6 971
Subscribers
No data24 hours
-367 days
-20230 days
Posts Archive
6 971
የጥያቄው መልስ:-
"መኖር ይሻላል ሁለት ጊዜ አትሙት" ነው።
እግዚአብሔር ለሰው ልጆች የሰጠው ትልቅ ጸጋ የመኖር እድል ነው። አንድ ሰው ሲፀነስ ከሶስት መቶ ሚሊዮን በላይ ከሆኑ የወንድ ዘሮች ውስጥ አንዷ ዘልቃ መሄድ የቻለችው ያቺ እድለኛ ዘር እኛ እንደሆነን አንዳንዴ ይዘነጋናል። መኖር ስለቻልን መኖር ቀለል ይልብንና ባልኖርስ የሚል ሀሳብ ውል ይለናል። በተሰጠን ዘመን እንደፈቃዱ ኖረን ቀኑ ሲደርስ ከፈጠረን ጌታ ጋር በሰማይ መኖር እንደምንቀጥል እርግጠኛ መሆን አለብን እንጂ ለመሞት (ዘላለም ከጌታ ለመለየት) መሞት የለብንም። በተሰጠን በዚህ የመኖር እድል ምን ያህል ዕድሉን ለሰጠን ጌታ እንደኖርን አንድ ቀን ሁላችንም መልስ እንሰጥበታለንና።
ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና፤ ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እየጠበቅን፥ ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል፤ ቲቶ ምዕ 2፡11
የተሳተፋችሁትን ሁሉ ከልብ እናመሰግናለን። አሸናፊዎችን በውስጥ መስመራችሁ እናገኛችኋለን።
ለወደፊቱ የጥያቄ መልሶችን ማጋራት ወይንም አንድ ሰው በምንም መልኩ ከአንድ በላይ መልስ ሲሰጥ ሲገኝ ከውድድር ውጪ እንደሚሆን ማሳሰብ እንወዳለን።
6 971
የጥያቄው መልስ:-
መኖር ይሻላል ሁለት ጊዜ አትሙት።
እግዚአብሔር ለሰው ልጆች የሰጠው ትልቅ ጸጋ የመኖር እድል ነው። አንዳንዴ መኖር ስለቻልን መኖር ይቀልብናል። አንድን ሰው ሲፀነስ ከሶስት መቶ ሚሊዮን የወንድ ዘር ውስጥ አንዷ ዘልቃ መሄድ የቻለችው እድለኛዋ እኛ እንደሆነን ይዘነጋናል ለአንቺ መኖር ምክንያት የሆነው
6 971
እንጠይቅዎ!
ከሰንጠረዡ በታች የተዘረዘሩትን የሚወክሉ ትክክለኛ ቃላትን አቅጣጫውን ጠብቀው በሰንጠረዡ ይሙሉና ከA እስከ J ያሉትን ቃላት በመልስ ሐረግ ቦታ አስገብተው ያገኙትን ሐረግ ይላኩልን፡፡ ያስታውሱ ሰንጠረዡን ትክክል ካገኙ የመልስ ሐረጉ ትክክል ይሆናል፡፡ መልስዎትን እስከ 16/6/2016 ድረስ በውስጥ መስመር ይላኩ፡፡ ሙሉ በሙሉ በትክክል ለመለሱ የመጀመሪያዎቹ 10 ተሳታፊዎች እያንዳንዳቸው 1000 ብር ሽልማት ያገኛሉ፡፡
6 971
እንደ ልብ
ቢሆንለት ሰው ሁሉ ከቤቱ ባይጠፋ የሚመኘው ነገር ሳይሆን አይቀርም። ያለምንም ገደብና ክልከላ ያሰብነውን ሁሉ እንደልባችን ማድረግ ብንችል ደስታ ከነተሳቢው ቤታችን ገባ ማለት ነበር ብለን እናስባለን። ችግሩ ጥግ ድረስ ሃብትና ዝና ያላቸውም ምን ባደርግ ደስታ ቤቴ ትገባለች የሚሉ መሆናቸው ነው።
Robin Williams ዓለማችን ካየቻቸው ድንቅና ስመጥር ፊልም ተዋናይና ኮሜዲ አንዱ ነበር። በSan Francisco የሚገኘው የ1,000ካሬ (ግቢው አይደለም) ቅንጡ ቤቱ ዋጋ 25ሚ ዶላር ነው። ዝናም ብቻ ሳይሆን ከ40 በላይ ለሆኑ የዕርዳታ ድርጅቶች ገንዘብ በመስጠትና በማሰባሰብ የተመሰገነና ደግ ነበር። ሆኖም በኛ ሃሳብ እንደልብ መሆን ያስችላል የምንለውን ሃብትና ዝና ትቶ በዚሁ ቅንጡ መኖሪያ ቤቱ ውስጥ በ2014 በስቅላት ራሱን አጥፍቷል።
የደጁ ስፋትና የመንገዱ ማማር፣ የሚጋፋውም ሰው መብዛት የመዳረሻውን ትክክለኛነት እንደማያሳይ ሁሉ በተቃራኒውም ጠባብና ችግር የበዛበት የብቸኝነት መንገድ ከመልካም አያደርስም ማለት አይደለም።
ማሰረጃ:
ማቴዎስ 7:13-14 “በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ሰፊ፥ መንገዱም ትልቅ ነውና፥ ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው፤ ወደ ሕይወት የሚወስደው ደጅ የጠበበ፥ መንገዱም የቀጠነ ነውና፥ የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው።"
ጠባቡ መንገድ ኢየሱስን መከተል ነው፣ ፍፃሜው ደግሞ አስተማማኝ።
6 971
እርስበርሳችሁ ተዋደዱ!
“አዲስ ትእዛዝ እሰጣችኋለሁ፤ ይኸውም እርስ በርሳችሁ እንድትዋደዱ ነው፤ እንግዲህ እኔ እንደ ወደድኋችሁ እናንተም እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ። እርስ በርሳችሁ ብትዋደዱ፣ ሰዎች ሁሉ የእኔ ደቀ መዛሙርት እንደ ሆናችሁ በዚህ ያውቃሉ።”
-ቅዱስ መፅሐፍ
ፍቅር ትዕዛዝ ነው፣ መውደድ የእግዚአብሔር ልጅነት መገለጫ ነው፣ መተጋገዝ፣ አብሮ ማደግ፣ ፈጣሪ በወደደን ልክ ሰዎችን መውደድ መቻል ፈጣሪን የመውደዳችን መገለጫ ነው። አምላክህን ታውቃለህ፣ ስለርሱ ፍቅር ደጋግመህ ታወራለህ፣ የታደሉህን በረከቶች ታስተጋባለህ፣ የመውደዱ ጥግ፣ የቸርነቱ መጨረሻ ያስደንቅሃል። ነገር ግን ከመደነቅና ከመገረም በላይ ያንተስ ምላሽ ምንድነው? ለርሱ ያለህን ፍቅር ለምትገልፅበት ትዕዛዝ ምንያህል ቀናኢ ነህ? የእርሱ ልጅ መሆንህን ለማስመስከር ምንያህል ትተጋለህ? የሰውን ልጅ መርዳትና ከልብ መውደድ የእግዚአብሔር አምላክ ልጅነት መገለጫ ከሆነ ስንቶቻችን ልጆቹ እንደሆንን እራሱ ፈጣሪ ያውቀዋል። ለወዳጅህ እንቅፋት እየሆንክ፣ በልብህ ጥላቻን ይዘህ፣ ለቂም በቀል እራስህን እያዘጋጀህ፣ በውስጥህ ንቀትን እያስቀመጥክ እንዴትም ስለ ፈጣሪ ልጅነት አፍህን ሞልተህ ማውራት አትችልም።
ደቀመዛሙርቴ፣ ተማሪዎቼ እንዲሁ ልጆቼ መሆናችሁ ይታወቅ ዘንድ እርስበርሳችሁ ተዋደዱ መባሉን ከልብህ አስገባው። ፍቅርን እየገፉ ጥላቻን እያገዘፉ፣ መውደድን ችላ እያሉ ልዩነትን እየሰበኩ፣ ይቅርታን እያንቋሸሹ ክፋትን እያጠናከሩ ስለፈጣሪ ልጅነት ማውራት አይቻልም። ወገን በችግር ውስጥ ሆኖ በረሃብ በጥማት እየተሰቃየ፣ ወንድም እህቶች የህይወት ካርታ ጠፍቶባቸው ሳለ አንድ ሰው ቢያንስ በቁስ ወይም በገንዘብ መርዳት ባይችል እንኳን ድምፅ በመሆን ህመማቸውን ሌሎች ጋር ማድረስ ሲችል ስላፈራው ንብረትና ስለደረሰበት ስኬት ደጋግሞ ቢያወራ ምንም ትርጉም የለውም። የአንዳችን መኖር ለአንዳችን ብርታት ሊሆን ይገባል፣ ያንተ ጥንካሬ ለወንድምህ ችግር መፍትሔ ማምጣት ይኖርበታል።
አዎ! ለብቻ ኖሮ ማለፍ፣ የእራስን ሆድ ብቻ መሙላት፣ ፅንፍ በያዘ ጥላቻ የሰውን ልጅ ማንቋሸሽ፣ ነገ ምን እንደሚሆን በማይታወቅ ሃብትና ንብረት ከልክ በላይ መመካት በምንም መመዘኛ በእግዚአብሔር ዘንድ ሊወደድ አይችልም። ብንወድቅ የሚያነሳን ፈጣሪ ነው፣ ብንስት የሚመልሰን የዘላለም አባታችን ነው፣ በጥፋት በበደል አንገታችንን ብንደፋ በይቅርታው ቀና የሚያደርገን ቸሩ አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር ነው። ትልቁ የምድር ጌጥ ንብረት፣ ዝና፣ ሰው ወይም ገንዘብ አይደለም ትልቁ ጌጥ የእግዚአብሔር ልጅነት ነው። ሌላው ሁሉ ትርፍና ጠፊ ነው። እርስበርስ በመዋደድ የፈጣሪያችንን ልጅነት እናስመስክር፣ በመልካም ስራ በእምነት ነፍሳችንን ወደ ፅድቁ መንገድ እንምራት።
═════════
ከምርጥ ፅሁፎች የተወሰደ
6 971
የመልአኩ ስብከት
ገብርኤልን ጋብዘነው ስበከን ብንለው
በዓውደ ምህረታችን ማይኩን ብናስይዘው
እግዜር ፊት የሚቆመው
የሰማዩን ክብር ጠንቅቆ የሚያውቀው
ግራ ለተጋባን ምን ብሎ ይመክረናል?
መሄጃው ለጠፋን ወዴት ሂዱ ይለናል?
ብዙ ጥያቄዋ 'እንዴት' የምትለው
መረጃው ከሳይንስ ለሚደናገረው
ለማርያም ያላትን ሳይደግመው አይቀርም
ለእኔ እንደሚመስለኝ ስብከት አይቀይርም።
የምንሰማውና ዓይናችን የሚያየው አልጋጠም ሲለን እኛም እንዴት ብንል ከእርሱ መልስ ፈልገን
መልአኩ 'እኔ' ብሎ አይለንም
መፍትሄ ፍለጋ ኪሱን አይዳብስም።
ምንም ሳያቅማማ ፈጥኖ የሚያደርገው
መልሱ ቀጥተኛ ስብከቱም አጭር ነው፣
"ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለም" ሉቃስ 1:37
6 971
መርገጥና መሄድ
መኪናዎች አጭርና ረጅም መብራት ያላቸው ሲሆን አጭሩ ከፊት ለፊት በቅርብ ያለውን መንገድ ሲያሳይ ሹፌሩ የሚሄድበትን መንገድ ትክክለኛነትና ከመንገድ ስቶ እንዳይወጣ ደግሞ ረጅሙን መብራት በመጠቀም በርቀት ያማትራል። መርከቦችም እንዲሁ ከፊታቸው ያለውን ውሃ በሰላም እየቀዘፉ እየሄዱ ያሉ ቢሆንም በትክክል ወደ መድረሻቸው እየሄዱ እንዳሉ ዋስትና ለማግኘት ኮምፓሳቸውን ይጠቀማሉ።
የሰው ሕይወትም እንዲሁ ነው፤ መሄድ ብቻ ሳይሆን መድረስም ያስፈልገናል። ንጉስ ዳዊት በመዝ. ዳዊት ምዕ 119 ቁ. 105 ላይ 'ሕግህ ለእግሬ መብራት፣ ለመንገዴም ብርሃን ነው' ይለዋል። የእግዚአብሔር ቃል ዛሬን የምውልበትን ምሪትን የሚሰጠኝ አጭር መብራት ሲሆን፣ ነገዬን ደግሞ ከብሩህ መድረሻዬ ለመድረስ የምጓዝበት ረዥሙ ብርሃኔ ነው ማለቱ ነው።
እውነት እኮ ነው፣ ዛሬን በ'ደስታ' ስንዘል ውለን ነገ ላይ የነፍሳችን ፍጻሜ ካላማረ ምን ይጠቅመናል? 'ሰው ዓለምን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱን ግን ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል' የሚለው ምንኛ ትክክለኛ ቃል ነው። ማቴዎስ ምዕ 16 ቁ 26
ትርጉም ትንታኔ የማያሻው ግልጽ የእግዚአብሔር ቃል "ልጁ ያለው ሕይወት አለው፤ የእግዚአብሔር ልጅ የሌለው ሕይወት የለውም" 1ዮሐንስ 5:12 ይላልና እባክዎ ሲጓዙ ኖረው ኖረው በፍፃሜው ከህይወት ደጅ መድረስዎን እርግጠኛ ይሁኑ።
6 971
የእግዚአብሔር ደስታ የጠፋውን ልጁን መልሶ ሲያገኘው ነው። በኃጢያቱ ምክንያት ከገነት የተባረረውን የሰው ዘር እንደገና በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን ሰው የእግዚአብሔር ልጅነትን ስልጣን ሲያገኝ እግዚአብሔር የጠፋውን ልጁን መልሶ አገኘው ማለት ነው ። ዮሐንስ 1:12
ስለዚህም ጠፍቶ (ከእግዚአብሔር ተለይቶ) በነበረ አንድ ልጅ መገኘት ምክንያት በሰማያት ታላቅ ደስታ እንደሚሆን ሉቃስ ምዕራፍ 15 ይነግረናል።
6 971
ምን አንድ ነገር?
ብዙ የማድረግ አቅም ያለው ሰው ወደ እናንተ መጥቶ የምትፈልጉትን አንድ ነገር ምን ላድርግላችሁ ብሎ ቢል ምን ትላላችሁ? ቤት፣ መኪና፣ ቢዝነስ፣ መማር፣ መስራት... መቼም የሰው መሻት ጥጉ ከነዚህ ብዙ የሚርቅ አይሆንም።
የዛሬው ጥያቄ ግን ሰማይንና ምድርን፣ በውስጡ ያለውንም ሁሉ የፈጠረ እግዚአብሔር ምን አንድ ነገር ሲሆንለት ደስ ይለዋል? የሚለው ነው። ወይስ እሱ የሁሉ ፈጣሪ አምላክ ስለሆነ ምንም አድርገን እርሱን ማስደሰት አንችልም ትላላችሁ። የእኛን ግምት ትተን እርሱ ራሱ ምን ሲሆንለት ደስ እንደሚለው የተናገረውን ማየት የግድ ይሆናል።
እግዚአብሔር ደስ የሚሰኝበትን አንድ ነገር በማሽማ መልኩ በቃሉ በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 15 በተለያዩ ምሳሌዎች ከ6 ጊዜዎች በላይ ተጠቅሷል። ምዕራፉን አንብቡና የምታገኙትን እግዚአብሄርን ደስ የሚያሰኝበትን አንድ ነገር ምላሻችሁን ፃፉልን።
ምክንያቱም እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘዉን አንድ ነገር ማወቅ እኛ ማድረግ ያለብንን አንድ ነገር ስለሚያሳየን ይህ ትልቅ ዕድል ነውና።
6 971
አንት ሰበበኛ
ከዛሬ 2000 ዓመታት በፊት የተነገረ የሚያስደንቅ አጭር ምሳሌ ነው።
አንድ ሰው ታላቅ እራት አዘጋጀና ታላላቅ የሚባሉ ሰዎችን ጋበዘ። እናም ሰዓቱ ሲደርስ እንዲመጡ መልዕክተኛ ሲልክባቸው አንደኛው ተጋባዥ የገዛሁትን መሬት ሄጄ ስለማይ ልመጣ አልችልም ይቅርታ፣ ብሎ መለሰ። ሁለተኛውም 5 ጥማድ በሬ ገዝቻለውና ልሞክራቸው እየሄድኩ ስለሆነ አልችልም ይቅርታ አለ። ሦስተኛውና የመጨረሻው ደግሞ ሚስት አግብቻለሁና አይሆንልኝም አለ።
እነዚህ 3 ሰዎች የቀረበላቸውን ጥሪ ላለመቀበል የሰጡትን ሰበቦች ስንመለከት
1ኛው የኔ የሚለው መሬት (አገር፣ ትውልድ...)
2ኛው ሥራ/ቢዝነስ
3ኛው ትዳር (ሚስት፣ ልጅ፣ ኑሮ) ናቸው።
ዛሬም እነዚህ ምክንያቶች ሰዎች የሚቀርብላቸውን የህይወት ግብዣ ላለመቀበል ከሚሰጡ ምክንያቶች ዋና ዋናዎቹ ናቸው።
ኢየሱስ እኔ ህይወት ነኝ፣ ወደ እኔ ኑ አለ እንጂ ማንንም ወደ ሃይማኖት አልጠራም።
በጌታ እየሱስ አምነህ በእግዚአብሔር መንግስት ለዘለዓለም በደስታ እንድትኖር ግብዣ ሲቀርብልህ ጥሪውን ላለመቀበል የምታቀርበው ያንተስ ምክንያት ምንድነው?
ምክንያትህ ምድር ቀሪ፣ ጥሪው ግን ለዘላለም ህይወት ነውና እባክህ ሰበብህን ትተህ የግብዣውን ጥሪ ተቀበል።
ሙሉ ታሪኩን የሉቃስ ወንጌል ምዕ 14 ቁጥር 16-24 ያንብቡ
6 971
2 ዓይነት መንበርከኮች
የመንበርከክ ትርጉም መሸነፍ፣ ራስን መስጠት፣ መገዛት፣ እሺ ማለት፣ ለተንበረከኩለት ክብር መስጠትን ሁሉ ይጨምራል።
ግና ዛሬ በእግዚአብሔር ፊት በፈቃዳችን በመንበርከክና ነገ በኃይል ተገደን በመንበርከክ መካከል ያለው ልዩነት ምንድነው?
1. በፈቃዳችንና ሁኔታዎች ሳያስገድዱን በፊት ስንበረከክ፣ አንተ ጌታ ነህ፣ እኔ ያንተ አገልጋይ ነኝ፣ ፈቃዴን ለፈቃድህ እሰጣለሁ ማለታችን ሲሆን ይህም ለአምላክ የሚቀርብ አምልኮ ይሆንልናል። ይህም ዛሬ መንበርከክ ስንችል ፈቅደን የምናደርገው ነገር ነው። በአምልኮአችንም ደስ የተሰኘው አምላክም ከወደቅንበት ያነሳናል፣ ነገአችንንም ያሳምርልናል።
2. በግድ መንበርከክ ግን የፈቃዳችን ምርጫ ሳይሆን ጉልበተኛ ነኝ፣ እችላለሁ፣ እምቢ አሻፈረኝ ስንል ኖረን ድንገት ልንቋቋመው የማንችለውና ከአቅማችን በላይ በሆነው ሀይለኛ ፊት ስንቆም ጉልበታችን ከድቶን ወድቀን የምንበረከክበት ነው። ችግሩ ይኼኛው መንበረከክ ነገአችንን የምንቀይርበትን ዕድል አይሰጠንም። ለምሳሌ በሞት አልጋ ላይ ያለ ወይም ከሞት በኋላ ባለው ፍርድ ወንበር ፊት የቆመ።
ስለዚህም ጥያቄው መቼ ትንበረከካለህ ነው እንጂ አንድ ቀን መንበርከክማ አይቀርም።
ፊልጵስዩስ 2፡10
ጊዜወርቅ 2024
@Bruh_Tesfa
