en
Feedback
Merega Tv = Ethio 360Media

Merega Tv = Ethio 360Media

Open in Telegram
8 780
Subscribers
-424 hours
-157 days
-1130 days
Posts Archive
ሰበር‼️ #Ethiopia : በኢትዮጵያ ድንበር አካባቢ የተተከሉ የሱዳን የኔቶርክ ማከፋፈያ ጣቢዎች መደብደባቸውን የገዳሪፍ ግዛት አስተዳደር ለሀገሪቱ ሚዲያዎች ተናገረ። አስተዳደሩ ለሚዲያዎች በሰጡት ቃል ላይ ከምሽቱ 3 ሰአት ጀምሮ ከአማራ ሀይል በተተከሶ ከባድ መሳሪያ ድንበር ላይ የተከልናቸው የቴሌኮም ማከፋፈያ ጣቢያቸው ወድመዋል ያለ ሲሆን በየትኛው አቅጣጫ የተተከሉ ማከፋፋያዎች እንደተደበደቡ ግን አልተናገረም ! በነገራችን ላይ የሱዳን ሲም ካርድ በሁመራና በመተማ በጉባ አቅራቢያ ቀበሌዎች ላይ ሙሉ አገልግሎት ይሰጥ ነበር። ከዚህ በፊት ሁመራ ላይ ሙሉ በሙሉ ኔቶርክ ሲቋረጥ ህዝብ በሱዳን ሲም ካርድ ሲጠቀም ቆይቷል። . ሱሌማን አብደላ

‼️ዛሬ ወደ ደብረ ታቦር ከባድ መሳሪያ ተወርውሮ እንደነበር ተሰምቷል።❗ የደቡብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ቀለመወርቅ ምህረቴ ዛሬ ወደከተማዋ የተወረወሩት የከባድ መሳሪያዎችን አስመልክቶ ፤ "ከባድ መሳሪያዎቹ ጠላት ያለ የሌለ አቅሙን ተጠቅሞ ደብረታቦርን የማጥፋት ከፍተኛ ፍላጎት ማሳያ ነው" ሲሉ ገልጸውታል። ዋና አስተዳዳሪው ፤ "ጠላት እየተመታ እግሬ አውጭኝ ብሎ እየፈረጠጠ ስለሆነ እንረጋጋ፤ አሁን ከወረወረው ውጭ ወደ ከተማችን ለመወርወር እንዳይችል እየተቀጠቀጠ ነው" ሲሉ አክለዋል። በሌላ በኩል የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የህወሓት ቡድን አባላት ሰርገው በገቡበት የጋሸና አካባቢ ሽንፈትን ተከናንበው ተደምስሰዋል ሲል አሳውቋል። የሀገር መከላከያ የደቡብ ዕዝና ሌሎች የፀጥታ አካላት ባደረጉት ፈጣን ኦፕሬሽን ድል መገኘቱ ተገልጿል። ከ4 የሰሜን ወሎ ወረዳዎች ህወሓት ተጠራርጎ እንደወጣ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ገልጿል።

ጌች ያለበት ቦታ ታውቋል። አሁን ያለው ደቡብ ጎንደር ፋርጣ ሳሊ ከምትባል የገጠር ከተማ ነው። ይህ ሰው ክትትል እየተደረገበት ሲሆን፣ ከፋርጣ ምድር ያመልጣል ብዬ አላስብም። *ጉና ላይ ዳግማዊ ድል ተመዝግቧል። የኢትዮጵያ ሕዝባዊ ሠራዊት ከ16 ጊዜ በላይ በማጥቃት፣ ጁንታው በጉና ተራራ ላይ የቀበራቸውን ዲሽቃ፣ መትረየስ፣ ባዙቃ፣ የረጅም ርቀት ተወንጫፊ ሮኬት፣ ፈንጂዎች፣ መገናኛ ሬዲዮኖች፣ የሳተላይት ስልኮችና ጥይቶችን በቁጥጥር ስር አውሏል። በትናንትናው እለት በዚሁ ተራራ ከ1500 በላይ ምርኮኛ መያዙን ጽፌ ነበር። *አሁን ጋሸና፣ እስታይሽ፣ ቀበሮ ሜዳ፣ አሁንተገኝ፣ ኮን፣ ሐሙሲት፣ እን አርቢት በሕዝባዊ ሠራዊቱ ቁጥጥር ስር ገብተዋል። *ጁንታው ዛሬ ረፋዱ ላይ እንጥፍጣፊ እድሉን ለመሞከር ከባድ መሳሪያ ወደ ደብረታቦር ከተማ መድሃኒዓለም ሰፈር ተኩሶ ነበር። አይቀጡ ቅጣት ሲቀጣ መውጫ አጥቶ ነው። ነገርግን ከዚህ በኋላ እንኳን መተኮስ የመተንፈስ እድል አይኖረውም። (ታደለ ጥበቡ)

photo content
+2

ሰበር ➖➖➖➖ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ እንኳን ሚግ ወፍ ስታልፍ እናያለን ያሉት ጄነራል ይልማ ዛሬ የግብጹን ድሮን አውርደውታል‼️ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ፎቶ ለማንሳት ከመሬት በ50,000 ጫማ የከፍታ ርቀት እየበረረ በሱዳን በኩል ወደ ኢትዮጵያ ሊገባ የነበረ የግብፅ ድሮን ሱዳን ድንበር ላይ እንዳለ በኢትዮጵያ ዘመናዊ አየር መቃወሚያ ተመቶ አመድ ሆኗል። ምንጭ Ethiopia News ን ጠቅሶ ግዕዝ ሚዲያ

በቱርክ የስራ ጉብኝት ለማድረግ ወደስፍራው ያቀኑት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የእንኳን ደህና መጡ አቀባበል ተደረገላቸው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቱርኩ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ጣይፕ ኤርዶኻን ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

ህወሓት ሂሳቡን የሚያወራርደው ከመላው ኢትዮጵያውያን ጋር እንጂ ከአማራ ህዝብ ጋር ብቻ አይደለም-አቶ ሙስጠፌ አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 12፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሃመድ በክልሉ ከተለያዩ ቢሮዎች ከተውጣጡ አመራሮች አና ሰራተኞች ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም በወቅታዊ ሀገራዊና ክልላዊ ጉዳዮች፣ በመንግሥት ሰራተኞች ኑሮ መሻሻል እንዲሁም አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ መክረዋል፡፡ ሰራተኛች በፍጆታ እቃዎች እና በኑሮ ውድነት፣ ከመስሪያ ቤቶች ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮች፣ በሰራተኞች ምደባና ደመወዝ ጋር ተያይዞ የተለያዩ ጥያቄዎች እና አስተያየቶችን አንስተዋል። በክልሉ የነበሩ አመራሮች ከአሸባሪው ህወሓት የሚቀበሉትን ተልዕኮዎች ለማስፈጸም ብቻ ሰራተኛውን ለስብሰባ ይጠራ እንደነበርም ነው የገለጹት፡፡ የመንግሥት ሰራተኞቹ አሸባሪውን የህወሓት ጁንታ በሚነዛው ፕሮፓጋንዳና መሠረተ ቢስ መረጃዎች እንደማይበገሩም ተናግረዋል። የሶማሌ ክልል ሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱልቃድር አብዲ÷ የመንግሥት ሰራተኞች የሚያነሷቸው ጥያቄዎች መፍትሔ እያገኙ መሆኑን በመጥቀስ÷ ሁሉም ባለው የትምህርት ደረጃ መሰረት እየተመደበ ነው ብለዋል፡፡ አቶ ሙስጠፌ ሙሃመድ በበኩላቸው÷ ከለውጡ በኋላ በሶማሌ ክልል ሁለንተናዊ ለውጥ እንደመጣና በክልሉ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በሰላም እየኖረ መሆኑን አውስተዋል፡፡ በሶማሌ ክልል ማንም ሰው በብሄሩና በአመለካከቱ ችግር እንደማይደርስበትና ለህግ ተገዥ ሆኖ ሃሳቡን በነፃነት የመግለጽ መብት እንዳለውም ጠቅሰዋል፡፡ ህወሓት በፕሮፓጋንዳ ሀገር የማፍረስ አቅም የለውም ያሉት አቶ ሙስጠፌ÷ አወራርዳለሁ የሚለው ሂሳብ ከአማራ ጋር ብቻ ሳይሆን ከመላው ኢትዮጵያውያን ጋር መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡ ከአሸባሪ ህወሓት ጋር ግንኙነት ያላቸው ግለሰቦች የክልሉ መንግሥት ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስድም አረጋግጠዋል፡፡ የመንግሥት ሰራተኞች ለህዝቡ ተገቢ አገልግሎት እንዲሰጡና ከወገንተኝነትና ከፍርሃት በጸዳ መልኩ ስራቸውን እንዲሰሩ መልዕክት ማስተላለፋቸውን ከሶማሌ መገናኛ ብዙሃን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሌጅ ለ8ኛ ጊዜ ያሰለጠናቸውን ምልምል የልዩ ኀይል ፖሊሶች እያስመረቀ ነው፡፡ የምልምል የልዩ ኀይል ፖሊሶቹ የምርቃ ስነ ስርዓት በደብረ ማርቆስ ከተማ እየተካሄደ መሆኑን አሚኮ ዘግቧል፡፡

photo content
+1

የምዕራብ ዕዝ 24ኛ ቴዎድሮስ ክ/ጦር በማይጠብሪ ግንባር በጠላት ላይ ከባድ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ አደረሰ‼ አሸባሪውን ቡድን በማደን እየደመሰሰ ነው‼ #Ethiopia : የ24ኛ ቴዎድሮስ ክፍለ ጦር በአሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ቡድን ላይ የማያዳግም ርምጃ እየወሰደ ነው፡፡ በዚህም ጦሩ በማይጠብሪ ግንባር በጠላት ላይ ከባድ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ ማድረሱን አስታውቋል፡፡ ክፍለ ጦሩ የተለያዩ መሣሪያዎችን ማርኳል፤ በአሁኑ ጊዜም የተበታተነውን የአሸባሪውን ቡድን አባላት በማደን እየደመሰሰ መሆኑን አመላክቷል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ወደ ቱርክ ሊያቀኑ ነው! #Ethiopia : ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከፕሬዝደንት ኤርዶሀን በቀረበላቸው ግብዣ መሰረት ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ነገ ወደ ቱርክ እንደሚያቀኑ የቱርክ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን መስሪያ ቤት ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡ ይህ ጉብኝት የሀገራቱ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረበትን 125 ኛ ዓመት የሚዘክር እንደሆነም ተገልጿል። መሪዎቹ በሀገራቱ ሁለትዮሽ ግንኙነት ሁለንተናዊ ገፅታዎች፣ ትብብርን ለማጠንከር ሊወሰዱ በሚገባቸው እርምጃዎች ላይ እንዲሁም ዓለም አቀፋዊና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።

አስቸኳይ መረጃ :- መረጃው ለሁሉም ተደራሽ እንዲሆን ሼር ይደረግ !!!! በሀሰተኛና ህጋዊ ባልሆነ ደብዳቤ የጥበቃ ኬላዎችን ለማለፍ ፣ በንቃት አካባቢውን እየተከታተለ የሚገኘውን ማህበረሰብ ለማደናገር ፣ ህገ ወጥ ስራዎችን እና ተፈላጊ ግለሰቦችን ለማሸሽ ከታች የተገለፁትን የሠሌዳ ቁጥር በመጠቀም እንቅስቃሴዎችን ለማድረግ የታሠበ እና በእንቅስቃሴም ያሉ መሆናቸውን በመረዳት ህዝባችን ተሽከርካሪዎቹን በንቃት ክትትል በማድረግ ለፀጥታ አካል አሳልፎ እንዲሠጥ ይደረግ ። የሰሌዳ ቁጥር - 35 ዕድ 4323 35 ዕድ 109 35 ዕድ 6581 35 ዕድ 062 35 ዕድ 4476 35 ዕድ 3387 12 ዕድ 017 4-አማ-03783 4-አማ-00149 ከላይ ከተገለፁት ተሽከርካሪዎች ውስጥ በእርዳታ ድርጅት ታርጋ ከተመዘገቡት ሁለቱ ተሽከርካሪዎች ህገ ወጥ መሳሪያ እና ፀጉረ ልውጥ ሰዎችን ይዘው በፀጥታ ሀይላችን የተያዙ ሲሆን ቀሪዎቹን አሁንም በንቃት ክትትል ማድረግ ይኖርብናል ። ህጋዊ ያልሆነውን ደብዳቤ ፣ የሰሌዳ ቁጥር እና የሹፌሮቹን ስም በተለጠፈው ፎቶ ላይ ያገኙታል ።

photo content

የሀገር መከላከያ ሠራዊትና የአማራ ክልል የጸጥታ ኀይል በማይጠብሪ ግንባር ከፍተኛ ድል እያስመዘገበ መሆኑን የ54ኛ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ኮሎኔል የሺበር አዳነ ተናገሩ። ባሕር ዳር፡ ነሐሴ 11/2013 ዓ.ም (አሚኮ) በማይጠብሪ ግንባር ለዳግም ወረራ የተነሳው አሸባሪውና ተስፋፊው የትህነግ ቡድን በሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ በአማራ ልዩ ኃይል፣ ሚሊሻና ፋኖ እየተደመሰሰ መሆኑን የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን የጋዜጠኞች ቡድን በግንባር ተገኝቶ ተመልክቷል። በማይጠብሪ ግንባር ያነጋገርናቸው የ54ኛ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ኮሎኔል የሺበር አዳነ እንደገለጹት ሽብርተኛው ትህነግ ከፍተኛ ኪሳራ ውስጥ ገብቷል። የመንግሥት የጸጥታ ኃይል ጠላትን ለማሸነፍ ሰፊ ቅድመ ዝግጅት አድርጎ መግባቱ እየተመዘገበ ላለው ድል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ኮሎኔል የሺበር አስታውቀዋል። ኮሎኔሉ ሽብርተኛው ትህነግ ከዓመታት በፊት የቀየሰውን የጦርነት ስልት እየተከተለ መሆኑን ነው የተናገሩት። ዋና አዛዡ አሸባሪው ቡድን በአሁኑ ወቅት ጦርነቱን በመሣሪያ ሳይሆን በሰው ማዕበል ለመምራት ጥረት እያደረገ ነው፤ አቅሙም እየተዳከመ መጥቷል፤ የትግራይ ወላጆችም ልጆቻቸው የእሳት ራት ከመሆናቸው በፊት ሊታደጓቸው ይገባልም ብለዋል። እንደ ኮሎኔሉ ገለጻ በመንግሥት የጸጥታ ኃይል ጠንካራ ክንድ የአሸባሪ ቡድኑ አባላት እየተደመሰሱ ነው፤ ሠራዊቱ በቀጣይም ጦርነቱን በድል ለማጠናቀቅ በሚያስችል አስተማማኝ ቁመና ላይ ይገኛል፤ በአሁኑ ወቅት የጸጥታ ኃይሉ ጠንካራ አደረጃጀት ድል እንዲያስመዘገብ አስችሎታል ብለዋል፡፡ ጠላትም በገባበት እንዲቀር እንዳደረገው እና የህልውና ዘመቻው በቅርቡ በአመርቂ ውጤት ይደመደማል ነው ያሉት ኮሎኔሉ። የሀገር መከላከያ ሠራዊት እና የአማራ ክልል የጸጥታ ኃይል ጠላትን ለመደምሰስ በሚያደረገው ተጋድሎ የኢትዮጵያ ሕዝብ ያልተቋረጠ ድጋፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስረድተዋል። ሠራዊቱ ሰንሰለታማ ተራሮችን ተጋፍቶ እያሸነፈ የመገስገሱ ምስጢርም ሕዝባዊ ደጀን በመኖሩ ነው ብለዋል። ሕዝቡም በቅርቡ ወደ ተረጋጋ ሰላም ይመለሳል ነው ያሉት የ54ኛ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ኮሎኔል የሺበር፡፡ ዘጋቢ፦ አዳሙ ሽባባው - ከማይጠብሪ ግንባር

photo content

የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሌጅ  ያሰለጠናቸውን  ልዩ  ኃይል ፖሊሶችን  እያስመረቀ ነው የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሌጅ  ያሰለጠናቸውን  ልዩ ኃይል  ፖሊሶችን ዛሬ እያስመረቀ መሆኑን የአማራ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።

photo content