en
Feedback
Merega Tv = Ethio 360Media

Merega Tv = Ethio 360Media

Open in Telegram
8 780
Subscribers
-424 hours
-157 days
-1130 days
Posts Archive
ትክክለኛ ውሳኔ ነው። በዘረፋ ያገኙንት ህንፃ በብድር እያስያዙ አሻጥር ሊፈጥሩ ነው። ‼

አሁን ለድርድር ዝግጁ ነን ፣ የቱርክ መንግስት ለመንግስት መሳርያ እያሰገባ ነው የኤርትራ መንግስት ዳግም ሊወረን ተዘጋጅቷል ። የህወሓቱ ቃል አቀባይ ጌታቸው ረዳ ከ AFP ጋር ያደረገው ሙሉ ቆይታ AFP :- በትላንትናው እለት የኢትዪጲያ መንግስት ለአንድ ወር የቆየውን የተኩስ አቁም ውሳኔውን በማንሳት ጦርነት ሊጀምር እንደሆነ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ፅ/ቤት አማካኝነት ገልጿል እና በዚህ የመንግስት ውሳኔ ላይ ያላችሁ አቋም ምንድነው? ?? ጌታቸው ረዳ :- በመጀመሪያ ተኩስ አቁም የሚባለው ጨዋታ ነው። 8 ወር ሙሉ ተደብድበናል ፣ ተወረናል ፣ ባጠቃላይ ትልቅ ጉዳት ነው የደረሰብን ። ነገር ግን አፈር ልሰን በሚባል ደረጃ እንደገና አገግመን ስንጠናከር ወዲያው አብይ አህመድ ተኩስ አቁሚያለሁ አለ ። ወደ ጥያቄው መልስ ስገባ የአብይ ውሳኔ የሚጠበቅ ነው ።ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ 2 ክልሎችን በጥቂት ቀናት ውስጥ ተቆጣጥረናል። ይህ አስደንግጦት ነው ለዳግም ጦርነት እየቀሰቀሰ ያለው። የኛ ውሳኔ በተቻለን አቅም እንታገላለን ነው ባጭሩ AFP :- በሰሞኑ ጦርነት በተለይ በአፋር ክልል በናንተ ሀይሎች ከ250 በላይ ህፃናት እና ሴቶች ፣ስደተኞች ጥቃት ደርሶባቸው እንደሞቱ መንግስት እየገለፀ ነው ።በዚህ ጉዳይ ያለዎት አስተያየት ምንድነው? ጌታቸው ረዳ:- በአፋር ግንባር የተከሰተው ድርጊት እንደ ግለሰብ እኔንም አሳዝኖኛል ። ግን በጦርነት መካከል ንፁሃን ይጎዳሉ ይህ ግን መከሰት አልነበረበትም ። በአፋር ግንባር ድል ብንቀናጅም በርካታ የኛም ተዋጊዎች መስዋት ሆነዋል። ብዙ ሀይል በዛ ግንባር ነው ሉዝ ያደረግነው ግን እጅ ሳንሰጥ እየታገልን ነው AFP :- በትግራይ ክልል ድጋሚ ጦርነት ተቀስቅሶ የባለፈውን አይነት እልቂት እና ኪሳራ ከመድረሱ በፊት ለምንድነው ከፌደራል ከመንግስት ጋር በድርድር ችግሩን ለመፍታት ያልተሳካላችሁ ? ጌታቸው ረዳ:- በኛ በኩል ከበቂ በላይ ጥረት አድርገናል ከዚህ ቀደም ያወጣነው ባለሰባት ነጥብ አቋም እንዳለሆኖ አሻሽለን ያስማማል ፣ ያደራድራል ብለን ያሰብነውን መደራደሪያ አቅርበናል። ለአለም አቀፉ ማህበረሰብም እንዲያደራድረን ተማፅነናል። አሁንም እያልን ያለነው " ቅድሚያ እንደራደር ፣ ግጭት ለረዥም አመታት አይተነዋል ፣ ኪሳራ እንጂ ትርፍ የለውም"ብለን ለመንግስት ገልፀናል። ነገር ግን አብይ እኛ ካልጠፋን እንቅልፍ አልወስድ ብሎት የህወሀት ሀይልን ለማጥፋት ለ120 ሚሊዮን ህዝብ ጥሪ አድርጎ ይሄው በትላንተናው እለት ብቻ በርካታ ከባድ መሳሪያዎችን እያስጠጋ ነው። AFP:- በአሁን ወቅት የሰብአዊ እርዳታ እየገባነው? ጌታቸው ረዳ :- መንግስት መቐለን በተቆጣጠረ ጊዜ የገቡ የነበሩ የተወሱ እርዳታ ምግቦች አሉ ።እንዲሁም ከሰሞኑ በአፋር በኩል የገቡ ከ400 በላይ መኪኖች እርዳታ አለ። ነገር ግን ይህ በቂ አይደለም ። በርካታ ህዝብ አሁንም የርሀብ ስጋት ላይ ነው AFP:- ወደ ኤርትራ እንሂድ የኤርትራ መንግስት ጋርስ ለመደራደር አላሰባችሁም? ማለት ኤርትራም ጋር ከባድ ፍጥጫ ላይ ስላላችሁ ጌታቸው ረዳ :- የሻዕቢያ መንግስት ለስሙ መንግስት ይሁን እንጅ ኢሳያስን የሚያዘው አብይ ነው። አብይ ኢሳያስን ውረር ካለው ይወራል። የጋራ ጠላት ያገናኛቸው ስለሆኑ። ከሻዕቢያ መንግስት ጋር ለመወያየት አይታሰብም።

በደ/ብርሃን ከተማ የአሽከርካሪዎች የእንቅስቃሴ ገደብ ተጣለ። በደብረ ብርሃን ከተማ #ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ የተሸከርካሪዎች የእንቅስቃሴ የሰዓት ገደብ ይፋ ሆኗል። የሰዓት ገደቡ ይፋ የሆነው የሰሜን ሸዋ ዞን የመንገድ ትራንስፖርት መምሪያ ፣ የዞን እና የከተማ ትራፊክ አስተባባሪዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ከደብረ ብርሃን ታክሲ አሽከርካሪ የቦርድ አመራሮችና የማህበር አመራሮች ጋር በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ ውይይት ከተደረገ በኃላ ነው። በዚህ መሰረት ፦ 1ኛ. ከዛሬ ነሃሴ 6 ቀን 2013 ዓ/ም ጀምሮ የከተማ ታክሲ ከጠዋቱ 11፡00 እስከ ምሽት 2፡30 ድረስ ብቻ እንቅስቃሴ ማድረግ የሚቻል ሲሆን የሌሊት ስምሪት ተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ የሚቀር ይሆናል። 2ኛ. የህዝብ ማመላለሻ ተሸከርካሪዎች ከጠዋቱ 12፡00 ሠዓት እስከ ምሽት 2፡30 ድረስ ብቻ የሚንቀሳቀሱ ይሆናል። እያንዳንዱ የከተማው ማህበረሰብ ተደራጅቶና ከጸጥታ አካላት ጋር ተቀናጅቶ 24 ሰዓት አካባቢውን ነቅቶ መጠበቅ እንዳለበትና የተለየ አጠራጣሪ ነገሮችን ሲመለከቱ በአካባቢው ላሉ የጸጥታ አካላት በመጠቆም የመረጃ አካል እንዲሆኑ ተጠቁሟል። በየኬላዎች የጸጥታ አካላት ከአካባቢው ወጣቶች ጋር በመቀናጀት የተጠናከረ ፍተሻ ከባጃጅ እስከ ትልልቅ ተሸከርካሪዎች ተግባራዊ የሚደረግ ይሆናል። መረጃዉ የደ/ብርሃን ኮሙዩኒኬሽን ነው።

ከፍተኛ ጥንቃቄ ደሴና ኮምቦልቻ አማራ ሆኖ፣ ደሴና ኮምቦልቻ የሆቴል የሸቀጥ ዋጋ የጨመረ አልሰማሁም። ደሴና ኮምቦልቻ ጅምላ አከፋፋይ፣ የሸቀጣሸቀጥ ነጋዴዎች፣ ባለ ፔኒሲዮኖች፣ ትራንስፖርተሮች የሆኑ ብዙ ጁንታዎች አሉ። ሻጥር እየፈጠሩ ነው። በከተማዎቻችን ውስጥ ተቀመጥው በኢኮኖሚ ዘርፍ የትሕነግ አዋጊና ተዋጊ ሆነው እየሠሩ ነው። የደሴና የኮምቦልቻ ከተማ ሕዝም ስም እያጠለሹም ነው። እነዚህን ጁንታዎች የደሴ እና የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደሮችና የፀጥታ ኃይል እነዚህን ጁንታዎች እርምጃ ሊወስድባቸው ይገባል። # Wubshet Mulat

photo content
+1

አሸባሪው ህወሓት በጋሊኮማ በንፁሀን አርብቶ አደሮች ላይ የፈፀመውን አሰቃቂ ጭፍጨፋ አስመልክቶ በአፋር ክልል የሶስት ቀን ሀዘን ታወጀ ********** (ኢ.ፕ.ድ) አሸባሪው የህወሀት ጁንታ በአፋር ክልል በፈንቲ ረሱ በጋሊኮማ ጊዚያዊ መጠለያ ተጠልለው የነበሩ በንፁሀን አርብቶ አደሮች ላይ የፈፀመውን አሰቃቂ ጭፍጨፋ አስመልክቶ ከዛሬ ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት የሀዘን ቀን እንዲሆን የአፋር ክልል መንግስት አውጇል። የአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ አሚና ሴኮ ይህን ጉዳይ አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ ጁንታው በጋሊኮማ በንፁሀን ላይ ያደረሰው ጭፍጨፋ እጅግ ዘግናኝ እንደነበር ገልፀው የክልሉ መንግስትም ይህን ጥልቅ ሀዘን አስመልክቶ የሶስት ቀናት ሀዘን ማወጁን ገልፀዋል። ታሪክ የማይረሳው 107 ህፃናትን፣ 89 ሴቶችን እና 44 አዛውንቶችን ህይወት የቀጠፈውን አረመኔያዊ ጭፍጨፋ ያካሄደው የህወሀት ጁንታ ድንገት በከፈተው በከባድ መሳሪያ የታገዘ ጥቃት ንፁሃን አርብቶ አደሮች መገደላቸውና መቁሰላቸው እንዲሁም በመጋዝን የነበረ የአስቸኳይ እርዳታ ሙሉ በሙሉ ማውደሙ ይታወሳል። ጁንታው ገና ቀድሞ በረሀ እያለ የነበረውን የአፋርን መሬቱ ወደ ራሱ የማካለል ቅዠትን በግርግር መፈፀም የሚያስችለው መስሎት በፈፀመው ወረራ አርብቶ አደሩን ማህበረሰብ የጥቃት ሰለባ አድርጎታል። አሽባሪው ህወሀት በተለይም በጋሊኮማ ዘግናኝ የዘር ማጥፋት ጥቃት ፈፅሟል፤ ይህንንም ዘግናኝ ጭፍጨፋ አስመልክቲ በአፋር ክልል ውስጥ ከዛሬ ነሀሴ 05 /2012 እስከ ነሀሴ 07/2013 ድረስ የሀዘን ቀን እንዲሆንና የአፋር ክልል ባንዲራም ዝቅ ብሎ እንዲውለበለብ የክልሉ መንግስት ወስኗል። ይህን የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ ኢ ሰብአዊ ድርጊት ውድ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች በያሉበት ሆነው እንዲቃወሙና እንዲያወግዙ ክልሉ ጥሪውን አስተላልፈዋል።

መዘናጋት ማቆም አለብን! ዛሬ የተኩስ አቁሙ እንደተነሳ ግልፅ ሆኗል። ይህ ማለት ግን ጦርነቱን የሆነ አካል ይጨርሰዋል ብሎ እጅን አጣጥፎ መቀመጥ፣ የተጀመረውን የሕልውና ትግል መርሳት አለብን ማለት አይደለም። እንዲያውም ዝግጅት የሚያስፈልገው ከአሁን በኋላም ነው! 1) ትህነግ የሚተኩስብንን መሳርያ የወሰደው ከመከላከያ ሰራዊቱ ነው። ሰራዊቱን በሕዝብ አስከብቦ የፈፀመውን ወንጀል አንድ ቀን በይፋ ሲነገር ብዙ ቁጣ የሚቀሰቅስ ነው። ብዙ ጀግኖቻችን "እጃችን አንሰጥም" ብለው ራሳቸውን ሰውተዋል። ከተማ ውስጥ የሚያልፍ የሰራዊቱ አባል ላይ በርበሬ በትነው መሳርያ የቀሙ፣ ያስገደሉ አሉ። ትህነግ ከአንዴም ሁለቴ ገድሎ መሳርያውን የቀማው መከላከያ ሰራዊት ላይ ትኩረት ያደረገው ሀገርና ሕዝብ የማዳን አቅም ስላለው ነው። መሳርያ ስላለው ነው፣ የተሻለ ስልጠና ስላለው ነው። ትህነግ በዚህ መጠን ጎድቶ ሀገር ለማፍረስ የሰራበትን ሰራዊት ተቀላቅሎ ሕዝብን መጠበቅ፣ ሀገርን ማዳን ያስፈልጋል። 2) ቅሬታዎች አሉ። የሰራዊቱ አባላት "ሸሽተዋል፣ መሳርያ አስረክበዋል" ተብለው ይወቀሳሉ። ልብ ያለው ገብቶ ያን መሳርያ ለሕዝብ ማዳኛ መጠቀም ነዋ! አጋጣሚው ተመቻችቷል። ሌላውን ከመውቀስ ገብቶ ስልጠናውን ወስዶ፣ መሳርያውን ለሀገር ጠበቃ፣ ለሕዝብ መጠበቂያ ማድረግ ነው። የምን ዳር ቆሞ ወቀሳ ነው? ተጠርተሃል። ሰራዊቱን ተቀላቀል ተብለሃል! 3) ኮ/ል ሻምበል ድንጋይ ተንተርሶ ትህነግን እረፍት የሚነሳው መከላከያ ሰራዊት ውስጥ ሆኖ ነው። የምታደንቀው ጄ/ል አበባው ያለፈው በዚሁ ተቋም ነው። ጄ/ል ተፈራ ማሞ ያለፈው በዚሁ ተቋም ነው። ያውም የትህነግን ዘረኝነት ችሎ፣ አብዛኛዎቹ ታግለው። መስዋዕትነት ከፍለው። የምታከብረውን ጀኔራል ለመሆን ተራ ወታደር ለመሆን መመዝገብ ይጠበቅብሃል። ባለ ከዘራው ከዘራ የያዘው ለጌጥ አይደለም። ሲፋለም ቆስሎ ስለነበር ነው። ቆስሎም ሲያዋጋ ነው የከረመው። መስዋዕትነት ይጠይቃል። የምታደንቃቸውን ሆኖ መገኘትን ይጠይቃል። እድል ተመቻችቶልሃል ተቀላቀል። 4) የሰራዊቱ አባላት ሲሸሹ "አትሸሹ" ብለህ መንገድ ላይ ይዘሃል፣ ተቆጥተህ፣ ለምነህ መልሰሃል። አንተ ብትሆን ኖሮ መለመን አይጠበቅብህም። ሌላውን ከመለመን ራስህ ገብተህ የበኩልህን ማድረግ ነው። ተጠርተሃል። ተቀላቀል! 5) የሆነ ችግር ሲፈጠር "መከላከያ ሰራዊቱ የት ሄዶ ነው?" አይደል የምትለው? ዘብ ይሆናል፣ ሊሆን ይገባል ብለህ ስለምታስብ ነው። ራስህ ዘብ መሆን ነው። እድል ተመቻችቶ፣ ግባ ተብለሃል! 6) ብዙ ጊዜያትን ተዘናጋን። ባለፈው 9 ወራት ብዙ ተዘናጋን። ወጣቱ ተቀላቀል ሲባል አልሰማ ብሎ፣በመጨረሻ የ15 ቀን ስልጠና ላይ ተጣደፈ። ደንበኛ ስልጠና ማግኘት ሲችል፣ መሳርያና እውቀት መያዝ ሲችል አልፈልግም ብሎ ከተማው ሲወረር ለመሸሽ የተገደደ አለ። ቢታጠቅ ለራሱ ቀርቶ ለሕዝብና ለሀገሩ መሆን በቻለ ነበር። ይህ ወረራ ብዙ አስተምሮናል። መዘናጋት አስጠቂ መሆኑን አሳይቶናል። ትናንት ንቀን፣ እንደዋዛ ያሳለፍናቸው እንደሚቆጩን አሳይቶናል። 7) ድሮ ትህነግ መከላከያ ሰራዊቱን በብዛት ያዘው ብለን ስንወቅስ ነበር። ወገኖቻችን በማንነታቸው ተፈናቀሉ ብለን ጮኸናል። አሁን "ና ግባ" ስትባል ሳታቅማማ ግባ። ገብተህ ችግር ካለ ታርማለህ። ግን ለድርድር የሚቀርብ አይደለም። የሕዝብና የሀገር መዳኛ ነው። ቁጭ ብለህ አይተህ ነገ ሀገር ቢፈርስ ትርፍህ ፀፀት ብቻ አይደለም። አንተም አትተርፍም። ለመፀፀት አትበቃም! መከላከያን ተቀላቀል። ሌላ መዘናጋት አያስፈልግም! ችግር ቢኖር ውስጥ ሆነህ ትፈታዋለህ! ትታገላለህ! ትህነግ ሊያጠፋው የፈለገውን ኃይል ገብተህ አጠናክር! መሳርያውንና እውቀቱን ለሕዝብና ሀገር ዘብ አውል! ልዩ ኃይሉን የሚቀላቀለው አበረታች ነው። ልዩ ኃይል ግን መድፍ የለውም። አውሮፕላን የለውም። ይህን መሳርያ ተጠቅመህ ሀገር የምታድነው መከላከያን ስትቀላቀል ነው። ከልዩ ኃይሉ በተጨማሪ መከላከያ ሰራዊቱን መቀላቀል አዋጭ ነው! መከላከያ ሰራዊቱን መቀላቀል ትክክል የማይመስለው ካለ ሁለት ሶስት ጊዜ ያስብ! መከላከያ ሰራዊቱን ተቀላቀሉ! (ጌታቸው ሽፈራው)

photo content
+1

ሰበር በብርሸለቆ መሰረታዊ ውትድርና ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት የ34ኛ ዙር ምልምል ሰልጣኞች የመክፈቻ ስነ ስርዓት ተካሄደ። ኢትዮጵያ ወይም ሞት‼

ሰበር ‼️ ወደ መርሳ ሾልኮ ገብቶ የነበረው ዱቄታም ጁንታ በጀግናው መከላከያ ሰራዊታችንና በአማራ ሕዝባዊ ሃይል ታጭዶ ተወቅቷል። በህይወት የተረፈውም እግሬ አውጭኝ ብሎ ፈርጥጧል። የአባ-ገትዬ አገር መርሳም በልጆቿ ቁጥጥር ስር ገብታለች። በተባበረ ክንድ ህልውናችንን እናስቀጥላለን፤ ትህነግና ቅርፊቶቿን ታሪክ እናደርጋቸዋለን‼️ በThomas Jejaw Molla

photo content

ወንድሞቼ እንዳይኮላሹ፣ ሕዝቤ እንዳይዋረድ እዘምታለሁ!

photo content

የባሕር ዳር ከተማ በምሽት የተሽከርካሪ እንቅስቃሴ ተገደበ። የከተማው አስተዳደር ከወቅታዊ የጸጥታ ሁኔታ ጋር በተያያዘ በምሽት የሚንቀሳቀሱ የባለ ሶስት እግር የታክሲ አገልግሎት ሰጭ ተሽከርካሪዎች ቁጥር እንዲገደብ መወሰኑን አስታውቋል።የከተማ አስተዳደሩ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ዘመነ ዘውዱ ለዶቼ ቬለ እንደገለፁት ከባለሶስት እግር ተሽከርካሪ (ባጃጅ) ማህበራት ጋር በተደረገ ስምምነት መሰረት 120 ባጃጆች ብቻ የሌሊት የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጡ ተወስኗል፡፡ በቁጥር የተለዩ እነዚሁ ተሽከርካሪዎች ከምሽት 3 ሰዓት እስከ ንጋት 11 ሰዓት ድረስ አገልግሎት እንደሚሰጡ ኃላፊው ተናግረዋል።ዶይቸ ቨሌ እንደዘገበው በከተማዋ በሕዝብ ማመላለስ ስራ (የታክሲ አገልግሎት ) የተሰማሩ ከ4,000 በላይ ባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪዎች (ባጃጆች) ይገኛሉ። የደሴ ከተማ አስተዳደር ከዛሬ ጀምሮ ተፈጻሚ የሚሆን የምሽት የሰዓት እላፊ ታውጇል።

የደቡብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ ቀለመወርቅ ምህረቴ ለክብርና ለህልውና ዘመቻ የአርበኝነት ጥሪ አቀረቡ፡፡ ዋና አስተዳዳሪው በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ለሕዝቡ ባስተላለፉት መልዕክት "ጀግንነትክን ሊፈትንህ ክብርህን ሊገፍህ ወራሪና ባንዳ ከደጃፍህ ደርሷል፤ ይህ ቡድን ባለፉት 50 ዓመታት አንተን ለማጥፋት ትግል ያደረገ ስለመሆኑ ለአንተ አይነገርህም" ብለዋል፡፡ አሸባሪው የትህነግ ቡድን ሀገርን ሊያፈርስ እና አማራን ሊያንበረክክ ከውስጥና ከውጭ ባንዳዎች ጋር አንድ ሆኖ ሕዝብን መከራ ለማስከፈል ያለ የሌለ ኀይሉን ተጠቅሞ የሞት ሽረት እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ አሸባሪ ቡድኑ ባለፉት ቀናት ከሰሜን ወሎ ደጋማ አካባቢዎች ለማስወጣት ከፍተኛ አቅም እንዳለን ትናንት በጨጨሆ ግንባር በዋለው አውደ ውጊያ እንደታየ ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም በደቡብ ጎንደር ዞን ላይ ጋይንት፣ ታች ጋይንት፣ ነፋስ መውጫ፣ ሰዴ ሙጃ፣ እብናት፣ ጉና በጌምድር እና መቀጠዋ ወረዳዎች የሚገኝ ትጥቅ ያለው አርበኛ ወደ ግንባር ተንቀሳቅሶ እየተፋለሙ ካሉ ወንድሞቹ ጋር በመሰለፍ ጠላትን አይቀጡ ቅጣት እንዲቀጣ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ደራ፣ ፎገራ፣ ሊቦ ከምከም፣ አንዳቤት፣ ፋርጣ፣ ደብረታቦር፣ ወረታ፣ መካነ ኢየሱስ፣ አዲስ ዘመን፣ እስቴ እና ስማዳ ትጥቅ ያለው ወገን በአደረጃጀቱ የግንባር ጥሪ እስኪደረግለት አካባቢውንና ሕዝቡን ነቅቶ እንዲጠብቅ አሳስበዋል፡፡ ሁሉም ባለው የኀይል አደረጃጀት በመጠቀም፣ ከመሪዎች አመራር በመቀበል፣ የሚሠጠውን መመሪያ ብቻ በመፈጸምና ከዚህ ውጭ የሚሆን ኀይል ሲያጋጥምም ከአካባቢው መዋቅር ጋር በመነጋገር በቁጥጥር ስር ማዋል እንደሚገባው ገልጸዋል፡፡ "መሪዎችህ ከዘማች አርበኛቸው ጋር ጠላትን እየተፋለሙ ነው፤ መሪህ ግንባር ኾኖ አንተ ከቤትህ እንዳትውል፤ በፈጣሪ ስም ይዥሀለሁ" ብለዋል፡፡ አሚኮ

#ቅድመ_ማስጠንቀቂያ‼️ _ለውጫሌ ወጣቶች _ለሃይቅ ወጣቶች የወያኔ ወታደር ገጠራማውን ቦታ ከወልዲያ ወደ ኮምቦልቻ የሚሄደውን የአዋሽ ኮምቦልቻ ሀራ ገበያ የባቡር መንገድን Access road ለመጠቀም እየሞከሩ ነው። _ ከሃራ ከተማ ወደ #ጉባላፍቶ ወረዳ የገጠር ቀበሌዎች የባቡር መስመር የሚያልፍባቸውን የገጠር ቀበሌዎች የጎጉር ቀበሌ ተራራማማ ቦታ የቂሌአዳሜ ቀበሌ ተራራማማ ቦታና በአካባቢው!! _ #ሀብሩ ወረዳ ገጠራማ ቀበሌዎች ጃሮታ ካምኛ መርሳ ፋጂ ጊራና ካምኝ ገጠራማ ቀበሌዎች አካባቢ ያሉ ተራራዎችን በአካባቢው _ #ተሁለደሬ ወረዳ ቀበሌ 027 ሚሌ ኮትቻ እሰከ ቀበሌ 016 ጣቢሳ ድረስ ያሉትን ተራራማ ቦታዎች!! _ በሁሉም የአማራ ክልል አካባቢ ጥንቃቄ እና ጥበቃ የሚያስፈልገው እንዳለ ሆኖ የህወሓት ወታደሮች ወደ ደሴና ኮምቦልቻ ይሄንን Access road ለመጠቀም እየሞከሩ ነውና ቅድመ ጥንቃቄ ያስፈልጋል፡፡ በውስጥ መስመር የተላከ መረጃ!!

photo content

photo content
+2

የሕወሓት ምርኮኞች👇

በአሁኑ ሰአት በአማራ ቴሌቪዥን የትህነግ የደም እጆች የሚል ዶክመንተሪ እየተላለፈ ይገኛል። እንድትመለከቱት እንጋብዛለን