲጠጣ በጥፋት ላይ ጥፋት
ባዶ የልደት ቀን የከሰረ ዓውደ ዓመት።
ያንን ባለልደት፣ በሩ ተዘግቶበት ውጪ የቆመውን
‘ልደትህ እንዴት ነበር?’
ብዬ ብጠይቀው ምን ይመልስ ይሆን?
6 971
ልደት ቀን ሲከበር ሁለም እንደሚያውቀው
ቀኑ ስለሆነ ልጁ ደስ እንዲለው
ይህ ቀረ ሳይባል አቅም በፈቀደ ሁለም ይደረጋል
ስሙ እየተጠራ ይዘመርለታል
ባለልደቱ ልጅ ከመሀል ላይ ቆሞ
እንደ ንጉስ ሆኖ አምሮና ተውቦ
መልካም ልደት ሲባል ዙሪያውን ተከብቦ
በልጆች ጨዋታ በወላጆች ደስታ
ተከብሮ ይውላል ደምቆ በስጦታ
ልጁም ደስ ይለዋል፣ ክብር ይሰማዋል
ምነው በዓመት ሶስቴ በተወለድኩ ይላል
እናም ብርሃነ ልደቱ ገና መጣ ሲባል
ታላቅ ዓውደ ዓመት ትልቅ ክብረ በዓል
በኢትዮጲያ አሜሪካ በምድር ዙሪያ ጭምር
የሚወደድ ዕለት፣ በድምቀት ሚከበር
ቤቱ ሞቆ… ውጩ ደምቆ
ከተማው መንገዱ ሲብለጨለጭ መብራት
ሻጭና ሸማቹ የሚናጠቁበት
ሽር ጉድ ይባላል ሁሉም ደስ ብሎታል
የኢየሱስ ልደት ሚከበር ይመስላል
ሳንታ እንደሆን እንጂ ልጁ ግን ተረስቷል
ባለልደቱ ልጅ መሃል ባልቆመበት
ባዕድ ባዕድ መዝሙር ስሙ ማይጠራበት
ሲበላ ሲጠጣ በጥፋት ላይ ጥፋት
ባዶ የልደት ቀን ባዶ ዓውደ ዓመት።
ያንን ባለልደት በሩ ተዘግቶበት ውጪ የቆመውን
ልደትህ እንዴት ነበር? ብዬ ብጠይቀው ምን ይመልስ ይሆን?
6 971
ግልጥ ሚስጥር
ብዙ ጉዳዮች ከጀርባቸው ውስብስብ ነገር ስለሚኖራቸው የባለሙያዎችን ትንታኔ፣ ምክርና ውሳኔ ይጠይቃሉ። አንዳንዴ ህመማችን ሌላ ሆኖ የሚሰማን ህመም ግን የራስ ምታት ወይንም ብርድ ብርድ ማለት ሲሆን ሐኪም ማማከር ግድ ይሆንብናል። ነገር ግን ሲርበን ወይንም በእንቅልፍ እጦት ሰውነታችን ሲደክምብን ሚስጥሩ ግልጥ ስለሆነ የሐኪም ምክር ሳያስፈልገን በጥሩ ጉርሻ እና እንቅልፍ እንታከማለን።
በዕለት ተዕለት በሚያጋጥሙን ግልጥ በሆኑ ምድራዊ ጉዳዮች ላይ ይህንን ዓይነት እርምጃ የምንወስድ ከሆነና የሰማይ መንገድን አስመልክቶ ግልጥ ሆኖ በተጻፈልን ላይ በተመሳሳይ የማንም ሃይማኖታዊ ትንታኔ ሳያስፈልገን ውሳኔ የማናደርግበት ምክንያት ምንድነው?
እስኪ ይህንን አንብቡት። ከእናንተ መረዳት በላይ የሆነ ግልጽ ያልሆነና ትንታኔ የሚያስፈልገው ምን ሚስጥር አለው?
“ኢየሱስም፦ እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።”
Jesus answered, “I am the way and the truth and the life. No one comes to the Father except through me.” ዮሐንስ ወንጌል ምዕ14 ቁ.6
“መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና።”
Salvation is found in no one else, for there is no other name under heaven given to mankind by which we must be saved.” ሐዋርያት ሥራ ምዕ4 ቁ.12
ጊዜወርቅ '23
@Bruh_Tesfa
6 971
የዛሬ ገጠመኝ
በምኖርበት ከተማ በዕለተ እሁድ ታዋቂ የማራቶን ሩጫ ውድድር እንደሚካሄድና ከተማውን ለሁለት የሚከፍለው ዋና ጎዳናም ሙሉ በሙሉ ለትራፊክ ዝግ እንደሚሆን ሰሞኑን በዜና ሲነገር ሰምቼአለሁ፣ ሰማሁኝ እንጂ ከልቤ ግን አላኖርኩትም።
እናም የሰማሁትን ማስጠንቀቂያ ዘንግቼ እሁድ ጠዋት ተነስቼ ወደ ከተማ ለመሄድ ውድድሩ እየተካሄደ ባለበት መስመር አቅጣጫ ለ20 ደቂቃ ያህል ተጉዤ ልክ መንገዱን የማቋርጥበት ላይ ስደርስ መንገዱ በፖሊስ መኪና ከተዘጋበት ቦታ ጋር ተፋጠጥኩ። ማስጠንቀቂያውን ሰምቼ ለምን ልብ አላልኩም? በራሴ ተበሳጨሁ። ፖሊሶቹስ ምን አለበት ከ2 እና 3 ኪሜ በፊት ማስጠንቀቂያ ቢለጥፉ? እየተነጫነጭኩ የተዘጋውን መንገድ በላዩ የሚሻገር ድልድይ መንገድ ለማግኘት እንደገና ለ15 ደቂቃ ተመልሼ በሌላ አቅጣጫ መሄድ ነበረብኝ።
ሁልጊዜ ግን እንዲህ ሌላ አማራጭ መንገድ ማግኘት አይሳካም። ምርጫ ማስተካከል የሚቻለው እስትንፋስ በአፍንጫችን እስካለ ድረስ ብቻ ስለሆነ። ዛሬ የምትመርጠው መንገድ መድረሻህን ይወስናል። ችግሩ ግን ደርሰህ መሳሳትህን ካየህ በኋላ አይይ ያኛው መንገድ ይሻለኛል ማለት አለመቻሉ ነው።
"በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ሰፊ፥ መንገዱም ትልቅ ነውና፥ ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው፤ ወደ ሕይወት የሚወስደው ደጅ የጠበበ፥ መንገዱም የቀጠነ ነውና፥ የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው።" የማቴዎስ ወንጌል ምዕ7 ቁ.14
ዛሬ ይህንን ጽሁፍ ስታነብ እስትንፋስህ ካንተ ጋር ስላለች ወደ ጥፋት ወይንም ወደ ሕይወት የሚወስደውን የፈልግከውን መንገድ ለመምረጥ ትችላለህ። ነገን ግን ማን ያውቃል።
"እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት።" ዮሐንስ ወንጌል ምዕ17 ቁ. 3
ጊዜወርቅ '23
@Bruh_Tesfa
6 971
‘መረባጠባ’
ዓሣ በማጥመድ የካበተ ዕውቀት የነበራቸው ሰዎች ሌሊቱን ሙሉ ሲደክሙ አድረው ንጋት ላይ ምንም ዓሣ ስላልያዙ በባዶነት ስሜት ቆሻሻ አግበስብሶ የወጣውን ባዶ መረብ እያጠቡ ነበር።
‘መረባጠባ’ ማለት ያዋጣናል ያልነውን ሥራ በብዙ ውጣውረድና ድካም ስንሰራ ቆይተን ጥሩ ውጤት ወይንም ደሞዝ በምንጠብቅበት ጊዜ ልፋታችን ሁሉ ከንቱና ውጤት አልባ ሲሆንብን ነው።
ታዲያ በዚህ ጊዜ ኢየሱስ ወደ እነርሱ መጣና ሲያጠምዱ በነበረበት ታንኳ ገብቶ እዚያ የተሰበሰቡትን አስተምሮ ከጨረሰ በኋላ ‘አሁን መረቦቻቸሁን በዚህ በኩል ጣሉ’ አላቸው። ስምዖን የተባለውም ዓሣ አስጋሪ “ሌሊቱን ሁሉ አድረን ስንደክም ምንም አልያዝንም፤ ነገር ግን በቃልህ መረቦቹን እጥላለሁ” አለው። ይህንም ባደረጉ ጊዜ መረቦቻቸው እስኪቀደዱ እጅግ ብዙ ዓሣ ያዙ።
የእነዚህ ዓሣ አጥማጆች የስኬታቸው ቁልፍ በነበራቸው የዓሣ ማጥመድ ዕውቀታቸው ወይም ሌሊቱን ሲለፉ በማደራቸው ላይ ሳይሆን የሚቀድመው እንዲቀድም ታንኳቸውን ለጌታ በመስጠታቸው፣ ደግሞም መረባቸውን እንደቃሉ በመጣላቸውና አድርጉ ያላቸውን በመታዘዛቸው ላይ ነበር። በዚህ ጊዜ በዕድሜአቸው አይተውት የማያውቁትን ብዙ ዓሣ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ሰበሰቡ።
ብዙ ተስፋ ያደረግከው መና ሆኖብህ በመረብ አጠባ ላይ ያለህ ወንድሜ/እህቴ የሚቀድመውን አስቀድም፣ ሕይወትህን ስጠው፣ ከዚያም እንደቃሉ ለመኖር ጨክን፣ ታዘዘው። እርሱም ድካምህን ይባርክልሃል።
(ለሙሉ ታሪኩ ሉቃስ ወንጌል ምዕ 5ን ያንብቡ)
ጊዜወርቅ '23
@Bruh_Tesfa
