6 971
Subscribers
No data24 hours
-367 days
-20230 days
Posts Archive
6 971
ሰው ከሸመገለ በኋላ ሊወለድ እንደሚችል ያውቃሉ?
እንዴት ካሉ፣ ከእርሶ በፊት ይህ እንዴት ይቻላል ብሎ ጠይቆ ስለነበረው ሰው ታሪክና ለጥያቄው የተሰጠውን መልስ ያንብቡ።
ይሄ መወለድ በደግም ሆነ በክፉ ዘላለምን የሚወስን በጣም ቁልፉ ጉዳይ ነውና በዮሐንስ ወንጌል ምዕ3 ላይ እንዴት መወለድ እንደሚቻል የተጻፈውን ያንብቡና ያንኑ ያድርጉ።
አንብበው ጥያቄ ካለዎም ያገኙን።
6 971
የሰው ቤት አታበላሽ!
በጥንት ዘመን ሰዎች ወደ መቅደስ ሲመጡ ይዘው መምጣት ያለባቸው የመስዋዕት እንስሳ ወይም የአስራት ስጦታ ነበር።
ሆኖም የየራሳቸውን ከቤታቸው ድረስ ይዘው ሲመጡ ያለውን ድካም ለማቅለል በሚል ሌሎች "ለእግዚአብሔር የሚቀርብ" የሚል ታርጋ የተለጠፈባቸውን እንስሶች ሰብስበው በመቅደስ ግቢ ውስጥ ገበያ አቆሙ። ዮሐንስ ወንጌል 2:13 ጀምሮ
ይህንን የተመለከተው ኢየሱስ ጅራፍ አበጅቶ ከብቶቹን በሙሉ አስወጣ፣ የነጋዴዎችንም ገበታ ገለባበጠና "የአባቴን ቤት የንግድ ቤት (የወንበዴዎች ዋሻ ማቴ21:13) አታድርጉት አለ።
ከዚህ ታሪክ ዝቅ ብሎ ዮሐ2:21 ላይ ስለ መቅደስ ሲናገር "መቅደስ" የእግዚአብሔር ማደሪያ የሆነው ሰውነታችን መሆኑን ኢየሱስ ገልጿል።
'ለእግዚአብሔር' በሚል፣ ለሃይማኖት ባለ ቅንዓት፣ ኑሮን ቀለል ለማድረግ ወይም በሌላ ምክንያት የሰውነት መቅደሳችንን የሚያረክሱ ነገሮችን በልባችን ሰብስበን ከሆነ የመቅደሱና የቤቱ ባለቤት አይወደውምና ጅራፍ ሳያነሳ በፊት እኛው ቤቱን እናጽዳለት።
ጥያቄ ቢኖርዎ ያግኙን።
6 971
የቶዮታ መኪና መስራች የሆኑት Mr Toyoda የመጀመሪያዋን መኪና በ1936 ሲፈበርኩ በመኪናው ላይ እንዲሁ ያለ ሥራ/ዓላማ የፈጠሩት አንድም የመኪና አካል የለም።
Mr Toyoda እንኳን እንዲህ ባለ ጥንቃቄ እያንዳንዱን የመኪና አካል በዓላማ የሚገጥሙ ከሆነ በመልኩ የሰራህ እግዚአብሔር አንተን እንዴት ያለ ዓላማ እንዲሁ በምድር ላይ ያስቀምጣል፣ እንዴትስ የአንተ በሕይወት መኖር የአጋጣሚ ጉዳይ ነው ብለህ ታስባለህ?
ደግሞም በመኪናው ላይ ያሉት አካላት ለራሳቸው ጥቅምና ደስታ የተፈጠሩ ሳይሆን መኪናው የተሰራበት ዋና ዓላማ ዕውን እንዲሆን የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ ታስበው የተሰሩ ናቸው። እግዚአብሔር በእኛ ተጠቅሞ የልቡን ሃሳብና ፈቃድ ሲፈጽም የሚሆንልን ደስታና በረከት መኖሩ እውነት ነው፣ እንጂ የተፈጠርንበት ዓላማ በእኛ ደስታ ጀምሮ በእኛ ደስታ ላይ እንዲያበቃ አይደለም።
የተፈጠርክበትን ዓላማ እወቅ፣
የተፈጠርክበትን ዓላማ ለመጨበጥ ትጋ፣
ለተፈጠርክበት ኑር።
"በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በፊቱ ደስ የሚያሰኘውን በእናንተ እያደረገ፥ ፈቃዱን ታደርጉ ዘንድ በመልካም ሥራ ሁሉ ፍጹማን ያድርጋችሁ..."
ዕብራውያን 13:21
6 971
የመንግስት ትዕዛዝ ሆኖባት እንጂ ሴት ልጅ ወሯ ከገባ በኋላ በእንስሳ ጀርባ ላይ ተቀመጣ ረጅም መንገድ ለመሄድ የምትወጣበት ጊዜ አልነበረም። ነገር ግን የማርያም ጉዞዋ ራሱ የጀመረው በእሺታ ስለነበር አቅሟ ባይፈቅድም ለህዝብ ቆጠራ ከዮሴፍ ጋር ወደ ኢየሩሳሌም ልትሄድ ተነሳች።
አመሻሽተው ከተማ ሲደርሱ ለእንግዶች ማረፊያ የሚሆኑ ቦታዎች ሁሉ ቀድመው ስለተያዙ የሚያርፉበት አላገኙም። በዚህ መሃል እርሷ ደግሞ ቀኗ ደርሶ ምጥ እያፋፋማት ነበር። ምጥ ይዟት የምታቃስትን ሴት ሊያስጠጋ የሚፈቅድ በሌለበት አንድ እሺ ባይ ተገኘ፣ የበረት ባለቤት። ህፃን ለመቀበል የሚሆን ጽዱና ንጹህ ቦታ ባይኖረውም እሺ ፈቃድ ግን ተገኝቶበታልና ማርያምና ዮሴፍ በዚያ አርፈው ጌታ የሆነው አዳኝ በዛ የበረት ስፍራ ተወለደ። ከኢየሱስ በዚያ መወለድ የተነሳ ያ በረት እስካሁን የሚጎበኝ የተከበረ ስፍራ ሊሆን በቅቷል።
ጌታ ልብህን ወይንም እሺ ፍቃድህን ስጠኝ ሲልህ ንጹህና ፍፁም የሆነ ነገር ስላለብህ ሳይሆን ያንኑ ማንነትህን ቀድሶና ቀይሮ የከበረ ማንነትን ከውስጥ ሊያወጣ ነውና አንድ እሺን አትንፈገው።
ጥያቄ ቢኖርዎ ይላኩልን!
6 971
በተሸነፈው አትሸነፍ
በዳዊትና በጎልያድ መካከል ፍልሚያ ከመደረጉ በፊት አንድ ውል ነበራቸው። ያውም ጎልያድ ካሸነፈ፣ ከዳዊት ጀርባ ያለው ህዝብ ሁሉ ለጎልያድ ህዝብ ባሪያ ሊሆን፤ ዳዊት ካሸነፈም እንዲሁ በተቃራኒው ከጎልያድ ጀርባ ያለው ህዝብ ለዳዊት ህዝብ ባሪያ ሊሆን ተስማምተው ነበር። በውጤቱም በእግዚአብሔር ስም የወጣው ዳዊት ጎልያድን ስላሸነፈ ድሉ የህዝቡ ሁሉ ድል ሆኖ ጠላቶቻቸውን አሳደዷቸው።
እኛም በየቀኑ ከፊታችን የሚቆሙ ዓለም፣ ሥጋና ሰይጣን የሚባሉ ጠላቶች አሉብን። ዋነኛ የጦር መሳሪያቸው ደግሞ ኃጥያት ነው። የምስራቹ ግን መሪያችን ኢየሱስ ሁሉንም በመስቀሉ ስላሸነፋቸው፣ የእርሱ ድል ደግሞ የእኛም ድል ነውና በስሙ እየረገጥናቸው ሄደን በፍጻሜውም ከእርሱ ጋር በሰማይ ለዘላለም እንኖራለን።
ሆኖም ሰልፋችን ከአሸነፈው ጌታ ጋር ካልሆነ በተሸነፈው ተሸንፈን የዘላለም ፍጻሜአችንም ከተሸነፈው ጋር በሲኦል እንዳይሆንብን ከወዲሁ ሰልፋችንን እናስተካክል።
"ልጆች ሆይ፥ እናንተ ከእግዚአብሔር ናችሁ አሸንፋችኋቸውማል፥ በዓለም ካለው ይልቅ በእናንተ ያለው ታላቅ ነውና።" 1ኛ ዮሐንስ ምዕ1:4
ጥያቄ ቢኖርዎ ይላኩልን!
6 971
ዕድለኛ ነዎት
በዚህ በአዲስኪዳን የምህረት ዘመን መኖር እንዴት ታላቅ ዕድል እንደሆነ አስተውለው ያውቃሉ?
እግዚአብሔር ፍጹም ፃድቅ ስለሆነና የህግ መተላለፍን ስለማይታገስ የኃጥያትን ዋጋ እጅ በእጅ የሚከፍልበት ዓይን ለዓይን፣ ጥርስ ለጥርስ ፍርድ የሚሰጥበት 'ብሉይኪዳን' የሚባል የህግ ዘመን ነበር።
ዛሬስ? እግዚአብሔር ዛሬም የጽድቅና የቅድስና ደረጃ ለውጥ ወይም የህግ ማሻሻያ አላደረገም። እንደ ድሮው ዛሬም ደም ሳይፈስ ስርየት የለም፣ ኃጢአትንም ደግሞ በሞት ይቀጣል።
በአዲስኪዳን የሆነልን እድሳት ነገር ጻድቅ የሆነው ኢየሱስ የኃጥያታችንን ዕዳ በመስቀል ላይ ስለከፈለልን ዛሬ በኛ ላይ ዓይን ለዓይን ፍርድ አይሆንብንም፤ በእኛ ፋንታ በሞተልን በኢየሱስ ከእግዚአብሔር ምህረትን የምንጠይቅበት የንስሐ ዕድል ተሰጥቶናልና።
ንስሐ ማለት ግን ለበደላችን ምህረትን ማግኘት ብቻ ሳይሆን "የሰረቀ ከእንግዲህ ወዲህ አይስረቅ ነገር ግን... በገዛ እጆቹ መልካምን እየሰራ ይድከም" እንደሚል የህይወት አቅጣጫ ለውጥንም ይጠይቃል። ኤፌሶን ምዕ 4ን ያንብቡ።
ሆኖም ግን ይህንን በአዲስኪዳን በኢየሱስ ያገኘነውን የንስሐ ዕድል አለመጠቀም ምህረት የሌለውና የዘላለም ሞት ፍርድ ያለበት እንደሆነም ማወቅ ተገቢ ነው።
ጥያቄ ቢኖረዎ ያገኙን።
6 971
ስኬት ምንድነው?
ስኬት አብዛኛው ሰው የፈለገውን ሲያገኝ፣ ከአሰበበት ሲደርስ፣ ህልሙን ሲጨብጥ ተሳክቶለታል ይባላል።
በዚህ ትርጉም ከሄድን፣ የልቡን ምኞት ያገኘው ሎጥ እጅግ የተሳካለት ሰው ሊባል ነው። እውነታው ግን ለዓይኑ ያማረውንና የተመኘውንም አግኝቶ ሕይወቱ የኪሳራ እንደነበረና ከዓመታት ድካም በኋላ ነፍሱን ሊያድን ባዶ እጁን እንደወጣ ታሪኩን እናውቃለን።
ምክንያቱም እውነተኛ ስኬት ሰው የተመኘውን ገንዘብ፣ ቁሳቁስ፣ ኑሮ... ሲያገኝ ሳይሆን እግዚአብሔር ካሰበለት ሲደርስና ያሰበውን ስራ ሲፈጽም ብቻ ነው።
መጽ/ቅ "ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም" እንደሚል ተሳካ የሚባለው እግዚአብሔር ለእያንዳንዳችን አስቀድሞ ካሰበልንና ከተፈጠርንበት ዓላማ ላይ ስንደርስ ነው። ኤርምያስ 29:11
ችግሩ ግን የፈጠረን ለምን እንደፈጠረን ካልተገለጠልን፣ እኛ ደግሞ ያለ ዓላማ መኖር የማንችል ፍጡራን ስለሆንን ሌላ የራሳችንን ሰው ሰራሽ/አርተፊሻል ዓላማ ልንፈጥርን እሞክራለን።
"እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።" ኤፌሶን 2:10
ይህንን እንወቅ! እግዚአብሔር እኛን የፈጠረውም ሆነ አስቀድሞ ያሰበውን መልካም ስራ በእኛ የሚሰራው በክርስቶስ ኢየሱስ ነው። ኢየሱስን ሳንይዝ እግዚአብሔር ያሰበውን መልካም ስራ በእኛ ይሰራል ብሎ ማለት የሚታሰብ አይደለም።
6 971
በአጋጣሚ ከከተማ ውጪ ለስራ ስለወጣን የባለፈውን ጥያቄ ማበረታቻ በተባለው ቀን ባለማድረጋችን ይቅርታ እንጠይቃለን። በሳምንቱ መጨረሻ ከመስክ እንደተመለስን እንልካለን።
6 971
ለተሳትፎ የሚያሸልም ጥያቄ
ከላይ "ፀሎት" በሚል ርዕስ የቀረበውን ጽሁፍ አንብበውታል? ፀሎት እኛን ወደ እግዚአብሔር የሚያስጠጋ፣ እግዚአብሔርንም ወደ እኛ የሚያቀርብ እጅግ ጉልበታም መሣሪያ ነው።
ፀሎት ለአንተ/ለአንቺ ምንድነው?
- እንደ ልጅ በአባት እግር ስር የምትቀመጥበትና አባትህን እያደንቅከው ዝርዝር ጉዳዮችህን የምታወራበት፣ እሱም በልቡ ባለው ጉዳይ አንተን የሚያነጋግርበት ጊዜ ነው?
- ልትፈጽማቸው ከሚገቡ ከሃይማኖት ስርዓቶች ውስጥ አንዱ ስለሆነ ግዴታህን በታማኝነት የምትወጣበት ጊዜ ነው?
- እንደ መድረክ ጽሑፍ አቅራቢ አንተ ብቻ ተናጋሪ ሆነህ ንግግርህን አነብንበህ ስትጨርስ ከመድረክ የምትወርድበት ጊዜ ነው?
- ወይንም ሌላ ምንም ዓይነት የጸሎት ልምድ ካለዎት ከ7 መስመር በማያንስ ጽሑፍ ፀሎት ለእርሶ ምን እንደሆነ ልምድዎን ያካፍሉን።
ለተሳታፊነትዎ የስልክ ካርድ መሙያ 250ብር እንልክልዎታለን።
6 971
ከቶ ምን ይፈይዳል?
"ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን" ብዬ ስል ካለው ክብር በላይ ሌላ ክብር ልጨምርለትና ወደ አዲስ የክብር ደረጃ ከፍ ላደርገው ሳይሆን "በእኔም ሕይወት ላይ ክብርህ እንዲታይ እፈቅዳለሁ" ለማለት እንደሆን እንጂ እሱ የሌለውን ከእኔ ምን ክብር እጨምርለታለሁ?
እናም...
እግዚአብሔር ይመስገን እያልኩ -
ጌታ በሕይወቴ ካልተመሰገነ (በኔ ምክንያት ስሙ ከተነቀፈ)...
እግዚአብሔር ትልቅ ነው እያልኩ -
በትንሽዋ ልቤ ትልቁን ቦታ ካልሰጠሁት...
እግዚአብሔር ሁሉን ይችላል እያልኩ -
የልቤን በር ቆልፌ እሺታዬን/ፈቃዴን ከከለከልኩት...
እግዚአብሔር ኃያል እያልኩ...
ኃይሉ በህይወቴ እንዲገለጥ ዕድል ከነፈግኩት...
አልፋ ኦሜጋ እያልኩት -
ከጠዋት እስከ ማታ በሕይወቴ ምንም ቦታ ካልሰጠሁት...
ከቶ ምን ይፈይዳል?
6 971
ፀሎት
-ልጅና አባት አብረው የሚያወሩበት - "አባታችን ሆይ"
-ለአምላክ ምስጋናና አምልኮ የምናቀርብበት
-ንስሐ የምንገባበት ይቅርታ የምንጠይቅበት
-ለእኛ ልመና፣ ለሌሎች ምልጃ የምናቀርብበት
-የእግዚአብሔርን ታላቅ ኃይል የምንለማመድበት
-ከእግዚአብሔር ቃል/ መመሪያ የምንቀበልበት
-በረከቱን ለኛና ለምድራችን የምንቀበልበት
-ትእዛዝ ነው እንድንፀልይ ታዝዘናል
-ከፈተና የምናመልጥበትና ፈተናንም የምናሸንፍበት
ያላንተ አልችልም፣ ባንተ ግን እችላለሁ እምነት ያለበት
ፀሎት ወደማን፣ እንዴት
-ጌታ ቅርብ ነው በነገር ሁሉም በጸሎትና ምስጋና ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ መናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ ፊልጵ 4:6
-በመንፈስ ፀልዩ፣ በአባትና ልጅ መካከል እንደሚሆን እንጂ ሁልጊዜ በቅደም ተከተል፣ ቃላት በመደጋገም ያልሆነ፣ ህይወት ያለበት ኤፌሶን 6:18
-በኢየሱስ ስም ፀልዩ - አብ በስሜ የምትለምኑት ሁሉ ይሰጣችኋል ዮሐንስ 16:23
ይህን ይወቁ
-በምድር ያሉ ሰዎች ሁሉ በአንድ ጊዜ ቢፀልዩ እግዚአብሔር ሁሉንም መስማት ይችላል።
-መስማት ብቻም ሳይሆን የልባቸውን ሀሳብ (intention) ጭምር ያውቃል
-መስማት ብቻም ሳይሆን ደግሞ ይመልሳል።
ለዚህ ሁሉ ፍጥረት ጥያቄና ፀሎት መልስ ያለው እግዚአብሔር አይገርምም!
6 971
በሰጠን እንስጠው
በፈጠረው ምላስ በውሸት መስከረው
በሰጣቸው ልሳን ሞልጨው ሞልጨው
ስራ እንዲሰሩበት ብረት ቢሰጣቸው
አቅለጠው ቀጥቅጠው
እጁን በእጁ ወጉት ምስማሩን አሹለው
ያም አልበቃ ብሎ
የፈጠረውን ዛፍ ጠርበው አስተካክለው
እንጨት ላይ ሰቀሉት በሰራው እጃቸው።
ታሪክ አይደገምም ዛሬም በኛ ዘመን
አውጥተን አንግፋው በሰራው እጃችን
በተሰጠን ምላስ አሜን ልንልበት
ጌታዬ እንበል እንጂ ክህደት አናውራበት
በተሰጠን እግር ከሚወደን ጌታ ከምንሸሽበት
እግሮቹ ስር ወድቀን እንንበርከክበት።
6 971
ፍቅር ቋንቋ ነው
ቋንቋ በተናጋሪና አድማጭ መካከል የሚደረግ የሁለትዮሽ ቅብብል ስለሆነ ተናጋሪው የሚናገረውን ሰሚው ይረዳዋል፣ ሰምቶም ምላሽ በመስጠት እየተግባቡ ይቀጥላሉ።
ፍቅርም እንዲሁ በአፍቃሪ እና ተፈቃሪ መካከል የሚደረግ ቋንቋ በመሆኑ አፍቃሪ በፍቅር ሲናገር ተፈቃሪ ተቀብሎ የፍቅር ምላሽ በመስጠት እየተግባቡ እንደሚቀጥሉ ይጠበቃል።
ታዲያ የሰውን ልጅ ከእግዚአብሔር ጋር ሊያስታርቅ የኃጢያታችንን ዕዳ ለመክፈል ራሱን ለመስቀል ሞት አሳልፎ በመስጠት በፍቅር ቋንቋ ላናገረን ጌታ የሰጠነው ምላሽ ምንድን ነው?
ከሁሉም የሚቀድመው ምላሽ ቋንቋውን መረዳት ወይንም ዕውቅና መስጠት ይሆናል። በመቀጠልም ለተደረገልን ማመስገን ከዚያም ለዚህ ፍቅር መኖር።
ይህ ምላሽ በአንድ ዐ.ነገር ቢጠቃለል እንዲህ ሊባል ይችላል።
"ጌታ ሆይ የእኔን ኃጢአት የሞት ፍርድ ልትወስድ በመስቀል ላይ ስለሞትክልኝ እና ልጅ ስላደረከኝ አመሰግንሃለሁ። እግዚአብሔር ሆይ ስለ እኔ በፈሰሰው የክርስቶስ ደም ሃጥያቴን ይቅር በለኝ። በቀረኝ ዘመን በፍቅርህ ውስጥ ላንተ ለመኖር እሻለሁና አግዘኝ። አሜን!"
6 971
አያድርገውና ዛሬ ብትሞት ነፍሰህ የት ትገኛለች? (ጥያቄውን ለመመለስ ቢረዳዎ ዮሐንስ ወንጌል ምዕ 3 ቁ. 16 እስከ 18 ያንብቡ)
6 971
ጨርሶ ነግሮናል
አንዱ እንዲህ ሌላው እንዲያ ውስጤ ደግሞ ወዲያ እያለ ግራ ከሚያጋቡኝና ከሚያወዛግቡኝ፣ ምን አለበት እግዚአብሔር ራሱ በቀጥታ ከሰማይ ድምጹን አሰምቶ ቢያናግረኝና ቢገላግለኝ ብለው አስበው ያወቃሉ?
ይህንን እኛ ብቻ ሳንሆን እግዚአብሔርም በመልኩ ከሰራው ሰው ጋ ጉዳይ ስላለው በቀጥታ መነጋገር ይፈልጋል። ችግሩ ግን ሰው የእግዚአብሔርን በድምጽ በቀጥታ ሰምቶ ቆሞ በህይወት መሄድ የሚችል ፍጡር አለመሆኑ ነው።
በዘጸአት ምዕ20 ቁ19 እግዚአብሔር ህዝቡን በሲና ተራራ ላይ በድምጽ ሊያናግር ሲጀምር እንኳን ደምፁን ሊሰሙ መቆም አቅቷቸው ተርበድብደው፣ ሙሴን “አንተ ተናገረን እኛም እንሰማለን፤ እንዳንሞት ግን እግዚአብሔር አይናገረን” አሉት ይላል።
ስለዚህም እግዚአብሔር እኛ በሚመስል ሰው በኩል ካልተናገረን በቀር የመስማት አቅም እንደሌለን የሚያውቅ ሰማይን ከፍቶ በድምጽ ሲናገር የተናገረው “በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት፡” ብሎ ጨርሶ ነግሮናል ማቴዎስ 17:5። እናም እግዚአብሔር እንዲናገረኝ እፈልጋለሁ የምንል ወንድሜ/እህቴ ሰውና የእግዚአብሔር ድምጽ ሆኖ የመጣው ኢየሱስን እንስማ።
ኢየሱስ ደግሞ በበኩሉ “እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም" ብሎናልና እንወቅበት። ዮሐ14:6
6 971
እንዴት ይቻላል?
ሃይማኖተኛ መሆን በማይጠፋው በገሃነም እሳት ከመጣል (ከዘላለም ሞት) ያድናል? ሃይማኖት ከዘለዓለም ሞት ካዳነ ትክክለኛውና የእግዚአብሔር የሆነው ሃይማኖትስ የቱ ነው? ደግነቱ እግዚአብሄር እስላምም ክርስቲያንም አለመሆኑ በጀን እንጂ። ለዚህም ነው በጌታ ፊት ለፍርድ ስንቆም ክርስትያን በዚህ እስላም በዚያ ቁሙ የማንባለው። ታዲያ ከዘላለም ሞት ለማምለጥና ከእግዚአብሔርም ጋር ለዘላለም በገነት ለመኖር (ለመዳን) እንዴት ይቻላል?
እግዚአብሔር ፍፁም ንጹህና ቅዱስ እንደመሆኑ ከእርሱ ጋር የሚኖር ማንም እንዲሁ ፍጹምና ንፁህ እንዲሆን የግድ ነው (እንደ መላእክት)። ችግሩ ለኃጢአታችን የሚበቃ መስዋዕት አቅርበን ካልነፃን በቀር ማንም ሰው በእግዚአብሔር ፊት ንፁህ መሆን አለመቻሉ ነው።
በየቀኑ ለሰራነው ኃጢአት የሚበቃ መስዋዕት ማቅረብ እንደማንችል ሲያውቅ እግዚአብሔር ራሱ ሰው ሆኖ የሰውን የኃጢያት ዕዳ ሊከፍል በመስቀል ላይ የመስዋዕት ደሙን አፈሰሰልን። ስለዚህም ለሃጢያቴ በፈሰሰው የክርስቶስ ደም ሙሉ በሙሉ ስላጠበኝና ልጁ ስላደረገኝ በእግዚአብሔር አባቴ ፊት ለመቅረብና አብሬው ለዘላለም ለመኖርም እችላለሁ የምለው።
ታድያ እንዲህ ያለ የታመነ ማረጋገጫ እያለልህ በምድር የሰራሁት ደግነት እና ክፉ ሥራ በሚዛን ሲመዘን ደጉ ሚዛን ከደፋ ከዘላለም ሞት ተርፋለሁ ብለህ ነፍስህን በ'ምናልባት' ሚዛን ላይ ለምን ታቆያታለህ? ከትንሽ ኃጢአት ጋር እንኳን ታግሶ አብሮ መኖር የማይሆንለት አምላክ ያ መልአክ የነበረውንና ክፋት የተገኘበትን ሰይጣንን አውጥቶ ከጣለው እንዴት የሰራሁት ደግነት ከክፉ ሥራዬ ከበለጠ እድናለሁ ትላለህ?
የሰው ንጽህና በመታጠብ እንጂ ባለመቆሸሽ አይሆንምና ከኃጢያትህ ሊያነፃህ በፈሰሰልህ የክርስቶስ ደም ታጥበህ ዳን!
ጥያቄ አለዎት? በውስጥ መስመር ይጠይቁን።
