en
Feedback
ብሩህ ተስፋ

ብሩህ ተስፋ

Open in Telegram
6 971
Subscribers
No data24 hours
-367 days
-20230 days
Posts Archive
በመጽ/ቅ የተጻፉልን የቅዱሳን ታሪክ በሙሉ ለትምህርታችን ተጻፉልን እንጂ እውነት፣ መንገድ፣ ህይወት የሆነው ግን የኢየሱስ ስም ብቻ ነው።
Anonymous voting

ቃሉ ስለ ኢየሱስ "መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለም" የሚለው ቃል የታመነ ነው። ሐዋ. ሥራ 4:12
Anonymous voting

በመጽ/ቅ ከተጻፈው በላይ መጨመር መቅሰፍት ይጨምራል ፤ ከተጻፈውም ማጉደል ከህይወት ያጎድላል። ራዕይ 22:18-19
Anonymous voting

በመጽ/ቅ በተጻፈውና በሃይማኖቴ ደንብና ስርዓት መካከል የማይስማሙ ጉዳዬች ቢኖሩ የመጨረሻው ገዢ በመጽ/ቅ የተጻፈው ነው።
Anonymous voting

መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል ስለሆነ የማይታየውን እግዚአብሔርን በቃሉ ውስጥ እናየዋለን።
Anonymous voting

መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል ነው።
Anonymous voting

የዳቦ ሃሳብ የሰይጣን ፈተና ቁጥር 1 ምን እንደሆነ ያውቃሉ? ኢየሱስ 40 ቀናት ከጾመ በኋላ እንደተራበ አውቆ ሰይጣን ያቀረበለት የመጀመሪያው ፈተና የዳቦ ሃሳብ ነው። ዳቦ ሳይሆን የዳቦ ሃሳብ። ምክ
የዳቦ ሃሳብ የሰይጣን ፈተና ቁጥር 1 ምን እንደሆነ ያውቃሉ? ኢየሱስ 40 ቀናት ከጾመ በኋላ እንደተራበ አውቆ ሰይጣን ያቀረበለት የመጀመሪያው ፈተና የዳቦ ሃሳብ ነው። ዳቦ ሳይሆን የዳቦ ሃሳብ። ምክንያቱም መጀመሪያ በተራበ ሆድህ የዳቦ ሃሳብ ያስገባብህና አንተም በምናብህ ጥጋብን ስትጎመዥ፣ ዳቦውንም ሳታገኝ ሃሳብህንና ፈቃድህን ከቁጥጥሩ ስር ማስገባት ቀላል እንደሆነ ስለሚያውቅ ነው። በዚህ የዳቦ ሃሳብ አልሸነፍ ሲለው የሰይጣን ፈተና በዛ ብቻ አልቆመም። ስገድልኝና ክቡር፣ ሀብታም፣ ታዋቂና ዝነኛ መሆንን እሰጥሃለሁ አለው። ይህ ፈተና የክብር፣ የገንዘብና የዝና ሃሳብ ስላለበት ሰዎች በቀላሉ የሚወድቁበት ፈተና ነው። አሁንም ግብዣው የሃሳብ ነው። በመጨረሻም ለኢየሱስ የቀረበለት "እስኪ እራስህን ቁልቁል ወርውር" የሚል የነፍስ ግድያ ጥያቄ ነበር። የመጨረሻው ጥያቄ የሰይጣንን የመጨረሻ ፍላጎቱን በግልጽ ያሳየናል፣ ነፍሳችንን ማጥፋት። ሰይጣን በጥጋብ እና በገንዘብ ሃሳብ ምኞት እያስዋኘ ያማልልሃል እንጂ ነፍስህን ካልሰጠኸው ምንም እንደማይሰጥህ እወቅ። ነፍስን የሚያህል ክቡር ነገር በገንዘብ መለወጥ ደግሞ የመጨረሻ አላዋቂነት ነው። በተቃራኒው "ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል" እንደሚል እግዚአብሔር ልጁን ሰጥቶ ፍቅሩን የገለጠልን ገና ያኔ ኃጢአተኞች ሳለን ነው እንጅ ይህንንና ያንን አድርግና ጻድቅ ሆነህ ስትገኝ ህይወትን እሰጥሃለሁ አላለም። የእግዚአብሔር ዓላማ ህይወት ስለሆነ የዘላለም ህይወትን በኢየሱስ ተሰጥቶናል። እርሱን በማመን የሚገኘውን ህይወት መቀበልና አለመቀበል ግን የእኛ ፈንታ ነው።

ይታያል! ምን አለበት 'አንድ ጊዜ እግዚአብሔርን ባየውና እውነተኛ አምላክ እንደሆነ ባውቅ' ብለው አስበው ያውቃሉ? በአንድ ወቅት ከ12ቱ አንዱ "አብን አሳየንና ይበቃናል" ብሎ ኢየሱስን ጠይቆ "እኔ
ይታያል! ምን አለበት 'አንድ ጊዜ እግዚአብሔርን ባየውና እውነተኛ አምላክ እንደሆነ ባውቅ' ብለው አስበው ያውቃሉ? በአንድ ወቅት ከ12ቱ አንዱ "አብን አሳየንና ይበቃናል" ብሎ ኢየሱስን ጠይቆ "እኔን ያየ አብን አይቷል።" የሚል መልስ ተሰጥቶታልና ይህን ጥያቄ ለመጠየቅ አንተ የመጀመሪያው አይደለህም። ዮሐንስ 14:9 በተፈጥሮው የሰው ልጅ ለማመን ማየት ይፈልጋል፣ ችግሩ ግን ያላየነው ካየነው፣ የምናውቀው ከማናውቀው እጅግ የሚበልጥ በመሆኑ እምነታችንን በዓይናችን ብቃት ላይ መመሥረት አያዋጣንም። ያም ብቻ ሳይሆን መጽ/ቅ "የሚታየው የጊዜው፣ የማይታየው የዘላለም ነው" ስለሚል አይተን የተቀበልነው ዕውቀት ከሞት ወዲያ ማዶ ወዳለው ዘላለም የሚሻገር አይደለም። 2ኛ ቆሮንቶስ 4:18 ሰው በተፈጥሮ በሚያየው ነገር ልክ የተወሰነ እንደሆነ የሚያውቅ አምላክ የማይታየው እግዚአብሔር ሰው ሊያየው በሚችል መልክ ሥጋ ለብሶ መጣ፣ እርሱም ኢየሱስ ነው። ኢየሱስ "የማይታይ አምላክ ምሳሌ ነው (image of the invisible God)" ይለናል ቆላስይስ 1:15። ያላመንኩት ስላላየሁት ነው እንዳትል የማይታየው አምላክ የሚታይና የሚዳሰስ ሰው ሆኖ መጥቷልና ላለማመን ምንም ሰበብ የለም። አምነህ እንድትድን እግዚአብሄር ይርዳህ።

በሩ እስቲ ከላይ በመግቢያው ቀስት ጀምረው ትክክለኛውን መስመር ከተከተሉ በመውጫው ቀስት መውጣት ይሆንልዎታልና ይሞክሩ። ልብ ብለን ስናስበው በር የሚያስገርም ነገር አለው። ይከፈታል፣ ይዘጋል፤ ማለት
በሩ እስቲ ከላይ በመግቢያው ቀስት ጀምረው ትክክለኛውን መስመር ከተከተሉ በመውጫው ቀስት መውጣት ይሆንልዎታልና ይሞክሩ። ልብ ብለን ስናስበው በር የሚያስገርም ነገር አለው። ይከፈታል፣ ይዘጋል፤ ማለትም መግባት አለመግባታችን፣ መድረሻችንም ጭምር በበሩ ይወሰናል። ለአሁኑ 3 ዓይነት በሮችን እንመልከት። 1ኛው ቁልፍ አለን፣ የኛ ነው፣ (ለምሳሌ ቤታችን) መግባት በፈለግንበት ሰዓት ከፍተን እንገባለን። 2ኛው የኛ ባይሆንም በሩ ክፍት በሆነበት ሰዓት ማንም መግባት እና አገልግሎት ማግኘት የሚችልበት ነው (ለምሳሌ ባንክ)። 3ኛው በሩ ሁልጊዜ ዝግ ሲሆን የጥሪ ወይም የይለፍ ወረቀት ካለን ብቻ የምንገባበት ነው (ለምሳሌ ቤተ መንግስት)። ከነዚህ ሁሉ ለየት የሚለው ግን በሩን ሌላ ቁልፍ ያለው ሰው የሚከፍተውና የሚዘጋው ሳይሆን በሩ ላመኑት ብቻ ለመከፈት የራሱ ፈቃድ ያለው ነው። ማለትም ካመንን ያስገባናል፣ ካላመንን ዝግ ይሆንብናል። ምክንያቱም በሩ ከእንጨት ወይ ከብረት የተሰራ ሳይሆን ህያው ስለሆነ። ኢየሱስ እንዲህ አለ "በሩ እኔ ነኝ፤ በእኔ የሚገባ ቢኖር ይድናል..."። ዮሐንስ 10:9 ኢየሱስም “እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።" ዮሐንስ 14:6 ይኼኛው በር ከብዙ በሮች አንዱ የሆነና በየትኛው በር ልግባ የሚባልበት የምርጫ ወይም የአማራጭ ጉዳይ ፈጽሞ አይደለም። በእርሱ ብቻ ካልሆነ በቀር ማንም ወደ ዘላለም ህይወት መግባት አይችልም፣ በሩ ራሱ ክርስቶስ ነውና። በክርስቶስ ኢየሱስ እመንና ለዘላለም በህይወት ኑር።

ጠያቂ አያሳጣን ያኔ በልጅነት ክፍል ውስጥ ሳለን እጁን አስር ጊዜ እያወጣ ጥያቄ መጠየቅ የሚወድ ተማሪ ትዝ ይልዎታል? አንዳንዴ ሊደወል ደቂቃ ሲቀር እጁን ሲያወጣ ተማሪውን ቢያበሳጭም እርሱ በሚጠይቀ
ጠያቂ አያሳጣን ያኔ በልጅነት ክፍል ውስጥ ሳለን እጁን አስር ጊዜ እያወጣ ጥያቄ መጠየቅ የሚወድ ተማሪ ትዝ ይልዎታል? አንዳንዴ ሊደወል ደቂቃ ሲቀር እጁን ሲያወጣ ተማሪውን ቢያበሳጭም እርሱ በሚጠይቀው ጥያቄ ምክንያት ብዙዎች ብዙ የማያውቁትን ነገር እንዲያውቁ ምክንያት ይሆነላቸው ነበር። ታምራትና ምልክትን ብቻ አይተው ኢየሱስን ከሚከተሉ ሰዎች መካከል አንድ ቀን አንድ ጥያቄ ኢየሱስን ጠየቁት። ጥያቄው የሁላችንም ነው። መልሱም እጅግ ግልጽና ቀጥተኛ ለሁላችንም የሚሆን ነው። ጥያቄ:- የእግዚአብሔርን ስራ እንድንሰራ ምን እናድርግ? የኢየሱስ መልስ:- "ይህ የእግዚአብሔር ስራ እርሱ በላከው እንድታምኑ ነው።" ዮሐንስ 6:28-29 እግዚአብሔር በላከው በልጁ በክርስቶስ ኢየሱስ ማመን ሃይማኖታዊ ስርዓት አይደለም። ሰዎች እግዚአብሔርን ለማስደሰት በብዙ ውጣ ውረድ ብዙ ስርዓቶችን ለመፈፀም ብዙ ይደክማሉ። በጎ ስራን ማድረግ መልካም ቢሆንም እግዚአብሔር እጅግ የሚወደውን ስራ መስራትን ግን አይተካም፣ ይኸውም በልጁ ማመን። ይህንን ይወቁ፣ በልጁ ማመናችን ዘላለማችንን ይወስናል። "ልጅንም አይቶ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወትን እንዲያገኝ የአባቴ ፈቃድ ይህ ነው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።” ዮሐንስ ወንጌል 6:40

የስራ ህግና የእምነት ህግ የሚባሉ ሁለት ህጎች እንዳሉ ያውቃሉ? ሮሜ 3:27ን ይመልከቱ በስራ ህግ ለመጽደቅ በህጉ የተዘረዝሩትን እጅግ ብዙ አድርግ/አታድርግ ህጎችን በሙሉ መፈፀምን ይጠይቃል። ነገር
ስራ ህግና የእምነት ህግ የሚባሉ ሁለት ህጎች እንዳሉ ያውቃሉ? ሮሜ 3:27ን ይመልከቱ በስራ ህግ ለመጽደቅ በህጉ የተዘረዝሩትን እጅግ ብዙ አድርግ/አታድርግ ህጎችን በሙሉ መፈፀምን ይጠይቃል። ነገር ግን ብዙውን ህግ እድሜ ልክ ጠብቀው በአንዲቱ ቀን በአንዷ ህግ ከተላለፉ በሁሉ እንደወደቁ ተቆጥሮ ከጽድቅ ይሻራሉ። ሰው ደግሞ በሃሳብና በድርጊት በየቀኑ ስለሚስት በስራ ህግ ለመጽደቅ የማይታሰብና እጅግ ከባድ ነው። በሌላ በኩል የእምነት ህግ ሰው በስራው ለመጽደቅ የሚያስችለው ብቃት እንደሌለው አውቆ ሰው በሚያልፍበት ሃጥያት ሁሉ ተፈትኖ ፃድቅ ሆኖ በተገኘው ጌታ በማመን የሚገኝ ጽድቅ ነው። ለመጽደቅ ጻድቅ የሆነውን ጌታ በማመንና በመቀበል ብቻ እንደሆነ ስለሚያስረዳ ይሄኛውም ህግ ነው - ግን የእምነት ህግ። እርስዎ ለመጽደቅ የትኛውን መንገድ ይመርጣሉ - በስራ ወይንስ በእምነት? "...ለሚያምኑ ሁሉ የሆነ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኘው የእግዚአብሔር ጽድቅ ነው፤" ሮሜ 3:22 "ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤" ዮሐንስ ወንጌል 1:12 ጥያቄ ቢኖርዎ ይላኩልን!

ደህና ሲሉህ ሳለህ ሃኪሞችንና ነርሶችን ጠጋ ብላችሁ ስለ አንድ ሰው ሁኔታ ብትጠይቋቸው አተነፋፈሱንና የልብ ምቱን ቆጥረው እንዲሁም ሌሎች የጤነኛነት መገለጫ ምልክቶች መሟላትና መጉደል መርምረው "ዛሬ
ደህና ሲሉህ ሳለህ ሃኪሞችንና ነርሶችን ጠጋ ብላችሁ ስለ አንድ ሰው ሁኔታ ብትጠይቋቸው አተነፋፈሱንና የልብ ምቱን ቆጥረው እንዲሁም ሌሎች የጤነኛነት መገለጫ ምልክቶች መሟላትና መጉደል መርምረው "ዛሬ ማደሩን እንጃ" ብለው የማስጠንቀቂያ ምልክታቸውን ለቤተሰብ ሹክ ይላሉ። እንደሚሉትም ውሎ አድሮ ስንብት ሲሆን አይተናል ሰምተናል። የሰው ልጅ ህይወት እንዴት ነው ብለን ይህንኑ ጥያቄ መጽሀፍ ቅዱስን ብንጠይቅ የሚሰጠን መልስ ግን ፍጹም ልዩ ነው። የሰው ህይወት አደጋ ላይ ነው የሚባለው ትንፋሹ ቁርጥ ቁርጥ ማለት ሲጀምር፣ የልብ ምቱ ሲደክምና አይኖቹ ሲስለመለሙ ሳይሆን እንደ አበባ አብቦ የብዙዎች ዓይን ማረፊያ ሆኖ ሳለ፤ እንደ ለምለም የሜዳ ሳር ብዙዎች በደስታ የሚያርፉበት ሆኖ ሳለ፤ እየገነፈለ አለሁ አለሁ እንደሚል እንፋሎት ሆኖ ሳለ የሰው ህይወት ያን ጊዜ "ዛሬ ማደሩን እንጃ" ብለን ማሰብ እንዳለብን ይነግረናል። ደግሞም ብዙዎች አሉ ብለን ያልናቸው ድንገት ሽኝት ሆኖባቸው አይተናል፣ ሰምተናል። ስለዚህም እወቅበት። አለሁ ይመስገነው! ደህና ነኝ! በምትልባት በዛሬዋ ቀን ላንተ ሲል ደሙን ባፈሰሰለህ በኢየሱስ በማመን በንስሃ ከአምላክ መታረቅ ይሁንልህ። በኋላ ካልክ ሊረፍድ ይችላልና።

photo content

የእግዚአብሔር ቁጣ አንድ ነገር እጅግ በጣም አስፈልጎን ሱፐር ማርኬት ለመግዛት ሄደን የፈለግነው ነገር ሱቅ ውስጥ እያለ ማግኘት ቢያቅተን ሠራተኞች እንዲረዱን እንጠይቃለን። ነገር ግን ያ የፈለግነው
የእግዚአብሔር ቁጣ አንድ ነገር እጅግ በጣም አስፈልጎን ሱፐር ማርኬት ለመግዛት ሄደን የፈለግነው ነገር ሱቅ ውስጥ እያለ ማግኘት ቢያቅተን ሠራተኞች እንዲረዱን እንጠይቃለን። ነገር ግን ያ የፈለግነው ነገር በጥቁርና ነጭ ስሙ ተጽፎ ፊት ለፊታችን ተቀምጦ ካየን በቃ ማንንም ምንም መጠየቅ ሳያስፈልገን የመጣንበትን ጉዳይ እንፈጽማለን። መጽ/ቅ እግዚአብሔር የፍቅር፣ የምህረትና የርህራሄ አምላክ እንደሆነ እንደሚነግረን ሁሉ ደግሞም "የእግዚአብሔር ቁጣ" የሚባል ነገርም እንዳለ በጥቁርና ነጭ (በግልጽ) ተጽፎ እናገኛለን። ይሄንን ለመረዳት ትርጉምና ትንታኔ የሚያሻው እንዳልሆነ እስኪ ራስዎ ይህንን ጥቅስ አንብበው ይረዱ:- "በልጁ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ በልጁ የማያምን ግን የእግዚአብሔር ቍጣ በእርሱ ላይ ይኖራል እንጂ ሕይወትን አያይም።” ዮሐንስ ወንጌል ምዕ 3 ቁ. 36 ይህ ቃል ምንም ትንታኔና ማብራሪያ የሚያሻው አይደለም። ምክንያቱም በግልጽ 'በልጁ የማያምን የእግዚአብሔር ቁጣ በእርሱ ላይ ይኖራል' ስለሚል በልጁ በማመን በህይወት ኑር እንጂ በእግዚአብሔር ቁጣ ስር እየኖርክ ድንገት ሞት እንዳይቀድምህና ለዘላለም ከእርሱ መለየት እንዳይሆንብህ ያስጠነቀቃልና። በልጁ ማመን ማለት ምን ማለት ነው የሚል ጥያቄ ቢኖርዎ ይላኩልን፣ በቃሉ ከተጻፈው በመነሳት በምንችለው ልንረዳዎ እንሞክራለን።

ከኃጥያት አትጫወት በሰሜን አሜሪካ በብዛት የሚገኘው rattlesnake መርዘኛ ከሆኑ የእባብ ዝርያዎች አንዱ ነው። ይህ እባብ በተፈጥሮ ጭራው ላይ ያሉ ጠንካራ ዶቃ መሰል ቀለበቶችን በማንቀጫቀጭ ሊያ
ከኃጥያት አትጫወት በሰሜን አሜሪካ በብዛት የሚገኘው rattlesnake መርዘኛ ከሆኑ የእባብ ዝርያዎች አንዱ ነው። ይህ እባብ በተፈጥሮ ጭራው ላይ ያሉ ጠንካራ ዶቃ መሰል ቀለበቶችን በማንቀጫቀጭ ሊያጠቃው የመጣውን በላተኛ ያስጠነቅቅበታል። ይህ እባብ ጭንቅላቱ ከተቆረጠ በኋላ እስከ 1 ሰዓት ጊዜ ውስጥ የሚነካውን ማንንም በደመነፍስ አፉን ከፍቶ በጥርሱ በመውጋት መርዙን የመርጨት አቅም ያለው መሆኑ ነው። ስለዚህም ሞቷል የምንለውን እንኳን በእጃችን እንዳንነካ ይመከራል። ሰይጣን በክርስቶስ ኢየሱስ ሞትና ትንሣኤ ተሸንፏል። ሆኖም ተሸንፏል ብለን ከተሸነፈው ጋር የኃጢያት ጨዋታ ቢያምረን ሁኔታ ጠብቆ እንደሚናደፍ ከእባቡ ምሳሌ እንማራለንና ከኃጢአት ርቀን ካሸነፈው ጌታ ጋር ተስማምተን መኖር ይሁንልን።

-2147483648_-210163.webp7.42 KB

በጣም ብዙ ተሳትፎአችሁና መልሶቻችሁ ደርሰውናል፣ እናመሰግናለን። ጥያቄዎቹን ለመመለስ በሚል የእግዚአብሔርን ቃል በጥቂቱም ለማንበብ ያገኛችሁት ዕድል የከበረ ነውና በርቱ። ሆኖም ባለፈው የጥያቄ ዙር እንዳሳሰብነው በዚህኛውም ዙር ብዙ መቀዳዳት እንዳለ ለመታዘብ ችለናል። ስለዚህም ባለፈው ዙር በይሁንታ እንዳለፍነው ማለፍ ስለማይኖርብን ከተቀዱት መልሶች የመጀመሪያውን መላሽ ብቻ ለመውሰድ ተገድደናል። ለወደፊቱም በዚህ ረገድ በቀናነት የምናደርገውን ጥረት በታማኝ ተሳትፎአችሁ (መልሱን ሳይሆን ቻነሉን ብቻ በማጋራት) እንድትደግፉን በትህትና እንጠይቃለን። እንደተለመደው ለተመረጡት አሸናፊዎች እየደወልን ሽልማታቸውን የምንልክ ይሆናል።

የሚያሸልም ጥያቄ እስከ አርብ 23/9/16 ድረስ የእነዚህን ጥያቄዎች ትክክለኛ መልስ በውስጥ መስመር ለሚልኩ የመጀመሪያዎቹ 10 ተሳታፊዎች 1000 ብር ሽልማት አሸናፊ ይሆናሉ። 1. መላኩ ገብርኤል ኢየሱስ ከሚለው ሌላ እንዲጠራበት ለማርያም የነገራትን ሌሎች 2 ስሞችን ጥቀስ። ሉቃስ ምዕ 1 2. ኢየሱስን ለመግደል የመጀመሪያውን ሙከራ ያደረገው ማነው? ማቴዎስ 2 3. ኢየሱስ አገልግሎቱን በስንት ዓመቱ ጀመረ? ሉቃስ 3 4. ኢየሱስን የተከተሉት የመጀመሪያዎቹ ሁለት ደቀ መዛሙርት ስም ማን ይባላል? ዮሐንስ ወንጌል 1 5. ኢየሱስ የተጠመቀበት ወንዝ ስም ማን ይባላል? ማቴዎስ 3 6. ኢየሱስ 5000 ሰው በተአምር ከመገበ በኋላ የተረፈው ምግብ ስንት መሶብ ሆነ? ማቴዎስ 14 7. የኢየሱስን እግር በፀጉሯ ያበሰችው ሴት ስም ማን ይባላል? ዮሐንስ ወንጌል 12 8. የመጽሐፍ ቅዱስ ሕግጋትን በሙሉ ይጠቀልላሉ ብሎ ኢየሱስ ያስተማራቸው 2ቱ ትዕዛዛት ምንድናቸው? ማቴዎስ 22 9. ጌታ ባስተማረውና 'አባታችን ሆይ' በሚባለው ጸሎት መጨረሻ ላይ የተጠቀሱት 3 ልመናዎች ምንድናቸው? ማቴዎስ 6 10. ከመጨረሻው እራት በኋላ ከመያዙ በፊት ኢየሱስ ሊጸልይ የሄደበት ቦታ ስም ምን ይባላል? ማቲዎስ 26 11. ኢየሱስን አሳልፎ ለመስጠት ይሁዳ ከካህናት የተቀበለው ገንዘብ መጠን ስንት ነው? ማቴዎስ 26 12. ይሁዳ ጥሎ በሄደው ቦታ የተተካው ደቀመዝሙር ስም ማን ይባላል? ሐዋርያት ሥራ ምዕ 1 13. የሞት ፍርድ ሊፈረድበት የነበረና ኢየሱስ በምትኩ የተሰቀለለት ነፍሰ ገዳይ ስም ማን ይባላል? ማቴዎስ 27 14. የኢየሱስን ሥጋ ለመቅበር ፈቃድ ጠይቆ ከመስቀል ያወረደው ሰው ስም ማን ይባላል? ማርቆስ 15 15. ዘጠኝ የመንፈስ ፍሬዎች አሉ። 1ኛውን፣ 7ኛውንና 9ኛውን የመንፈስ ፍሬ ጥቀስ። ገላትያ 5 16. ለኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ወንጌል የመሰከረለት ሐዋሪያ ስም ይባላል? ሐዋርያት ሥራ 8 17. የኢየሱስ ተከታዮች ለመጀመሪያ ጊዜ 'ክርስቲያን' ተብለው የተጠሩት በየትኛው ከተማ ነበር? ሐዋርያት ሥራ 11 የጎደለውን ሙላ:- 18. _ ያለው ህይወት አለው፣ _ _ የሌለው ህይወት የለውም። 1ኛ ዮሐንስ ምዕ 5 19. በ_ ቀድሳቸው፣ ቃልህ _ ነው ። ዮሐንስ ወንጌል ምዕ 17 20. ከተመሠረተው በቀር ማንም ሌላ መሠረት ሊመሠርት አይችልምና፥ እርሱም _ _ ነው። 1ኛ ቆሮንቶስ 3 ሌሎችም ጥያቄውን በመመለስ ተሸላሚ እንዲሆኑ ያድርጉ። @Bruh_Tesfa

ያለማነቱ እግዚአብሔር በባህርዩ ከፊት የሚመራ መሪ እንጂ ከኋላ የሚከተል ተመሪ አይደለም፤ ሁሉን የፈጠረ ሃያል አምላክ እንጂ ማንም እጁን የሚጠመዘዘው ደካማ ፍጡር አይደለም፤ የነገሥታት ልብ በእጁ ነ
ያለማነቱ እግዚአብሔር በባህርዩ ከፊት የሚመራ መሪ እንጂ ከኋላ የሚከተል ተመሪ አይደለም፤ ሁሉን የፈጠረ ሃያል አምላክ እንጂ ማንም እጁን የሚጠመዘዘው ደካማ ፍጡር አይደለም፤ የነገሥታት ልብ በእጁ ነው፣ እንደ ፈሳሽ ውሃ እንደወደደ ወዲህ ወዲያ ያደርጋል* እንጂ ከማንም ምንም ትእዛዝ የሚቀበል አይደለም፤ የሚከተሉትን በጎች በመልካም የሚመራ ደግ እረኛ እንጂ ለህልውናው እረኛ የሚያሻው በግ አይደለም። ሆኖም የዛሬ 2000 ዓመት ይህ እግዚአብሔር ማንነቱን ትቶ 'የእግዚአብሔር በግ' ሆኖ የሰው ስጋ ለብሶ ወደ ምድር መጣ። አምላክ ሆኖ ሳለ ጲላጦስ ዳኝነት በተሰየምበት እየሱስ ደግሞ ተከሳሽ ሆኖ በቆመበት ሸንጎ "ልሰቅልህ ወይም ልፈታህ ሥልጣን እንዳለኝ አታውቅም?"** እስከሚባል ድረስ 'ሃያል' ማንነቱን ለእኔና ለእናንተ ሲል ተወ። እኛን ለማዳን ሲል ክብሩን ትቶ ስለመጣ የአባቱን ፈቃድ እስከ መስቀል ሞት ድረስ እንኳን ሊታዘዝ ራሱን አሳልፎ ሰጠ። ሆኖም ግን በመስቀል ላይ ሳለ 'የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክ እስቲ ውረድ' ብለው እንዳላገጡበት ሰዎች አንተም 'አምላክ እንዴት ይሞታል' እያልክ በባዶ እንድትመራመር ሳይሆን ይኼ ጌታ የሆነውን የሆነው ለእኔ ነው እንድትል ነው። ጌታ እየሱስን እንደ ግል አዳኝ አድርጎ መቀበል ማለት ይኸው ነው። *ምሳሌ 21፣:1 **ዮሐንስ 19:10 ጥያቄ ቢኖርዎ ይላኩልን!