en
Feedback
Merega Tv = Ethio 360Media

Merega Tv = Ethio 360Media

Open in Telegram
8 780
Subscribers
-424 hours
-157 days
-1130 days
Posts Archive
photo content

93% የሚሆነው የኢትዮጲያ ሕዝብ ለክብሩ የሚጨነቅ ከሆነ በአሜሪካ የሚረዳውን 7% ሕዝብ በበቂ ሁኔታ መመገብ ይችላል። ያ ብቻ ሳይሆን በሌቦችና በወስላቶች አማካኝነት ከእኛው እየተዘረፈ የምዕራቡን ዓለም ባንኮች እያደለበ የሚገኘው ገንዘባችን 7% የሚሆነውን ሕዝባችንን ከመመገብ በላይ ብዙ ግድቦች፣ ሆስፒታሎችና ትምህርት ቤቶች ይገነባል።

photo content

የኢትዮጵያ አየር ኃይል በጋይንት ግምባር ያወደመው ታንክ!

photo content

ወደ አኺራ ሄዷል | የነሺዳው ንጉሥ አረፈ # Ethiopia | አንጋፋው የጥበብ ሰው ሙሐመድ አወል ሙሐመድ ሳላህ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ! በበርካታ የጥበብ ስራዎቹ የምናውቀው ድምፀ መረዋው ሙሐመድ አወል ሳላህ ባደረበት የልብ ህመም ምክንያት ነሐሴ 16 ቀን 2013 ዓ,ም ህይወቱ ማለፉን ከቤተሰቦቹ ሰምተናል። ትውልዱ በደሴ ከተማ አራዳ አካባቢ ከእናቱ ከወይዘሮ ሰዕዲያ ሰዒድ አህመድ እና ከአባቱ ሐጅ ሙሐመድ ሳላህ አህመድ በ1958 ነበር። ትምህርቱንም በወ/ሮ ስህን ትምህርት ቤት ከተከታተለ በኋላ ወደ ውትድርናው አለም በመቀላቀል ሃገሩን ሲያገለግል ቆይቷል። በወታደር ቤትም በሙዚቀኝነት ሲያገለግል ቆይቶ ወደሳውዲ ዓረቢያ በማቅናት ለ7 ዓመታት ቆይታ አድርጎ ወደ ሃገሩ በመመለስ የጥበብ ስራውን ቀጥሎ ነበር። በኋላም የዓለማዊውን የሙዚቃ አለም እርግፍ አድርጎ በመተው ወደ መንፈሳዊ ህይወት በማዘንበሉ ህይወቱ እስካለፈችበት እለት ድረስ ሙሉ በሙሉ ኢስላማዊ ኪነጥበብብ ሲያገለግል ቆይቷል። ሙሐመድ አወል በሙዚቃው ዓለም ከሰራቸው ስራዎች ባሻገር በእስልምናው ዓለም በርካታ የጥበብ ስራዎችን አበርክቷል። የለኝ በጎ ሥራ፣ ሙሐመድ ተብዬ፣ እመስገጃሽ ላይ ታገሺ፣ ውዴታ እስከጀነት እና ሌሎችም የተካተቱበት ሦስት አልበሞችንና በርካታ ነጠላ ነሺዳዎችን አበርክቷል። ሙሐመድ አወል ሳላህ ከሚታወቅበት የጥበብ ሥራ በላቀ መልኩ የበጎ ተግባራት ላይ ከፍተኛ ተሳትፎ እንዳለው የቅርብ ወዳጆቹ ይመሰክራሉ። ባለትዳር እና የ6 ልጆች አባት የሆነው ሙንሺድ ሙሐመድ አወል ሳላህ ለረጅም ግዜ የዘለቀ ልብ ታማሚ የነበረ ሲሆን በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ህክምናውን ሲከታተል ቆይቶ በትላንትናው ሌሊት ከሌሊቱ 9 ሰዓት አካባቢ ህይወቱ እንዳለፈች ሰምተናል። የቀብር ስርዓቱም ኮልፌ በሚገኘው የሙስሊም መካነ መቃብር ዛሬ ነሐሴ 17 ቀን ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ እንደሚፈፀም ለማወቅ ችለናል። ለመላው ቤተሰቦቹ፣ ወዳጆቹና ለመላው ኢትዮጲያውያን የጥበብ ቤተሰቦች መጽናናትን እንመኛለን። አሏህ (ሱ.ወ) ጀነተል ፊርደውስ ይወፍቀው

photo content

የእርዳታ ድርጅቶች ለትህነግ ስንቅ እየቋጠሩ ነው! ከስር በፎቶ የምትመለከቱት USAID ወደ ትግራይ የላከው እርዳታ ነው። ከፍተኛ ኃይል የሚሰጥ በርሃብ ለተጎዱ ሰዎች ተብሎ የመጣ ነው። እየተጠቀመበት ያለው ግን ጥጋበኛውና ወራሪው ትህነግ ነው። የእርዳታ ድርጅቶች የተፈናቃይና በርሃብ የተጎዳውን ሕዝብ ቁጥር እስከ 10 እጥፍ በማሳደግ እርዳታ ይወስዳሉ። አባዝተው በወሰዱት መሰረት የተረፈውን ለትህነግ ይሰጡታል። ትህነግ እየተዋጋ ያለው የሰብአዊ እርዳታውን ስንቅ አድርጎ ነው። የአፋርና የአማራ ሕዝብ ይህ እርዳታ አይለፍብን ቢል ምን ይፈረድበታል?

photo content

የማይቀረውን ሲረዱ! ግብፅ 2.5 ቢልዮን ዶላር ወጪ በማድረግ ጨዋማውን የውቅያኖስ ውሀ ለመጠጥ የማዋል ፕሮጀክት ይፋ አርጋለች። Afrik21 እንደዘገበው ፕሮጀክቱ 17 የውቅያኖስ ውሀ የማጣርያ ጣብያዎችን የሚገነባ ሲሆን 2.8 ሚልዮን ሜትር ኪዩብ ውሀ በቀን ለማቅረብ ያግዛል። ይህም ግብፅ በህዳሴ ግድብ ምክንያት የውሀ መጠን ይቀንስብኛል ብላ በማሰቧ እንደሆነ ተገልጿል። የሌላ ሀገር የኤሌክትሪክ አመንጪ ግድብ ፕሮጀክት ላይ የሙጥኝ ከማለት በቅርብ የሚገኝ የውሀ ሀብትን እንዲህ ለመጠቀም መጣር ያዋጣል፣ ይህንንም አሁን አሁን እየተረዱት የመጡ ይመስላል።

photo content
+2

ወራሪው ኃይል የፈፀመው ውድመት አማራውን ጨፍጭፈው፣ ሀብትና ንብረቱን ለማውደም አላማ አድርገው በፈፀሙት ወረራ ጉና ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅን በፎቶው በሚታየው መልኩ አውድመውታል። በየደረሱበት ተቋማትን ዘርፈው እንዲህ አውድመዋቸው ነው የሄዱት። ወራሪዎቹ ጊዜ ቢያገኙ ከዚህ በላይ ውድመት እንደሚፈፅሙ ግልፅ ነው። ከንብረት ውድመትና ዘረፋ በተጨማሪ በየአካባቢው የተፈፀመው ጭፍጨፋ ከምናስበው እጅጉን የከፋ ነው። አሸባሪው ትህነግ የወረራቸው ቦታዎች ሲለቀቁ የፈፀመብን ውድመት ስንሰማ ከአእምሯችን በላይ እንደሚሆን ግልፅ ነው! ይሄ ኃይል ተጨማሪ ጭፍጨፋና ውድመት ሳያደርስ ግብአተ መሬቱን ማፋጠን ያስፈልጋል።

ልዩ መረጃ ‼️ #Ethiopia : ከጉና በተጨማሪ ጀግናው ሰራዊታችን የአማራ ልዩ ሀይል ፋኖ ሚሊሻ ጋሳይ እና ክምር ድንጋይን የጁንታው ታጣቂ ደምስሶ ሙሉ ለሙሉ ተቆጣጥሮታል::

photo content

photo content
+1

የአሸባሪው የትህነግ ኮሎኔል ተማርኳል። ከሀዲው ሌ/ኮሎኔል ገ/ህይወት ገ/አላፍ ይባላል። ጋሳይ ግንባር የወገን ጦር አባሮ የያዘው ጂንታ ኮሎኔል ነው። በእጁ በርከት ያሉ የሀሽሽ ብስኩቶች፤ 4 የተለያዩ መታወቂያዎች፣ የባንክ ደብተሮች ተይዘውበታል። አገርና ስርዓት የማፍረስ ተልዕኮ እንደተሰጣቸውና አሁን ግን ጦራቸው እንደተበተነባቸው ይናገራሉ። የደቡብ ጎንደር ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት

photo content
+2

በቤኒሻንጉል ግሙዝ ክልል ለጥፋት ተልዕኮ ሲንቀሳቀስ በቁጥጥር ስር የዋለው ሜ/ጀ ማዕሾ በየነ።

አሸባሪው የህወሓት ቡድን በሁመራ በኩል 12 ጊዜ የማጥቃት ሙከራ ቢያደርግም ተደምስሷል #Ethiopia : አሸባሪው የህወሓት ቡድን በሁመራ በኩል 12 ጊዜ ጥቃት ለማድረስ ሙከራ ቢያደርግም በሕዝቡና በፀጥታ አካላት ትብብር መደምሰሱን ኮሎኔል ደመቀ ዘውዴ ገለጹ። ኮሎኔል ደመቀ ከመገናኛ ብዙሃን ጋር በነበራቸው ቆይታ አሸባሪው የህወሓት ቡድን በሁመራ በኩል ለ12 ጊዜ ጥቃት ለማድረስ ሙከራ ቢያደርግም በሕዝቡና በፀጥታ ሀይል ትብብር መደምሱንን ተናግረዋል። ቡድኑ ዳግም በሁመራ በኩል ጥቃት ለማድረስ ቢሞክር መቀበሪያው ይሆናል ነው ያሉት ኮሎኔሉ። የአካባቢው ማኅበረሰብ በቂ ዝግጅት በማድረግ አሸባሪውን ቡድን የመደምሰስ አቅም ላይ ይገኛል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።